ፍትሕ ለአምሓራ!
Open in Telegram
ፍትህ ልብን ትጠግናለች! #እኛ፣ የፍትህ አወቅ አበው ልጆች ነን! የፍትህ አደባባዩን በክንዳችን እንፈጥራለን!
Show more1 261
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-3130 days
Posts Archive
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ - Moaa Media
#ለአምሓራዊ የህልውና ትግል በክብር፣ ለክብር የተሰጠች ህያዊት ነፍስ‼️
በምስራቅ አማራ ቀጠና ምዕራብ ወሎ ግንባር ከወር በፊት በርካታ ጠላትን ጥሎ በክብር የተሰዋው እና በስሙ ክፍለጦር የተሰየመለት አርበኛ ሳጅን አደም አሊ [አባናደው]❗️
ሰልፋችን፣ የመስመራችንም አስኳለ አላማ የአምሓራዊነትን ህልውና አፅንቶ ወደ ቀደመ ክብሩ መመለስ፣ ዋስትና ሰጭ ፍትህ መስጠት፣ #ሰዋዊነት የምድሯ የፍቅር ቋንቋ እንዲሆን፣ ሁሉ ዐቀፍ ሰላም እንዲሰፍን መትጋት ነው!
የዚህ ቅዱስ ሰልፍ ፊት መሪ ሰልፈኞች ፅኑዐን ፃድቃንም ናቸው። ግፈኞችን እየጣሉ፣ ፋሽስቶችን እያንቀጠቀጡ የሚወድቁ ህያው ነፍሰኞች።
ሳጅን አርበኛ ሰማዕቱ ፋኖ አደም አሊ ዛሬ ታሰበ… በድል ማግስት ሀውልት አቁመን ጀብደ ግብሩን እንተርክለታለን!
ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!
////////////////////🎤🎤🎤//////////////////////
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ነሀሴ 03/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
#አጋርን እየገፉ፣ ድል ከወዴት ነው❓
=============================
ኦርቶዶክስ ተኮር ጀኖሳይድ እና ጭፍጨፋን፣ እንዲሁም የመንግስት ተቋማዊ ፀረ ኦርቶዶክስ ጥቃትን ለመመከት ራሱን ያደራጀ ከየትኛውም አካል የሆነ ንቃት ፈጣሪ መዋቅር… ለአምሓራ ፋኖ ትግል ተጨማሪ እድል ፈጣሪ እና ጠላትን ቀናሽ በረከት ነው።
አምሓርነት በደም ጥራት የሚለካ የመሰባሰቢያ አውድ አይደለም። አምሓራ በእሴቱ፣ በታሪክ፣ በባህል፣ በእምነት እና ፖለቲካዊ እጣ ፋንታ የተጋመዳቸው ህብረ አምሓራውያንን አቃፊ የፖለቲካ ሀልዮት መከተል ያለበት የግዱን ነው።
የሞዐ ተዋህዶ መነሻ የትግል አጀንዳ እና ጥያቄዎቹን ማስመለሻ የትግል ስልቶች፣ ከፋኖ የትግል ስልት ጋር አስታርቆ እና ገምዶ በጋራ መታገል ጥበበኝነት ይጠይቃል።
መገፋፋቱ እና መፈራረጁ ግን፣ አክሳሪ ነው።
ሆኖም፣ በሞዐ ተዋህዶም ሆነ፣ በፋኖ ስም… የህዝብ አቋም እና አጀንዳ ያልሆነ ውዥንብር ፈጣሪ ሰርጎገብ ግለሰቦች፣ ከዳንኤል ክብረት እና የደህንነት ተቋሙ ጋር እየተናበቡ ከፋፋይ መናጆ መርዛማ ወሬ እየረጩ፣ እያሳለጡ እንደማይሆን ማረጋገጫ የለንም።
ጉዳዩ፣ በጥንቃቄ መመርመር ይሻል።
የእምነት ተኮር ጀኖሳይድን ለመዋጋት፣ የእምነቱ ልሂቃን ተደራጅተው አገዛዙን መቃወም መጀመራቸው ሊታገዝ ሊበረታታም የሚገባ እንጅ፣ እያደናገሩ መግፋት አደገኛ ነው።
ይልቅ፣ ግዙፍ ሀቅም ሆነው የአገዛዙን እድሜ ማሳጠር ላይ ባለ ግዙፍ ሚና እንዲሆኑ ማገዝ ይገባናል።
ኦርቶዶክስ ተኮር ጥቃት እና ጀኖሳይድ እስካለ… ኦርቶዶክስ ተኮር ተከላካይ መዋቅርን ገፍቶ ማጠናገር ያስፈልጋል። ከፋኖ ትግል ጋርም የሚጣጣም ጋርዮች፣ ጥምረት እና አንድነት እንዲመጣ መስራት ነው።
ከዚያ ውጭ፣ የእምነት ማህበረ ትስስሬ ከአምሓራዊ እጣ ፋንታ ጋር የተለነቀጠ ነው የአምሓራ ትግል ይመለከተኛል፣ አግዛለሁ ብለው ለሚመጡት፣ በመካከላችን ላሉትም ጓዳዊ ስስት፣ በጥበብ አብሮ መራመድን ካላሳየን… ትግላችን፣ መመርመር አለበት!
ከ80% በላይ የአምሓራ ህዝብ ኦርቶዶክሳዊ ሆኖ ሳለ… በእምነት ድንበር ዝምድና የትግልህ ባለሚና ሆኜ ሀገርን ከፋሽስቱ አገዛዝ ለማላቀቅ እሰራለሁ ብሎ የሚመጣን መግፋት ጤነኛነት አይደለም።
የአምሓራ ትግል፣ ስብዕናዊ ነፃነትን የመሻት ነው።
በዚህ ትግል ውስጥ፣ የአምሓራ ትግል ኮዝ የገባቸው፣ የአመኑበት ሁሉ ሁለአቀፍ ድጋፍ የሚያደርጉበት የጋራ ግንባር ነው። በዋናነት አምሓራው፣ ሲቀጥል ሁሉም ህልውናዊ አደጋውንም ሆነ በእሴቶቹ የተጋመዱት ህዝቦች በተጋሩት በደል ምክንያት ከጎኑ ተሰልፈው የሚዋጉበት በባለቤትነትም የሚመሩት ትግል ነው።
ይሄን፣ ህብረ ብዙ ባለ እሴት ሰልፈኛ በጥበብ መርቶ ለድል ለማብቃት ግን፣ ከወያኔ እና ኦነግ ያልተኮረጀ፣ በጭፍን ጥላቻ እና የስሜት ድንበራን የተሻገረ፣ የአባት አምሓሮችን ጥበበ አመራር ፀጋው ያደረገ ባለ ብርሃን ዘንግ ብሄርተኛ መሆን ያሻል።
ትውልዱ፣ ለዚያ አሻጋሪ ፍኖት ራሱን ያዘጋጅ!
ያኔ፣ መጭው ዘመን፣ መካሻችን ይሆናል!
#ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#Moaa Media /Aug1/2025
ሞዐ ሚዲያ
#ሐምሌ
26/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የምክክር ኮምሽኑ ተመራጭ ተሳታፊዎች ወደ ትጥቅ ትግል ገቡ❗
ፋሽስቱ ኦህዴድ ብልፅግና ዋና አዘጋጅ ሆኖ በፈጠረው የድራማ መድረክ "ሀገራዊ ምክክር" በተባለው የምንደኛ አዛውንቶች መሀበር ውስጥ በግብዣ ከተሳተፉ አመራሮች መካከል ስርዓቱን በኃይል ለመጣል የትጥቅ ትግል ለመጀመር ወደ ኤርትራ የገቡ አመራሮች መኖራቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል።
በሀገራዊ ምክክሩ ከተሳተፉ አመራሮች ውስጥ በአፋር ክልል የካቢኔ አባላት፣ የክልሉ ምክር ቤት አባላት እና የፀጥታ አካላት ጭምር ወደ ኤርትራ ገብተው ትጥቅ ትግል መጀመራቸው ተሰምቷል። በተመሳሳይ በአምሓራ ክልልም ለዚሁ ድራማ ታጭቱው የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች እና የአመራር አባላት ፋኖን እየተቀላቀሉ መሆኑን ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ደርጅቶች ሕብረት ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት ዙሪያ የመጀመሪያ ዙር ክትትል ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
በአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከዚህ ቀደም በግጭት ምክንያት አጀንዳ ማሰባሰብ ያልተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን የገለጹም ሲሆን፤ "አሁን ደግሞ በአፋር ክልል በምክክር ሂደት የነበሩ ሰዎች አብዛኛዎቹ ወደ ጫካ እየኮበለሉ ነው" ብለዋል፡፡
ይህ ድርጊት የሚያመላክተው ህዝቡ በአገዛዙ ፍፁም ተስፋ የቆረጠ እና ወደ መጨረሻው አማራጭ የመግባት ፍላጎቱ ይበልጥ መጨመሩን ነው።
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
22/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
#ሰበር ዜና❗
በአርማጭሆና መተማ ከሀምሌ 11/2017 ዓም ጀምሮ በቀጠለው ሶስተኛ ዙር ማጥቃት በሽህ የሚቆጠር የዓብይ አህመድ አገዛዝ ሰራዊት ከፊሉ ሲደመሰስና ሲማረክ ቀሪው እግሬ አውጭኝ ብሎ በርካታ የአርማጭሆ ከተሞች የነበረውን ወታደራዊ ቤዝ ለቆ ወደ ጎንደር ከተማ አቅጣጫ እየፈረጠጠ ይገኛል።
በ5 ቀናት የተመረጠ ማጥቃት ብትንትኑ የወጣው የፋሽስቱ ጦር እጅ ነብሱን ለማትረፍ እጅ እንዲሰጥ የተጠየቀ ሲሆን ፈቃደኛ ሳይሆን በቀረው ላይ የድምሰሳ ተልዕኮ እንዲፈፀም ለሰራዊታችን ትዕዛዝ ተሰቷል።
ይህ መረጃ እስከተዘጋጀበት ሰዓት ድረስ በርካታ ጠላት ረግፎ የበርሃ መሬት መቀበሪያው የሆነ ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያም ተማርኳል።
ከአብርሃ ጅራ ወደ ማሰሮደንብ ከ80 ኪ.ሜ በላይ ወደ ኃላ ፈርሶ እየሸሸ ሲሆን እስከ አሁን ድርማጋ፣ሞገሴ፣ዘመነበሪቅ፣ቶርካ፣ማዓርሽ፣ደለሳ፣ደረቅ አምቦ የመሳሰሉ ከተሞችና አካባቢው ከጠላት ሙሉ በሙሉ ነፃ ሁኗል።
ነፃ የወጣው ወገናችን በየከተሞች በነቂስ ወቶ ደስታውን እየገለፀ ሲሆን በመሸሽ ላይ የሚገኘውን ወንጀለኛ ሰራዊት አሳዶ በመደምሰስ ተልዕኮ ተሳታፊም ሁኗል።
በርካታ ምርኮ መሳሪያ የተገኘ መሆኑ የተረጋገጠ ቢሆንም በተለያዩ ሶሻል ሚዲያ በአሃዝ የተገለፁ ምርኮዎችን በተመለከተ ለጊዜው በኔትወርክ ችግር ማረጋገጫ ማስረጃ አልተገኘም።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና
በላይ ዘሀቀ ዕዝ
ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
16/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የኦርቶዶክስ ቤተ እምነቶች የመንግስት ፖለቲካዊ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ወጭ እና ሲመት ማክበሪያ በሚል በአስገዳጅ መመሪያ እየተዘረፉ ነው‼️
በዚህ ጉዳይ የአሶሳ ሀገረ ስብከት ምዕመናንም የሚሰማ ካለ ድምጻችንን አሰሙልን እያሉ ነዉ።
ሰሞንኑ የወለጋ ሕዝብ ጳጳስ የለዉም ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንም እየተጣሰ ነዉ፣ በአገዛዙ ካድሬዎች ሙዳዬ ምፅዋት እየተገለበጠ ነው ብለን መፖሰታችን፣ ብዙዎች እየደወሉ በዉስጥ መስመርም እንዲፅፉ ምን ወለጋ ብቻ እኛጋም ብዙ ችግር እየተፈጠረ ነዉ እያሉኝ ነዉ።
ከነዚያም መካከል የአሶሳ ሀገረ ስብከት ምዕመናን እና ቤተ እምነቶቹ ይጠቀሳሉ።
እኛጋ እንኳን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መጣሱ የተለመደ ነዉ ብንጮህም የሚሰማን አጣንና ዝም አልን የአሁኑ ግን ከወትሮዉ የተለየና መልኩን ቀይሮ በቀጥታ እና ደረቅ ትዕዛዝ የመጣ ፈተና ነዉ አሉኝ።
እኔም ምንድነዉ ብዬ ጠየኳቸዉ እነርሱም እንዲህ አሉኝ👇
በዓለ ሲመቴን አክብሩልኝ በሚል ሰበብ ከየአጥብያዉ ቤተ ክርስቲያን የገንዘብ ዘረፋ ተይዟል አሉኝ። እንዴት? አልኳቸዉ እነርሱም በዝርዝር አቀረቡልኝ ለምሳሌ:-
ከመንበረ ሰላም ቅ/ገ/120000
ከመንበረ ስብሐት ቅ/ማርያም=105000
ከደብረ ሲና ቅ/ሚካኤል=100000ብር
ከኢንዚ መ/ሕያዋን=115000ብር
ከአረጋዊ ቤ/ክ=50000ብር
ኡራኤል ቤ/ክ=40000ብር
እስጢፋኖስ ቤ/ክ=20000ብር
ልደታ ማርያም ቤ/ክ=10000ብር
እንባ ሰባት ኪዳነምህረት ቤ/ክ=40000ብር
እንባ አራት ኪዳነምህረት ገዳም=40000ብር
ሩፋኤል ገዳም=50000ብር
አራት ማህበራት ከእያንዳንዱ=50000ብር
በዚህ መልኩ በግዳጅ ተጥሎብን እየተዘርፍን ነዉ እያሉ ነዉ። ከዚህም በላይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት ጠብቆ የሚያስጠብቅልን አገልገልሎት አገልግሎ የሚያስገለግል አባት እንዲመደብልን ወደሚመለከት አካል ድምጽ እንድትሆኑልን በትህትና እንጠይቃለን። እዚህ ያሉት ብዙዎ ከካድሬ ጋር ተመሳጥረው ቤተ እምነቷን የሚዘርፉ ናቸው። ሲሉ መልዕክት አድርሠውናል።
የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
16/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ - Moaa Media
+1
እስራኤል፣ የጋዛ ፍልስጤማዊያንን በኢትዮጵያና ሌሎች ኹለት አገሮች ለማስፈር የአሜሪካን ድጋፍ እንደጠየቀች "አክሲዮስ" የተሠኘ የአሜሪካ ድረገጽ ዘግቧል። የእስራኤል የስለላ ድርጅት የኾነው የሞሳድ ባለሥልጣናት፣ እስራኤል በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ፣ ሊቢያና ኢንዶኔዥያኛ መንግሥታት ጋር እየተነጋገረችበት መኾኑን ለአሜሪካ ባለሥልጣናት እንደነገሯቸው ዘገባው ጠቅሷል። የአሜሪካው ሴናተር ክሪስ ሆለን፣ የጋዛ ፍልስጤማዊያንን በግዳጅ በሌሎች አገራት ለማስፈር ማሰብ "እጅግ የሚያስቆጣ" እና "አሳፋሪ" ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ክፉኛ ተችተዋል። ሴናተሩ፣ አሜሪካ ለዚህ እቅድ ድጋፍ ማድረገም ኾነ በማናቸውም መንገድ መተባበር እንደሌለባት አሳስበዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በዘገባው ዙሪያ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በይፋ ያለው ነገር የለም።
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
13/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
#የፋሽስቱ ጦር በመተማ ተደመሰሰ‼️
የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይግዛት እዝ ፋኖዎች በመተማ ሰሜናዊ አቅጣጫ ጎርጃምስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የገባውን የሰው በላና ባንዳ ቡድን አስከሬኑን መሰብሰብ እስኪያቅተው ዶግ አመድ መደረጉን አርበኛ ጋዜጠኛ ቴድሮስ ከበደ ገለጸ።
ይህንን ገዳይ ቡድንን አስቀድሞ ከቦት ያደረው የፋኖ ሃይል ከሞት የተረፈውንም እስከ ኮኪት አሳዶታል ብሏል።
ገዳይ ቡድኑን ለማገዝ ከሸዲ በአስር ጎማ የጭነት መኪና ቢመጣም ሙሉ በሙሉ ከነተሽከርካሪው መደምሰሱም አስታውቋል።
በዚህ የተናደደው የከተማዋ ከንቲባ ነው የሚባለው ባንዳና ቡድኑ የከተማዋን ወጣትና ነዋሪ ሲደበድቡና ሲያሰቃዩት መዋላቸውንም ገልጹዋል።
ከለሊቱ 12 ጀምሮ እስከ 6 ሰአት ሲራገፍና ሲከመር የዋለው ይህው ቡድን አክሬኑንና ቁስለኛውን ሰብስቦ ሚጭንበት ሲያጣ የግለሰቦችን ተሽከርካሪና ባጃጅ ጭምር በግዴታ በመቀማት መውሰዱንም አርበኛ ጋዜጠኛ ቴድሮስ ከበደ ባደረሰን መረጃ አመልክቱዋል።
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
13/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
እናውቃለን፣ የወደብ አጀንዳው የአረብ ኢምሬቶች ነው፣ የአብይ አህመድ አይደለም፣ እርሱ ተላላኪ ነው። ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቄ
"ፋሽስታዊ እና ህዝብ ጠሉ ብልፅግና አገዛዝ ከሚያጯጩኸው የባህር በር አጀንዳ ጀርባ የአረብ ኤምሬቶች ወደብን ጠቅልሎ የማስፋፋት ፍላጎት አለ" በማለት የኤርትራው ፕሬዝደንት ሲናገሩ ተደመጡ።
"በግልፅ ሲታይ እነዚህ የብልፅግና ፓርቲ አጀንዳዎች በመሉ፣ የብሄራዊ ጥቅም አጀንዳ ሳይሆኑ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዝደንት [መሐመድ ቢን ዛይድ] ያላቸው በቀጠናው ወደቦችን አስፋፍቶ የመያዝ አጀንዳ አካል ነው።"
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
12/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የፋሽስቱ ኃይል በጅምላ ተቀበረ‼️
በደጋ መልካ በተካሄደ እልህ አስጨራሽ ውጊያ አንድ ኦራል ተሽከርካሪ ሙሉ የሰው ሃይል ተደምስሷል።
በጎንደር እብናት የአለቆቹና የጓደኞቹን አስከሬን ሊለቅም በ11 ተሽከርካሪ ተጭኖ ወደ ደጋ መልዛ ከመጣው የሰው በላና የባንዳ ቡድን አንድ ኦራል ሙሉ ሃይሉን እንደጫነ ገደል ገብቶ ማለቁን የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መልካሙ ጣሴ ገለጸ።
በአካባቢው ከ70 በላይ የባንዳውን ቡድን ጨምሮ ከ300 በላይ የሚሆነው ሃይል ሰሞኑን በነበረው ውጊያ በአካባቢው መደምሰሱን ይናገራል።
እናም ይሄ ገዳይ ቡድን የአለቆቹን ጨምሮ ከ300 በላይ የሚሆነውን የሰው በላውን ቡድን አስከሬን ለመልቀም ከ700 እስከ 800 የሚደርስ ሃይሉን በ11 ኦራል ተኸርካሪ ጠቅጥቆ ወደ ደጋ መልዛ መምጣቱን አስታውቋል።
ይሄ ቡድን አስከሬኑን ለመልቀም ሲመጣ ደግሞ አቅጣጫ ቀይሮና የባንዳው ቤተሰቦችን ልጆቻችንን አምጡ ጥያቄን ለመሸሽ ጭምር ነበር ይላል።
ነገር ግን ከመቀጠዋ ተነስቶ ደጋ መልዛ የደረሰው የእቴጌ ጣይቱ ክፍል ጦር ፋኖ አካባቢውን መክበቡን የሰማው ገዳይ ቡድን ተቆርጬ እንዳልቀር በሚል ከ80 በላይ የሚሆነውን ሃይሉን ከአቅም በላይ በአንድ ኦራል ከአቅም በላይ ጠቅጥቆ ለማምለጥ መሞከሩን ይናገራል።
ነገር ግን ብዙም ሳይርቅ ጨጨሆ አቦ ላይ ገደል ገብቶ ወደ እብናት ሆስፒታል ከተወሰዱትና በከባዱ ከቆሰሉት ውጪ ከ70 እና ከ75 በላይ የሚሆነው ሃይሉ በሙሉ አልቆ በጅምላ መቀበሩን በአይናችን አይተናል ይላል።
የተርፈውም ሃይል ከመከበቡና ከመቆረጡ በፊት ፈርጥጦ ደብረታቦር መግባቱንም ነው የገለጸው።
Ethio 360
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
12/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የዓለም ባንክ ገምጋሚ ቡድን ላከ‼️
ዓለም ባንክ፣ በኢትዮጵያ በገንዘብ የሚደግፋቸውን በርካታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም የሚገመግሙ በርካታ የባለሙያዎች ቡድኖች ማሠማራቱን ከባንኩ ምንጮች መስማቱን በመጥቀስ ሪፖርተር ዘግቧል። ቡድኖቹ የአፈጻጸም ችግሮች ባሉባቸው ፕሮጀክቶች ላይ ማስተካከያዎችን እንደሚደርጉ፣ የቴክኒክ ምክሮችን እንደሚሠጡና ፕሮጀክቶቹ የማኅበራዊና የአካባቢ ጥበቃ መርኾዎችን ያከበሩ መኾናቸውን እንደሚያረጋግጡ ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ባንኩ ባንድ ጊዜ በርካታ የፕሮጀክት ገምጋሚ ቡድኖችን በአገሪቱ ማሠማራቱ "ያልተለመደ" ወይም "የተለየ ትርጉም" የሚሠጠው ነገር እንዳልኾነ ጋዜጣው ላቀረበው ጥያቄ የባንኩ ሃላፊዎች ምላሽ ሠጥቷል ተብሏል። ዓለም ባንክ ባኹኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ በክልሎችና በአገር ዓቀፍ ደረጃ የሚተገበሩ 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር የተመደበላቸው 47 የልማት ፕሮጀክቶች አሉት።
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
12/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
🔥የሁለቱ አባይ ሸለቆ ብርጌድ አስደናቂ ጀብድ‼️
ዛሬ ሀምሌ 12/2017ዓ.ም
ሁለቱ ወንድማማች ብርጌዶች በመካነ ሰላም ሀሙስ ገበያ ፣መቅደላ ከተማ እና ተዋ በተባሉ ከተሞች በአረመኔዉ ሰራዊት ላይ ጥቃት በመፈፀም ሀሙስ ገበያን የተቆጣጠሩ ሲሆን በተጨማሪ ሁለት ከተሞች ላይ ከፍተኛ ዉጊያ ተከፍቷል::
አፋጎ 9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር አባይ ሸለቆ ብርጌድ ፍፁም ሻለቃ ሻለቃ 1 የአባይን ድልድይ ተሻግሮ ከአፋብኃ ቁ2 አባይ ሸለቆ ብርጌድ ጋር በጋራ በመሆን በመካነ ሰላም ለሊቱን በአረመኔዉ ወታደር ላይ ጥቃት ፈፅመዋል።
አ.ፋ.ጎ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር አባይ ሸለቆ
ብርጌድ ሻለቃ 1 እና አ.ፋ.ብ.ኃ ኢንጂነር ደሳለኝ ክ/ጦር ወሎ ቀጠና ቁ2 አባይ ሸለቆ ብርጌድ በጋራ ጥምረት በመፍጠር በመካነ ሰላም መቅደላ ከተማ ተዋ እና ሀሙስ ገበያ በተባሉ ሶስት ከተሞች ላይ ዉጊያ በማድረግ ድል ተቀናጂተዋል።
በሶስቱም ከተሞች የአረመኔዉ ወታደርና ሆዳደሩ የአማራ አድማ ብተናና ሚሊሻ የመሸገበት ቢሆንም የጀግኖቹ ልጆች ከለሊቱ 8:00-12:30 ድረስ በተለያዩ አቅጣጫወች በሚገርም ቅንጂት በየምሽጉ በርካታ ቦንቦችን በመጣል ዉጊያዉን ጀምረዉ በድል አጠናቀዉታል።
የአባይ ሸለቆ ብርጌድ ሻለቃ 1 ከዚህ ቀደም በመርጦለ ማርያም በተደረገ ተደጋጋሚ ዉጊያ ብዙ የሰዉና የመሳሪያ ምርኮ ያገኘና የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ በሆነዉ የሚሊሻ ተቋም ላይ እንዲፈራርስና ተስፉ እንዲቆርጥ ካደረጉ ሻለቃወች ግንባር ቀደሙ የሆነና በተደጋጋሚ ምሽግ ሰባሪ መሆኑም ይታወቃል።
ሻለቃዉ ዛሬም በመካነ ሰላም ሀሙስ ገበያና ተዋ በተባሉ ከተሞች ሰፍሮ የነበረዉን አማራ ጠል አረመኔ ወታደር ሲያደባየዉ ያደረና በርካቶችን ወደላይኛዉ የሸኘበት እና ህዝቡን ያስደሰተበት ከወንድም አፋብኃ ብርጌዶች ጋር ከፍተኛ የቀጠና ትስስር የታየበት እና ወደፊትም በጋራ የተጠና ስራ መስራት የተሻለ ዉጤት እንደሚያስገኝ ያዩበት ዕለት ሆኖ ዉሏል።
ለሊቱን ባላሰበዉና ባልጠበቀዉ ሰዓት ጥቃት የተከፈተበት ጠላት አመት ሙሉ የገነባዉ ምሽግ ተርብ ከሆኑ የፋኖ ጥይት ግንባሩን ከመባል ሊያድኑት አልቻሉም።
ጥቃቱን መቋቋም ያቃተዉ የብርሃኑ ጁላ ወታደር ነፍሱን ለማትረፍ ጥይቱን ወደሰማይ በሩምታ የድረሱልኝ ጥሪ ሲያሰማ ያደረ ሲሆን የሞተዉ ሞቶ የቀረዉን በከባድ መሳሪያ ሽፋን በመስጠትና ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ሰራዊት ወደቦታዉ በማንቀሳቀስ ማትረፍ ችለዋል።
ከአራት ሰዓት በላይ በቆየዉ እልህ አስጨራሽ ዉጊያ ለግዜዉ ቁጥሩ ያልታወቀ ሻንበል መሪዉንና በርካታ አባሎቹን ሙትና ቁስለኛ ያደረጉት ሁለቱ ወንድማማቾች አ.ፋ.ጎ አባይ ሸለቆ ብርጌድና አ.ፋ.ብ.ኃ ወሎ ቀጠና ቁ2 አባይ ሸለቆ ብርጌድ በጋራ ጥምረት በሰሩት ኦፕሬሽን በርካታ ድሎች ያገኙና አድማ ብተናዉ እርስ በርሱ እንዲታኮስ የሆነ ሲሆን አሁንም ለተጨማሪ ጥቃት ቦታወችን ከበዉ የያዙና ሀሙስ ገበያን እንደተቆጣጠሩ ይገኛሉ።
፦ወደፊትም የቀጠና ትስስሩ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል።
በጋራ መናበብና ወንድማማችነት ለህዝባችን ለአላማችን በፅናት እንቆማለን እናሸንፋለን
©አ.ፋ.ጎ 9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር
የህ/ግንኙነት ፋኖ ዘላለም ደስታ
12/11/2017 ዓ.ም
የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
11/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
+3
#ሞላሌ ከተማ በፋኖ እጅ ገባች‼️
የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር ክፍለ ጥሮች ከእዙ ቃኝ ጋር በጋራ በመሆን ባካሄዱት ውጊያ የሞላሌ ከተማን መቆጣጠራቸው ታውቋል።
ለተከታታይ ቀናት በዘመቻ ሰማእታት ውጊያቸውን በየግንባሩ ሲያደርጉ የቆዩትና በኮሩስር ያሉት ራንቦ ክፍለጦር፣ የምኒሊክ ክፍለጦር ፣ የዕዙ ቃኝ እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር እንዲሁም አባት አርበኞች ዛሬም ከለሊቱ 11 ጀምሮ ይህንን የሰው በላና የባንዳ ቡድን ገና ከማለዳው ገጥመው እያራገፉት መሆኑን ይናገራል።
እነዚህ ውጊያዎች በሁለት ከተሞች የተካሄዱ ሲሆን በሁለቱ ከተሞችም የወገሬ እና የሞላሌ ከተሞች መሆናቸውንም የኮሚኒኬሽን ክፍሉ በመረጃው አስፍሯል።
በሁለቱ የመንዝ አውራጃ ከተሞች በተመሳሳይ ሰዓት ከለሊቱ 11:00 የጀመረውና በመናበብ ይሄንን ገዳይ ቡድን እያራገፈው ያለው የፋኖ ሃይል በዚህ ውጊያ የመንዝ ማማ ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችውን የሞላሌ ከተማን በእጁ ማስገባቱን የራንቦ ክፍለጦር የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ፋኖ ግዛቸው አጋጨው ለአፄ አምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ባደረሰው መረጃ ማስታወቁንም ይናገራል።
ይሄ ዜና እየተጠናቅረ ባለበት ሰአትም በሁለቱም ግንባሮች ተጠናክሮ የቀጠለው ውጊያ ይህንን ገዳይና ባንዳ ቡድን አስከሬንና ቁስለኛ በማድረግ ቀጥሏል ሲልም የአፄ አምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ባደረሰን መረጃ አመልክቷል።
Ethio 360
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
11/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
#Update;
#ካህኑ_ተረሽነዋል!
እናት ፓርቲ ሐምሌ 5 ቀን ባወጣው የሐዘን መግለጫ፣ በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ፣ ሰኮራ ኪዳነ ምኅረት አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወንድማቸው ወገኔ ጌታነህ ታፍነው መወሰዳቸውን ገልጸን ነበር። ዛሬ ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በደረሰን መረጃ መሠረት ካህኑና ወንድማቸውን ቤታቸው ድረስ በማምጣት ረሽነዋቸው ሄደዋል።
ፓርቲያችን የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ፤ የሃይማኖት አባቶችን ዒላማ ያደረገ የታቀደ ግድያ በጽኑ ያወግዛል።
ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!
እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፲፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
#የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ
11/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
+1
የHIV መድሃኒት በይፋ ጥቅም ላይ ሊውል ነው‼️
የኤችአይቪ መድሃኒት
በቅርቡ በአለም ጤና ድርጅት ተገምግሞ ተግባር ላይ እንዲውል የተፈቀደውን "Lenacapavir" የተባለውን አዲሱን የHIV መድሀኒት ሀገራት እንዲጠቀሙ የአለም ጤና ድርጀት ምክርሃሳብ መስጠቱን CNN ዘግቧል ። መድኃንቱን በቅድሚያ ለቫይረሱ እጅግ ተጋላጭ የሆኑ አካላት መጠቀም እንዳለባቸው የተብራራ ሲሆን መድሃንቱ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የራሱን ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል ። የአለም ጤና ድርጅት ለመድኃኒቱ እውቅና ሰጥቶ በተግባር ላይ እንዲውል ማረጋገጫ የሰጠ ቢሆንም ወደ አፍሪካ እና ሌሎች ደሃ ወደሆኑ ሀገራት ዘንድ መቼ ልደርስ እንደሚችል አይታወቅም ።
መረጃው የCNN ነው።
#ሞዐ ሚዲያን በየገፃችሁ ሸር በማድረግ፣ የመረጃ ቋቷን በመቀላቀል የሀቅ አምሓራዊ ሰልፉን አግዙ፣ በቅርቡ We are coming to You Tube!‼️‼️‼️
የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
1 261
Repost from ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
⚖⚖⚖⚖ሞዐ ችሎት⚖⚖⚖⚖
============================
በተለያዩ መዝገቦች በሽብር ወንጀል የተከሰሱ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ሀምሌ 4/2017 ፍ/ቤት ቀርበው ሂደቱን ተከታትለዋል።
አውሎግሶን አንድነት-Awulogson Andinet ፣ ሀምሌ 4/2017 ፣ አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ
በተለያዩ መዝገቦች የአማራ ማንነታቸውን እንደ ወንጀል በቆጠረው የኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ሀምሌ 4/2017 በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበዋል።
ከመከላከያ ፣ ከፌደራል ፖሊስ ፣ ከዐቃቤ ሕግ እና ከማ/ቤት ቀጥሎ ፍ/ቤት የአገዛዙ የጭፍን ጥላቻ እና የሀሰት ትርክት ፖለቲካ ማስፈፀሚያ ሆኗል በሚል በበርካታ የማንነት ፣ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ዘንድ በየጊዜው እየተወቀሰ መሆኑ ይታወቃል።
ሀምሌ 4/2017 በነበረው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ችሎትም በ4 የተለያዩ መዝገቦች የተካተቱ የግፍ እስረኞች ከማ/ቤት ቀርበው ሂደቱን ተከታትለዋል።
(1) በእነ ዶ/ር ወንድ ወሰን አሰፋ መዝገብ ፦
ተከሳሾች በቀደመ ቀጠሮአቸው መሰረት በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ተገኝተዋል።
መዝገቡ የተቀጠረው ዐቃቤ ሕግ ቀሪ ምስክሮችን ለማስመስከር ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ በሚል አቤቱታ ማቅረቡን ተከትሎ በከሳሽ እና በተከሳሾች ጠበቆች መካከል የተደረገውን ክርክር መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር።
በመሆኑም በእለቱ ፍ/ቤቱ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠውን በቂ ጊዜ በአግባቡ ተጠቅሞ ምስክሮችን ለማቅረብ አልቻለም በሚል እስካሁን የመሰከሩት የ67 ምስክሮችን ቃል መርምሮ ብይን እንደሚሰጥ አሳውቋል።
እስካሁን ከ96 ምስክሮች መካከል 67 የመሰከሩ ሲሆኑ 2 የሚሰጡት ቃል ተመሳሳይ ነው የተባሉ በድምሩ 69 ምስክሮች የቀረቡ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ዐቃቤ ሕግ ከግንቦት 5 እስከ ሰኔ 16/2017 ድረስ የተሰጠውን 41 ቀናት ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲልም የ56 እና 54 ቀናት ረዣዥም ቀጠሮዎች የተሰጡት ቢሆንም ጊዜውን በአግባቡ ለመጠቀም አልቻለም ብቻ ሳይሆን ምስክሮችን ላለማቅረቡ የሚሰጠው ምክንያትም ተመሳሳይና የማያሳምን ነው በማለት ነው ተጨማሪ ጊዜ መሰጠት ተገቢ አይደለም ሲል የወሰነው።
ስለሆነም ጠበቆች በሰነድ ማስረጃ ላይ አስተያዬት እንዲሰጡ በሚል ለሀምሌ 8/2017 ቀጠሮ ይዟል።
(2) በእነ እስራኤል መስፍን መዝገብ ፦
በዚህ መዝገብ ፋኖን በመቀላቀል እና ስልጠና መስጠትን ጨምሮ በተለያየ መልኩ በመደገፍ በሚል የሽብር ወንጀል ሁለት ሰዎች የተካተቱ ሲሆን በእለቱ ከቂሊንጦ ማ/ቤት በችሎት ተገኝተዋል።
መዝገቡ የተቀጠረው የዋስትና ክርክር ለማድረግ ሲሆን በከሳሽ ዐቃቤ ሕግ እና በተከሳሾች ጠበቃ መካከል የዋስትና ክርክር ተደርጓል።
በመጨረሻም ፍ/ቤቱ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት በሚል ለሀምሌ 15/2017 ቀጠሮ ሰጥቷል።
(3) በእነ ዘነበ ሽታ መዝገብ ፦
ተከሳሾች በችሎት የተገኙ ሲሆን መዝገቡ የተቀጠረው ተከሳሾች የመከላከያ ምስክሮችን እንዲያሰሙ በሚል ነበር።
ይሁን እንጅ ተከሳሾች የመከላከያ ምስክሮችን ከማሰማታችን በፊት ዐቃቤ ሕግ አለ ያለውን የሲዲ ማስረጃ እንድንሰማ በማ/ቤት በኩል ይመቻችልን ሲሉ ጠይቀዋል።
ፍ/ቤቱም ለጥቅምት 27/2017 ተለዋጭ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን እስከዚያው ግን የቂሊንጦ ማ/ቤት የሲዲ ማስረጃውን ማዳመጥ የሚችሉበትን ሁኔታ እንዲያመቻችላቸው ትዕዛዝ ሰጥቷል።
(4) በእነ ተመስገን ጌትነት መዝገብ ፦
በመዝገቡ በሌሉበት የተከሰሱትን 3 ሰዎች ጨምሮ 12 ሰዎች ተካተዋል ፤ ከመካከላቸው 9 የሚሆኑት ተከሳሾች ከቂሊንጦ ማ/ቤት በችሎት ተገኝተዋል።
ቀጠሮው የተሰጠው ዐቃቤ ሕግ ቀሪ ምስክሮችን አቅርቦ እንዲያሰማ በሚል ነበር።
ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ከ2 ወራት ጊዜ ቀጠሮ በኋላ ምስክሮችን ለማቅረብ አለመቻሉ ታውቋል።
ጠበቆችም ዐቃቤ ሕግ ምስክር አቀርባለሁ በሚል ሆነብሎ ደንበኞቻቸውን እያጉላላ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁን እንጅ ፍ/ቤቱ እንደገለፀው ዐቃቤ ሕግ ለሀምሌ 7/2017 የተፈቀደለት ጊዜ ስላለው በእለቱ ቀሪ ምስክሮችን ለማቅረብ ካልቻለ መከራከር እንደሚቻል ጠቁሟል።
ዐቃቤ ሕግ በእነ ተመስገን ጌትነት መዝገብ 25 ምስክሮች አሉኝ ቢልም እስካሁን 12 ብቻ አስመስክሯል።
ፍ/ቤቱ "የዘገዬ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል" የሚል መፈክር ቢኖረውም በተግባር ግን ከመፈክር ባለፈ ሲፈፅመው አይስተዋልም።
የሞዐ ሚዲያ ቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላችን join አድርጉ።
#ድል ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ሐምሌ 03/2017 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
@Moamediamoresh
https://t.me/moaamediaamharawi
https://t.me/Moamediamoresh
