8 057
Subscribers
+3124 hours
+1267 days
+1 47530 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+181
in 2 channels
August '26
+1 485
in 5 channels
Get PRO
July '26
+224
in 0 channels
Get PRO
June '26
+162
in 0 channels
Get PRO
May '26
+145
in 0 channels
Get PRO
April '26
+87
in 0 channels
Get PRO
March '26
+183
in 1 channels
Get PRO
February '26
+271
in 2 channels
Get PRO
January '26
+338
in 1 channels
Get PRO
December '25
+450
in 6 channels
Get PRO
November '25
+708
in 5 channels
Get PRO
October '25
+226
in 1 channels
Get PRO
September '25
+304
in 2 channels
Get PRO
August '25
+642
in 5 channels
Get PRO
July '25
+414
in 2 channels
Get PRO
June '25
+307
in 0 channels
Get PRO
May '25
+259
in 0 channels
Get PRO
April '25
+274
in 1 channels
Get PRO
March '25
+251
in 3 channels
Get PRO
February '25
+430
in 0 channels
Get PRO
January '25
+902
in 0 channels
Get PRO
December '24
+362
in 0 channels
Get PRO
November '24
+283
in 2 channels
Get PRO
October '24
+766
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 09 September | +17 | |||
| 08 September | +34 | |||
| 07 September | +13 | |||
| 06 September | +19 | |||
| 05 September | +12 | |||
| 04 September | +19 | |||
| 03 September | +21 | |||
| 02 September | +24 | |||
| 01 September | +22 |
Channel Posts
| 2 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መጪዉን የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የበዓል ስጦታዎችን አበርክተዋል። በጸ/ቤቱ ድጋፍ ለሚያድጉ ሕፃናት የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ አበርክተዋል። #PMOEthiopia | 1 205 |
| 3 | https://www.facebook.com/share/v/1DxgZqMmw7/ | 1 029 |
| 4 | መዲናችን አዲስ አበባ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ከአፍሪካ ቀዳሚ ፣ ከዓለም 2ኛ ከተማ ሆነች!
ለመላዉ የከተማችን ነዋሪዎች እና አብራችሁን ተባብራችሁ የሰራችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የፎቶ ስላይ ዲንግ ቅንብር
ጳጉሜ 04 / 13 / 2018 ዓ.ም | 1 089 |
| 5 | መዲናችን አዲስ አበባ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ከአፍሪካ ቀዳሚ ፣ ከዓለም 2ኛ ከተማ ሆነች!
ዘኒዮርክ ታይምስ (The New York Times) ይዞት በወጣው ዘገባ፣ የቦታዎች ስጋትየሚያጠናና የሚተነብይ (AlphaGeo) ጂኦስፓሻል ኩባንያ በዓለም ላይ ካሉ ትልልቅ ከተሞች የ72 ቱን የአየር ንብረት የመቋቋም አቅም (Resilience) ደረጃ መድቧል። በዚህ መሠረት የተቀመጠውን መስፈርት በሟሟላት፣ ከተማችን አዲስ አበባ ከአፍሪካ ቀዳሚ ከዓለም ሁለተኛ ከተማ በሆን ተቀምጣለች ።
ከተማችን አዲስ አበባ እንደስሟ ውብ፣ ንፁህ እና ለመኖር ምቹ ከተማ እናደርጋለን ብለን በገባነው ቃል መሠረት፣ የአፍሪካ ኩራት በአጭር ጊዜ የከተማ ልማት ለውጥ ተምሳሌት በመሆን ላይ ነች።
ለመላዉ የከተማችን ነዋሪዎች እና አብራችሁን ተባብራችሁ የሰራችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 1 194 |
| 6 | #የኅብር_ ቀን !
ጷግሜን 4/ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ።
ጷግሜን 4 የኅብር ቀንን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልእክት !
ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች!
በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።
እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።
አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ! | 1 683 |
| 7 | እንኳን አደረሳችሁ!
ጳጉሜ 4 <<የህብር ቀን>>
በህብረታችን ብዕር ፣ ብሩህ አገራዊ ታሪክ እንፅፋለን! | 1 514 |
| 8 | "ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው፤ ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 1 811 |
| 9 | #ጳጉሜን 3 #የፅናት_ቀን !!
የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑን በመግለፅ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች አከበሩ የፎቶ ስላይድ ቪዲዮ ቅንብር ገፅታ ።
ጳጉሜ 03 / 13 / 2018 ዓ.ም | 2 173 |
| 10 | የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑ ተገለጸ፡፡
(ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ጷግሜ 3 የፅናት ቀንን ብሄራሲ መዝሙር በመዘመር የብሄራዊ ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀል አክብረዋል፡፡
በመርሀግብሩ የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ኃላፊነትና ተሳትፎ ጭምር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ በገቢ አሰባሰብ በትኩረት መስራት ይገባል ተብሏል፡፡
የአዲስ አመት መሸጋገሪያ የሆነችው የጳጉሜ ወር ቀናት በተለያዩ ሀገራዊ ድሎችን በሚዘክሩ ስያሜዎች እየተከበሩ እንደሚገኙ በመድረኩ የተጠቆመ ሲሆን ቀደምት አባቶቻችን በአንድነት ቆመው የፀናች ሀገርን እንዳስረከቡን ሁሉ የአሁኑ ትውልድም ሀገርን በሚያፀኑ የልማትና የለውጥ ስራዎች በአንድነት በመቆም የሀገርን ፅናት ማረጋገጥና ማስቀጠል ይገባል ተብሏል፡፡
#ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ፣ ለአዲስ አበባ ብልፅግና !! | 2 206 |
| 11 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጽናት ቀን ያስተላለፉት መልዕክት፦ የሀገራችን በራስ የመቆም አቅም የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት ነው
*******
በጽናት ቀን ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ እንደማይቻል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም፣ በዚህ የጽናት ቀን ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር እንደምንዘክር አስታውቀዋል።
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቁመዋል።
ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። | 2 381 |
| 12 | በመጨረሻም አቶ መሀመድ አብዱራሃማን አክለው እንደገለፁት የማንሰራራት ቀንን መንፈስ በመያዝ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠል የከተማዋን ዘላቂ ልማት የሚደግፍ ፍትሀዊ ፣ ውጤታማ እና ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት የመገንባት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስገንዝበዋል ።
ፍትሀዊ ገቢ አሰባሰብ ለአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ብልፅግና ! | 2 052 |
| 13 | ባለፉት ዓመታት በገቢ ዘርፉና በበጀት አጠቃቀም የተመዘገቡ ውጤቶች የከተማዋን የማንሰራራትና ብልፅግና ጉዞ አይቀሬነት አመላክች መሆናቸው ተገለፀ።
ጳጉሜ 2 / 2018 ዓ.ም : አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በሬዲዮ የቀጥታ ስርጭት ባስተላለፈው መልእክት አጠቃላይ የሪፎርም ስራዎችን በማቀናጀትና የፋይናንስ አቅምን በማጎልበት በገቢ አሰባሰብ ላይ የጎላ ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ለውጥ ማስመዝገቡን ተችሏል ተብሏል፡፡
ይህ የተገለፀው የቢሮው የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራሃማን በዛሬው ዕለት ከአዲስ ሚዲያ ራድዮ ጋር በነበራቸው ልዩ ቆይታ ነው::
ኃላፊው በቆይታቸው እንደገለፁት የጳጉሜ የማንሰራራት ቀን በጠንካራ የገቢ መሰረት ላይ የሚገነባ እንደመሆኑ ቢሮው ዘመናዊ የዲጂታል አሰራርን እና የታክስ ህግ ማስከበር ስራዎችን አቀናጅቶ በመተግበር ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት ችሏል ብለዋል ።
ይህ የተቀናጀ የሪፎርም እንቅስቃሴ ግብር ከፋዩ ህግን በማከበር ግብሩን በወቅቱ እና በታማኝነት እንዲከፍል በማድረግ የከተማዋን ገቢ በማሳደግ ረገድ የነበሩ ተዳክመው የቆዩ አሰራሮች እንዲያንሰራሩና የልማት በጀት በራስ አቅም እንዲሸፈን ማስቻሉንም ጠቁመዋል ::
በተጨማሪም የተተገበሩት ዘመናዊ የአሰራርና የአደረጃጀት ማሻሻያዎች የታክስ ስወራን በመቀነስ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ግልጽነትን በመፍጠር እና የግብር ከፋዩን እንግልት በማስቀረት የታክስ አስተዳደሩን ወደ ላቀ የስራ ባህል ያሸጋገሩ መሆናቸውን አብራርተዋል። | 2 018 |
| 14 | ነሐሴ 29 2018
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ባሉ የመኪና መሸጫዎች ከተወሰደው እርምጃ ለመሸሽ መኪናቸውን የሰወሩ የመኪና አስመጪዎችን ለማግኘት የመጋዘን ፍተሻ እንደሚጀምር የገቢዎች ቢሮ ተናገረ፡፡
በከተማዋ ያሉ የመኪና ማከማቻ መጋዘኖች የት እንዳሉና ምን እንደያዙ ተለይተው ታውቀዋል ብሏል ቢሮው፡፡
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከሰሞኑ የመኪና አስመጪነት ፍቃድ ሳይኖራቸው በኮሚሽን ስራ ፍቃድ የመኪና መሸጫዎችን በመክፈት ሲሸጡ የነበሩ የኮሚሽን ሰራተኞችን ፍቃድ ማገዱንና የሚሸጡትን መኪና ለአስመጪዎች እንዲመልሱ ማድረጉን በትላንትናው እለት በሰጠው ማብራሪያ አስረድቷል፡፡
እርምጃው የተወሰደው አሰራሩ ህግን ያልተከተለ፤ ከተማዋ ከፍተኛ መጠን ያለው ግብር ከዘርፉ እንድታጣ ያደረገ እንዲሁም ህጉን ተከትለው ከውጭ ያስመጡትን መኪና በራሳቸው መሸጫ የሚሸጡ አስመጪዎች በገበያው ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ የሚያደርግ መሆኑንም ቢሮው ጠቅሷል፡፡
ከሰሞኑ ቢሮው የወሰደው እርምጃ በርከት ያሉ የመኪና መሸጫዎችን ያዳረሰ ቢሆንም አሁንም ከእርምጃው ለማምለጥ በየቦታው ባለ መጋዘን ያከማቹ ግለሰቦች አሉ፤
እነዚህን ለማግኘት ቢሮው በከተማ ደረጃ በተዋቀረው ግብረ ሃይል የመጋዘን ፍተሻ፣ የበር ለበርና የመኪና ቁጥጥር ማድረግ እንደሚቀጥል የገቢዎች ቢሮ የህግ ተገዢነት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ አቶ መሃመድ አብዱረህማን ተናግረዋል፡፡
አቶ መሃመድ የግብር ስወራ ይፈፀማል ያሉበትን ምክንያት ሲያስረዱ እነዚህ የኮሚሽን ሰራተኞች በመኪና መሸጫዎች ለሚሸጡት መኪና ደረሰኝ የሚቆርጡት ከሸጡበት ዋጋ በታች ነው፤ገንዘቡንም ከገዢው የሚቀበሉት በተለያዩ የባንክ አካውንቶች ነው ይላሉ፡፡
የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ለገዢው ባለቤትነትን ሲያስተላልፍ የሚገኘው የመኪና ዋጋ ይኸው ደረሰኝ የተቆረጠበት ብቻ በመሆኑ ትክክለኛውን የመሸጫ ዋጋና የተሰወረውን ግብር የምናገኝበት መንገድ የለም ሲሉም ያስዳሉ፡፡
እነዚህ የተደበቁ አስመጪዎች በራሳቸው መንገድ ወደ ህጋዊ አሰራሩ እንዲገቡ ጥሪ ያቀረቡት ሃላፊው ይህ ሳይሆን ቀርቶ በሚደረገው ፍተሻ መኪኖቹ ከተያዙ ከዚህ ህጋዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እወቁት ብለዋል፡፡
ዘገባውን ያድምጡ.....
https://tinyurl.com/97kc6363
ምንታምር ፀጋው | 2 066 |
| 15 | https://youtu.be/YkhyKIzxkwU?si=8XIzzASDAdLuMaNP | 1 |
| 16 | https://youtu.be/YkhyKIzxkwU?si=8XIzzASDAdLuMaNP | 2 240 |
| 17 | የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያበስሩ፤ እመርታዊ ዕድገቷን የሚያፋጥኑ ፅኑ መሠረቶች ላይ እየተገነቡ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንም ሥርዐቱን ለማጽናት እና መሻታቸዉን እውን ለማድረግ ያላቸዉን ቁርጠኝነት በመንግሥት ጥሪዎች በሚያሳዩዋቸው ተሳትፎዎች እየገለጹ ነው፡፡
በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ከሌሊት እስከ ሌሊት ፈተናዎችን ተቋቁመዉ ድምፅ መስጠታቸዉ እና ውጤቱን በደስታ መቀበላቸው፤ በአረንጓዴ ዐሻራ በየዓመቱ እያደገ የመጣ ተሳትፎ እና ስኬት ማስመዝገባቸው፤ የልዩነት ሐሳቦችን በሰላማዊ መንገድ ለመግራት ሀገራዊ ምክክርን መምረጣቸው ኢትዮጵያውያን በመደመር መንግሥት ትልሞች ላይ የያዙትን የጋራ ተስፋ እና ለስኬቱም እያደረጉ ያለዉን ርብርብ የሚያሳይ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ሥርዐትን በማንበር፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመከተል፤ የከተሞችን ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ ወደ ገጠር በማላመድ፤ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን በመሻሻል፤ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቱን በማዘመንና በማስፋፋት ለኢትዮጵያ ኹለንተናዊ ብልጸግና ፅኑ መሠረት እየተቀመጠ ነው፡፡ ለዚህም ነው ጳጒሜን 2ን “የማንሰራራት ቀን” በሚል ስያሜ እያከበርን የምንገኘው፡፡
ጳጒሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication | 1 982 |
| 18 | የፕሬስ መግለጫ
እንኳን ለጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች ነው፡፡ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ፖሊሲዎች እና ዕቅዶች እየተመራች ለኹለንተናዊ ብልጽግና እየተጋች ትገኛለች፡፡ በየዘመን አንጓዉ ያጋጠሟትን ፈተናዎች በተደመረ ዐቅም እየተሻገረች፤ ከችግሮች እና ፈተናዎች ዕድሎችን መንጭቃ እያወጣች፤ ነገዋን በጠንካራ መሠረት ላይ እያጸናች ነው፡፡
ለዘመናት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ከዓድማስ እስከ ዓድማስ የሚያውለበልበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነገዉን ታሳቢ አድርጎ እንደ ቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ባሉ መሠረተ ልማቶች እና ኹለንተናዊ ለውጦች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡ ፡፡ ነባር እና ዐዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየለሙ እና ተደራሽነታቸዉ እያደገ ነው፡፡ ግብርናችን ከዝናብ ጥገኝነት እየተላቀቀ እና የገጠሩም የከተሜዉም የሥራ ዕድል እየኾነ ነው፡፡ የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችን ከውኃ፣ ከነፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል እንዲኾኑ የመደመር መንግሥት ሌት ተቀን እየሠራ ነው፡፡
ከተሞቿ ጎስቋላ ገጽታቸዉ እየተቀየረ እና ነገን እየዋጁ፤ መሠረተ ልማቶቿ እየተስፋፉ እና እየተቀናጁ፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ዐቅሟ እየተጠናከረ፤ የቀጣናዉ የታዳሽ ኃይል ማእከልነቷ እያደገ፤ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እያዋለች ለመጪዉ ትውልድ ኹለንተናዊ ብለጽግና እየሠራች ነው፡፡ | 2 216 |
| 19 | "የማንሠራራት ቀን
ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!
ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።"
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 1 914 |
| 20 | የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው
ከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡
በኦሮሞ ባህል ዘንድ የክረምቱን መውጣትና የጸደይ መዳረሻን ለማብሰር ከሚከናወኑ ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “የጎቤ” እና “ሺኖዬ” ጨዋታ ተጠቃሽ ነው።
AMN | 2 363 |
