664
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#UPDATE ፡ በራፋህ በደረሰ የእስራኤል አየር ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 40 አልፏል።
- Sky News Arabia
Share | @TheNewsReports
#BREAKING ፡ እስራኤል በራፋህ በሚገኝ የነዋሪዎች ድንኳን ላይ ባደረገችው የአየር ጥቃት ያደረሰች ሲሆን ይህም ከፍተኛ እሳት አስነስቷል።
እስካሁን በትንሹ 45 ሰዎች ተገድለዋል።
ሙሉ በሙሉ የተቃጠሉ አስከሬኖች ከአካባቢው ተገኝተዋል።
Share | T.me/TheNewsReports
#ማስታወሻ ከቻናሉ፡
እኛ እንደ ቻናል በተቻለን አቅም ሚዛናዊ የዜና አቅርቦት ለመስጠት እየሞከርን ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሆኖ የአባላቶቻችን ቁጥር ከምንሰራው ስራ አንፃር ለኛ ብርታት የሚሆነን እንኳን አይደለም።
ይህ ነገር ተስፋ አስቆራጭ ነው። ቢሆንም ግን እንደሌሎች ቻናሎች አሰልቺ ማስታወቂያ መደርደር እና "ሼር አድርጉልን" እያልን መጨቅጨቅ አልፈለግንም። በሚገርም ሁኔታ ግን ዘገባ ከዚሁ ቻናል እየወሰዱ ምንም የፅሁፍ ለውጥ እንኳን ሳያደርጉ በራሳቸው ገፅ ላይ የሚለጥፉ ቻናሎችን አይተናል።
ስለዚህ እባካችሁ ቻናሉ ይጠቅማል ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ቢያንስ ለአንድ ወዳጅ ሼር በማድረግ ተደራሽ እናድርገው።
T.me/TheNewsReports
T.me/TheNewsReports
#እስራኤል እና አለም አቀፉ ፍርድቤት
ቻይና፣ አሜሪካ፣ እስራኤል፣ የመን፣ ሊቢያ፣ ኳታር እና ኢራቅ፤ አጠቃላይ 7 ሀገራት ለአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት እውቅና አልሰጡም።
የፍርድቤቱ ትዕዛዝ ምንም ያህል አስገዳጅ ቢሆኑም ትዕዛዙን የማይቀበሉ ሀገራት ሲኖሩ ወይም ፍርድቤቱ ትዕዛዙ ተፈፃሚነት እንደሌለው ካረጋገጠ ቀጥታ ወደ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታዉ ምክር ቤት ጉዳዩ ይሄዳል። በዚህም ትዕዛዙ በሃይል እንዲፈፀም ድምፅ ይሰጥበታል።
እንደሚታወቀው ፍርድቤቱ ሰሞኑን እስራኤል በራፋህ ላይ የምታደርሰውን ጥቃት እንድታቆም ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም እስራኤል ትዕዛዙን እንደማትቀበል ይፋ አድርጋለች። ቀጥሎ ምን አለ?
የፍርድቤቱ ትዕዛዞች በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ናቸው። ይሁን እንጂ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ አሁን በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ይብራራል እንዲሁም ሀገራት በአንድነት የፍርድ ቤቱን ትዕዛዞች ለማስፈጸም አንድ እርምጃ ለመውሰድ መወሰን ይችላሉ። የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎችም በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ናቸው።
ሆኖም ዩናይትድ ስቴትስ እስራኤልን ከአለም አቀፍ ህግ መጣስ ከሚያስከትላቸው መዘዞች ለመከላከል በታሪክ የምትጠቀመውን ድምፅን በድምፅ የመሻር "ቬቶ" ስልጣን አላት።
አሜሪካ በፀጥታው ምክርቤት የሚቀመጠውን የእርምጃ ትዕዛዝ እስካልደገፈች ድረስ በሚያሳዝን ሁኔታ ምንም ሃይል እስራኤልን ማስቆም እንደማይችል ማመን ግድ ሊሆን ይችላል።
Share | T.me/TheNewsReports
#NEW ፡ የዩኤስ አፈ ጉባኤ ማይክ ጆንሰን፦
"ዛሬ ማታ ከ76 ዓመታት በላይ ያሳካነውን ስኬትን እንዲሁም ከብዙ ሺህ ዓመታት በፊት ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ እና ለያዕቆብ የተገባውን የተስፋ ቃል ፍጻሜ እናከብራለን።
ይህም ከባቢሎን ግዞት፣ እስላማዊ ከሊፋዎች እና ከናዚ የዘር ማጥፋት የተረፈው ቃልኪዳን ነው። የጽዮናውያን ህልም እውን ሆኗል"
Share | T.me/TheNewsReports
#JUST_IN ፡ የኔቶ ዋና አዛዥ ጄንስ ስቶልተንበርግ፦ "በሩሲያ ግዛት ውስጥ ኢላማዎችን ለመምታት የኔቶን ጦር መሳሪያ መጠቀሚያ ጊዜው አሁን ነው!"
Share | T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ ኢንስታግራም ተቋርጧል።
#ለብዙ ተጠቃሚዎች ስቶሪ እና መሰል ነገሮች እየሰሩ አይደለም።
@TheNewsReports
#BREAKING 🚨 ፡ አለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት እስራኤል በደቡባዊ ጋዛ ራፋህ ከተማ የምታደርገውን ወታደራዊ ጥቃት እንድታቆም ማዘዙን ስካይ ኒውስ በሰበር ዜና አውጥቶታል።
@TheNewsReports
#NEW ፡ የስፔን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዮላንዳ ዲያዝ፦ "ፍልስጤም ከወንዙ እስከ ባህሩ ድረስ ነፃ ትሆናለች"
T.me/TheNewsReports
ገና ከጅምሩ ነበር የእስራኤል ባለስልጣናት ሃማስን በእስራኤል ላይ ያደረሰውን ጥቃት ከ9/11 ጋር እያነጻጸሩ የነበረው። እነሱ በመሠረቱ ልክ እንደ አሜሪካ በ‹‹ፀረ ሽብር ጦርነት›› ምላሽ እንሰጣለን ቢሉም ለሰው ሕይወትም ሆነ ለዓለም አቀፍ ሕግ ግድ የለሽ መሆናቸውን አሳይተዋል።
ለ9/11 ቀጥተኛ ምላሽ ዩኤስ ኢራቅን እንዴት እንደወረረ አለም ያስታውሳል። ያኔ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ኮፊ አናን ወረራውን ህገወጥ ነው ቢሉትም አሁን፣ እስራኤልም ተመሳሳይ ነገር እያደረገች ነው - በራሳቸው የ9/11 ስሪት ምላሽ ህገወጥ ጦርነት ጀምረዋል። ሃማስ ባደረገው ድርጊት በጋዛ የሚገኙትን ፍልስጤማውያን ሁሉ እየቀጣቸው ነው፣ ይህም የአለም አቀፍ ህግን የሚጻረር ነው።
እስራኤል የራሳቸውን 9/11ን ለመበቀል ዩናይትድ ስቴትስ ከሰራችው ስህተት ምንም እንዳልተማረች ግልፅ ነው። እነሱ እንደ አሜሪካ ናቸው፤ የግጭቱን መንስኤዎች በትክክል ሳይገልጹ እና ብጥብጡን ለማስቆም ሳይሞክሩ በተቻለ መጠን ብዙ ደም ለማፍሰስ ቆርጠው ተነስተዋል።
እስራኤል በዚህ መንገድ ብትቀጥል እና በመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ጦርነት ከከፈተች በጉዳዩ ላይ ለሚመለከተው ሁሉ የማይታሰብ ውጤት ይኖረዋል። እስራኤላውያን፣ ፍልስጤማውያን፣ እና ሌሎችም በአከባቢው እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሀገራት ጭምር መከራ ይደርስባቸዋል። በፍፁም ሊስተካከል የማይችል ቅዠት!
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሁን ገብቶ አንድ ነገር ማድረግ አለበት። ያለፈውን ስህተት መድገም እና መካከለኛው ምስራቅን ወደ ሌላ ትርጉም የለሽ የሞትና የስቃይ ዘመን መግፋት አንችልም። እኛ ማድረግ ያለብን የመጀመሪያው እና ዋናው ነገር እስራኤል በፍልስጤማውያን ላይ የምታደርሰውን ግፍ ማስቆም ነው።
መካከለኛው ምሥራቅ ሌላ ትልቅ ጦርነት ማስተናገድ አይችልም፣ ነገር ግን በጋዛ የፍልስጤማውያንን ጭፍጨፋ ለረጅም ጊዜ ቁጭ ብሎ ያያሉ ማለት የማይሆን ነገር ነው።
ቴሌግራም፦ T.me/TheNewsReports
ቢሊየን ዶላሩ የማነው..?!
አንዳንድ አለም አቀፍ ሚዲያዎች ለእስራኤል እና ሀማስ ጦርነት መጀመር እንደ መንስኤ ከሚያነሱት መካከል ጦርነቱ ሳይጀመር አሜሪካ እና ኢራን ያደረጉት የ6 ቢሊየን ዶላር ስምምነት ዋነኛውና ተጠቃሹ ነው። ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ዘ-ጋርዲያን ባስነበበው ዘገባ አሜሪካ ይህን ያደረገችው አምስት በስህተት የታሰሩ የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ሰዎችን ለማስለቀቅ እንደሆነ ገልጿል።
በመሠረቱ እውነቱን እንነጋገር ከተባለ መጀመሪያውኑ ገንዘቡ የአሜሪካ ሳይሆን የኢራን ነው። አሜሪካ ይህን ስምምነት ስትፈራረም እግረ መንገዷን ለኢራን የነዳጅ ቀረጧን እየከፈለች እንጂ ለ5 ዜጎቿ ብቻ ብላ በቢሊየን የሚቆጠር ዶላር ጭራሽ ደግሞ ከኒውክሌር ባላንጣዋ ኢራን ጋር እንኳን ልትስማማ አታስበውም ነበር። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለሲ.ኤን.ኤን በሰጡት ቃልም ገንዘቡ ከጅማሮው የኢራን እንደነበር ገልጿል።
አሁን ላይ በተነሳው የእስራኤል-ሀማስ ጦርነትም ሀማስን በመደገፍ የምትታማዋ ኢራን ሀማስ መጀመሪያ ጥቃት እንዲያደርስ ይህ የአሜሪካው ስምምነት እንደ ድጋፍ ሆኖታል ሲሉ አንዳንድ ሚዲያዎች ይናገራሉ። ይህንን አስመልክቶ ኤንቢሲ የዜና ጣቢያ ባወጣው መረጃ መሠረት ኢራን ለሀማስ የመሳሪያ ድጋፍ ብታደርግም ከዚህ የገንዘብ ድጋፍ እንዳላደረገች ቢሊየን ዶላሩም ቀጥታ ከአሜሪካ የተሰጠ ሳይሆን ከደቡብ ኮሪያ ባንክ ወደ ኳታር እንደተላከ እና እዛው ኳታር ባለ ባንክ ውስጥ እንደተቀመጠ ኢራንም ይህንን ገንዘብ በምንም አይነት መልኩ እንዳይደርሳት ተደርጓል።
ኢራን ይህንን ገንዘብ ቀጥታ መጠቀም ባትችልም ለሰብዓዊ እርዳታ እና መሰል በጎ ተግባራት እንደፈለገች ማዘዝ እንደምትችል ተገልጿል።
ሼር ያድርጉ፦ T.me/TheNewsReports
#URGENT ፡ እስራኤል ለፍልስጤም ሀገርነት እውቅና መሰጠቱን አስመልክቶ ከኖርዌይ እና ከአየርላንድ አምባሳደሮቿን መጥራቷ ተሰምቷል።
የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስትር እስራኤል ካትዝ ለአየርላንድ እና ኖርዌይ ግልፅ እና የማያሻማ መልእክት ልከዋል።
ካትዝ፦ "እስራኤል ሉዓላዊነቷን የሚያደፈርሱ እና ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላትን በመጋፈጥ ዝም አትልም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአየርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሞን ሃሪስ ሀገራቸው ከኖርዌይ እና ከስፔን ጋር በመሆን ለፍልስጤም መንግስት እውቅና ሰጥታለች ብለዋል። በዚህም ብዙ ሀገራትም ይህንኑ ሊከተሉ እንደሚችሉ አስታውቀዋል።
ቴሌግራም፦ T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ ፖሊቲኮ እንደዘገበው አየርላንድ እና ስፔንን ጨምሮ ሶስት የአውሮፓ ሀገራት ፍልስጤምን እንደ ሉዓላዊ እና ነጻ ሀገር ዛሬ እውቅና ይሰጣሉ።
@TheNewsReports
#BREAKING 🚨 ፡ በራፋህ ትልቁ ምግብ አቅራቢ የተመድ የሰራተኞች ኤጀንሲ በዛሬው እለት ሁሉንም የምግብ አቅርቦት ማቆሙ አስታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዛሬው ዕለት በደቡባዊ ጋዛ ራፋህ ከተማ በአቅርቦት እጥረት እና በፀጥታ እጦት ምክንያት የምግብ ስርጭቱን ማቆሙን አስታውቋል።
እንዲሁም ኤጀንሲው ላለፉት ሁለት ቀናት ከዩናይትድ ስቴትስ በኩል ምንም አይነት የእርዳታ መኪኖች እንዳልገቡም ተናግሯል። በዚህም በቁጥር ሊገለፁ የማይችሉ እና ከእስራኤል ጥቃት የተረፉ ፍልስጤማውያን ለረሃብ እንደሚጋለጡ ነው የተነገረው።
- Le Monde
T.me/TheNewsReports
