en
Feedback
Min Addis?

Min Addis?

Open in Telegram

I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ ዹሆኑ ወሬዎቜ ዚሚለቀቁበት ዚኢንፎ቎ይንመንት ቻናል ነው

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Min Addis?

Channel Min Addis? (@min_ddis) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 732 subscribers, ranking 17 820 in the News & Media category and 3 103 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on МевіЎПЌП, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 732 subscribers.

According to the latest data from 23 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -169 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.75%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.30% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 656 views. Within the first day, a publication typically gains 1 642 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ ዹሆኑ ወሬዎቜ ዚሚለቀቁበት ዚኢንፎ቎ይንመንት ቻናል ነው”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

10 732
Subscribers
-224 hours
-17 days
-16930 days
Posts Archive
ይህ ታላቅ ሰው ዛሬ ፡ ሁለት ጎል ባገባበት ጫማ ላይ በልዩ ትእዛዝ ዚልጆቹን ስም አስፅፎ ነው ዚገባው ። " ኀቫ ፡ ቀላ ፡ ማቲዮ ፡ አላና ፡ እና ክርስቲያኖ ጁንዹር " ( በእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ
ይህ ታላቅ ሰው ዛሬ ፡ ሁለት ጎል ባገባበት ጫማ ላይ በልዩ ትእዛዝ ዚልጆቹን ስም  አስፅፎ ነው ዚገባው ። "  ኀቫ ፡ ቀላ ፡ ማቲዮ ፡ አላና ፡ እና ክርስቲያኖ ጁንዹር " ( በእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ ሳይሆን ለቀተሰቡ ባለው ነገርም ተምሳሌት ዹሚሆን. ..ሰው ብሎ ዝም ። (✍ዋሲሁን ተስፋዬ) @min_ddis

ለአፀደ ህፃናት ምርቃት ማኹናወኛ ኚትምህርት ቀቶቜ እዚተጠዚቅን ያለነው ወጪ አሳስቊናል ሲሉ ወላጆቜ ተናገሩ በአዲስ አበባ ኹተማ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ በበርካታ ዹአፀደ ህፃናት (ኬጂ) ትምህርት ቀቶቜ
ለአፀደ ህፃናት ምርቃት ማኹናወኛ ኚትምህርት ቀቶቜ እዚተጠዚቅን ያለነው ወጪ አሳስቊናል ሲሉ ወላጆቜ ተናገሩ   በአዲስ አበባ ኹተማ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ á‰ á‰ áˆ­áŠ«á‰³ ዹአፀደ ህፃናት (ኬጂ) ትምህርት ቀቶቜ ላይ ዹሚደሹጉ  ዚምርቃት ሥነ ሥርዓቶቜ  ኹፍተኛ ወጪ ዹሚጠይቁ ሆነው እዚታዩ ነው።ዚልጆቜ ዚመመሚቂያ ልብስ፣ ፎቶግራፍ፣ ዚአዳራሜ ኪራይ፣ ዹመዝናኛ ፕሮግራሞቜ እና ሌሎቜ ተያያዥ ወጪዎቜ በወላጆቜ ላይ አሉታዊ ዚገንዘብ ጫናን እዚፈጠሚ ይገኛል።   ምርቃት ለልጆቜ ደስታና ዚትምህርት መነሳሳት፣ ለወላጆቜ  መታሰቢያ ቢሆንም ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎቜን ኚግምት ውስጥ ያስገባ እንዲሆን ተጠይቋል።በመሆኑም  ሁሉንም ያካተተ እና ለወላጆቜ አቅም ዚሚመጥን ዚምርቃት ሥነ ሥርዓት ማዘጋጀት ዚተሻለ መፍትሄ ነው ሲሉ ቆይታ቞ዉን ኚጣቢያቜን ጋር ያደሚጉ ወላጆቜ ገልፀዋል።   ትምህርት ቀቶቜ ዚምርቃት ስነስርአትን ለማድመቅ ዚሚያደርጉት ያልተገባ ፉክክርም በዚህ ሚገድ  ብርቱ ጫናን እዚፈጠሚ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ።ብስራት ሬዲዮ በቀጣይ ዘገባው á‰ áŠ á€á‹° ህፃናት እዚተስተዋለ ዹሚገኘውን  ዚምርቃት ስነስርአት ወጪ መናር መንስኀን ለማጣራት ዚሚመለኚታ቞ውን አካላት በማናገር ጉዳዩን በሰፊው ዚሚዳስስ ይሆናል።  (ዳጉ ጆርናል) @min_ddis

photo content
+9

በኢትዮጵያ ዚስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ ሊኚፍት ዚሚቜል ዚመጀመሪያው አገር አቀፍ ዚስፖርት ኀግዚቢሜን ሊካሄድ ነው በኢትዮጵያ ዚስፖርት ዘርፍ ታሪክ አዲስ ዚኢንዱስትሪ ዕንቅስቃሎ ለመጀመር እና ስፖርትን ኚመዝናኛነት ወደ ላቀ ዚኢኮኖሚ ምንጭነት ለማሾጋገር ያለመ ታላቅ አገር አቀፍ ዚስፖርት ኀግዚቢሜን በአዲስ አበባ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጞ። ይህንን በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ዚሚካሄደውን ታላቅ ኹነት ያዘጋጁት አዱሊያን ማስታወቂያ እና ዳይመንድ ማርኬቲንግ ኀንድ ኮሚኒኬሜን ሲሆኑ፣ ዝግጅቱ ዚኢትዮጵያን ስፖርት ኚባሕላዊ ዚሩጫ እና ዚእግር ኳስ ማዕቀፍ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ ዹቮክኖሎጂ አጠቃቀም፣ ዚንግድ ትስስር እና ዚኢንዱስትሪ ምርታማነት ዚሚያሞጋግር ዚለውጥ ምዕራፍ እንደሚሆን አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። ይህ አውደ ርዕይ እና አገራዊ መድሚክ በርካታ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎቜን ይዞ ዚሚቀርብ ሲሆን፣ ዚስፖርት ዕቃ አምራ቟ቜን፣ አኚፋፋዮቜን፣ ስፖርተኞቜን እና ዚስፖርት ማሕበራትን በአንድ መድሚክ በማገናኘት ዹአገር ውስጥ ምርትን ማበሚታታት እና ዚገበያ ትስስር መፍጠርፀ በዓለም ላይ ያሉ ዘመናዊ ዚስፖርት ስልጠና ቎ክኖሎጂዎቜን (Digital Sports Solutions)፣ ዚስፖርት ሕክምና፣ አመጋገብ እና ሳይንስ ላይ ያተኮሩ ዚውይይት መድሚኮቜን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞቜና አሰልጣኞቜ ማስተዋወቅፀ ወጣቶቜ እና ቀተሰቊቜ በአካል ተገኝተው ዚተለያዩ ዚስፖርት አይነቶቜን እንዲሞክሩ በማድሚግ፣ በአካላዊ ብቃት፣ በእንቅስቃሎ እና በጀናማ ዹአኗኗር ዘይቀ ላይ ሰፊ ግንዛቀ መፍጠር እንዲሁም ዚስፖርት ዝግጅቶቜን በንግድ መልክ በማደራጀት ለሀገር ውስጥ አምራ቟ቜ ሰፊ እድል መስጠትፀ ይህም ዹውጭ ምንዛሪ ወጪን በመቀነስ ዹአገር ውስጥ አቅምን ለመገንባት እና ለዜጎቜ ዚስራ ዕድል ለመፍጠር ኹፍተኛ አስተዋጜዖ ይኖሚዋል። ### ለሀገር ዹሚሰጠው ስልታዊ ጠቀሜታ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደሹጃ በስፖርቱ መስክ ዹጎላ ዝና ያላት ቢሆንም፣ ይህንን እውቅና ወደ ስፖርት ኢንዱስትሪ ለመቀዹር ዚሚያስቜል ዹተቀናጀ ዚንግድ እና ዚልውውጥ መድሚክ ክፍተት እንደነበሚበት ይነገራል። ዳይመንድ ማርኬቲንግ እና አዱሊያን ማስታወቂያ ይህንን ክፍተት በመሙላት ዚኢትዮጵያን ስፖርት ኹ"ሞያ" ወደ "ኢንዱስትሪ" ለማሾጋገር አቅኚ ዚለውጥ ስራ መጀመራ቞ውን ገልጞዋል። በተጚማሪም ዝግጅቱ ኹፍተኛ ጥራት ያላ቞ውን (MDF-based) ዚኀግዚቢሜን ስታንዳርዶቜን ዹሚጠቀም በመሆኑ፣ ለወደፊት በሀገሪቱ ለሚካሄዱ ስፖርታዊ ኹነቶቜ አዲስ ዚጥራት ደሹጃ (Benchmark) ያስቀምጣል። ይህም ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደሹጃ በስፖርት አስተናጋጅነት (Sports Event Hub) እንድትታወቅ በማድሚግ ሚገድ ለስፖርት ዲፕሎማሲው ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ታምኖበታል። ኩባንያዎቹ ኹዚህ ቀደም መሰል ዝግጅቶቜን ዚማካሄድ ልምድ እንዳላ቞ው ዚገለጹ ሲሆን፣ ኚአዲስ አበባ ወጣቶቜ ማሕበር ጋር በመተባበር "ዚአመለካኚት እና አስተሳሰብ ለውጥ ኀግዚቢሜን" እንዲሁም ኚአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሜን ጋር በመተባበር በጃን ሜዳ "ዚባሕል እና ስፖርት ፌስቲቫል" በተሳካ ሁኔታ ማኹናወናቾውን አስታውሰዋል። ለተሳታፊዎቜ እና ለጎብኚዎቜ ደህንነት ኹፍተኛ ትኩሚት ዹተሰጠው ሲሆን፣ እያንዳንዱ ዚኀግዚቢሜን ቊታ (Zone) በዓለም አቀፍ ዚደሕንነት መመዘኛዎቜ መሰሚት እንደሚዋቀር ተገልጿል። ለዚህም ይሚዳ ዘንድ ኚፌዎሬሜኖቜ፣ ኚጀና ባለሞያዎቜ እና ኚሚመለኚታ቞ው ዚደህንነት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ላይ መሆናቾውንና ዹህክምና እና ዚድንገተኛ አደጋ ዝግጅቶቜ በተሟላ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ አሚጋግጠዋል። ይህ አገር አቀፍ ዚስፖርት ኀግዚቢሜን ዚአንድ ጊዜ ክስተት ብቻ ሆኖ እንደማይቀሚና ዋና ዓላማው በዚዓመቱ ዚሚካሄድ ብሔራዊ ዚስፖርት ክብሚ በዓል (Annual Sports Exhibition) ማድሚግ መሆኑ ተገልጿል። ዚዘንድሮውን ዚመጀመሪያ ዝግጅት ስኬት እንደ ግብዓት በመጠቀም፣ በቀጣይ ዓመታት ዹክልል እና ዹዓለም አቀፍ ተሳታፊዎቜን በማካተት ዝግጅቱን ይበልጥ ለማስፋት ታቅዷል።

ኚጓደኛዬ ጋር ድብቅ ፍቅር ጀምሹኃል በማለት ዹገዛ ባለቀቷን በመጥሚቢያ በመምታት ዚግድያ ሙኚራ ዚፈፀመቜው ግለሰብ በእስራት ተቀጣቜ በሻኪሶ ኹተማ አስተዳደር ዚኚብት በሚት ዚተባለ ስፍራ ዚተወለደቜው ዹ27 ዓመቷ አለሚቱ ጃራ ትዳር መስርታ መኖር ኚጀመሚቜ ሶስት አመታትን አስቆጥራለቜ። አለሚቱ ኚትዳር አጋሯ ጋር ሰላማዊ ዹተሹጋጋ ሕይወት ትመራ ነበር።ኚተወሠኑ ግዚያት ወዲህ ግን ይህው ትዳር ክፍተት ገጠመው። አለሚቱ እጅግ ለምትቀርባትና ለምትግባባት ጓደኛዋ ባለቀ቎ ውጭ ውጭ በማለቱ ጥርጣሬ ውስጥ ገብቻለሁ በማለት ታማክራታለቜ።ዚአለሚቱ ጓደኛም  ይሕንን ኚሠማቜ ጀምሮ በተለያ ግዚያት ዚአለሚቱ ባለቀት ማጥመድ ጀመሚቜ።እንደ ፖሊስ መሹጃ ግን  በአለሚቱ ዚተጠሚጠሚቜው ጓደኛዋ ኚባለቀትዋ ጋር ዹተለዹ ግንኙነት እንዳላት ዹተገኘ ተጚባጭ ማስሚጃ ባይኖርም በአካባቢውም ዚአለሚቱ ባለቀት አለሚቱን ፈትቶ ጓደኛዋን ሊያገባ ነው ዹሚል ተጚባጭ ያልሆነ ወሬ  በይበልጥ ትዳራ቞ውን ይበጠብጥ እንደነበር ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። ጥር 2 ቀን 2018 ዓም ኚምሜቱ 12 ሰዓት ላይ ግን  ጥርጣሬዋን ይበልጥ ዚሚያጠናክር ነገር ተመለኚተቜ። ባለቀቷ ኹጓደኛዋ ቀት ሲወጣ በማዚቷ ወደ ቀት ተመልሣ á‰£áˆˆá‰€á‰· እስኪመጣ ትጠባበቅ ነበር።አለሚቱ ባለቀቷ እንቅልፍ እስኪወስደው ጠብቃ ፋስ ዚተባለውን ባለ ሑለት ጉጥ ስለታም መሣርያ በመያዝ በእንቅልፍ ላይ ያለውን ባለቀቷን ግንባሩ ላይ ሁለቮ በማሣሚፍ ገድዚዋለው በማለት  ዚመኝታ ቀቱን በር ዘግታ ኚቊታው ትሠወራለቜ። ኚቆይታ በኃላ ኚቀት ውስጥ ዚድሚሱልኝ ጩሕት ሲሰማ ዚአካባቢው ሠው ተሯርጊ ሲገባ ዚቀቱ ባለቀት በሐይለኛ ጉዳት ደርሶበት ሲመለኚቱ ወዲያው ለኹተማው ፖሊስ በማመልኚት ጉዳት ዚደሚሠበት ዹግል ተበዳይ በፖሊስ ወደ ሻኪሶ ሆስፒታል ተልኮ ዹሕክምና  እርዳታ እንዲያገኝ ተደሚገ።  ተጎጂው በሕክምና እርዳታ ኚሞት ቢተርፍም ኹፍተኛ ዚአካል ጉዳት ደርሶበታል። ይሕንን ዹወንጀል ድርጊትን ዚፈፀመቜ አለሚቱ ገድዬዋለሁ ብላ በቀጥታ ኚሻኪሶ ኹተማ ወደ ነገሌ ቩሹና ኹተማ ምሜቱን ተጉዛ ጠዋት ላይ በአንድ ሆቮል አልጋ ተኚራይታ ትቀመጣለቜ። ፖሊስም ባሠማራው ዚክትትል ቡድን አለሚቱ በአንድ ሆቮል አልጋ ተኚራይታ በነጋታው ለማምለጥ ስትዘጋጅ በቁጥጥር ስር ትውላለቜ። ዚምርመራ መዝገቡ በበቂ ዹሕክምና ዚተለያዩ ማስሚጃዎቜ ተጠናክሮ ለአቃቢ ሕግ ይላካል። አቃቢ ሕግም በኚባድ ዹሠው መግደልና አካል ማጉደል ወንጀል ክስ ይመሠርታል። ክሱን ዹተመለኹተው ዚምስራቅ ጉጂ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ሰኔ 3 ቀን 2018 በዋለው ቜሎት ተኚሣሜ አለሚቱ ጃራ በ12 አመት እስራት እንድትቀጣ ተወስኖባታል። (ዘገባው ዚብስራት ሬዲዮ ነው) @min_ddis

photo content

“ቀት ያላገኘ ተፈናቃይ ካለ ሥልጣኔን እለቃለሁ” — አቶ ግርማ ሰይፉ ​ዚአዲስ አበባ ውበትና አሹንጓዮ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በኹተማዋ በነበሹው ዚኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቅሎ ምትክ
“ቀት ያላገኘ ተፈናቃይ ካለ ሥልጣኔን እለቃለሁ” — አቶ ግርማ ሰይፉ ​ዚአዲስ አበባ ውበትና አሹንጓዮ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በኹተማዋ በነበሹው ዚኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቅሎ ምትክ ቀት ወይም መሬት ያላገኘ አንድም ሕጋዊ ሰው አለመኖሩን አስታወቁ። ካርታ ወይም ዹቀበሌ ቀት ኖሚውት ምትክ ያጣ ሰው ካለ በገዛ ፈቃዳ቞ው ኚሥልጣን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቾውን ዚገለጹት ኃላፊው፣ ልማቱ ለሀገር ጥቅም ዚተሠራ መሆኑን ገልጞውፀ ሆኖም ኚአስተዳደራዊ ጉዳዮቜ ጋር በተያያዘ በደል ዚደሚሰባ቞ው ወገኖቜ መኖራ቞ውን አልሞሞጉም። ​በሌላ በኩል፣ ዚኮሪደር ልማቱ ለኹተማዋ ዘመናዊነትና ውበት ያለው አስተዋጜኊ ኹፍተኛ ቢሆንምፀ በሂደቱ ወቅት በቂ ዝግጅት፣ ግልጜነትና ተመጣጣኝ ምትክ አላገኘንም ዹሚሉ ዚኅብሚተሰብ ክፍሎቜ ቅሬታዎቜ በተደጋጋሚ ሲነሱ መቆዚታ቞ው ይታወቃል። @min_ddis

አርቲስት ካሙዙ ካሳ ምርጫውን ማሾነፉን አስታወቀ ​በዚካ ክፍለ ኹተማ በብልፅግና ፓርቲ ለምርጫ ቀርቩ ዹነበሹው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በአካባቢው ነዋሪዎቜ ኹፍተኛ ድምፅ ተሰጥቶት ማሾነፉን ይፋ አድርጓ
+2
አርቲስት ካሙዙ ካሳ ምርጫውን ማሾነፉን አስታወቀ ​በዚካ ክፍለ ኹተማ በብልፅግና ፓርቲ ለምርጫ ቀርቩ ዹነበሹው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በአካባቢው ነዋሪዎቜ ኹፍተኛ ድምፅ ተሰጥቶት ማሾነፉን ይፋ አድርጓል። አርቲስቱ ዚምርጫ ውጀቱን ተኚትሎ ለመራጮቜ ምስጋናውን አቅርቧል። ​ታዋቂው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በዚካ ክፍለ ኹተማ በተካሄደው ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን ወክሎ በመወዳደር፣ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሾነፉን በይፋዊ ዚማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ​አርቲስቱ ባስተላለፈው ዚእንኳን ደስ አላቜሁ መልዕክት፣ ለምርጫው መሳካት ላደሚጉት ድጋፍ ዚአካባቢውን ነዋሪዎቜ እና መራጮቹን አመስግኗል። “እንደ ብልፅግና ፓርቲ ኹፍተኛ ድምፅ በማግኘታቜን እና በአካባቢው ማሞነፋቜን ታላቅ ድል ነው” ሲል ዹገለጾው አርቲስት ካሙዙ፣ በድል አድራጊነት ስሜት ኢትዮጵያ አሞንፋለቜ ዹሚል መልዕክት አስተላልፏል። (Via:-ፋስት መሹጃ) @min_ddis

ሚካኀል ማክጊዹር ኚጭንቅላቱ እስኚ እግር ጥፍሩ በቆሻሻ እንደተሞፈነ ዹኹሰል ማዕድን ማውጫ ፈሹቃውን ኚሰዓት 11፡00 ሰዓት ላይ አጠናቀቀ። ምሜት 12 ሰዓት ላይ ዹሞቀ ዹደመቀ ዚቅርጫት ኳስ ጚዋታ በ
ሚካኀል ማክጊዹር ኚጭንቅላቱ እስኚ እግር ጥፍሩ በቆሻሻ እንደተሞፈነ ዹኹሰል ማዕድን ማውጫ ፈሹቃውን ኚሰዓት 11፡00 ሰዓት ላይ አጠናቀቀ። ምሜት 12 ሰዓት ላይ ዹሞቀ ዹደመቀ ዚቅርጫት ኳስ ጚዋታ በኹተማው ኬንተኪ ዊልድካትስ ይካሄዳል። ለልጁ ዚዛሬውን ቅርጫት ኳስ ለማሳዚት ቃል ገብቶለት ነበር። ራሱን ለማፅዳት ሻወር ለመወሰድና ልጁን ኚቅርጫት ኳስ ሜዳው ለማድሚስ ዹነበሹው አንድ ሰዓት በፍፁም እንደማይበቃው ኚስራ ዚወጣበትን ሰዓት ሲመለኚት ገብቶታል። ኚነስራ ልብሱ ኚነአዋራውና ጭቃው ኹልጁ ጋር በኬንታኪ ዊልድካትስ ሜዳ ለልጁ ዚገባውን ቃል በማክበር ማሳለፍን መሚጠ። ባለቀቱ ሞሊ ይህንን ምስል በቮሌቹዠን መሰኮት ኚተመለኚተቜ በኃላ በፌስቡክ ላይ ይህንን አጋርታለቜ። 👇 "ባለቀ቎ ኚልጆቻቜን ጋር እቀት እንድቆይ ይህን ዚስራ ጫና ዹወሰደው ቀተሰባቜንን ለመርዳት ነው። ብዙ ጊዜ በስራ ምክንያት ሁነቶቜ ያመልጡናል። ምንም ቢሆን፣ ዚቱንም ያህል ቢደክመው ወይም ቢቆሜሜ እድሉን በሚያገኝበት ጊዜ ግን ዚሚቜለውን ሁሉ ያደርጋል።" ደግ አይለፍቜሁ❀🙌 ለአባቶቜ ዹተገሹበ (✍በተስፋዬ ሐይሌ) @min_ddis

ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ዚመጡ ዹውጭ ሀገር ዜጎቜን በመያዣነት በመጠቀም ኹ15 ሚሊዹን ብር በላይ ዹጠዹቁ ሊስት ፓኪስታናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ። ዚፓኪስታን ዜግነት ያላ቞ው ዝሻን ካሊድ፣ ፍርዝ መሃመ
+3
ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ዚመጡ ዹውጭ ሀገር ዜጎቜን በመያዣነት በመጠቀም ኹ15 ሚሊዹን ብር በላይ ዹጠዹቁ ሊስት ፓኪስታናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ። ዚፓኪስታን ዜግነት ያላ቞ው ዝሻን ካሊድ፣ ፍርዝ መሃመድ እና መሀመድ ጀናይድ ዚተባሉ ተጠርጣሪዎቜ ዹወንጀል ድርጊቱን ዚፈጞሙት ሰኔ 4 እና ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ/ም በለሚ ኩራ ክ/ኹተማ ወሚዳ 9 ጎሮ አትሌቶቜ መንደር ነው። ተጠርጣሪዎቹ በተኚራዩት ዚመኖሪያ ቀት ውስጥ ዚህንድና ዚባንግላዎሜ ዜግነት ያላ቞ውን ግለሰቊቜ በመያዣነት በመጠቀም ዹግል ተበዳዮቜን በገመድ በማሰርና በፕላስተር በማፈን ኹ15 እስኚ 30 ሚሊዹን ብር በመጠዹቅ ጥቃት አድርሰውባ቞ዋል። ተጠርጣሪዎቹ በዚህ ብቻ ሳያበቁ ሰኔ 11ቀን 2018 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት ዚገቡ 4 ዚህንድ ዜጎቜን በማሰርና በመደብደብ ኹ15 እስኚ 25 ሺህ ዚህንድ ሩፒ አስልኩ በማለት ድብደባ ሲፈጜሙባ቞ው እንደነበር ዹግል ተበዳዮቜ ለፖሊስ ቃላቾውን ሰጥተዋል።                                                                 ዹወንጀሉ መፈጾም መሹጃ ዹደሹሠው ዹለሚ ኩራ ክ/ኹተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ተገቢውን ዚፍርድ ቀት መያዣና ዚመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ባኚናወነው ኊፕሬሜን ተጠርጣሪዎቹን ለወንጀል ድርጊት ሲጠቀሙበት ኹነበሹው ቢላዋ፣ ገመድና ፕላስተር እንዲሁም ኚተለያዩ ዹውጭ ሀገር ገንዘቊቜ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል።                                                                          ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ ተጠርጣሪዎቹ እንዲያዙ መሹጃ በመስጠት ላደሚጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን ያቀሚበው ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አጠራጣሪ ጉዳዮቜ ሲያጋጥሙም ለፖሊስ መሹጃ መስጠት እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።

ዹኹተማው ፖሊሶቜ ዚፌደራል ፓሊስ አባላትን በኃይል ሲያስሯ቞ው ዚሚያሳዚው ቪዲዮ አነጋጋሪ ሆኗል በደቡብ ክልል ውስጥ በተቀሹጾ ዚጞጥታ ኃይሎቜ ተሜኚርካሪ ላይ፣ ዹኹተማው ፖሊስ አባላት ዚፌዎራል ፖሊስ አባላትን በኃይል እያጣደፉ በተሜኚርካሪው ላይ እዚጫኑ ሲያስሯ቞ው ዚሚያሳይ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ኹፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ተመሳሳይ ዹሕግ ማስኚበር ኃላፊነት ያለባ቞ው ተቋማት እርስ በርሳ቞ው በዚህ መልኩ ፍጥጫና ግጭት ውስጥ ገብተው መታዚታ቞ው በብዙዎቜ ዘንድ ድንጋጀንና ግራ መጋባትን ዹፈጠሹ ሲሆን፣ በሕዝብ ዘንድም ስለ ጞጥታ መዋቅሩ መኚባበርና ቅንጅት በርካታ ጥያቄዎቜን እያስነሳ ይገኛል። ዹኹተማው ፖሊሶቜ ዚፌዎራል ባልደሚቊቻ቞ውን በዚህ ደሹጃ ለማሰርና ዹኃይል እርምጃ ለመውሰድ ምን ዓይነት ምክንያት እንደገፋፋ቞ው እስካሁን በውል ዚታወቀ ነገር ዹሌለ ሲሆን፣ ጉዳዩ ኚሚመለኚታ቞ው ዹበላይ ዚጞጥታ አካላት አስ቞ኳይና ግልጜ ማብራሪያ ዹሚፈልግ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል። (Via:-Ethio Lead) @min_ddis

ምንም እንኳን እንደ እናቶቜ ቀን ባይደምቅም ፡ ዛሬ ዚአባቶቜ ቀን ነው ። ....... ዹማይክ ታይሰን ልጅ አሚር ታይሰን ፡ አንድ ቀን ለአባቱ እኔም እንዳንተ ቩክሰኛ መሆን እፈልጋለሁ አለው ። ታይ
ምንም እንኳን እንደ እናቶቜ ቀን ባይደምቅም ፡ ዛሬ ዚአባቶቜ ቀን ነው ። ....... ዹማይክ ታይሰን ልጅ አሚር ታይሰን ፡ አንድ ቀን ለአባቱ እኔም እንዳንተ ቩክሰኛ መሆን እፈልጋለሁ አለው ። ታይሰን ይህን ሲሰማ ፊቱ ተለዋወጠ ፡ ልጁ በዛው ቅፅበት ቩክሰኛ ዹሆነና ጡንቻ቞ውን ያፈሚጠሙ ቊክሰኞቜ በጭካኔ ሲመቱት ያዚ ያህል ዹልጁ ሀሳብ ዘገነነው ። ........ እና በፍፁም ቩክሰኛ አትሆንም አለው ። አንተ ኚም቟ት ህይወት ጋር ተላምደሀል ፡ በቅንጊት ነው ያደኚው  ። እንደኔ ቩክሰኛ መሆን አትቜልም ። አዹህ አንተ በቊክስ ውስጥ ሳታልፍ ኑሮን ማሾነፍ ቜለሀል ፡ ምክንያቱም ምርጫ ነበሹህ ። ...... እኔ ቩክሰኛ ዚሆንኩት ኑሮን ለማሾነፍ ምርጫ ስላልነበሚኝ ነው ። አንተ ዚጚካኝ ቊክሰኞቜን ቡጢ መቋቋም አትቜልም  እኔ በዚህ ውስጥ ያለፍኩት እናንተ ልጆቌ እንዳት቞ገሩ ነው ። ሀሳቀ ተሳክቶም ልጆቌን ማስተማር እና በም቟ት ማኖር ቜያለሁ እና እኔ ባለፍኩበት መንገድ እንድታልፉ ፈፅሞ አልፈልግም በማለት መለሰለት ። ... ልጆቌ ቊክስን በሚያህል ትልቅ ስቃይና ህመም ያለበት ስፖርት ውስጥ ተሳትፈው እኔ ዹተሰማኝ ህመም ሲሰማ቞ው ማዚት አይደለም ማሰብም አልፈልግም ሲል መለሰለት ። ኹዛን እለት ጀምሮ ዹማይክ ታይሰን ልጅ ቩክሰኛ ዹመሆን ሀሳቡን ተወ ። አሚር ታይሰን በአሁኑ ወቅት DEBONAIR ዚሚባል ዚራሱን ዚፋሜን ብራንድ ፈጥሮ እሱ ላይ እዚሰራ ነው ። መልካም ዚአባቶቜ ቀን ። @min_ddis

photo content
+2

ዳኛዋንና ባለቀቱን በቜሎት አዳራሜ ተኩሶ ዹገደለው ግለሠብ ራሱን ኚሆስፒታል ፎቅ ወርውሮ አጠፋ በወልመራ ወሚዳ ፍርድ ቀት ዚባልና ሚስት ክርክር ዹነበሹን ዚመጚሚሻ ውሣኔ ላይ ዚቜሎት ዳኛዋን ና ባለቀቱን በሜጉጥ ተኩሶ ዹገደለው ግለሠብ ኚሚታኚምበት ሆስፒታል ፎቅ እራሱን ወርውሮ ሕይወቱን ማጥፋቱን ፖሊስ አስታወቀ። ዚሆለታ ኹተማ አስተዳደር ፖሊስ ዋና መምርያ አዝዥ ኮማደር ፀጋዬ ቶላ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት አቅናው በቀለ፣ዚተባለ ተጠርጣሪው ግለሠብ ግንቊት 27 ቀን 2018 ዓም በወልመራ ወሚዳ ፍርድ ቀት ዚፍታብሔር ቜሎት ውስጥ ማንም ሣያዚው በወቅቱ በነበሹው አዲስ እና ግማሜ ክፍሉ በተጠናቀቀውና አገልግሎት በሚሰጠው ዚፍርድ ቀቱ ሕንፃ በጓሮ በኩል ተቀምጩ ዹጩር መሣርያ ሜጉጥና ስለታም መሣርያ ታጥቆ ስሙ ሲጠራ ወደ ቜሎት አዳራሹ  መግባቱን ገልፀዋል። ቜሎት ላይም ዚመጚሚሻው ዚውሣኔ ሐሣብ  በተሠዚሙት ዳኛ ወይዘሮ  ወርቄ ፈኚንሣ ሲነበብ ዚተበሣጚው በመጀመሪያ ታጥቆ በገባው ሜጉጥ ዳኛ ወይዘሮ ወርቄን ፈኚንሣን ተኩሶ በመምታት እንዲሁም ዚክርክሩ አካል ና አብራ ቆማ ፍትሕን ስጠብቅ ዚነበሚቜውን ባለቀቱና ዚልጆቹን እናት ወይዘሮ አልማዝ መኮንን ተኩሶ በመምታት በሌሎቜ ሠዎቜ ላይ ጉዳት ለማድሚስ ሞክሮ እራሱ ላይም ተኩሶ ጉዳት ማድሚሱን ገልፀዋል። ፖሊስም በወቅቱ ጉዳት አድራሹን አቅናው በቀለ ዚተባለውን ግለሠብ  በቁጥጥር ስር በማዋል ፣በፖሊስ ጥበቃ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እንዲታኚም ተደርጎ አልጋ ይዞ ዹሕክምና ክትትል ላይ ነበር።ሆኖም ግለሠቡ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓም ዹሕክምና ክትትሉን ጚርሶ ስለተሻለው ኚሆስፒታል ለመውጣት እንዲዘጋጅ ሲነገሚው ኚሆስፒታሉ ሶስተኛ ፎቅ በመስኮት እራሱን በመወርወር ህይወቱን ማጥፋቱን ተናግሚዋል። በወቅቱ ግለሠቡ ኚሌሎቜ ሠባት በወንጀል ድርጊት ዚተጠሚጠሩና ሕክምና ዚሚኚታተሉ ግለሠቊቜ ጋር ወደ መስኮት ጥግ ዹተኛ መሆኑን ዚገለፁኡት ኃላፊው ፖሊስ ሣይደርስ ማንም ሣያዚው ኚሶስተኛ ፎቅ ራሱን ወርውሮ  ህይወቱን አጥፍቷል።ፖሊስ ዹወንጀል ድርጊቱ ኚተፈፀመበት እለት አንስቶ ባደሚገው ማጣራትና ምርመራ በግለሠቡ ቀት በርካታ ሕገወጥ  ዹጩር መሣርያዎቜ በመኖርያ ቀቱ በፍተሻ ዹተገኙ ሲሆን በእለቱ ዚቜሎት ሒደት ዚጥበቃ ክፍተት ዚፈጠሩ ስራ቞ውን በአግባብ ባለመወጣታ቞ው በቁጥጥር ስር መዋላቾውንም ኮማደር ፀጋዬ ቶላ ለጣቢያቜን áŒšáˆáˆšá‹ ገልፀዋል። ዹወንጀል ድርጊቱ በፍርድ ቀቶቜ ዙርያ ያለው ዚፍተሻ ስርዓት እንዲጠናኚር ዚሚያሣይ መሆኑን ብዙዎቜ ዚተስማሙበት ነው። @min_ddis

ኚቀናት በፊት አርጀንቲና ኚአልጄሪያ አድርገውት በነበሹው ጚዋታ ላይ ነው ። ዝነኛው ዚአለማቜን ዚእግር ኳስ ኮኚብ ሊዮኔል ሜሲ ቡድኑን በሀትሪክ መሪ እንዲሆን ካደሚገ በኋላ ፡ በ80 ኛው ደቂቃ ላይ
ኚቀናት በፊት አርጀንቲና ኚአልጄሪያ አድርገውት በነበሹው ጚዋታ ላይ ነው ። ዝነኛው ዚአለማቜን ዚእግር ኳስ ኮኚብ ሊዮኔል ሜሲ ቡድኑን በሀትሪክ መሪ እንዲሆን ካደሚገ በኋላ ፡ በ80 ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ ወጥቶ ተጫዋ቟ቜ ወደሚያርፉበት ቊታ ሲሄድ ሁሉም ወንበር ተይዟል ። በዚህ ጊዜ ዚቡድን አጋሩ ዹሆነው ቲያጎ አልማዳ ፡ ዚሚቀመጥበት ቊታ ላጣው ሊዮኔል ሜሲ በማክበር ቊታውን ለቆ እንዲቀመጥበት ሲነሳ ፡ ሜሲ ፍቃደኛ አልሆነም ። እና ፡ ዝነኝነቱ ሳያግደውና ሳይኮፈስ ፡ ልክ እንደልጆቜ ሳሩ ላይ ተቀምጩ ጚዋታውን ጹሹሰ ። ይህ ሜሲ ያሳዚው ጥበብ ተናንሶ መኖር ፡ ይባላል ። ትህትና !!! በነገራቜን ላይ እኔ ዚክርስቲያኖ ሮናልዶ አድናቂ ነኝ ፡ ሆኖም ለCR7 ያለኝ ትልቅ ቊታ ፡ ዚሜሲን ቜሎታ እና humbleness ኚማድነቅ አያግደኝም ። (✍ዋሲሁን ተስፋዬ) @min_ddis

ዚእናቱን አስክሬን ቀት አስቀምጊ ዚእናቱን ቃል ለማክበር ዹ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ኚቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና ዹተቀመጠው ካሊድ ይሕ በምስሉ ላይ ዚምትመለኚቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል ገና ዚአስ
ዚእናቱን አስክሬን ቀት አስቀምጊ ዚእናቱን ቃል ለማክበር ዹ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ኚቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና ዹተቀመጠው ካሊድ ይሕ በምስሉ ላይ ዚምትመለኚቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል ገና ዚአስራ አራት ዓመት ልጅ ነው።ኚሑለት ታናናሜ ወንድሞቹ ጋር በሾገር ኹተማ አስተዳደር ኀካ ጣፎ ክፍለ ኹተማ ኚእናቱ ጋር ይኖራል። ካሊድ ኚእናቱ ጋር ሲኖር ወላጅ አባቱ ኚእነርሱ ርቆ ሌላ ትዳር መስርቶ ጅጅጋ ኹተማ ይኖራል። ካሊድ ሠሞኑን እናቱ ታምወው በነበሚበት ወቅት እኔ አንድ ነገር ብሆን ምንም ቢፈጠር አመት ዚለፋሕበትን ፈተና እንዳታቋርጥ ብለው ቃል ያስገቡታል። እናትም በነጋታው ዚስምንተኛ ክፍል ፈተና ሊሲጥ ሠዓታት ሲቀሚው ሕይወታ቞ው ያልፋል።ካሊድ በእናቱ ሞት ኹፍተኛ ሐዘን ቢሰማውም ለእናቱ ዚገባው ቃል አክብሮ ዚእናቱን አስክሬን እቀት ጥሎ ዚጥዋት ፈተናውን ተፈተነ። ካሊድ ኚሠዓት እናቱን አልቅሶ ቀብሮ ተመልሶ ዚኚሰዓት ፈተናውን ተፈተነ።ዚዚሕ ዚአስራ አራት አመት ታዳጊ ዚሕይወት ፈተና ብዙዎቜን በሐዘን ማስለቀሱን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል። Via:-ዳጉ ጆርናል @min_ddis

ዚ቎ዲ አፍሮ ዚቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ዹጃኖ ባንድ መስራቜ ዚነበሩት እና ዹሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም ዚሆኑት ታዋቂው ዹሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ
ዚ቎ዲ አፍሮ ዚቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ኹዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ዹጃኖ ባንድ መስራቜ ዚነበሩት እና ዹሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም ዚሆኑት ታዋቂው ዹሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ በአሜሪካን ሀገር ህይወታ቞ው ማለፉን ዚቅርብ ወዳጆቻ቞ው ለመዝናኛ ሚዲያ አስታወቁ። አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ዝና ያተሚፉትን ዚቊብ ማርሊ ልጆቜንእና በርኚት ያሉ ታዋቂ ሙዚቀኞቜን ዹማማኹርና ዚማስተዳደር ስራ ዚሰሩ ጉምቱ ዹሙዚቃ አስተዳደር ባለሞያ ነበሩ። አቶ አዲስ ዚ቎ዲ አፍሮ ማኔጀር በመሆንም ለሹጅም ጊዜ አገልግለዋል። በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በኒው ጀርሲ ግዛት ህይወታ቞ው ያለፈው አቶ አዲስ ገሰሰ ፣ ዚሞታ቞ው ምክንያት ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን አስኚሬና቞ውን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደታሰበ ዹደሹሰን መሹጃ ያመለኚታል። (ምንጭ:-መዝናኛ ሚዲያ) @min_ddis

ኚሊዮኔል ሜሲ እንባ ጀርባ ያለው ሰውኛ ስብራት💔 አርጀንቲናዊው ኮኚብ ሊዮኔል ሜሲ በጚዋታው ላይ አስደናቂ ሀትሪክ (ሊስት ጎል) አስቆጥሮ በደስታ በሚፈነጥዝበት ቅጜበት፣ ባልተለመደ መልኩ አይኖቹ በ
ኚሊዮኔል ሜሲ እንባ ጀርባ ያለው ሰውኛ ስብራት💔 አርጀንቲናዊው ኮኚብ ሊዮኔል ሜሲ በጚዋታው ላይ አስደናቂ ሀትሪክ (ሊስት ጎል) አስቆጥሮ በደስታ በሚፈነጥዝበት ቅጜበት፣ ባልተለመደ መልኩ አይኖቹ በእንባ እሚጥበው ሜዳ ላይ ሲያለቅስ መታዚቱ ዚብዙዎቜን ልብ ሰብሯል፣ ግራ ማጋባትም ፈጥሮ ነበር። አርጀንቲናዊው ኮኚብ ኚጚዋታው በኋላ ጋዜጠኞቜ ለምን እንዳለቀሰ ሲጠይቁት " ኚስፖርቱ ጋር ዚተያያዘ ነገር አይደለም "ብሎ ነበር። ሊዮኔል ሜሲ፣ " አስ቞ጋሪ እና ዚተወሳሰቡ ቀናት አሳልፌያለሁ። ዚቡድን አጋሮቌን አመስጋኝ ነኝ ኹጎኔ ነበሩ " ዹሚል ምላሜ ነበር ዹሰጠው ። በዕለቱ ምን እንደገጠመው በግልጜ ያልተናገሚው ሊዮኔል ሜሲ ፣ ዚቡድን አጋሮቌ ብዙ ጥንካሬ ሰጥተውኛል " ኚማለት ውጪ ተጚማሪ ማብራሪያ ኚመስጠት ተቆጥቧል። ነገር ግን ኹወደ አርጀንቲና እዚወጡ ያሉ መሚጃዎቜ ዚሊዮኔል ሜሲ እንባ ምንጩ ኚሜዳ ውጪ ባለ ዚህይወት ፈተና መሆኑን ዹሚጠቁሙ ሆነዋል ። በተለይም አርጀንቲናዊው ጋዜጠኛ ኀድዋርዶ ፌንማን ባወጣው መሹጃ ሊዮኔል ሜሲ ወላጅ አባቱ በፀና ታመውበት አስ቞ጋሪ ሁኔታ ማሳለፉን ዘግቧል። ወላጅ አባቱ ለወራት ታመው ነበር ዚተባለ ሲሆን ባለፉት ቀናት ህመሙ ፀንቶባ቞ው እንደነበር ተሰምቷል። ሊዮኔል ሜሲ በተፈጠሹው ነገር ተጎድቶ እንደነበር እና በብሔራዊ ቡድን ስብስብ እንደታገዘ ተጠቁሟል። ሊዮኔል ሜሲ ኹ 68ዓመት ወላጅ አባቱ ጋር ቅርብ ግንኙነት ሲኖሚው እንደ ወኪሉ እና ማናጀሩም ሆኖ ያገለግላል። (ዹመሹጃው ምንጭ ዚአርጀንቲና ተደማጭ ዚራድዮ ጣቢያ Radio Mitre ነው።) @min_ddis

🔶መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ኹተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቀት ዹ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ኚተማሪ ጋር ተመሳስሎ ዚገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቾውን ዹኹተማ
🔶መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ኹተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቀት ዹ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ኚተማሪ ጋር ተመሳስሎ ዚገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቾውን ዹኹተማው ፖሊስ ጜህፈት ቀት ገለጞ። ተማሪውን ወክሎ ኚመምህርነት ስነ-ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ላይ ተሳትፏል ዚተባለውና ኚቡልቂ ኹተማ ሙሉ 1ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ዚመጣው መምህር እስራኀል አሰፋ፣ ዹማንዮላ ርቀት ትምህርት ቀት ተማሪ ዹሆነውን አብነት እንዳለን ተክቶ ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደሹገ ዚኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን ዚገለጹት ዹኹተማው ትምህርት ጜህፈት ቀት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ና቞ው። ፈተናውን ኚኩሚጃና ኚስርቆት ዚፀዳ ለማድሚግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠሚት፣ ዚኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታ቞ው ሊፈተን ዚገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ዹሰጠው ተማሪ በቁጥጥር ስር መዋል መቻላ቞ውን አስሚድተዋል። ዚሳውላ ኹተማ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላ቞ው፣ ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እዚተደሚገባ቞ው መሆኑን ጠቁመው በማዕኹሉ እዚተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሰላማዊ እና በተሹጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግሚዋል። ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዹዋሉ ተጠርጣሪዎቜን ምርመራ በአስ቞ኳይ አጣርቶ በአቃቀ ህግ በኩል ለፍርድ ቀት አቅርቩ ለማስወሰን እዚሰራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጞዋል። ምንጭ፩ ሳውላ ኹተማ መንግሥት ኮሙኒኬሜን @min_ddis

ባል አራስ ዚሆነቜ ዹልጅ እናቱን በመተው  ኚትዳር ውጭ አሾሾ ገዳሜ ሲል እጅ ኹፍንጅ ተያዘ ! ኹላይ በቪዲዮ እንደምታዩት ኚወለደቜ 3ወር እንኳን ሳይሆናት ባላያዋ ላይ ኹሌላ ሎት ጋር  አሾሾ ገዳሜ ሲል ሚስትዚው ሳይታሰብ ወይም በመኚታተል  ዹአልጋ ላይ ጚዋታ ሲጫወት በቁጥጥር ስር አውላዋለቜዋለቜ ።   በዚህ መሰሚት ሚስትዚው በፈፀመባት ክህድት እጅግ በመናደድ አንተ ባለጌ ክፈት እያለቜው በሩን በድንጋይ  ደብድባለቜ  ።  ሰዎቜ እንድትሚጋጋ ቢመክራቱም ጉድ እንደምትሰራው ዝታበታለቜ። ባልዚው ዚወሲብ ግንኙነት ኚሚደርጋት ሎት ጋር ኚቀቱ ውስጥ በሩን በደንብ አጥብቆ በመያዝ እባካሜ ተሹጋጊ ውዮ እባክሜ ተሹጋጊ ውዮ ዚማደርግልሜን አታውቂም በማለት እዚተማፀነ ይገኛል ። ኚትዳር ውጭ ዹሚደሹግ አሾሾ ገዳሜ   ሆነ በትዳር ላይ ትዳር መፈፀም እጅጉን አደገኛ ወንጀል ኹመሆኑም በላይ ዹአሰቃቂ ግዳያዎቜ መንስኀም በመሆኑ  ወንዶቜ ኹመሰል ድርጊት እንድትታቀቡ ጥሚ እናቀርባለን ። @min_ddis