es
Feedback
Min Addis?

Min Addis?

Ir al canal en Telegram

I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ የሆኑ ወሬዎች የሚለቀቁበት የኢንፎቴይንመንት ቻናል ነው

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Min Addis?

El canal Min Addis? (@min_ddis) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 10 584 suscriptores, ocupando la posición 17 943 en la categoría Noticias y medios y el puesto 3 141 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 10 584 suscriptores.

Según los últimos datos del 27 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -97, y en las últimas 24 horas de -17, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 29.18%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.25% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 090 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 615 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ የሆኑ ወሬዎች የሚለቀቁበት የኢንፎቴይንመንት ቻናል ነው

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 28 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

10 584
Suscriptores
-1724 horas
-627 días
-9730 días
Archivo de publicaciones
ይህንን ፎቶ ተመልከትልኝ : ይህንን ህዝብ አይተህ እዘንለት . ይህ ፎቶ በአማራ ክልል በፌዴራል መንግስቱ ሀይሎች እና በፋኖ ተዋጊዎች መካከል በሚካሄድ ውጊያ በመኪና ሲሄዱ የነበሩ ተሳፋሪዎች ናቸው።
ይህንን ፎቶ ተመልከትልኝ : ይህንን ህዝብ አይተህ እዘንለት . ይህ ፎቶ በአማራ ክልል በፌዴራል መንግስቱ ሀይሎች እና በፋኖ ተዋጊዎች መካከል በሚካሄድ ውጊያ በመኪና ሲሄዱ የነበሩ ተሳፋሪዎች ናቸው። ከተባራሪ ጥይት ለመትረፍ ከለላ ይዘው የተደበቁ ተሳፋሪዎች ናቸው : እዚህ ቦታ ላይ ያለውን ጭንቅ በደንብ የሚረዳው እዚህ ቦታ ላይ እና እዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ የሚያውቅ ሰው ቢሆንም እኛም ግን ፎቶውን አይተን ብቻ አንዳች ውርርርርር የሚያደርግ ስሜት ይሰማናል። የጥይት  ድምፅ እንዳያስደነግጠው ጡቷን እንደ ጋሻ የተጠቀመች እናት፤ . ወንድ ሆኖ ብርታት ቢኖረውም አጉል ቦታ ላይ በአጉል ሰአት ወንድነቱ የተፋለሰበት አባት፤ . ሚስቱን እና ልጁን በእቅፍ ከጥይት ያድን ይመስል ጥብቅ አድርጎ ያቀፈ አባት፤ እዚህ ቦታ ላይ መሆን፤ ይህንን ጭንቅ ማየት፤: አቅም የማጣት ስሜት፤ ምናልባትም የመጨረሻዋን ልመና ፈጣሪን መለመን፤ ለዚህ ነው ሰላምን የምንመኘው፤: ለዚህ ነው በመግባባትና በእርቅ የምናምነው፤ ነገ እዚህ ቦታ ላይ ላለመሆን !! (✍️በዘመላክ እንድርያስ) @min_ddis

አትሌት ሊ ሜይዠን (Li Meizhen) በ2024 በቻይናው የሄንግሹይ ማራቶን ውድድር ላይ ያሳየችው ፅናት አሁንም በዓለም ዙሪያ የብዙዎችን ልብ እያንቀሳቀሰ ይገኛል​። በ34ኛው ኪሎ ሜትር ላይ አሰቃ
አትሌት ሊ ሜይዠን (Li Meizhen) በ2024 በቻይናው የሄንግሹይ ማራቶን ውድድር ላይ ያሳየችው ፅናት አሁንም በዓለም ዙሪያ የብዙዎችን ልብ እያንቀሳቀሰ ይገኛል​። በ34ኛው ኪሎ ሜትር ላይ አሰቃቂ የሴትነት የተፈጥሮ ህመም እና የደም መፍሰስ ቢያጋጥማትም ውድድሩን አቋርጣ ከመውጣት ይልቅ ህመሙንና ስቃዩን ተቋቁማ በ2 ሰዓት ከ35 ደቂቃ አጠናቃለች። ​ይህ አጋጣሚ የአንድ አትሌት ጥንካሬ ብቻ አይደለም የሴቶች ተፈጥሮአዊ የፅናትና የመቋቋም አቅም ማሳያ እንጂ። ​ ለቤተሰቧና ለልጆቿ ስትል አመመኝ አትልም ​ለያዘችው ዓላማና ለሕልሟ እስከ መጨረሻው ትፋለማለች። ፈተናዎች በበዙባት ቁጥር ይበልጥ ጠንክራ ሆና ትቆማለች። (ዙምራ-ቱብ) @min_ddis

የክፍል አለቃውን የገደለው ታዳጊ በእስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት‼ የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በጅማ ከተማ በሚገኘው ሔርማታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ነው። የከተማው ፖሊስ እንዳስታወቀው
+2
የክፍል አለቃውን የገደለው ታዳጊ በእስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት‼ የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በጅማ ከተማ በሚገኘው ሔርማታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ነው። የከተማው ፖሊስ እንዳስታወቀው ሙአዝ ቢላል የተባለው ተማሪ የሚማርበትን ክፍል ሲረብሽ ቆይቶ በመስኮት በኩል ከመማሪያ ክፍሉ ዘሎ ወደ ውጭ ይወጣል። ይህን የተመለከተው የክፍሉ አለቃ ለምን እንዲህ ታደርጋለህ በማለት ይጠይቀዋል። ድርጊቱም ትክክል እንዳልሆነ ይነግረዋል። በወቅቱ ተማሪውን በመቆጣት የተሰጠውን ሀላፊነት ይወጣል። በዚህ ምክንያት ሁለቱ ተማሪዎች መካከል ግጭት ይፈጠራል። ልትናገረኝ አይገባም" በማለት የተበሳጨው ተማሪ ሙአዝ ቢላል አስቀድሞ ጩቤ ደብቆ ይዞ ወደ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ገብቶ ነበርና የክፍል አለቃ የነበረውን ተማሪ ሙሳብ መሀመድን በያዘው ስለት ወግቶ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደርጋል። ተከሳሽም በፖሊስ ተይዞ ምርመራ ተጣርቶበት ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ሀምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተማሪ ሙአዝ ቢላል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ15 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። ምንጭ:- የጅማ ከተማ ፖሊስ @min_ddis

የማንቸስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉይጂ ዶናሩማ ተሞሸረ የማንቸስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ እና የጣሊያን ብሔራዊ ቡድን አምበል ጂያንሉይጂ ዶናሩማ በትውልድ ሀገሩ ጣሊያን ሎኮሮቶንዶ በሚገኘው ኪዬዛ ማድሬ
የማንቸስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉይጂ ዶናሩማ ተሞሸረ የማንቸስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ እና የጣሊያን ብሔራዊ ቡድን አምበል ጂያንሉይጂ ዶናሩማ በትውልድ ሀገሩ ጣሊያን ሎኮሮቶንዶ በሚገኘው ኪዬዛ ማድሬ ዲ ሳን ጆርጆ ማርቲሬ ቤተክርስቲያን የልጅነት ፍቅረኛውን አሌሲያ ኤሌፋንቴን ዛሬ አግብቷል። ዶናሩማ የውስጥ ዲዛይነር (interior designer) የሆነችውን አሌሲያን እ.ኤ.አ. በ2016 በገዛ ትውልድ ከተማቸው ካስቴላማሬ ዲ ስታቢያ የተዋወቃት ሲሆን፣ በ2024 ሊዮ የተባለ ወንድ ልጅ ወልደዋል። ጥንዶቹ ባለፈው ግንቦት ወር ላይ “የረጅም ጊዜ ውል ተፈራርመናል” በሚል የኢንስታግራም መልዕክት መተጫጨታቸውን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። በዚህ ደማቅ የሰርግ ስነ-ስርዓት ላይ በርካታ የእግር ኳስ ዝነኞች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ፔፕ ጋርዲዮላ፣ አርሊንግ ሃላንድ፣ ሳንድሮ ቶናሊ፣ ፓኦሎ ማልዲኒ ፣ የሲቲው አማካኝ ማቲኦ ኮቫቺች እና ኒኮሎ ባሬላ ይገኙበታል። የሚገርመው ነገር፣ በሰርጉ ላይ የታደሙት ማልዲኒ እና ጋርዲዮላ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን ስለመምራት በዚህ ሳምንት አስቀድመው ውይይት አድርገው ነበር። (Daniel Gebremariam) @min_ddis

20 ዓመት የሚሆናትን የገዛ ሴት ልጁን አ ስ ገ ድ ዶ የግብረ *ስጋ ግንኙነት የፈፀመው አባት በ9 ዓመት እስራት ተቀጣ በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ ከሆኑት ኢንስፐክተር
20 ዓመት የሚሆናትን የገዛ ሴት ልጁን አ ስ ገ ድ ዶ የግብረ *ስጋ ግንኙነት የፈፀመው አባት በ9 ዓመት እስራት ተቀጣ በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ መንደር ሰባት ነዋሪ ከሆኑት ኢንስፐክተር ግርማ ጌታቸው እና ከወ/ሮ መስከረም ሙሉጌታ ተወላጅ የሆነችው ወጣት ሐና ግርማ ዕድሜዋ 20 ዓመት የደረሰና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ፤ ወላጅ አባቷ መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በቀን 6/9/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ቡና እያፈለች ባለችበት ከኋላ በመምጣት በጉልበት ወደ መኝታ ክፍል በማስገባት የለበሰችውን ቀሚስ በማውለቅ በጉልበት የግብረ ስጋ በመፈፀም ክብረ ንጽህናዋን ሲገረሰስ ልጅቷ ባሰማችው የድረሱልኝ ጩኸት ጎረቤት ደርሶ አስጥሏታል። ስለ ጉዳዩ ጥቆማ የደረሰው ፖሊስ ፣ አስፈላጊውን የማጣራት ስራ በመስራት በህግ ሲታይ ቆይቶ የምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በተከሳሹ ላይ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የ9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል ሲል የምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ዘግቧል ። (መረጃው የምዕራብ ዓባያ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ነው) @min_ddis

የደቡብ ወሎ ገዳም ጥቃትን በተመለከተ ፓትርያርኩ መግለጫ አወጡ፤ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. በተፈጸመው ጥቃት ላይ መግለጫ አውጥተዋል። በመግለጫቸው፣ በጥቃቱ የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፣ በርካቶች መቁሰላቸውን እና በገዳሙና በንዋየ ቅድሳቱ ላይ ውድመት መድረሱን ከሀገረ ስብከቱ መግለጫ በከፍተኛ ሐዘን መስማታቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይም፣ በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ በመግለጽ ድርጊቱ የሚያሳዝንና በፍጹም ተቀባይነት የሌለው የተወገዘ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ፓትርያርኩ እንዳሉት፣ የጸሎት፣ የትምህርት፣ የሰላምና የመንፈሳዊ እሴት ማዕከል የሆኑትን ገዳማት መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ክብርን፣ የሕግ የበላይነትንና የሀገር ሰላምን የማስጠበቅ ኃላፊነት ያላቸው በየደረጃው የሚገኙ ባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪ አካላትም የሚመለከታቸው ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል። አሰቃቂውን ጥቃት የፈጸሙ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ፣ ሌሎች ገዳማትና አድባራት ደኅንነታቸው እንዲጠበቅ እና ለተጎዱትም ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። በመጨረሻም፣ ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በስብአዊ ድጋፍ እንዲቆሙ አሳስበው፣ ለተበደሉት ፍትሕ፣ ለቆሰሉት ፈውስ፣ በግፍ ሕይወታቸውን ለተነጠቁት ዕረፍተ ነፍስ፣ ለቤተ ክርስቲያኒቱና ለሀገሪቱ ፍጹም ሰላም እንዲሰጥ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። @min_ddis

photo content

የራቁታቹን ፎቶ በሶሻል ሚድያ እለቃለሁ በማለት አስፈራርቶ ክብረ ንጽህና የገረሰሳ እና የግብረስጋ ድፍረት በደል ወንጀል የፈጸመው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ   በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 7ኛ ወንጀል ችሎት የቀረበው ተከሳሽ ፀጋዬ ሲሳይ ስዩም እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው መኖሪያ ቤቱ የ14 አመት እድሜ ያላቸውን የግል ተበዳዬችን ‹‹ላስጠናችሁ›› በማለት ለእህቱ ልጅ በማስጠራት በ2018 ዓ.ም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ስለፈጸመባቸው በዐቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፡፡   ተከሳሽ ግንቦት  30 ቀን 2018 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 10፡00 ሲሆን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ አካባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የ14 አመት እድሜ ያላትን የግል ተበዳይ  ‹‹ላስጠናሽ›› ብሎ በማስጠራት እና ከወንጀል ድርጊቱ በፊት ገላዋን ስትታጠብ ያነሳትን ፎቶ ‹‹ፌስቡክ ላይ እለቅብሻለሁ›› በማለት በልጅነት አእምሮዋ አስፈራርቶ የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና ክብረ ንጽህናዋ እንዲገረሰስ ያደረገ በመሆኑ በፈጸመው የግብረ ስጋ  ድፍረት ወንጀል ዐቃቤ ህግ ከሶታል፡፡   በሁለተኛ ክስ ተከሳሽ የወንጀል ህግ አንቀጽ 626/1/ን በመተላለፍ  ሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 11፡00 ሲሆን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው እንቁላል ፋብሪካ ይገዙ ሜዳ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የ14 ዓመት እድሜ ያላትን የግል ተበዳይ ‹‹ላስጠናሽ›› ብሎ በእህቱ ልጅ በማስጠራት የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና ክብረ ንጽህናዋ እንዲገረሰስ ያደረገ በመሆኑ በግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፡፡   ዐቃቤ ህግም በጉዳዩ ላይ የሰው እና የሰነድ ማሰረጃዎችን ያቀረበ ሲሆን ተከሳሽም በዐቃቤ ህግ የቀረበበትን የሰው እና የሰነድ ማሰረጃ ማሰተባበል ባለመቻሉ ድረጊቱን መፈጸሙ በማስረጃ ተረጋግጦ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበታል  ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት ሁለቱም የወንጀል ህጎች ሲሆኑ ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ የተከሰሰው በተደራራቢ ክሶች ስለሆነ   በወ/ህ/አንቀጽ 85 መሰረት ከብዶ እንዲወሰን ያቀረበውን ጥያቄ ፍ/ቤቱ ተቀብሎ ሀምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወንጀለኛው የቀደመ ሪከርድ ስለሌለበት አንድ ማቅለያ በመያዝ በ10 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡ @min_ddis

photo content

ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ? የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪ
ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ? የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል። ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል። ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር። በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል። Via:-አዲስ አድማስ @min_ddis

ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ ሊለቅ መሆኑ ታወቀ ​ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አዲስ የሙዚ
ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ ሊለቅ መሆኑ ታወቀ ​ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa’ee Jireenya Koo!» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አዲስ የሙዚቃ በቅርብ ቀን ለአድናቂዎቹ እንደሚያቀርብ ታወቀ። ​ድምጻዊው የህይወቱን ጉዞ እና ገጠመኝ የሚያንጸባርቅበት እንደሆነ የሚጠበቀውን ይህንን አዲስ የሙዚቃ ሥራውን አስመልክቶ ይፋዊ የማስተዋወቂያ ፖስተር ባሰራጨበት ወቅት፣ ሥራው በቅርቡ እንደሚለቀቅ አረጋግጧል። (መረጃው የፋስትመረጃ ነው) @min_ddis

ተወዳጁ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብ ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ፣ በታላቋ ብሪታንያ ለንደን ከተማ የሙዚቃ ኮንሰርቱን ለታደሙት የዲያስፖራ ማኅበረሰብ አባላት በተሳካ ሁኔታ አቅርቦ ካጠናቀቀ በኋላ፣ በገጠመው ድን
ተወዳጁ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብ ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ፣ በታላቋ ብሪታንያ ለንደን ከተማ የሙዚቃ ኮንሰርቱን ለታደሙት የዲያስፖራ ማኅበረሰብ አባላት በተሳካ ሁኔታ አቅርቦ ካጠናቀቀ በኋላ፣ በገጠመው ድንገተኛ የጤና እክል ምክንያት ወደ ሀገር ቤት መመለሱን አስታውቋል። ድምጻዊው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ በአውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ በዊልቸር ላይ ተቀምጦ የሚያሳይ ምስል በማጋራት፣ አድናቂዎቹን ያሳሰበ አጭር መልእክት አስተላልፏል። በመልእክቱም "ታምሜ ገባሁ፤ ስለሁሉ ግን እግዚአብሔር ይመስገን!!" በማለት የገለጸ ሲሆን፣ የሙዚቃ ኮንሰርቱን አቅርቦ ከጨረሰ በኋላ ስለገጠመው የጤና እክል ዓይነትም ሆነ ስለ ህመሙ ዝርዝር ሁኔታ እስከአሁን ድረስ ያብራራው ነገር የለም። ጎሳዬ ተስፋዬ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው፣ በልዩ የድምጽ ቃናውና በተወዳጅ የፍቅር ዜማዎቹ ከፍተኛ አድናቆትን ካተረፉ ታላላቅ አርቲስቶች አንዱ ነው። በለንደን የነበረውን ታላቅ የሙዚቃ ኮንሰርት በድምቀት አቅርቦ ከጨረሰ በኋላ ይህ የጤና እክል ማጋጠሙን ተከትሎ፣ በርካታ የሙዚቃ አፍቃሪዎች፣ የጥበብ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ፈጣን የህክምና ማገገም እንዲያገኝና ወደ ቀድሞ ሙሉ ጤናው እንዲመለስ ያላቸውን ልባዊ ምኞትና ጸሎት በመግለጽ ላይ ይገኛሉ። (Via-:ዘ-ሐበሻ) @min_ddis

ኢትዮጵያዊው ኮከብ ቃሉ ፑቲክ ከዓለም አቀፉ ኢንስታግራም ጋር በመተባበር አዲስ ሥራ አቀረበ ከ680 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ካለው የኢንስታግራም ኦፊሴላዊ ገጽ ጋር በመተባበር ድንቅ የቪዲዮ ሥራውን ያ
ኢትዮጵያዊው ኮከብ ቃሉ ፑቲክ ከዓለም አቀፉ ኢንስታግራም ጋር በመተባበር አዲስ ሥራ አቀረበ ከ680 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ካለው የኢንስታግራም ኦፊሴላዊ ገጽ ጋር በመተባበር ድንቅ የቪዲዮ ሥራውን ያቀረበው ተወዳጁ የይዘት ፈጣሪ ቃሉ ፑቲክ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረትን ሳቢ ሆኗል። በርካታ ኢትዮጵያውያን የኪነጥበብ አፍቃሪያን የቃሉን ተሰጥኦ፣ ጥረት እና ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ የማደግ ብቃት በመመልከት ወደፊት በታላቅ ስኬት እንደሚጓዝ በመመኘት ድጋፋቸውን ሲገልጹለት ቆይተዋል። አሁን ደግሞ የመጀመሪያውን ትልቅ ምዕራፍ በይፋ የጀመረ ሲሆን፣ ወደፊትም በልዩ ተሰጥኦው ዓለምን ማስደመሙን እንደሚቀጥል ትልቅ እምነት ተጥሎበታል። @min_ddis

ኢትዮጵያዊው ኮከብ ቃሉ ፑቲክ ከዓለም አቀፉ ኢንስታግራም ጋር በመተባበር አዲስ ሥራ አቀረበ ከ680 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ካለው የኢንስታግራም ኦፊሴላዊ ገጽ ጋር በመተባበር ድንቅ የቪዲዮ ሥራውን ያቀረበው ተወዳጁ የይዘት ፈጣሪ ቃሉ ፑቲክ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረትን ሳቢ ሆኗል። በርካታ ኢትዮጵያውያን የኪነጥበብ አፍቃሪያን የቃሉን ተሰጥኦ፣ ጥረት እና ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ የማደግ ብቃት በመመልከት ወደፊት በታላቅ ስኬት እንደሚጓዝ በመመኘት ድጋፋቸውን ሲገልጹለት ቆይተዋል። አሁን ደግሞ የመጀመሪያውን ትልቅ ምዕራፍ በይፋ የጀመረ ሲሆን፣ ወደፊትም በልዩ ተሰጥኦው ዓለምን ማስደመሙን እንደሚቀጥል ትልቅ እምነት ተጥሎበታል። @min_ddis

ህፃን አቅፋ የ12ኛ ክፍል ፈተና  ለመውሰድ የተቸገረችውን እናት ሕፃኑን ተቀብላ ፈተናውን ተረጋግታ እንድትወስድ ያደረገች የፖሊስ አባል አድናቆት ተቸራት በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ የ12ኛ  ክፍል ብሔራዊ ፈተና እየተሠጠ ባለበት ወቅት አንዲት ተፈታኝ እናት ሕፃን ልጅ አቅፋ ፈተናውን ለመፈተን ሞክራ ነበር።  ተፈታኟ እናት እቤት ልጅዋን የሚይዝላት ሰው በማጣቷ በቀጥታ አራስ ሕፃን ልጇን ይዛ በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ ውስጥ ገብታ የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመፈተን በመገደዷ ሕፃንዋን ልጅ አቅፋ  ለመፈተን ባደረገችው ጥረት በልጃ ለቅሶና መነጫነጭ ፈተናውን በትኩረት ለመፈተን ተቸግራ ነበር። በዚያ ቅፅበት የእናቲቱን ጭንቀት ያየችና የተረዳች በወቅቱ የፈተናው ሒደት ፀጥታ በማስከበር ላይ ያለች የፌደራል ፖሊስ አባል የሆነች ረዳት ሳጅን ራቢያ አብደላ  ህፃኗን ከእናቷ ተቀብላ በእቅፍዋ በመያዝ እናቲቱ ተረጋግታ ፈተናውን እንድትወስድ አድርጋለች።ፖሊስነት እናትነት ና ርሕራሔ ነው የምትለው ረዳት ሣጅን ራቢያ አብደላ የእናቲቱ የወደፊት ሕይወት ሊቀይር የሚችለውን የፈተና እድል በዚሕ አጋጣሚ እንዳይሰናከል የተመደበችበት የጥበቃ ስራ ጐን ለጐን እናት የምትወስዳቸውን የትምሕርት  ፈተናዎችን በሙሉ አጠናቃ እስክትወስድ ልጇን በእንክብካቤ ይዛ አቆይታለች። የረዳት ሣጅን ራቢያ አብደላ የፖሊስነት ተግባር በተመለከተ የደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ ማሕበረሠብ አባላት ፣ ይሕ ርሕራሔ የተሞላበትና ሰብዓዊነት የታከለበት ተግባር ማንኛውም ዜጋ በተሠማራበት የስራ መስክ መልካም ተግባር እንዲፈፅም ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ አድናቆታቸውን ገልፀዋል።የሕፃኗ እናት በበኩላ ልጄን ከወለድኩ ቅርብ ቀናት በመሆኑ እቤት ትቼ ለመምጣት የሚጠብቅልኝ ሠው በማጣቴ ይዤ እንድፈተን ቢፈቀድልኝም፣የልጅቱ ጩኽት ና መነጫነጭ ለአመታት የለፋሑበትና የወደፊት ሕይወቴን ሊቀይር የሚችለውን ፈተና  ተረጋግቼ ለመውሰድ ተቸግሬ ነበር ።   የፖሊስ አባሏ ይሕን አይታ ልጅቱን ተቀብላኝ እንደኔ በመንከባከብ ፈተናውን በሙሉ ልቤ ተረጋግቼ እንድፈተን አድርጋኛለች።እሕቴ ክብር ይገባሻል ፣ፖሊስ ሕግን ማስከበር ብቻ ሳይሆን ሠውን በክብር ና በርሕራሔ ማገልገል መሆኑን በተግባር አሳይተሻልና መልካም ሠው መሆን ትልቅ ማዕረግ ነውና  የአንቺን አርያ ሌሎች ይከተሉ እላለሁስትል ገልፃለች።  አንድ የመልካም ተምሣሌት ተግባር፣ለሌሎች አርአያ እንዲሆን ማበረታታት ደግሞ ከሁሉም አካላት ይጠበቃል ያሉት የደብረ ታቦር ነዋሪዎች ናቸው። (ዳጉ ጆርናል) @min_ddis

photo content

ተወዳጁ ድምፃዊ ታደለ ሮባና ባለቤቱ አርጀንቲናን ለመደገፍ በስፍራው ተገኝተዋል❗️ @min_ddis
ተወዳጁ ድምፃዊ ታደለ ሮባና ባለቤቱ አርጀንቲናን ለመደገፍ በስፍራው ተገኝተዋል❗️ @min_ddis

የሚያሳዝን ዜና... ወጣቷ እናት ራሷን አጠፋች...!! 💔😭 በዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ቤቷን ዘግታ በራሷ ሽጉጥ ራሷ ላይ ተኩሳ ተገኘች። ወደ ቅድስት ማርያም ሆስፒታል ተወስዳ የህክመና እርዳታ ቢደረግላ
+2
የሚያሳዝን ዜና... ወጣቷ እናት ራሷን አጠፋች...!! 💔😭 በዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ቤቷን ዘግታ በራሷ ሽጉጥ ራሷ ላይ ተኩሳ ተገኘች። ወደ ቅድስት ማርያም ሆስፒታል ተወስዳ የህክመና እርዳታ ቢደረግላትም ሕይወቷን ማትረፍ አልተቻለም። ታጋይ ብርኽቲ ተኽላይ በጀግንነቷ የምትታወቀው እሷ ምን አጋጠማት እስከዚህ ድረስ እንዲህ ያለ ከባድ ውሳኔ እንድትወስን ያደረጋት ምን ይሆን?? በዚህ ዓመት ትዳር መስርታ ህፃን ልጇን ትታ ከእኛ ተለይታለች። በ10/11/2018 ዓ.ም. በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የቀብር ሥርዓቷ ተፈጽሟል። 🙏 ነፍሷ በገነት ትረፍ! ለቤተሰቦቿም እግዚአብሔር መጽናናትን ይስጥ። Via:-አብረኸት ገ/እግዚአብሔር @min_ddis

የእግር ኳስ ታሪክን የጻፈው የፔሌ ማሊያ 4.9 ሚሊዮን ዶላር ተሸጠ የቀድሞው የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፔሌ በ1958ቱ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ የለበሰው ማሊያ 4 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላ
+1
የእግር ኳስ ታሪክን የጻፈው የፔሌ ማሊያ 4.9 ሚሊዮን ዶላር ተሸጠ የቀድሞው የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፔሌ በ1958ቱ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ የለበሰው ማሊያ 4 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር ተሽጧል፡፡ በዚያ ዓለም ዋንጫ ብራዚል ስዊድንን በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት በሆነችበት የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ፔሌ ሁለት ግቦቸን አስቆጥሮ ነበር፡፡ በወቅቱ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ሲያሳካ የ17 ዓመት ወጣት የነበረው ፔሌ የዓለም ዋንጫን ማሸነፍ የቻለ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ነው፡፡ በአጠቃላይ ሦስት ጊዜ ከሀገሩ ብራዚል ጋር የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች (17) በመሆን አሁንም ድረስ ክብረወሰኑን ይዞ ይገኛል። በ1986 የዓለም ዋንጫ ላይ ዲያጎ ማራዶና በእንግሊዝ ላይ 'የእግዜር እጅ' በመባል የሚታወቀውን ግብ ሲያስቆጥር የለበሰው ማሊያ በ2022 በ7 ነጥብ 1 ሚሊየን ፓውንድ መሸጡ ይታወሳል፡፡ የፔሌ ማሊያ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋች ማራዶና ቀጥሎ ከፍተኛ ዋጋ የወጣለት የእግር ኳስ ማሊያ ሆኗል። @min_ddis

በሰሜን ኮሪያ ራስን ማጥፋት በሀገር ክህደት ሊያስቀጣ ነው❗️ በሰሜን ኮሪያ ራስን ማጥፋት በሶሻሊስት ሥርዓቱ ላይ የተፈጸመ የሀገር ክህደት ወንጀል ተደርጎ እንዲቀጣ የሚል መመሪያ በሀገሪቱ መሪ ኪም
በሰሜን ኮሪያ ራስን ማጥፋት በሀገር ክህደት ሊያስቀጣ ነው❗️ በሰሜን ኮሪያ ራስን ማጥፋት በሶሻሊስት ሥርዓቱ ላይ የተፈጸመ የሀገር ክህደት ወንጀል ተደርጎ እንዲቀጣ የሚል መመሪያ በሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን መተላለፉን ዓለም አቀፍ ሪፖርቶች ጠቁመዋል። ይህ ያልተለመደ ውሳኔ የተላለፈው በሀገሪቱ ውስጥ ራስን የማጥፋት ድርጊት እየጨመረ በመምጣቱ ሲሆን፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት በየክልላቸው መሰል ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ መከላከል ካልቻሉ በግላቸው ተጠያቂ እንደሚሆኑ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። ይሁን እንጂ ከሀገሪቱ የሚወጡ መረጃዎች ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግባቸው በመሆኑ፣ ይህ መመሪያ በሰሜን ኮሪያ መንግሥት በኩል በይፋ አልተረጋገጠም። ይህ አዲስ ፖሊሲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበ ሲሆን፣ በሰዎች የአእምሮ ጤና፣ በመንግሥት ቁጥጥር እና በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ላይ አዲስ ክርክር አስነስቷል። ተቺዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንደሚናገሩት ከሆነ፣ ድርጊቱን በሕግ መከልከል መንግሥት ሰዎችን ወደ ተስፋ መቁረጥ የሚገፉትን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ከመፍታት ይልቅ፣ ለገጽታውና ለርዕዮተ ዓለሙ ብቻ እንደሚጨነቅ የሚያሳይ ነው ብለዋል። (አዲስ አድማስ) @min_ddis

Min Addis? - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @min_ddis