664
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#JUST_IN ፡ በኒውዮርክ ያለው የተባበሩት መንግሥታት ሰንደቅ ለኢራኑ ፕሬዝዳንት እና ለባለስልጣናቱ ሞት ትውስታ ሲባል በግማሽ ዝቅ ተደርጓል።
T.me/TheNewsReports
+1
#BREAKING ፡ ፈረንሳይ፣ ቤልጂየም እና ስሎቬንያ የእስራኤል እና የሃማስ መሪዎች ላይ የቀረበውን የእስር ማዘዣ ጥያቄ ደግፈዋል።
T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ የእስራኤል ባለስልጣናት በብዙዎች ዘንድ ሚዛናዊ የዜና ምንጭ ተደርጎ የሚወሰደውን አሶሺዬትድ-ፕረስ ላይ ወረራ አድርገዋል።
የእስራኤል የኮሙዩኒኬሽን ሚኒስቴር ባለስልጣናት በዛሬው እለት ከሰአት በኋላ በደቡባዊ ስዴሮት ከተማ አሶሺዬትድ-ፕረስ ቦታ ደርሰው መሳሪያዎቹን እንዳለ ወስደዋል ተብሏል።
በወቅቱ ሚዲያው በሰሜን ጋዛ ላይ እስራኤል እያደረሰች የነበረውን ጥቃት በቀጥታ ስርጭት እያስተላለፈ ነበር። በዚህም ሳቢያ ባለስልጣናቱ ወደ ቢሮው በማቅናት ካሜራን ጨምሮ አስፈላጊ የሚባሉ የቀረፃ እና የቢሮ እቃዎችን ወስደዋል።
- ዘገባው የራሱ የአሶሺዬትድ ፕረስ ነው።
T.me/TheNewsReports
#JUST_IN ፡ "የአይሲሲ አቃቤ ህግ ለኔታንያሁ ያቀረበው የእስር ማዘዣ ጥያቄ አሳፋሪ ነው" - የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን
ብሊንከን፦ "አቃቤ ህጉ እስራኤልን ከሃማስ ጋር እኩል ማድረጉን ውድቅ እናደርጋለን። አሳፋሪ ነው። ሃማስ ጨካኝ ነው። ከጅምላ ጭፍጨፋ(ከናዚው) በኋላ በአይሁዶች ላይ እጅግ የከፋውን የጅምላ ጭፍጨፋ ያካሄደ አሸባሪ ድርጅት ነው። አሜሪካውያንን ጨምሮ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎችን አግቷል"
T.me/TheNewsReports
#TheUntold
ኢብራሂም ረዒሲ ፤ #የቴህራኑ ገዳይ!
(The Executioner of Tehran)
በትላንትናው እለት በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸውን ካጡ የኢራን ባለስልጣናት መካከል ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ረዒሲ በዋነኝነት ይቀመጣሉ።
ኢብራሂም ረዒሲ ማናቸው..?
በፈረንጆቹ 2021 ነሀሴ ወር በኢራን ፕሬዝዳንትነት የተመረጡት ረዒሲ ፕሬዝዳንት ከመሆናቸው በፊት በኢራን ፖለቲካ ስር ከባድ ስም እና ዝና ያላቸው ነበሩ። ከዚህም ውስጥ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1988 በኢራን ውስጥ ከተፈፀመው የጅምላ የፖለቲካ እስረኞች ጭፍጨፋ ጋር ስማቸው አብሮ ይነሳል።
የ1988 ጭፍጨፋን በበላይነት ከመሩት አራት ዳኞች መካከል አንዱ የሆኑት ረዒሲ በአሜሪካ ማዕቀብ ስር የነበሩ ሲሆን ይህንን ውንጀላ ግን በይፋ እሳቸውም ሆኑ ቴህራን አይቀበሉትም። በዚህም ኢራን እ.ኤ.አ. በ1989 በሞቱት አብዮታዊ መሪ በአያቶላ ሩሁላህ ኹሜኒ የጅምላ ግድያ መፈጸሙን አምና አታውቅም።
እንደ አንዳንድ ዘገባዎች ከሆነ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 30,000 ይደርሳል የሚሉ ሲሆን አምነስቲ ኢንተርናሽናል በ2018 ባወጣው ሪፖርት ግን 5,000 የሚሆኑት ተገድለዋል ያለ ሲሆን እውነተኛው ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆን ይችላል ሲል ገልጿል።
እ.ኤ.አ. በ1988 የበጋ ወቅት የተፈፀመው የኢራን አገዛዝ የፖለቲካ እስረኞች እልቂት በቴህራን እውቅና ተሰጥቶት ባያውቅም በቅርብ ታሪክ ውስጥ ካሉት ጨለማዎች ውስጥ አንዱ ሆኖ ይቆያል። ይህ ጭፍጨፋ ምንም እንኳን አሜሪካ ማዕቀብ ብትጥልም በምዕራቡ ዓለም በአንጻራዊ ሁኔታ የማይታወቅ ነው።
ግድያው የጀመረው በ1988 በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ ሲሆን ለብዙ ወራት ቀጥሏል። እስከ 30,000 የሚደርሱ የፖለቲካ እስረኞች ወይም ከዚያ በላይ፣ አብዛኞቹ የኢራን ህዝባዊ ሙጃሂዲን ድርጅት (PMOI) አክቲቪስቶች ተጨፍጭፈዋል ይላል ዘ-ዲፕሎማት በጋዜጣው።
በጊዜው የኢራን ጠቅላይ መሪ የነበሩት አያቶላ ኹሜኒ በ1988 አውጥተውት የነበረው አዋጅ እንዲህ ይላል፦ "በማንኛውም ደረጃ የPMOI (የኢራን ህዝባዊ ሙጃሂዲን ድርጅት) አባል ሆኖ የቀጠለ መገደል አለበት። የእስልምናን ጠላቶች በአስቸኳይ ደምስሷቸው!” በመቀጠልም "…በመላው ሀገሪቱ በእስር ቤት የሚገኙ እና ለድርጅቱ(PMOI) ላላቸው ድጋፍ ፅኑ የሆኑት በአላህ ላይ ጦርነት እየከፈቱ ነው እና በሞት እንዲቀጡ ተፈርዶባቸዋል። በአላህ ላይ ለሚዋጉ ሰዎች ምሕረትን ማሳየት የዋህነት ነው" የሚል ነበር።
በዚህም ግድያው ብዙም ሳይቆይ ተጀመረ እና በየቀኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞች እየተሰቀሉ እና አስከሬኖቻቸው በፍጥነት በሁሉም የኢራን ዋና ዋና ከተሞች በተለይም በደቡብ ቴህራን በሚገኘው በካቫራን የመቃብር ስፍራ መቅበሩን ተያያዙት።
በዚህ መሃል ግን አንድ ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ።
በወቅቱ ለአስር አመታት ያህል አያቶላ ኹሜኒን ይተካሉ ተብለው የተሾሙት የሀይማኖት አባት አያቶላ ሁሴን-አሊ ሞንታዘሪ የጅምላ ግድያውን በመቃወም ኹሜኒን በመፃረር ቆሙ። ነገር ግን ኹሜኒ ምንም አይነት ምህረት እንዳይደረግ በማለት ሁሉም እስረኞች ታዳጊዎችን እና ነፍሰ ጡር እናቶችን ጨምሮ ወዲያውኑ እንዲገደሉ አዘዙ።
የኹሜኒ ወራሽ ተደርገው ሲታሰቡ የነበሩት አያቶላ ሞንታዘሪ ግድያውን በመቃወማቸው ምክንያት በፍጥነት ከኹሜኒ ተተኪነት ወርደው በመጋቢት መጨረሻ 1989 ከስራ ተባረሩ። በፈረንጆቹ ታኅሣሥ 2000 ሞንታዝሪ በግድያው ወቅት የነበረውን ሁኔታ በማሳተም የኹሜኒን ጭፍጨፋ እና ጭካኔ አስደንጋጭ ዝርዝሮችን ቢያጋልጡም የኢራን ባለስልጣናትን ተጠያቂ የሚያደርግ አካል ጠፋ።
ብዙ ምስክሮች እንዳሉት አያቶላህ ሩሁላህ ኹሜኒ ከመሞታቸው አንድ አመት አስቀድሞ በ1988 ጭፍጨፋውን ካካሄዱት የአራት ሰው ኮሚቴ ውስጥ ኢብራሂም ረዒሲን መርጠው ነበር። ይህም ብቻ አይደለም ረዒሲ በ20 አመቱ በኢራን የቴህራን ትልቅ የሳተላይት ከተማ የሆነችው የኸራጅ አውራጃ ከዛም ለሀመዳን አውራጃ አቃቤ ህግ ሆኖ የተሾመ ሲሆን በኋላም በ1985 የቴህራን ምክትል አቃቤ ህግ ሆኖ በማገልገል ታማኝነቱን አረጋግጧል።
ኢራን ስለ 1988 ጅምላ ግድያ ምንም ባትልም ረዒሲ በግድያው ውስጥ እጁ እንዳለበት በመብት ተሟጋቾች ውንጀላ ሲጠየቅ በ2021 ለዜና ኮንፈረንስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፦ "አንድ ዳኛ አቃቤ ህግ የህዝቡን ደህንነት ከጠበቀ ሊመሰገን ይገባዋል" አክለውም "እስካሁን በያዝኳቸው የኃላፊነት ቦታዎች ሁሉ የሰብአዊ መብት ጥበቃ በማድረጌ ኩራት ይሰማኛል" ብለው ጉዳዩን አለባብሰው አልፈዋል። ረዒሲ በፈረንጆቹ 2021 በፕሬዝዳንትነት በአያቱላህ አሊ ኻሜኒ ሲመረጡ ይህንኑ ታማኝነታቸው ታይቶ ይመስላል።
#ማስታወሻ፦ የቀድሞ ጠቅላይ መሪ አያቱላ ሩሁላህ ኹሜኒ እና ጊዜያዊው ጠቅላይ መሪ አያቱላ ኣሊ ኻሜኒ የተለያዩ ሰዎች ናቸው።
- ይህን ፅሁፍ ስናዘጋጅ ሮይተርስ እና ስካይ ኒውስን በዋቢነት ተጠቅመናል።
ቴሌግራም፦ T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ አለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የሃማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ላይ እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በጋዛ ላይ በደረሰው የጦር ወንጀል እና በሰብአዊነት ላይ ለተፈፀሙ ወንጀሎች ክስ የእስር ማዘዣ ሊያወጣ መሆኑን ሲኤንኤን ዘግቧል።
አለም አቀፉ ፍርድቤት ለእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት እና ለሌሎች ሁለት የሃማስ ከፍተኛ አመራሮች - ለአልቃሳም ብርጌድ መሪ ሙሐመድ ዲያብ ኢብራሂም አል-ማስሪ እና ሙሐመድ ዴይፍ በመባል ለሚታወቁት እንዲሁም ለሀማስ የፖለቲካ መሪ እስማኤል ሃኒዬህ የእስር ማዘዣ ሊያወጣ ይችላል።
T.me/TheNewsReports
#UPDATE ፡ ፕሬዝዳንት ፑቲን በኢራን ፕሬዝዳንት ረዒሲ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል።
ፕሬዝዳንት ፐቲን ለአያቶላ ኻሜኒ በሰጡት መግለጫ፦ "ከሰዒድ ኢብራሂም ረዒሲ ጋር ብዙ ጊዜ የመገናኘት እድል አግኝቼ ነበር፣ እናም የዚህን አስደናቂ ሰው ትዝታ እስከመጨረሻው አኖራለሁ"
በፕሬዝዳንት ፑቲን መመሪያ መሰረት የፍለጋ ስራዎችን ለመርዳት ሁለት አውሮፕላኖች፣ ሄሊኮፕተሮች እና 50 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከሩሲያ በመጓዝ ላይ እንደነበሩ አይዘነጋም።
T.me/TheNewsReports
ለኢራኑ ፕሬዝዳንት እና ለሌሎች ባለስልጣናት ሰውነት መገኘት የቱርኩ AKINCI ዩኤቪ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።
T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሁሴን አሚር አብዱላሂያን ከኢራን ፕሬዝዳንት ረዒሲ ጋር ሄሊኮፕተራቸው ተከስክሶ መሞታቸው ተገልጿል።
@TheNewsReports
#BREAKING ፡ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ረዒሲ ሄሊኮፕተር መገኛ ቦታ ተደርሷል።
- ተስኒም የዜና ወኪል የአካባቢውን የአብዮቱን ጠባቂ አዛዥ ጠቅሶ ዘግቧል።
@TheNewsReports
#BREAKING ፡ ቱርክ ከኢራን ባለስልጣናት ጥያቄ በኋላ ባይራክታር AKINCI ዩኤቪ ድሮን እና የምሽት ራዕይ የታጠቀውን ኩጋር ሄሊኮፕተር ወደ ኢራን እንደምትልክ የቱርክ መከላከያ ሚኒስትር ተናግሯል።
T.me/TheNewsReports
#JUST_IN ፡ "ሩሲያ ኢራንን ለመርዳት ዝግጁ ናት" - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛኻሮቫ ሞስኮ ለችግሩ መንስኤ የሆኑትን ምክንያቶች መመርመርን ጨምሮ በማንኛውም መንገድ ለመርዳት ዝግጁ መሆኗን ገልፃለች።
እንዲሁም ሳውዲ አረቢያ ለአስርት አመታት ከኢራን ጋር ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ የነበረች ቢሆንም ድጋፍ ለመስጠት ኢራንን እተባበራለሁ ብላለች።
@TheNewsReports
#UPDATE ፡ የኢራን ቀይ ጨረቃ፦ ቡድኖቻችን የሄሊኮፕተሩን ቦታ የሚገምቱበት ሶስት መጋጠሚያዎች ላይ ደርሰዋል፣ ነገር ግን ምንም አልተገኘም።
9 ሰዓታት አልፏል፤ ምንም የለም።
@TheNewsReports
#JUST_IN ፡ ኢራን ለምሽት ፍለጋ እንዲሆናት ከቱርክ የምሽት እይታን የታጠቀ ሄሊኮፕተር ጠይቃለች። ቱርክም ጥያቄውን ተቀብላለች።
T.me/TheNewsReports
#BREAKING ፡ የነፍስ አድን ቡድኖች የኢራኑን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራኢሲ ሄሊኮፕተር አንዳንድ ፍርስራሹን ማግኘታቸውን የኢራን መንግስት ቲቪ ዘግቧል።
@TheNewsReports
#JUST_IN ፡ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ረዒሲ በይፋዊ የኢንስታግራም ገፃቸው "ጸልዩልኝ" የሚል መልዕክት ተሰራጭቷል።
T.me/TheNewsReports
#JUST_IN ፡ እስራኤል ከኢራኑ ፕሬዝዳንት ሄሊኮፕተር አደጋ ጋር ምንም ግንኙነት የላትም ሲል የእስራኤል ቻናል 13፤ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
@TheNewsReports
#UPDATE ፡ አየሩ ጨለማ፣ ዝናባማ እና ጭጋጋማ ነው።
አሁንም የኢራኑ ፕሬዝዳንት ረዒሲ የነበሩበት የተከሰከሰው ሄሊኮፕተር አልተገኘም።
T.me/TheNewsReports
