ch
Feedback
Min Addis?

Min Addis?

前往频道在 Telegram

I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ የሆኑ ወሬዎች የሚለቀቁበት የኢንፎቴይንመንት ቻናል ነው

显示更多

📈 Telegram 频道 Min Addis? 的分析概览

频道 Min Addis? (@min_ddis) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 732 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 17 820,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 103

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 732 名订阅者。

根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -169,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.75%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.30% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 656 次浏览,首日通常累积 1 642 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
I blog about marketing and sales, and also provide Infotainment news. Want to place ads? Click here: https://telega.io/c/min_ddis ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ የሆኑ ወሬዎች የሚለቀቁበት የኢንፎቴይንመንት ቻናል ነው

凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。

10 732
订阅者
-224 小时
-17
-16930
帖子存档
ይህ ታላቅ ሰው ዛሬ ፡ ሁለት ጎል ባገባበት ጫማ ላይ በልዩ ትእዛዝ የልጆቹን ስም አስፅፎ ነው የገባው ። " ኤቫ ፡ ቤላ ፡ ማቲዮ ፡ አላና ፡ እና ክርስቲያኖ ጁንየር " ( በእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ
ይህ ታላቅ ሰው ዛሬ ፡ ሁለት ጎል ባገባበት ጫማ ላይ በልዩ ትእዛዝ የልጆቹን ስም  አስፅፎ ነው የገባው ። "  ኤቫ ፡ ቤላ ፡ ማቲዮ ፡ አላና ፡ እና ክርስቲያኖ ጁንየር " ( በእግር ኳስ ብቃቱ ብቻ ሳይሆን ለቤተሰቡ ባለው ነገርም ተምሳሌት የሚሆን. ..ሰው ብሎ ዝም ። (✍️ዋሲሁን ተስፋዬ) @min_ddis

ለአፀደ ህፃናት ምርቃት ማከናወኛ ከትምህርት ቤቶች እየተጠየቅን ያለነው ወጪ አሳስቦናል ሲሉ ወላጆች ተናገሩ በአዲስ አበባ ከተማ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በበርካታ የአፀደ ህፃናት (ኬጂ) ትምህርት ቤቶች
ለአፀደ ህፃናት ምርቃት ማከናወኛ ከትምህርት ቤቶች እየተጠየቅን ያለነው ወጪ አሳስቦናል ሲሉ ወላጆች ተናገሩ   በአዲስ አበባ ከተማ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በበርካታ የአፀደ ህፃናት (ኬጂ) ትምህርት ቤቶች ላይ የሚደረጉ  የምርቃት ሥነ ሥርዓቶች  ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ ሆነው እየታዩ ነው።የልጆች የመመረቂያ ልብስ፣ ፎቶግራፍ፣ የአዳራሽ ኪራይ፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞች እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎች በወላጆች ላይ አሉታዊ የገንዘብ ጫናን እየፈጠረ ይገኛል።   ምርቃት ለልጆች ደስታና የትምህርት መነሳሳት፣ ለወላጆች  መታሰቢያ ቢሆንም ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያስገባ እንዲሆን ተጠይቋል።በመሆኑም  ሁሉንም ያካተተ እና ለወላጆች አቅም የሚመጥን የምርቃት ሥነ ሥርዓት ማዘጋጀት የተሻለ መፍትሄ ነው ሲሉ ቆይታቸዉን ከጣቢያችን ጋር ያደረጉ ወላጆች ገልፀዋል።   ትምህርት ቤቶች የምርቃት ስነስርአትን ለማድመቅ የሚያደርጉት ያልተገባ ፉክክርም በዚህ ረገድ  ብርቱ ጫናን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ።ብስራት ሬዲዮ በቀጣይ ዘገባው በአፀደ ህፃናት እየተስተዋለ የሚገኘውን  የምርቃት ስነስርአት ወጪ መናር መንስኤን ለማጣራት የሚመለከታቸውን አካላት በማናገር ጉዳዩን በሰፊው የሚዳስስ ይሆናል።  (ዳጉ ጆርናል) @min_ddis

photo content
+9

በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት የሚችል የመጀመሪያው አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን ሊካሄድ ነው በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ታሪክ አዲስ የኢንዱስትሪ ዕንቅስቃሴ ለመጀመር እና ስፖርትን ከመዝናኛነት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ምንጭነት ለማሸጋገር ያለመ ታላቅ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ። ይህንን በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ታላቅ ኹነት ያዘጋጁት አዱሊያን ማስታወቂያ እና ዳይመንድ ማርኬቲንግ ኤንድ ኮሚኒኬሽን ሲሆኑ፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ስፖርት ከባሕላዊ የሩጫ እና የእግር ኳስ ማዕቀፍ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የንግድ ትስስር እና የኢንዱስትሪ ምርታማነት የሚያሸጋግር የለውጥ ምዕራፍ እንደሚሆን አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። ይህ አውደ ርዕይ እና አገራዊ መድረክ በርካታ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎችን ይዞ የሚቀርብ ሲሆን፣ የስፖርት ዕቃ አምራቾችን፣ አከፋፋዮችን፣ ስፖርተኞችን እና የስፖርት ማሕበራትን በአንድ መድረክ በማገናኘት የአገር ውስጥ ምርትን ማበረታታት እና የገበያ ትስስር መፍጠር፤ በዓለም ላይ ያሉ ዘመናዊ የስፖርት ስልጠና ቴክኖሎጂዎችን (Digital Sports Solutions)፣ የስፖርት ሕክምና፣ አመጋገብ እና ሳይንስ ላይ ያተኮሩ የውይይት መድረኮችን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞችና አሰልጣኞች ማስተዋወቅ፤ ወጣቶች እና ቤተሰቦች በአካል ተገኝተው የተለያዩ የስፖርት አይነቶችን እንዲሞክሩ በማድረግ፣ በአካላዊ ብቃት፣ በእንቅስቃሴ እና በጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም የስፖርት ዝግጅቶችን በንግድ መልክ በማደራጀት ለሀገር ውስጥ አምራቾች ሰፊ እድል መስጠት፤ ይህም የውጭ ምንዛሪ ወጪን በመቀነስ የአገር ውስጥ አቅምን ለመገንባት እና ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል። ### ለሀገር የሚሰጠው ስልታዊ ጠቀሜታ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርቱ መስክ የጎላ ዝና ያላት ቢሆንም፣ ይህንን እውቅና ወደ ስፖርት ኢንዱስትሪ ለመቀየር የሚያስችል የተቀናጀ የንግድ እና የልውውጥ መድረክ ክፍተት እንደነበረበት ይነገራል። ዳይመንድ ማርኬቲንግ እና አዱሊያን ማስታወቂያ ይህንን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ስፖርት ከ"ሞያ" ወደ "ኢንዱስትሪ" ለማሸጋገር አቅኚ የለውጥ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ዝግጅቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን (MDF-based) የኤግዚቢሽን ስታንዳርዶችን የሚጠቀም በመሆኑ፣ ለወደፊት በሀገሪቱ ለሚካሄዱ ስፖርታዊ ኹነቶች አዲስ የጥራት ደረጃ (Benchmark) ያስቀምጣል። ይህም ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት አስተናጋጅነት (Sports Event Hub) እንድትታወቅ በማድረግ ረገድ ለስፖርት ዲፕሎማሲው ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ታምኖበታል። ኩባንያዎቹ ከዚህ ቀደም መሰል ዝግጅቶችን የማካሄድ ልምድ እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማሕበር ጋር በመተባበር "የአመለካከት እና አስተሳሰብ ለውጥ ኤግዚቢሽን" እንዲሁም ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በጃን ሜዳ "የባሕል እና ስፖርት ፌስቲቫል" በተሳካ ሁኔታ ማከናወናቸውን አስታውሰዋል። ለተሳታፊዎች እና ለጎብኚዎች ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እያንዳንዱ የኤግዚቢሽን ቦታ (Zone) በዓለም አቀፍ የደሕንነት መመዘኛዎች መሰረት እንደሚዋቀር ተገልጿል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከፌዴሬሽኖች፣ ከጤና ባለሞያዎች እና ከሚመለከታቸው የደህንነት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ላይ መሆናቸውንና የህክምና እና የድንገተኛ አደጋ ዝግጅቶች በተሟላ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል። ይህ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን የአንድ ጊዜ ክስተት ብቻ ሆኖ እንደማይቀረና ዋና ዓላማው በየዓመቱ የሚካሄድ ብሔራዊ የስፖርት ክብረ በዓል (Annual Sports Exhibition) ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮውን የመጀመሪያ ዝግጅት ስኬት እንደ ግብዓት በመጠቀም፣ በቀጣይ ዓመታት የክልል እና የዓለም አቀፍ ተሳታፊዎችን በማካተት ዝግጅቱን ይበልጥ ለማስፋት ታቅዷል።

ከጓደኛዬ ጋር ድብቅ ፍቅር ጀምረኃል በማለት የገዛ ባለቤቷን በመጥረቢያ በመምታት የግድያ ሙከራ የፈፀመችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች በሻኪሶ ከተማ አስተዳደር የከብት በረት የተባለ ስፍራ የተወለደችው የ27 ዓመቷ አለሚቱ ጃራ ትዳር መስርታ መኖር ከጀመረች ሶስት አመታትን አስቆጥራለች። አለሚቱ ከትዳር አጋሯ ጋር ሰላማዊ የተረጋጋ ሕይወት ትመራ ነበር።ከተወሠኑ ግዚያት ወዲህ ግን ይህው ትዳር ክፍተት ገጠመው። አለሚቱ እጅግ ለምትቀርባትና ለምትግባባት ጓደኛዋ ባለቤቴ ውጭ ውጭ በማለቱ ጥርጣሬ ውስጥ ገብቻለሁ በማለት ታማክራታለች።የአለሚቱ ጓደኛም  ይሕንን ከሠማች ጀምሮ በተለያ ግዚያት የአለሚቱ ባለቤት ማጥመድ ጀመረች።እንደ ፖሊስ መረጃ ግን  በአለሚቱ የተጠረጠረችው ጓደኛዋ ከባለቤትዋ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዳላት የተገኘ ተጨባጭ ማስረጃ ባይኖርም በአካባቢውም የአለሚቱ ባለቤት አለሚቱን ፈትቶ ጓደኛዋን ሊያገባ ነው የሚል ተጨባጭ ያልሆነ ወሬ  በይበልጥ ትዳራቸውን ይበጠብጥ እንደነበር ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። ጥር 2 ቀን 2018 ዓም ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ግን  ጥርጣሬዋን ይበልጥ የሚያጠናክር ነገር ተመለከተች። ባለቤቷ ከጓደኛዋ ቤት ሲወጣ በማየቷ ወደ ቤት ተመልሣ ባለቤቷ እስኪመጣ ትጠባበቅ ነበር።አለሚቱ ባለቤቷ እንቅልፍ እስኪወስደው ጠብቃ ፋስ የተባለውን ባለ ሑለት ጉጥ ስለታም መሣርያ በመያዝ በእንቅልፍ ላይ ያለውን ባለቤቷን ግንባሩ ላይ ሁለቴ በማሣረፍ ገድየዋለው በማለት  የመኝታ ቤቱን በር ዘግታ ከቦታው ትሠወራለች። ከቆይታ በኃላ ከቤት ውስጥ የድረሱልኝ ጩሕት ሲሰማ የአካባቢው ሠው ተሯርጦ ሲገባ የቤቱ ባለቤት በሐይለኛ ጉዳት ደርሶበት ሲመለከቱ ወዲያው ለከተማው ፖሊስ በማመልከት ጉዳት የደረሠበት የግል ተበዳይ በፖሊስ ወደ ሻኪሶ ሆስፒታል ተልኮ የሕክምና  እርዳታ እንዲያገኝ ተደረገ።  ተጎጂው በሕክምና እርዳታ ከሞት ቢተርፍም ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶበታል። ይሕንን የወንጀል ድርጊትን የፈፀመች አለሚቱ ገድዬዋለሁ ብላ በቀጥታ ከሻኪሶ ከተማ ወደ ነገሌ ቦረና ከተማ ምሽቱን ተጉዛ ጠዋት ላይ በአንድ ሆቴል አልጋ ተከራይታ ትቀመጣለች። ፖሊስም ባሠማራው የክትትል ቡድን አለሚቱ በአንድ ሆቴል አልጋ ተከራይታ በነጋታው ለማምለጥ ስትዘጋጅ በቁጥጥር ስር ትውላለች። የምርመራ መዝገቡ በበቂ የሕክምና የተለያዩ ማስረጃዎች ተጠናክሮ ለአቃቢ ሕግ ይላካል። አቃቢ ሕግም በከባድ የሠው መግደልና አካል ማጉደል ወንጀል ክስ ይመሠርታል። ክሱን የተመለከተው የምስራቅ ጉጂ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 3 ቀን 2018 በዋለው ችሎት ተከሣሽ አለሚቱ ጃራ በ12 አመት እስራት እንድትቀጣ ተወስኖባታል። (ዘገባው የብስራት ሬዲዮ ነው) @min_ddis

photo content

“ቤት ያላገኘ ተፈናቃይ ካለ ሥልጣኔን እለቃለሁ” — አቶ ግርማ ሰይፉ ​የአዲስ አበባ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በከተማዋ በነበረው የኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቅሎ ምትክ
“ቤት ያላገኘ ተፈናቃይ ካለ ሥልጣኔን እለቃለሁ” — አቶ ግርማ ሰይፉ ​የአዲስ አበባ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በከተማዋ በነበረው የኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቅሎ ምትክ ቤት ወይም መሬት ያላገኘ አንድም ሕጋዊ ሰው አለመኖሩን አስታወቁ። ካርታ ወይም የቀበሌ ቤት ኖረውት ምትክ ያጣ ሰው ካለ በገዛ ፈቃዳቸው ከሥልጣን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ ልማቱ ለሀገር ጥቅም የተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ ሆኖም ከአስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በደል የደረሰባቸው ወገኖች መኖራቸውን አልሸሸጉም። ​በሌላ በኩል፣ የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ዘመናዊነትና ውበት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ቢሆንም፤ በሂደቱ ወቅት በቂ ዝግጅት፣ ግልጽነትና ተመጣጣኝ ምትክ አላገኘንም የሚሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታዎች በተደጋጋሚ ሲነሱ መቆየታቸው ይታወቃል። @min_ddis

አርቲስት ካሙዙ ካሳ ምርጫውን ማሸነፉን አስታወቀ ​በየካ ክፍለ ከተማ በብልፅግና ፓርቲ ለምርጫ ቀርቦ የነበረው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ድምፅ ተሰጥቶት ማሸነፉን ይፋ አድርጓ
+2
አርቲስት ካሙዙ ካሳ ምርጫውን ማሸነፉን አስታወቀ ​በየካ ክፍለ ከተማ በብልፅግና ፓርቲ ለምርጫ ቀርቦ የነበረው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ድምፅ ተሰጥቶት ማሸነፉን ይፋ አድርጓል። አርቲስቱ የምርጫ ውጤቱን ተከትሎ ለመራጮች ምስጋናውን አቅርቧል። ​ታዋቂው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ በየካ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን ወክሎ በመወዳደር፣ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ​አርቲስቱ ባስተላለፈው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት፣ ለምርጫው መሳካት ላደረጉት ድጋፍ የአካባቢውን ነዋሪዎች እና መራጮቹን አመስግኗል። “እንደ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ ድምፅ በማግኘታችን እና በአካባቢው ማሸነፋችን ታላቅ ድል ነው” ሲል የገለጸው አርቲስት ካሙዙ፣ በድል አድራጊነት ስሜት ኢትዮጵያ አሸንፋለች የሚል መልዕክት አስተላልፏል። (Via:-ፋስት መረጃ) @min_ddis

ሚካኤል ማክጊየር ከጭንቅላቱ እስከ እግር ጥፍሩ በቆሻሻ እንደተሸፈነ የከሰል ማዕድን ማውጫ ፈረቃውን ከሰዓት 11፡00 ሰዓት ላይ አጠናቀቀ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ የሞቀ የደመቀ የቅርጫት ኳስ ጨዋታ በ
ሚካኤል ማክጊየር ከጭንቅላቱ እስከ እግር ጥፍሩ በቆሻሻ እንደተሸፈነ የከሰል ማዕድን ማውጫ ፈረቃውን ከሰዓት 11፡00 ሰዓት ላይ አጠናቀቀ። ምሽት 12 ሰዓት ላይ የሞቀ የደመቀ የቅርጫት ኳስ ጨዋታ በከተማው ኬንተኪ ዊልድካትስ ይካሄዳል። ለልጁ የዛሬውን ቅርጫት ኳስ ለማሳየት ቃል ገብቶለት ነበር። ራሱን ለማፅዳት ሻወር ለመወሰድና ልጁን ከቅርጫት ኳስ ሜዳው ለማድረስ የነበረው አንድ ሰዓት በፍፁም እንደማይበቃው ከስራ የወጣበትን ሰዓት ሲመለከት ገብቶታል። ከነስራ ልብሱ ከነአዋራውና ጭቃው ከልጁ ጋር በኬንታኪ ዊልድካትስ ሜዳ ለልጁ የገባውን ቃል በማክበር ማሳለፍን መረጠ። ባለቤቱ ሞሊ ይህንን ምስል በቴሌቨዠን መሰኮት ከተመለከተች በኃላ በፌስቡክ ላይ ይህንን አጋርታለች። 👇 "ባለቤቴ ከልጆቻችን ጋር እቤት እንድቆይ ይህን የስራ ጫና የወሰደው ቤተሰባችንን ለመርዳት ነው። ብዙ ጊዜ በስራ ምክንያት ሁነቶች ያመልጡናል። ምንም ቢሆን፣ የቱንም ያህል ቢደክመው ወይም ቢቆሽሽ እድሉን በሚያገኝበት ጊዜ ግን የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል።" ደግ አይለፍችሁ❤️🙌 ለአባቶች የተገረበ (✍️በተስፋዬ ሐይሌ) @min_ddis

ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ የውጭ ሀገር ዜጎችን በመያዣነት በመጠቀም ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የጠየቁ ሦስት ፓኪስታናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ። የፓኪስታን ዜግነት ያላቸው ዝሻን ካሊድ፣ ፍርዝ መሃመ
+3
ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ የውጭ ሀገር ዜጎችን በመያዣነት በመጠቀም ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የጠየቁ ሦስት ፓኪስታናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ። የፓኪስታን ዜግነት ያላቸው ዝሻን ካሊድ፣ ፍርዝ መሃመድ እና መሀመድ ጀናይድ የተባሉ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት ሰኔ 4 እና ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ/ም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ አትሌቶች መንደር ነው። ተጠርጣሪዎቹ በተከራዩት የመኖሪያ ቤት ውስጥ የህንድና የባንግላዴሽ ዜግነት ያላቸውን ግለሰቦች በመያዣነት በመጠቀም የግል ተበዳዮችን በገመድ በማሰርና በፕላስተር በማፈን ከ15 እስከ 30 ሚሊየን ብር በመጠየቅ ጥቃት አድርሰውባቸዋል። ተጠርጣሪዎቹ በዚህ ብቻ ሳያበቁ ሰኔ 11ቀን 2018 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት የገቡ 4 የህንድ ዜጎችን በማሰርና በመደብደብ ከ15 እስከ 25 ሺህ የህንድ ሩፒ አስልኩ በማለት ድብደባ ሲፈጽሙባቸው እንደነበር የግል ተበዳዮች ለፖሊስ ቃላቸውን ሰጥተዋል።                                                                 የወንጀሉ መፈጸም መረጃ የደረሠው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ተገቢውን የፍርድ ቤት መያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ባከናወነው ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዎቹን ለወንጀል ድርጊት ሲጠቀሙበት ከነበረው ቢላዋ፣ ገመድና ፕላስተር እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገር ገንዘቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል።                                                                          የአካባቢው ነዋሪዎች ተጠርጣሪዎቹ እንዲያዙ መረጃ በመስጠት ላደረጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን ያቀረበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙም ለፖሊስ መረጃ መስጠት እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።

የከተማው ፖሊሶች የፌደራል ፓሊስ አባላትን በኃይል ሲያስሯቸው የሚያሳየው ቪዲዮ አነጋጋሪ ሆኗል በደቡብ ክልል ውስጥ በተቀረጸ የጸጥታ ኃይሎች ተሽከርካሪ ላይ፣ የከተማው ፖሊስ አባላት የፌዴራል ፖሊስ አባላትን በኃይል እያጣደፉ በተሽከርካሪው ላይ እየጫኑ ሲያስሯቸው የሚያሳይ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ተመሳሳይ የሕግ ማስከበር ኃላፊነት ያለባቸው ተቋማት እርስ በርሳቸው በዚህ መልኩ ፍጥጫና ግጭት ውስጥ ገብተው መታየታቸው በብዙዎች ዘንድ ድንጋጤንና ግራ መጋባትን የፈጠረ ሲሆን፣ በሕዝብ ዘንድም ስለ ጸጥታ መዋቅሩ መከባበርና ቅንጅት በርካታ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል። የከተማው ፖሊሶች የፌዴራል ባልደረቦቻቸውን በዚህ ደረጃ ለማሰርና የኃይል እርምጃ ለመውሰድ ምን ዓይነት ምክንያት እንደገፋፋቸው እስካሁን በውል የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን፣ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የበላይ የጸጥታ አካላት አስቸኳይና ግልጽ ማብራሪያ የሚፈልግ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል። (Via:-Ethio Lead) @min_ddis

ምንም እንኳን እንደ እናቶች ቀን ባይደምቅም ፡ ዛሬ የአባቶች ቀን ነው ። ....... የማይክ ታይሰን ልጅ አሚር ታይሰን ፡ አንድ ቀን ለአባቱ እኔም እንዳንተ ቦክሰኛ መሆን እፈልጋለሁ አለው ። ታይ
ምንም እንኳን እንደ እናቶች ቀን ባይደምቅም ፡ ዛሬ የአባቶች ቀን ነው ። ....... የማይክ ታይሰን ልጅ አሚር ታይሰን ፡ አንድ ቀን ለአባቱ እኔም እንዳንተ ቦክሰኛ መሆን እፈልጋለሁ አለው ። ታይሰን ይህን ሲሰማ ፊቱ ተለዋወጠ ፡ ልጁ በዛው ቅፅበት ቦክሰኛ የሆነና ጡንቻቸውን ያፈረጠሙ ቦክሰኞች በጭካኔ ሲመቱት ያየ ያህል የልጁ ሀሳብ ዘገነነው ። ........ እና በፍፁም ቦክሰኛ አትሆንም አለው ። አንተ ከምቾት ህይወት ጋር ተላምደሀል ፡ በቅንጦት ነው ያደከው  ። እንደኔ ቦክሰኛ መሆን አትችልም ። አየህ አንተ በቦክስ ውስጥ ሳታልፍ ኑሮን ማሸነፍ ችለሀል ፡ ምክንያቱም ምርጫ ነበረህ ። ...... እኔ ቦክሰኛ የሆንኩት ኑሮን ለማሸነፍ ምርጫ ስላልነበረኝ ነው ። አንተ የጨካኝ ቦክሰኞችን ቡጢ መቋቋም አትችልም  እኔ በዚህ ውስጥ ያለፍኩት እናንተ ልጆቼ እንዳትቸገሩ ነው ። ሀሳቤ ተሳክቶም ልጆቼን ማስተማር እና በምቾት ማኖር ችያለሁ እና እኔ ባለፍኩበት መንገድ እንድታልፉ ፈፅሞ አልፈልግም በማለት መለሰለት ። ... ልጆቼ ቦክስን በሚያህል ትልቅ ስቃይና ህመም ያለበት ስፖርት ውስጥ ተሳትፈው እኔ የተሰማኝ ህመም ሲሰማቸው ማየት አይደለም ማሰብም አልፈልግም ሲል መለሰለት ። ከዛን እለት ጀምሮ የማይክ ታይሰን ልጅ ቦክሰኛ የመሆን ሀሳቡን ተወ ። አሚር ታይሰን በአሁኑ ወቅት DEBONAIR የሚባል የራሱን የፋሽን ብራንድ ፈጥሮ እሱ ላይ እየሰራ ነው ። መልካም የአባቶች ቀን ። @min_ddis

photo content
+2

ዳኛዋንና ባለቤቱን በችሎት አዳራሽ ተኩሶ የገደለው ግለሠብ ራሱን ከሆስፒታል ፎቅ ወርውሮ አጠፋ በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት የባልና ሚስት ክርክር የነበረን የመጨረሻ ውሣኔ ላይ የችሎት ዳኛዋን ና ባለቤቱን በሽጉጥ ተኩሶ የገደለው ግለሠብ ከሚታከምበት ሆስፒታል ፎቅ እራሱን ወርውሮ ሕይወቱን ማጥፋቱን ፖሊስ አስታወቀ። የሆለታ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ዋና መምርያ አዝዥ ኮማደር ፀጋዬ ቶላ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት አቅናው በቀለ፣የተባለ ተጠርጣሪው ግለሠብ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓም በወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት የፍታብሔር ችሎት ውስጥ ማንም ሣያየው በወቅቱ በነበረው አዲስ እና ግማሽ ክፍሉ በተጠናቀቀውና አገልግሎት በሚሰጠው የፍርድ ቤቱ ሕንፃ በጓሮ በኩል ተቀምጦ የጦር መሣርያ ሽጉጥና ስለታም መሣርያ ታጥቆ ስሙ ሲጠራ ወደ ችሎት አዳራሹ  መግባቱን ገልፀዋል። ችሎት ላይም የመጨረሻው የውሣኔ ሐሣብ  በተሠየሙት ዳኛ ወይዘሮ  ወርቄ ፈከንሣ ሲነበብ የተበሣጨው በመጀመሪያ ታጥቆ በገባው ሽጉጥ ዳኛ ወይዘሮ ወርቄን ፈከንሣን ተኩሶ በመምታት እንዲሁም የክርክሩ አካል ና አብራ ቆማ ፍትሕን ስጠብቅ የነበረችውን ባለቤቱና የልጆቹን እናት ወይዘሮ አልማዝ መኮንን ተኩሶ በመምታት በሌሎች ሠዎች ላይ ጉዳት ለማድረስ ሞክሮ እራሱ ላይም ተኩሶ ጉዳት ማድረሱን ገልፀዋል። ፖሊስም በወቅቱ ጉዳት አድራሹን አቅናው በቀለ የተባለውን ግለሠብ  በቁጥጥር ስር በማዋል ፣በፖሊስ ጥበቃ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እንዲታከም ተደርጎ አልጋ ይዞ የሕክምና ክትትል ላይ ነበር።ሆኖም ግለሠቡ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓም የሕክምና ክትትሉን ጨርሶ ስለተሻለው ከሆስፒታል ለመውጣት እንዲዘጋጅ ሲነገረው ከሆስፒታሉ ሶስተኛ ፎቅ በመስኮት እራሱን በመወርወር ህይወቱን ማጥፋቱን ተናግረዋል። በወቅቱ ግለሠቡ ከሌሎች ሠባት በወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩና ሕክምና የሚከታተሉ ግለሠቦች ጋር ወደ መስኮት ጥግ የተኛ መሆኑን የገለፁኡት ኃላፊው ፖሊስ ሣይደርስ ማንም ሣያየው ከሶስተኛ ፎቅ ራሱን ወርውሮ  ህይወቱን አጥፍቷል።ፖሊስ የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመበት እለት አንስቶ ባደረገው ማጣራትና ምርመራ በግለሠቡ ቤት በርካታ ሕገወጥ  የጦር መሣርያዎች በመኖርያ ቤቱ በፍተሻ የተገኙ ሲሆን በእለቱ የችሎት ሒደት የጥበቃ ክፍተት የፈጠሩ ስራቸውን በአግባብ ባለመወጣታቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ኮማደር ፀጋዬ ቶላ ለጣቢያችን ጨምረው ገልፀዋል። የወንጀል ድርጊቱ በፍርድ ቤቶች ዙርያ ያለው የፍተሻ ስርዓት እንዲጠናከር የሚያሣይ መሆኑን ብዙዎች የተስማሙበት ነው። @min_ddis

ከቀናት በፊት አርጀንቲና ከአልጄሪያ አድርገውት በነበረው ጨዋታ ላይ ነው ። ዝነኛው የአለማችን የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ቡድኑን በሀትሪክ መሪ እንዲሆን ካደረገ በኋላ ፡ በ80 ኛው ደቂቃ ላይ
ከቀናት በፊት አርጀንቲና ከአልጄሪያ አድርገውት በነበረው ጨዋታ ላይ ነው ። ዝነኛው የአለማችን የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ቡድኑን በሀትሪክ መሪ እንዲሆን ካደረገ በኋላ ፡ በ80 ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ ወጥቶ ተጫዋቾች ወደሚያርፉበት ቦታ ሲሄድ ሁሉም ወንበር ተይዟል ። በዚህ ጊዜ የቡድን አጋሩ የሆነው ቲያጎ አልማዳ ፡ የሚቀመጥበት ቦታ ላጣው ሊዮኔል ሜሲ በማክበር ቦታውን ለቆ እንዲቀመጥበት ሲነሳ ፡ ሜሲ ፍቃደኛ አልሆነም ። እና ፡ ዝነኝነቱ ሳያግደውና ሳይኮፈስ ፡ ልክ እንደልጆች ሳሩ ላይ ተቀምጦ ጨዋታውን ጨረሰ ። ይህ ሜሲ ያሳየው ጥበብ ተናንሶ መኖር ፡ ይባላል ። ትህትና !!! በነገራችን ላይ እኔ የክርስቲያኖ ሮናልዶ አድናቂ ነኝ ፡ ሆኖም ለCR7 ያለኝ ትልቅ ቦታ ፡ የሜሲን ችሎታ እና humbleness ከማድነቅ አያግደኝም ። (✍️ዋሲሁን ተስፋዬ) @min_ddis

የእናቱን አስክሬን ቤት አስቀምጦ የእናቱን ቃል ለማክበር የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና የተቀመጠው ካሊድ ይሕ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል ገና የአስ
የእናቱን አስክሬን ቤት አስቀምጦ የእናቱን ቃል ለማክበር የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና የተቀመጠው ካሊድ ይሕ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል ገና የአስራ አራት ዓመት ልጅ ነው።ከሑለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከእናቱ ጋር ይኖራል። ካሊድ ከእናቱ ጋር ሲኖር ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ ሌላ ትዳር መስርቶ ጅጅጋ ከተማ ይኖራል። ካሊድ ሠሞኑን እናቱ ታምወው በነበረበት ወቅት እኔ አንድ ነገር ብሆን ምንም ቢፈጠር አመት የለፋሕበትን ፈተና እንዳታቋርጥ ብለው ቃል ያስገቡታል። እናትም በነጋታው የስምንተኛ ክፍል ፈተና ሊሲጥ ሠዓታት ሲቀረው ሕይወታቸው ያልፋል።ካሊድ በእናቱ ሞት ከፍተኛ ሐዘን ቢሰማውም ለእናቱ የገባው ቃል አክብሮ የእናቱን አስክሬን እቤት ጥሎ የጥዋት ፈተናውን ተፈተነ። ካሊድ ከሠዓት እናቱን አልቅሶ ቀብሮ ተመልሶ የከሰዓት ፈተናውን ተፈተነ።የዚሕ የአስራ አራት አመት ታዳጊ የሕይወት ፈተና ብዙዎችን በሐዘን ማስለቀሱን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል። Via:-ዳጉ ጆርናል @min_ddis

የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ
የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ በአሜሪካን ሀገር ህይወታቸው ማለፉን የቅርብ ወዳጆቻቸው ለመዝናኛ ሚዲያ አስታወቁ። አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የቦብ ማርሊ ልጆችንእና በርከት ያሉ ታዋቂ ሙዚቀኞችን የማማከርና የማስተዳደር ስራ የሰሩ ጉምቱ የሙዚቃ አስተዳደር ባለሞያ ነበሩ። አቶ አዲስ የቴዲ አፍሮ ማኔጀር በመሆንም ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል። በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በኒው ጀርሲ ግዛት ህይወታቸው ያለፈው አቶ አዲስ ገሰሰ ፣ የሞታቸው ምክንያት ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደታሰበ የደረሰን መረጃ ያመለከታል። (ምንጭ:-መዝናኛ ሚዲያ) @min_ddis

ከሊዮኔል ሜሲ እንባ ጀርባ ያለው ሰውኛ ስብራት💔 አርጀንቲናዊው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ በጨዋታው ላይ አስደናቂ ሀትሪክ (ሦስት ጎል) አስቆጥሮ በደስታ በሚፈነጥዝበት ቅጽበት፣ ባልተለመደ መልኩ አይኖቹ በ
ከሊዮኔል ሜሲ እንባ ጀርባ ያለው ሰውኛ ስብራት💔 አርጀንቲናዊው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ በጨዋታው ላይ አስደናቂ ሀትሪክ (ሦስት ጎል) አስቆጥሮ በደስታ በሚፈነጥዝበት ቅጽበት፣ ባልተለመደ መልኩ አይኖቹ በእንባ እረጥበው ሜዳ ላይ ሲያለቅስ መታየቱ የብዙዎችን ልብ ሰብሯል፣ ግራ ማጋባትም ፈጥሮ ነበር። አርጀንቲናዊው ኮከብ ከጨዋታው በኋላ ጋዜጠኞች ለምን እንዳለቀሰ ሲጠይቁት " ከስፖርቱ ጋር የተያያዘ ነገር አይደለም "ብሎ ነበር። ሊዮኔል ሜሲ፣ " አስቸጋሪ እና የተወሳሰቡ ቀናት አሳልፌያለሁ። የቡድን አጋሮቼን አመስጋኝ ነኝ ከጎኔ ነበሩ " የሚል ምላሽ ነበር የሰጠው ። በዕለቱ ምን እንደገጠመው በግልጽ ያልተናገረው ሊዮኔል ሜሲ ፣ የቡድን አጋሮቼ ብዙ ጥንካሬ ሰጥተውኛል " ከማለት ውጪ ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል። ነገር ግን ከወደ አርጀንቲና እየወጡ ያሉ መረጃዎች የሊዮኔል ሜሲ እንባ ምንጩ ከሜዳ ውጪ ባለ የህይወት ፈተና መሆኑን የሚጠቁሙ ሆነዋል ። በተለይም አርጀንቲናዊው ጋዜጠኛ ኤድዋርዶ ፌንማን ባወጣው መረጃ ሊዮኔል ሜሲ ወላጅ አባቱ በፀና ታመውበት አስቸጋሪ ሁኔታ ማሳለፉን ዘግቧል። ወላጅ አባቱ ለወራት ታመው ነበር የተባለ ሲሆን ባለፉት ቀናት ህመሙ ፀንቶባቸው እንደነበር ተሰምቷል። ሊዮኔል ሜሲ በተፈጠረው ነገር ተጎድቶ እንደነበር እና በብሔራዊ ቡድን ስብስብ እንደታገዘ ተጠቁሟል። ሊዮኔል ሜሲ ከ 68ዓመት ወላጅ አባቱ ጋር ቅርብ ግንኙነት ሲኖረው እንደ ወኪሉ እና ማናጀሩም ሆኖ ያገለግላል። (የመረጃው ምንጭ የአርጀንቲና ተደማጭ የራድዮ ጣቢያ Radio Mitre ነው።) @min_ddis

🔶መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማ
🔶መምህሩም ተማሪውም ታሰሩ በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህር እና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለጸ። ተማሪውን ወክሎ ከመምህርነት ስነ-ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ላይ ተሳትፏል የተባለውና ከቡልቂ ከተማ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ፣ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነውን አብነት እንዳለን ተክቶ ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው። ፈተናውን ከኩረጃና ከስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ የሰጠው ተማሪ በቁጥጥር ስር መዋል መቻላቸውን አስረድተዋል። የሳውላ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው፣ ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሰላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል። ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ ህግ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሰራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ሳውላ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን @min_ddis

ባል አራስ የሆነች የልጅ እናቱን በመተው  ከትዳር ውጭ አሸሸ ገዳሜ ሲል እጅ ከፍንጅ ተያዘ ! ከላይ በቪዲዮ እንደምታዩት ከወለደች 3ወር እንኳን ሳይሆናት ባላያዋ ላይ ከሌላ ሴት ጋር  አሸሸ ገዳሜ ሲል ሚስትየው ሳይታሰብ ወይም በመከታተል  የአልጋ ላይ ጨዋታ ሲጫወት በቁጥጥር ስር አውላዋለችዋለች ።   በዚህ መሰረት ሚስትየው በፈፀመባት ክህድት እጅግ በመናደድ አንተ ባለጌ ክፈት እያለችው በሩን በድንጋይ  ደብድባለች  ።  ሰዎች እንድትረጋጋ ቢመክራቱም ጉድ እንደምትሰራው ዝታበታለች። ባልየው የወሲብ ግንኙነት ከሚደርጋት ሴት ጋር ከቤቱ ውስጥ በሩን በደንብ አጥብቆ በመያዝ እባካሽ ተረጋጊ ውዴ እባክሽ ተረጋጊ ውዴ የማደርግልሽን አታውቂም በማለት እየተማፀነ ይገኛል ። ከትዳር ውጭ የሚደረግ አሸሸ ገዳሜ   ሆነ በትዳር ላይ ትዳር መፈፀም እጅጉን አደገኛ ወንጀል ከመሆኑም በላይ የአሰቃቂ ግዳያዎች መንስኤም በመሆኑ  ወንዶች ከመሰል ድርጊት እንድትታቀቡ ጥረ እናቀርባለን ። @min_ddis