9 220
Subscribers
-1024 hours
-987 days
-36630 days
Posts Archive
9 224
.
.
ታላቅ የፓናል ውይይት ... በቲክቶክ መድረክ ! ! !
ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሰማባቸውን መድረኮች አብዝቶ ለፈጠረው አምላክ ምስጋና ይገባ። ታሪካዊውን የፓናል ውይይት በመስጂድ ልናከናውን ቀጠሮ የያዝን ቢሆንም የመሰብሰብ እና የመወያየት መብታችንን በመንፈግ እንደተከለከልን የሚታወስ ነው። ሆኖም እነርሱ ከለከሉን ማለት ዝም ብለን እንቀመጣለን ማለት አይደለም። በሰፊው፣ ሁሉም በያለበት ሆኖ ይታደም ዘንድ በተመቻቸ ሁኔታ፤ ርዕሶቹም ሰፋ ብለው፤ በቅርቡ በቲክቶክ ታላቅ የፓናል ውይይት የሚኖረን ይሆናል።
የክብር እንግዶቻችን እንዳሉ ሆነው፤ መምጣት ሳይችሉ ቀርተው ሲቆጩ የነበሩት ባሉበት ሆነው እንዲሳተፉ በሚያስችል መድረክ፤ በውጭ ሀገርም ሆነው በሀገር ውስጥ ያሉ ተማሪዎች እና መላው ሕዝበ ሙስሊም የሚሳተፍ ይሆናል።
እስከዚያው መልዕክቱን ለሁሉም አድርሱ። የቲክቶክ ገፃችንን https://www.tiktok.com/@aaumsu?_r=1&_t=ZS-97D9UHuTcGO በመግባት Follow አድርጉ።
የሚታፈን ድምፅ የለም ! ለበዳዮች እጁን የሚሰጥ ትውልድም አይኖርም !!
ጥያቄ አለን ... ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
✍#fozi
9 224
.
.
#ብዥታ 🌑
ክፍል 13
በሩ ጋር ደርሼ ማንኳኳት ጀመረኩኝ እየተማሩ ስለነበር ክፍሉ ፀጥ ረጭ ብሏል አስተማሪው ወደኔ መጥቶ ምን እንደፈለኩኝ ጠየቀኝ አህመድን እንዲጠራልኝ ነገርኩት አህመድ ወደኔ መጣ የፈራሁት ባለመፈጠሩ አላህን እያመሰገንኩኝ ወደ አባቴ አደረስኩት ተያይዘው ዳይሬክተሩ ቢሮ ገቡ እኔም ውድ ክፍል ገባሁኝ ከዛ በኋላ አባቴ ብዙ ጊዜ ድንገት ትምርት ቤት መምጣት ጀመረ ታዲያ አንድ ቀን አህመድ ክላስ ፎርፎ ሲያጨስ አባቴ አየው ከዛ በኋላ አህመድ ቀጥታ ወደ መርከዝ ነበር የገባው እናቴ በጊዜው ከልክላ የነበረ ቢሆንም በአባቴ ምክንያት ሁለት አመት ቁርዓን ቀርቶ ወጣ ከዛ በኋላ አህመድ ተቀየረ እንደምታዪው ነው ቁጥብ ሆነ እንደውም ካንቺ ጋር ይቀራረባል ከአክስቶቼ ልጆች ጋር እንኳን አንድ ቤት ውስጥ አይቀመጥም አለችኝ ምናለ የድሮውን አህመድ ባውቀው ብዬ ተመኘሁኝ ቀኑን ወሬ ጨርሰን ተለያየን በማግስቱ ልንገናኝ ተነጋግረን ተለያየን
ሄለው አባቢ
ወዬ ኢሙ የት ነሽ ግርግር ይሰማኛል ?
እነ ኢኑ ጋር ሄጄ ነበር ታክሲ አጥቼ ቆሜያለው አልኩት
በቃ እዛው ጋር ጠብቂኝ መጣሁኝ ብሎ ስልኩን ዘጋው አርፍጄ ስለወጣሁኝ ታክሲ አዛ ነው በዛ ላይ ጨለምለም ብሏል አባቢ እስኪመጣ ኤርፎኔን ከቦርሳዬ አውጥቼ ዘፈን መስማት ጀመርኩኝ
"'ካንተ መለየቱ ምን ሆዴን ቢያስብሰው
እህል አልጣ እንጂ ምበላው ምቀምሰው
ፍቅርን ተርቦ የለም የሞተ ሰው"'
ማሜን ካኮረፈኝ ወዲ ዘፈን መስማት ጀምሬያለው ከዛም አለፍ ብሎ ቁርዓን ቤትም አልፎ አልፎ እንጂ አልገባም ቆሞ ይጠብቀኝ የነበረበትን ሳይ ይደብረኛል ያንን ቦታ ላለማየት በዛ ሰፈር አላልፍም ዘፈኑ አልቆ ሌላ ዘፈን ጀመረ
ይጠንክር.... ያርግልኝ እንጂ ልቤን አለት......... በጣም ጨልሟል አባቢ ምን ሆኖ ነው የቆየው ብዬ እያሰብኩኝ አባቢ ደወለ
"'ኢሙ የቱ ጋር ነሽ?"'
' ታክሲ መያዣው ጋር ቆሜያለው አልኩት '
አባቢ አይቶኝ ወደኔ መጣ ተቀምቼበት ከነበረው የሊስትሮ ወንበር ተነስቼ ወደሱ መሄድ ጀመርኩኝ አባቢን ሰላም ብዬ ይዞት ወደመጣው መኪና ገባን መቆጣት ጀመረ ሴት እንደሆንሽ ረሳሽው እንዴ? በዛ ላይ ህፃን ነሽ እንዴት እስከዚ ሰዓት ታመሻለሽ? አባቢ ይቅርታ ብዬ ሳምኩት የወላጅ አንጀት እሩህህ ነውና ወዲያው ቁጣው ወደ ፍቅር ተቀየረ
"የኔ ልጅ የሴት ልጅ ሂወት አንዴ ከተበላሸ ተበላሸ ነው ወንድ ልጅ በሴት ላይ ደደብ ነው አያዝንም" ብሎ እየመከረኝ ቤት ደረስን
ቤት ገብተን እንደ ነገሩ እራት በልቼ ከወንድሜ ጋር ተኛን ቀጣዩ ቀን እንደ ተለመደው እነ ኢኑ ጋር ሄድኩኝ አባቢ ከከባድ ማስጠንቀቂያ ጋር ነው ዛሬ እንድሄድ የፈቀደልኝ በጊዜ እንደምመለስ ቃል ገብቼለት ወጣሁኝ እነ ኢኑ ቤት ደርሼ ማንኳኳት ጀመርኩኝ የሆነች ትንሽዬ ልጅ በሩን ከፈተችልኝ ወደ ውስጥ ሳይ ብዙ ጫማዎች ታዩኝ ለልጅቷ ኢኑን እንድትጠራኝ ነግሬያት ከጊቢ ውጪ ቆምኩኝ ማሜ እና አህመድ ሲመጡ አየኋቸው ማሜን በማየቴ ደስ አለኝ ግን እኔን ሲያይ ዞሮ መመለስ ጀመረ አህመድ አጠገቤ ደርሶ 'እሺ ወይዘሪት ዛሬ ደግሞ አትገቢም እንዴ አለኝ?' አዎ ቤት ውስጥ እንግዳ አለ መሰለኝ ልመለስ አልኩት ’የምን መመለስ ነይ ግቢ' ብሎ በሩን ከፈተው አህሚ አልገባም አልኩት ትገቢያለሽ አለኝ ቆጣ ብሎ አልገባም ግርግር እንደማልወድ ታውቃለህ አልኩት
ስንከራከር ኢኑ ትገቢያለሽ ብላ እጄን እየጎተተች በጓሮ በር ወደሷ ክፍል አስገባችኝ "በሰላም ነው ይሄ ሁሉ ሰው' አልኳት ሂጃቤን መሬት ላይ ጥዬ ጋውኑ አባያዬን እያወለኩኝ አዎ ባክሽ የነኡሚ ዘመዶች ናቸው ለቅሶ ለመድረስ ከክፍላገር መተው ሊዘይሩን ገብተው ነው አለችኝ አይ ጥሩ ነው እኔኮ ልመለስ ነበር አልኳት ከሰው አልተፈጠርሽም እንዴ ለምን ሰው ትሸሻለሽ አለችኝ "የኔ አሮጊት እርቦኛል ሚበላ ካለ አምጪልኝ አትነዝንዢኝ ብዬ አልጋዋ ላይ በቁሜ ወደኩኝ እኔስ እችልሻለው ይብላኝ ለባልሽ ዝርክርክ ብላ የጣልኳቸውን ልብሶቼን አስተካክላ ልታመጣ ወጣች
እሷ ከመውጣቷ አህመድ ወደ ክፍሉ ገባ እኔ በጀርባዬ ተንጋልዬ ስልክ እየነካሁኝ ነበር ሲያየኝ ደንግጦ ወጣ እኔም በድንጋጤ ብርድ ልብስ ውስጥ ገባሁኝ ስራዬ እያሳቀኝ አይኔ አንድ የዲያሬ ደብተር ላይ አረፈ ለማየት ከአልጋው ወርጄ መራመድ ስጀምር ኢኑ ምግቡን ይዛ መጣች ተመልሼ የተፈጠረውን ነገርኳት በሳቅ ፍርስ ብላ ውሃ ለማምጣት ወጣች ተንደርድሬ ደብተሩን አንስቼ ደበኩት ውሃውን ይዛ እየሮጠች የክፍሉን በር ዘግታ መሳቅ ጀመረች አብረን በልተን እቃውን ማነሳሳቭ ጀመረች እኔ ሂጃብ ስላለበስኩኝ ከክፍሉ አልወጣም ኢኑ ወጥታ ስትቆይ ደብተሩን ገለጥኩት...............
ከ50❤️ በኋላ ይቀጥላል
ቶሎ ቶሎ እንዲለቀቅ አንብባቹ ስትጨርሱ 🥰👍❤️ ማድረግ እንዳትረሱ
✍#fozi
9 224
+1
.
.
ስራ ያጣ መነኩሴ
over time ይቀድሳል ማለት ይሄ ነው🤭
ግን ይቺ ai የምትባለው ነገር ታውቃለች ልበል ወይስ ሸይጣን ናት 👹🤔
አሰማመጠችኝ እኮ 🥲😅
መልካም ምሽት እና ጣፋጭ ህልም ይሁንላቹ🥰
✍#fozi
9 224
የአለማችን ዉዱ ሰዓት በምስሉ ላይ የምታዩት "Graff Diamonds Hallucination" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ለመስራት ደግሞ ከ2 ዓመት በላይ ይፈጃል። ዋጋው 55 ሚልዮን ዶላር ነው ወይም በኢትዮጵያ ሲመነዘር ከ8 ቢልዮን የኢትዮጵያ ብር በላይ ነው!😳
ለመግዛት inbox 🥀
@esm_halal @esm_halal✍#fozi
9 224
.
.
#ብዥታ🌑
ክፍል 12
አንድ ቀን እነ ኢኑ ጋር በሄድኩበት ከማሜ ጋር ተገናኘን ሁሉንም ሰላም ብያቸው ተቀመጥኩኝ እኔ ስቀመጥ ማሜ "'በቃ ልሂድ"'ብሎ ተነሳ ተከትዬው ወጣሁኝ ስጠራው ባልሰማ ትቶኝ ከጊቢ ወጣ ሮጬ እጁን ያዝኩት ማሜን ምን አጥፍቼ ነው በዝምታ የምትቀጣኝ?🥺
ምንም መልስ ሳይሰጠኝ አመናጭቆ እጁን ነጥቆኝ ሄደ ከዛ ቀን በኋላ እኔ ለማኝ እሱ ተለማኝ ሆነ ስራዬ ማልቀስ ሆነ በሁለታችን ምክንያት ጀማው ሚደብር ሁኔታ ላይ ወደቀ ክላስ መተው ካላገኙኝ እኔ እነሱ ጋር መሄድ ተውኩኝ ናቲ በኔ የመጣ ከማሜ ጋር ተኮራርፏል ከኤፊ ጋር ግን ተቀራርበዋል በፊት ማሜ እኔን እንደሚያደርገኝ እስከ ቤቷ ይሸኛታል ማሜ ከሴቶቹ ጋር ብቻ ነው የሚያወራው እኔና ናቲን ዘግቶናል በሁሉም አስለምኜዋለው የቀረኝ የኢኑ ወንድም አህመድ ብቻ ነው ለሱም እንዲያስታርቀን ስነግረው ያለ ኒካ ፍቅር ምንም ነው ብሎ ልቤን ሰበረው
አህመድ ጥሩ ልጅ ነው ግን በጣም ኮስታራ እና አንዳንዴ ደግሞ ገገማ ይሆናል ቀልድ አያውቅም ቢቀልድም ለትንሽ ደቂቃ ብቻ ነው በተለይ ከሱ ጋር ስለፍቅር ማውራት ሃራም ነው "'ያንተ ሚስትማ ፈረደባት ምን ብለህ ልታገባት ነው?"' ብለን ስንጠይቀው በጊዜው እናያለን ይለናል "'ጊዜው አሁን ቢሆንስ ምን ብለህ ልታገባት ነው?"' አልኩት
"አንቺን ሳስብ ለሊቱ እንደ ሱረቱል በቀራ ይረዝምብኛል ሳይሽ ደግሞ እንደ ሱረቱል ከውሰር ያጥርብኛል ብዬ ነዋ አለኝ" አህሚ ግን ፍቅር ይዞህ ያውቃል ?
የሚያስደነግጥ አነሳስ ተነሳና ሄደ እኔ ግራ ገብቶኝ ኢኑ ምን ተፈጥሮ ነው? አልኳት ""ባክሽ እሱ ሁሌ እንዲ ነው ፍቅር ሲባል ጂኒው ይነሳበታል ምን እንዳደረገችው አላህ ይወቀው አለችኝ"" እና ትከሻዬ ላይ ተኛች
ማናት? አልኳት ስለ አህመድ ብዙ የማታውቂው ነገር አለ አለችኝ እና ከትከሻዬ ላይ ተነስታ ለማውራት ተስተካክላ ተቀመጠች
አህሚ እኔን በ4 አመት ይበልጠኛል ከ2 አመት በፊት ዘጠነኛ ክፍል ሳይጨርስ ነው አባታችን ወደ ሌላ ከተማ ወስዶ የሂፍዝ ማዕከል ያስገባው ምክንያቱ ደግሞ ሱስ ውስጥ ገብቶ ነበር ሳይሄድ የነበረው አህመድ እንደ ናቲ ነበር ውሎው ከሴቶች ጋር ነበር ጊቢ ውስጥ አንድም የምታመልጠው ሴት አነበረችም ነገር ግን ውጤቱም ከፍ ያለ ነበር የሆነ ጊዜ ላይ የአህሚ ውጤት ሲታይ በጣም ወረደ አባቴ ትምርት ቤት ተጠርቶ ሄደ እንደተለመደው በልጅህ ኮርተናል ሳይሆን ልጅህ ውጤቱ ወርዷል ተከታተለው አሉት አባቴ እሳት ለብሶ ወደ ቤት መጣ እናቴ ልታረጋጋው ብትሞክርም አልቻለችም እንደለመድነው እኔና አህሚ ቤት ስንገባ ያልጠበቅነው የአባቴ ቁጣ ወረደብን እኔ በድንጋጤ ሳላውቀው ማልቀስ ጀምሬያለው አህሚ ግን ምንም ሳይመስለው ትቶት ወደ ክፍሉ ገባ አባቴ የባሰ ተናደደ ወደኔ ሲዞር እያለቀስኩኝ መሆኑን አየ ለምንድነው የምታለቅሺው ብሎ ጮኸብኝ ሄጄ አቀፍኩት ወዲያው አባቴ ተረጋጋ ያንን ቀን እንደ ምንም አለፍን ነገር ግን አህሚ ከዛ በኋላ ተቀየረ ክላስ መፎረፍ ጀመረ ያ ሳይበቃው ትምርት ቤት አካባቢ ከሚቀመጡ ዱርዬዎች ጋር መዋል ጀመረ እኔን ትምርት ቤት ጊቢ አስገብቶኝ የሚወጣባቸው ጊዜያቶች በዙ አባታችን ካወቀ እንደሚገለው ያውቃል ግን እየፈራ ክላስ ይፎርፋል በወሬ ወሬ የሆነ ሪሃና የምትባል ልጅ እንደወደደ እና ፍቅሩን እንደ ገፋችበት ሰምቼ ነበር ወሬ ይሆናል ብዬ ስላሰብኩኝ ለማሜ ጠየኩት ማሜ እውነት እንደሆነ ነገረኝ
ልጆች ኑ ምሳ ደርሷል አለች የኢኑ እናት መጣን ኡሚ አለች ኢኑ እንዴ ኢኑ ሳትጨርሺልኝ ልንሄድ ነው? ስንመጣ እጨርስልሻለው
ኧረ አልኳት በጥርጣሬ አይን ወላሂ አለችኝ አህመድ መጥቶ ምን እንደ ባልና ሚስት ያደርጋቹዋል ኑ ውጡ ብሎ ተቆጣን በሱ ቤት ተቆጥቷል እኛ ግን በሳቅ ፍርስ ነው ያልነው ጅሎች ብሎን ወጣ ነይ እንሂድ እዚው ሆነን ድጋሚ ከመጣ በዱላም አይምረንም ገገማ ነው አለች ኢኑ ከቅድሙ ይበልጥ እየሳቅን ወደ ሳሎን ወረድን እኔና ኢኑ አንድ ላይ ኡሚ አህመድ እና አባቱ አንድ ላይ በልተን ጨረስን የተበላበትን ካጠብን በኋላ እንድትነገረኝ ጠየኳት እሺ ብላ ማውራት ጀመረች "ከዛ በኋላ ስራዬ ሪሃና የምባለዋን ሴት መከታተል ሆነ እሷም እንደ አህመድ ከብዙ ወንዶች ጋር ነው የምትሆነው በጣም ቆንጆ ናት አንድ ቀን አባቴ ወደ ትምርት ቤት ድንገት መጣ እኔን አስጠርቶኝ አህመድን ከክፍሉ እንድጠራው ላከኝ እኔም የአህመድን ስራ ስለማውቅ በፍራቻ ወደ አህመድ ክፍል ሄድኩኝ..............
#ክፍል 13 ከ50❤️ በኋላ ይቀጥላል
ቶሎ ቶሎ እንዲለቀቅ አንብባቹ
ስትጨርሱ🥰👍❤️ ማድረጋቹን እንዳትረሱ
✍#fozi
9 224
.
.
እውነትም ፍቅር እውር ነው 😤
አሁንስ ፍቅር ዘጋኝ zegan😪 ✋🏾🫥
በዚ ፎቶ ላይ የጠፋውን ሬሳ ታሪክ አስቡ...🫨
✍#fozi
9 224
❤️🔥"የጠፋው ሬሳ" *🥵
💝ልብ አንጠልጣይ ተከታታይ ታሪክ💝
_#ክፍል 2
...ስልኬን አወጣሁና ጓደኛዬ ጋር ደወልኩ "ሄሎ ባርሰናይት እንዴት አደርሽልኝ" አልኳት "ሜርሲዬ ሰላም አድሬያለሁ ባባ እኮ መኪናውን ይዞ እየጠበቅንሽ ነው" አለችኝ "እሺ ባርሳዬ አሁን እደርሳለሁ ቻው" ብዬ ስልኩን ዘጋሁት...ባባ ማለት የባርሰናይት ፍቅረኛ ነው...እኔ ብቻ ነኝ እንጂ ሁለቱ ጓደኞቼ ጥንድ ናቸው...ወደ ጉዞው አምስት ሆነን ነው ምንሄደው ከደቂቃዎች ጉዞ በሗላ ጓደኞቼ ጋር ደረስኩ...ከመኪና ውስጥ ከሹፌሬ ጋር ዕቃዬን አወጣንና የባባ መኪና ላይ ጫንን..."ምንም አይነት ነገር ቢፈጠር ወይም የሚያጠራጥር ሁኔታ ውስጥ ከገባሽ ደውዪልኝ" አለኝ እጅግ የዋሁና የሚያሳዝነኝ ሹፌሬ "እሺ እደውላለሁ" አልኩና እቅፍ አርጌ ተሰናበትኩት ሹፌሬ እስኪሄድ ድረስ ጓደኞቼ ትንፍሽ አላሉም ነበር ልክ እሱ እንደሄደ..."ሜርሲ" ብላ ቅድስት ከመኪናው ዘላ ወረደች "ቅድስቴ" ብዬ እቅፍ አርጌ ሳምኳት ተራ በተራ ሁሉም ሰላም አለኝ "Rav 4" መኪና ውስጥ ገብተን ጉዞ ወደ ውቧ ከተማ አዳማ ናዝሬት ጀመርን...ጓደኞቼ ከሚያረጉት ነገር የማረገው ቢኖር መብላት ብቻ ነው ግን ምንም ቢያረጉ በጣም ነው ምወዳቸው እነሱም እደ ፍላጎታቸው ባልሆንም በጣም ይወዱኛል ባባ ለስለስ ያለ ዘፈን እኔ ግን ብዙም የዘፈን አድናቂ አልነበርኩምና ኤርፎኔን አውጥቼ መዝሙሬን ከፈትኩ...
፡
"እንደ ዋላ ውሃ እንዳማረው፣
በበረሃ ጥም እንደያዘው፣
ልቤ አንተን ይላል(2)...የሚለውን የሊሊን መዝሙር ከፈትኩኝ ብዙም ሳልቆይ ቅድስቴ ነካ ነካ አርጋ ጠራችኝ ኤርፎኔን አውልቄ "ወዬ" አልኳት "ልናጨስ ነበር አይደብርሽማ" አለችኝ "መኪናውን አቁሙና አጭሱ እኔም ራቅ ብዬ እቀመጣለሁ ከዛ እንሄዳለን" አልኳቸው በሀሳቤ ተስማምተው መኪናውን አቆሙ..."ሁለት ስቲክ ብቻ ነው ምንነፋው ይቅርታ እሺ ሜርሲ" አለኝ ባባ "አይ ችግር የለውም" አልኩት የቆምንበት ቦታ ከከተማ ወጣ ብለን ስለነበር በቅርብ የሚታየኝ በዛፍ የተከበበ ስፍራ ብቻ ነው ኤርፎኔን ሰክቼ ወደ ዛፉ ውስጥ ጉዞ ጀመርኩ ውሎዬን እንደ አዲስ የሚያስጀምር ደስ የሚል ቅዝቃዜ አለው ፀጥታው ሰው ከራስ ጋር እንኳን ቢነጋገር ያስተጋባል ብል ማጋነን አይሆንብኝም ከዛፎች ፍትጊያ እና ከሚረገፉት ቅጠሎች ውጪ ሌላ ምንም ድምፅ የለውም ፍፁም ሰላም የሞላበት ስፍራ...ሳላስበው ወደ ውስጥ ብዙ ተጓዝኩኝ ጫካው እንዳለቀ መሀል ላይ እጅግ ፅዱ ሰማያዊ የፏፏቴ ውሃ አለ ከላይ ተምዘግዝጎ መሬት ያለውን ድንጋይ ሲመታው የሚፈጠረው ድምፅና ፍንጥርጣሪ የተለየ ድባብ አለው እዚ ስፍራ ላይ ለአንድ ቀን ካምፕ አርገን ብናድር ብዬ ተመኘሁ ግን ቦታው በምሽት እንደሚያስፈራ ምንም ጥርጥር የለውም አንዳች ብርሃን የማይገፈው ድቅድቅ ጨለማ ነው...ፊቴን ለመታጠብ ወደ ውሃው ተጠጋሁ ልክ ስነካው ፍል ውሃ ነው ይሄ ቦታ የቱንም ያህል ቢያስፈራ ማደር አለብን አልኩኝ ወዲያውኑ ወደ ጫካው ሠውጫ አመራሁ...ምንጣፍ ከአንድ ዛፍ ጥላ ስር ዘርግተው አራቱም ተኝተዋል ይሄን ያህል መቆየቴን አላስተዋልኩትም ነበር...እንደውም በእንቅልፍ ለዛለ ሰውነታቸው ፍቱን መነቃቂያ..."ሄይ ጋይስ" ብዬ ጨውኩባቸው "ውይ ሜርሲ የት ጠፍተሽ ነው" አለችኝ ባርሰናይት "እኔ ያየሁትን ብታዩ እዚ መቼም አትተኙም" አልኳት "ምን አየሽ ሜርሲዬ አሳዪና" ብላ ሌሎቹንም ቀሰቀሰቻቸው ያወጡትን ዕቃ ሁሉ ወደ መኪናው መለሱና እኔን መከተል ጀመሩ...ከደቂቃዎች በሗላ ፍል ውሃው ጋር ደረስን "ወይኔ በፈጣሪ ሲያምር" አለች ቅድስቴ ዘላ ለመግባት ልብሷን እያወላለቀች ሙሉ ዕርቃኗን ቀረች ምንም ልብስ ገላዋ ላይ አልነበረም ወዲያውኑ ዘላ ገባች "እንዲ ፍል ውሃ" አለች እየተገረመች ባርሰናይትም ማውለቅ ጀመረች እነ ባባም እንደዛው እኔ ግን ዝም ብዬ እነሱን ማየት ጀመርኩ..."ተቀላቀዪን እንጂ" አለ የቅድስት ጓደኛ ብዙም ደስ ስለማይለኝ መልስ እንኳን አልሰጠሁትም ነበር "ሜርሲ" አለኝ ባባ እሺ ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ...ለራሴ እስኪገርመኝ ድረስ እጅግ ትልቅ ቅርፅ ነው ያለኝ አነስ አነስ ያሉ ጡቶች ነጥብ የሌለበት ጥርት ያለ ገላ ነው ያለኝ...ወንዶቹ እኔ ላይ ማፍጠጥ ጀመሩ "አረ ጡት ማስያዣውን አውልቂው አለች ቅድስት በሀሳቧ አለመስማማቴን በጭንቅላቴ ንቅናቄ አሳየሗትና ዘልዬ ገባሁ...እኔ ቅድስቴ እና ባርሰናይት እየተረጫጨን መጫወት ጀመርን ወንዶቹ ዳር ይዘው ይመለከቱናል...እስኪደክመን ተጫወትንና "ወጣን ለምን ዛሬ እዚ ካምፕ አርገን ለምን አናድርም" አልኳቸው "በቂ መጠጥ እና ምግብ አለን ለዛሬ ይበቃናል እንደር" አለ የቅድስት ጓደኛ ባርሳም ተስማማች እነ ቅድስቴም ሀሳቤን ተቀበሉ ሰውነታችን እስኪደርቅ አንሶላ ላይ ጋደም አልንና ትንሽ ቆየን ከዛም ልብሳችንን ለብሰን ከመኪና ውስጥ ዕቃ ለማምጣት ሄድን...የተለያዩ መጠጦች ሚለበሱ ልብሶች እና ምግቦችን አወጣን እኔ ከአገልግሌ ውጪ ሌላ ምንም አልነካም...የሚጠጣም ነገር ፈልቶ የቀዘቀዘ ውሃ አለኝ..."አንዴ ተመልሰን የቀረውን ዕቃ እናምጣ" አለ ባባ እሺ ብለን ሁላችንም ተመለስን መኪናችን ጋ እንደደረስን እጅግ በፍጥነት የሚመጣ የተጋጨ መኪና ማንሻነት የሚጠቅም መኪና ሲመጣ ተመለከትን እየቀረበን ሲመጣ መስታወቱ ላይ እና የፊት የመኪናው ክፍል በደም ተጨማልቋል በጣም በፍጥነት አለፈን ባባ ግን "አንተ ደደብ ቀስ አትልም" አለ መኪናው ወዲያውኑ ቀዘቀዘ እስከሆነ መንገድ ድረስ ወደ ሗላ ተመለሰ ስፖኪዮውን ወደ እኛ አቅጣጫ አስተካከለና ትንሽ ቆሞ መንገዱን ቀጠለ...ይሄ ነገር ምንም አላማረኝም ውስጤን ፍርሃት ፍርሃት አለኝ "ከዚ እንሂድ" አልኳቸው "አረ ሜርሲዬ አትፍሪ ሰው ገጭቶ እያመለጠ ይሆናል" አለች ቅድስቴ እኔን ለማረጋጋት "እሺ" አልኩና ወደ ውስጥ ጉዞ ጀመርን ውሃው ዳር እንደደረስን ሴቶቹ እንጨት ለቀማ ሄድን ወንዶቹ ደሞ ምንተኛበትን መስራት ጀመሩ በድንገት ከነ ባርሳ ተለይቼ ወደ ሌላ አቅጣጫ ሄድኩኝ ነይ እንጂ ስትለኝ ቅድስቴ ሽንቴን ልሸና ነው አልኳት ልክ ትተውኝ ሲሄዱ ወደ መኪናችን ሄድኩኝ ከመኪናችን በስተ ግራ በኩል በተቃራኒው አቅጣጫ የቅድሙ መኪና....
አንብባችሁ ስጨርሱ👍.........
✍#fozi
9 224
«ታጋሽ በመሆንህ የምታተርፈው እንጂ የምትከስረው ምንም ነገር የለም።»
👉 ታላቅ ብስራት ለታጋሾች
📖{ إنما يوفى الصابرون أجرهم بغير حساب }
➲«ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚስሰጡት ያለ ሂሳብ ነው፡፡»
📖{ اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ }
➲«በመታገስና በሶላት ታገዙ(ተረዱ)። አላህ ከታጋሾች ጋር ነው።»
📖{ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ }
➲«ታጋሾችን (በጀነት) አበስራቸው።»
📖{ وَاللَّهُ يُحِبُّ الصَّابِرِينَ }
➲«አላህ ታጋሾችን ይወዳል።»
📖{ واصبروا ان الله مع الصابرين }
➲«ትዕግስት አድርጉ። አላህ ከታጋሾች ጋር ነው።»
9 224
.
.
💔 "የጠፋው ሬሳ" ❤️🔥
💝ልብ አንጠልጣይ ተከታታይ ታሪክ💝
#ክፍል_፩
.......ሜርሲ
_እባላለሁ ቤተሰቦቼ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ናቸው የተወለድኩ ወድምም እህትም የሌለኝ የቤቱ ብቻ ልጅ ነኝ...ያልኩት ይደረግልኛል አንዲትም ሳትቀር በጣም ይሽቆጠቆጡልኛል ዛሬም ዕለቱ የትምህርት ማቆሚያ የክረምቱ ደግሞ መጀመሪያ ስለሆነ ከጓደኞቻችን ጋር ወጣ ብለን የመለያያ ፕሮግራም ለማድረግ እየተዘገጃጀሁ ነው ለሳምት እንቆያለን ስለተባለ ልብሶቼን በሻንጣ በውል አዘጋጀሁ..."ሜርሲ ሜርሲ" አለች የቤት ምግብ አብሳያችን አቤት ስንዱ አልኳት የመኝታ ክፍሌን መዝጊያ እየከፈትኩ "አቶ አላዛር ሊያናግሩሽ ይፈልጋሉ" አለችኝ "እሺ መጣሁ" አልኳት አቶ አላዛር ማለት ውዱ አባቴ ነው...የመኝታ ቤቱን እያንኳኳሁ "ልግባ አባቢ" አልኩት "ግቢ የኔ ልጅ" አለኝ በምላሹ እኔም ወደ ውስጥ ገባሁ "እንዴት አደርሽልኝ የኔ ልዕልት ነይ እስቲ" ብሎ ግንባሬን ሳመኝ "የቀኖቹ ባለቤት እሱ ይመስገን ዛሬም አዲስ ቀን አየሁ" አልኩት "የኔ አንደበተ ማር ቃሎችሽ እኮ እንደ ከርቤ ዕጣን ያውዳሉ"አለኝ አልጋው ጎን ተቀምጬ ፀጉሬን እየነካካ "አባቢ ደሞ ምን የተለየ ነገር ተናግሬ ነው" አልኩት "እኔ ያልኩትን ራሱ ብትደግሚልኝ እንደ አዲስ ብርቅ ሆኖብኝ ነው ምሰማው" ብሎ ፈገግ አለ "ማሚስ የት ሄዳ ነው በጠዋት" ብዬ ጠየኩት "ጉዞ ሄዳለሁ ብለሽ የለ ከስንዱ ጋር ለጉዞሽ የሚሆን ስንቅ እየሰሩልሽ ነው የሆቴል ምግብ እንደማትጠቀሚ እያወቀች ዝም ብላ አትለቅሽ" አለኝ "እውይ የኔ እናት ሄጄ ልጠምጠምባታ" ብዬ ከአልጋው ስነሳ "የተጠራሽበትን ዋና ጉዳይ ሳልነግርሽ ወዴት ልትሄጂ ነው" አለኝ "እሺ ንገረኝ" አልኩት ወድያውኑ "ት/ት ቤት የሚያመላልስሽ ሹፌር አብሮሽ እንዲሆን ነግሬዋለሁ ከከተማ ውጪ ማንም አጠገብሽ ሳይኖር ብቻሽን ልተውሽ አልፈልግም አሁን ይመጣል"አለ "አረ አባቢ ችግር የለውም ጓደኞቼ እኮ አሉ ብዙ ነን የኔ አሳቢ አባቴ አመሠግናለሁ በነፃነት እንድዝነናና ፍቀድልኝ አባቢ ይሄን ብቻ ተቸገርልኝ ደሞኮ አድጌያለሁ"አልኩት "እሺ እንዳልሽ ስልክሽ ግን ሁሌም ክፍት አርጊው በምንም አይነት ሁኔታ ዝግ እንዳይሆን እንደውላለን አንቺም ደውዪ" አለኝ ማስጠንቀቂያ በሚመስል ትዕዛዝ "እሺ የኔ አባት አታስብ" ብዬ ግንባሩን ስሚው ከክፍሉ ወጣሁ ከዛ ማሚ ከኔ ክላስ ስትወጣ አየሗት የኔ እናት ብዬ ጥምጥም አልኩባትና ጉንጯን ሳምኳት "አረ ቀስ ወዜን እንዳትመጪው" አለችኝ እቅፍ አርጋ እየሳመችኝ..."የኔ ልጅ በጣም ተጠንቀቂ እሺ ነገሮችን በማስተዋል አድርጊ" አለችኝ ለኔ እጅግ እንደምትሳሳ አይኗ ላይ ይነበባል "እሺ የኔ እናት አታስቢ እኔ ያንቺ ልጅ አድጌልሻለሁ እኮ" አልኳት "ፈጣሪ ይመስገን ጎርምሰሽልኛል መልካም መንገድ የኔ ልጅ ታዲያ ቶሎ ቶሎ ደውዪ እሺ እድንጨነቅ አታርጊን" አለችኝ "እሺ እናቴ" ብዬ ወደ መኝታ ክፍሌ ገባሁ ተለቅ ያለ አገልግል ጠረጴዛዬ ላይ ተቀምጧል አይ የኔ እናት ...ለጉዞዬ የመረጥኩትን ልብስ ለበስኩኝ እጅግ አማረብኝ ስለ ራስሽ አወራሽ አትበሉኝና...እጅግ በጣም ቆንጅዬ ሴት ነኝ የናቴ ልጅ ራሴን በጣም ነው ማቆለጳጵሰው ሌላ ማን ያቆለጳጵሰኛል "ስንዱ ዕቃዬን ታግዢኛለሽ" አልኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ በሩን ከፍቼ አንገቴን አስግጌ ጠራሗት "እሺ ሜርሲዬ" ብላ መጣች እሷ ሻንጣውን እኔ ደግሞ አገልግሉን ይዤ ወደ መውጫው ጉዞ ጀመርን "የኔ አባት እና የኔ እናት ትናፍቁኛላችሁ እስክንገናኝ ምወደው ፈጣሪዬ ምወዳቹን ይጠብቅልኝ"አልኳቸው ድምፄን ከፍ አድርጌ "እሺ ሰላም ግቢልን የኛ ልጅ" አለ አባቢ ማሚ መዳፏን እያወዛወዘች በፈገግታ ሸኘችኝ...የሳሎኑን በር ዘግቼ ወጣሁ የግቢ ጠባቂያችን "አምጪው ሜርሲዬ" ብሎ አገልግሉን ተቀበለኝ "አመሠግናለሁ አስራት አምላክ ይባርክህ" አልኩት "አሜን አለኝ በምላሹ "እና ምን አዲስ ነገር አለ" አልኩት "ምንም ሜርሲዬ ይነጋል ይመሻል ድጋሜ ይነጋል ድጋሜ ይመሻል" አለኝ በውስጤ "አይ የሰው ልጅ ምን አዲስ ነገር አለ ሲባል ምንም ይላል የዛሬውን ቀን ከዛሬ በፊት ያየውና ውሎ ያደረበት ይመስል"እላለሁኝ ግን ለአስራት መልስ አልሰጠሁትም ነበር...ጓደኞቼ ድረስ የሚያደርሰኝ ሹፌሬ ደጅ ላይ ቆሞ እየጠበቀኝ ነው "ሰላም አደርክ" አልኩትኝ ኮፈኑን እንዲከፍትልኝ በእጄ እየጠቆምኩት ወዲያው ከፈተው "አስራት አገልግሉን ከውስጥ አርገው ስንድዬ ሻንጣውን እዚ አስገቢው"አልኳቸው ሁለቱም "እሺ አሉኝ...እቅፍ አርጌ ሳምኳቸውና ሰላም ያገናኘን ብዬ ወደ መኪናው ገባሁ...
ክፍል2 ከ40like👍 በኋላ ይቀጥላል...........
✍#fozi
9 224
.
.
ውድና የተከበራቹ አንባቢያን
#ብዥታ ለተወሰነ ጊዜ አይለቀቅም
የጠፋው ሬሳ ☠
ወይም
የልብ ቁስል ❤️🩹
በብዙ ሰው የተመረጠው
ከሁለቱ አንዱ ታሪክ ይፃፋል።
✍#fozi
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
