en
Feedback
Ajeba Emmanuel united church

Ajeba Emmanuel united church

Open in Telegram

እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

Show more
259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
Voice message01:07

Voice message01:57

Voice message00:54

#ሰው_ተወልዶ_ነው_የሚያምነው_ወይንስ_አምኖ_ነው_የሚወለደው? እንዲህ ያለው ትምህርት “ኢየሱስ ቤዝዎቱ ለተወሰኑት ነው፣ የተወሰኑ የተባሉት ደግሞ አስቀድሞ የተመረጡት ናቸው፣ የሚድኑትም እነዛ አስቀድሞ የተወሰኑት ብቻ ናቸው፣ የሚድኑበት ቀን በደረሰ ጊዜ ደግሞ ሕይወት ሰጥቶ ከሞቱበት ይቀሰቅሳቸዋል። ስለዚህ ህይወት ሰጥቶ ነው እንጂ እንዲያምኑ የሚያደርገው አምነው አይደለም ህይወትን የሚሰጣቸው።” ብለው የሚያስተምሩ ሰዎች የገቡበት ጣጣ ነው። ልንጠይቅ የሚገባው ጥያቄ Does salivation precedes faith? (ድኅነት እምነትን(ማመንን) ይቀድማል?) የሚል ነው። ዳግም ውልደት ማለት ድኅነት(መዳን)፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መምጣት፣ ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገር፣ ወዘተ የሚሉትን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች የሚያካትት ነው። “ሰው ተወልዶ ነው የሚያምነው ወይንስ አምኖ ነው የሚወለደው?” የሚለው ጥያቄ “ሰው ከዳነ በኋላ ነው የሚያምነው ወይንስ አምኖ ነው የሚድነው? ሕይወት ካገኘ በኋላ ነው የሚያምነው ወይንስ ካመነ በኋላ ነው ሕይወት የሚያገኘው?” ከሚሉት ጥያቄዎች ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለሆነም በዚህች አጭር ጽሁፍ “ሰው አምኖ ነው የሚድነው ወይንስ ከዳነ በኋላ ነው የሚያምነው” የሚለውን እንመልሳለን። 1. ኤፌ 2፡8 “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም” For by grace you have been saved through faith. Τῇ γὰρ χάριτι ἐστὲ σεσωσμένοι διὰ πίστεως ⭕️ διὰ የሚለው ቃል መስተዋድድ (preposition) ሲሆን እንደየ አውዱ በሁለት ሁኔታ አንድ አረፍተ ነገር ውስጥ ሊገባ ይችላል። የመጀመሪያው በርቱዕ ተሳቢ ሙያ (Accusative case) የሚቀመጥ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በአገናዛቢ-ዘርፍ (Genitive cas) የሚቀመጥ ነው። በዚህ በኤፌ 2፡8 ላይ በርቱዕ ተሳቢ (Accusative case) ቢሆን ኖሮ የገባው ትርጉሙ “ለእምነት ሲባል” (for the sake of faith) ሊሆን ይችል ነበር። ስም (noun) የሆነው “አድኗችኋል” የሚለው የግሪክ ቃል σεσωσμένοι በአገናዛቢ-ዘርፍ (Genitive case) ስለተቀመጠ መስተዋድድ (preposition) የሆነው διὰ የተሰኘው ቃል በአገናዛቢ-ዘርፍ ተቀምጧል። ይህ ቃል በአገናዛቢ-ዘርፍ ሲመጣ ትርጓሜው “በእምነት በኩል ወይም በእምነት”(by means of faith or through faith) ተብሎ ይተረጎማል። በአረፍተ ነገሩ ውስጥ "በእምነት" διὰ πίστεως የሚለው ቃል የገባው ደግሞ እንደ “ምክንያት” ወይም እንደ “መሳሪያነት” (instrument) ነው። ይህ የቃል አጠቃቀም በግሪክ የቋንቋ ጥናት መሰረት "ምክንያታዊ አገናዛቢ-ዘርፍ" (Genitive of Means) ይባላል (የግሱ ድርጊት በምን እንደተፈጸመ የሚያሳይ ምክንያታዊ/መሳሪያዊ ቃል ነው)። ለምሳሌ አንድ ሰው “ሚስማሩን በመዶሻ መታሁት” ቢል፤ ምን ተጠቅሞ ወይም በምንድን ነው የመታው? ተብሎ ቢጠየቅ ምላሹ የሚሆነው “በመዶሻ” የሚል ነው። መዶሻ ድርጊቱ የተፈጸመበት መሳሪ (instrument) ሆኖ ስለገባ means ይሆናል። ልክ እንደዚሁ “እምነት”πίστεως የሚለው ቃል በኤፌ 2፡8 ላይ ግሱ (አድኖአችኋልና የሚለው ድርጊት) የሚፈጸምበት መሳሪያ ተደርጎ ተቀምጧል። ስለዚህ ለ-እምነት ሳይሆን የምንድነው በ-እምነት ነው የምንድነው። "ለ-እምነት" ቢሆነ ኖር ያዳነን የሚቀድመው “መዳን” ይሆን ነበር ነገር ግን "በ-እምነት" ስላዳነን ሳያምኑ መዳን እንደሌለ ያስገነዝበናል። 2. ሮሜ 3:21-256 አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ 22 እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ 23 ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ 24 በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። 25 እርሱንም እግዚአብሔር #በእምነት_የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥ 26 ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው። ⭕️ቁጥር 25 ላይ “በእምነት የሚገኝ” የሚለው የግሪክ ሐረግ διὰ τῆς πίστεως ነው የሚለው:: ይህ ሐረግ ከኤፌ 2፡8ቱ ጋር በመሃከል ከገባው መስተአምር (Article) τῆς (the) ውጪ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ በደሙ የሆነ ማስተሰሪያውን ሰዎች ያገኙት፣በጸጋው መጽደቅን የተቀበሉት በእምነት በኩል እንደሆነ ያስረዳል። ሰው ስለጸደቀ (ከጸደቀ በኋላ) ሳይሆን የሚያምነው ከአመን ነው የሚጸድቀው የሚል ትምህርት ያስተላልፍልናል። 3. ሐዋ 16:31 27 የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ። 28 ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፡— ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ ብሎ ጮኸ። 29 መብራትም ለምኖ ወደ ውስጥ ሮጠ፥ እየተንቀጠቀጠም ከጳውሎስና ከሲላስ ፊት ተደፋ፤ 30 ወደ ውጭም አውጥቶ፡— ጌቶች ሆይ፥ እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል? ኣላቸው። 31 እነርሱም፡— በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ፡ አሉት። And they said, Believe in the Lord Jesus, and you will be saved. ⭕️በዚህ በሐዋ 16፡31 ላይ የምንመለከተው ክንውን እንደሚያሳየን “ኢየሱስ ያድንህና ከዛ ታምናላችሁ” የሚል ትምህርት ሳይሆን “እመን ትድናላችሁ” የሚል መዳናቸው በማመናቸው በኩል የሚፈጸም እንደሆነ በግልጽ ያስቀምጣል። ይህ ማለት የሚያድናቸው እምነታቸው ነው ማለት እንዳልሆነ ልብ ይሏል:: የሚያድነው እግዚአብሔር በእምነት በኩል ነው:: ስለዚህ አንድ ሰው በክርስቶስ የማዳን ስራ አምኖ ይድናል እንጂ ከዳነ በኋላ የሚያምንበት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት የለም። ❗️በእርግጥ ሰው ሳያምን ሕይወት ካገኘ በኋላ የማመኑ ጥቅም ምንድን ነው? ሕይወት ካገኘ በኋላ ባያምንስ ሕይወቱ ይጠፋልን? አይ ሕይወት ካገኘ በኋላማ አለማመን አይችልም ከተባለ ታዲያ እምነት ምን ፋይዳ ይኖረዋል? የሚሉት ጥያቄዎች እንዳሉ ሆነው እንደ ዮሐ3: 16 “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና” ያሉ ጥቅሶች እንዲሁም እንደ ዮሐ 1:12 “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤” የሚሉ በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባት እንደሚያሳዩን ከሆነ “መቀበል፣” “ማመን” በዚህም መሰረት መዳን፣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን እንዲሁም የዘላለም ሕይወት ማግኘት እንደሚሆንልን ያስገነዝቡናል። የሚያድን እግዚአብሔር፣ ጸጋው ከእግዚአብሔር፣ ምህረት የሚያደርግ እግዚአብሔር እንዲሁም ሕይወት ሰጪ እግዚአብሔር እንደሆነ መዘንጋት የለበትም ይህ ሕይወት በእምነት በኩል ከእኛ ጋር ይዋሃዳል። አሜን❗️ 👉Haniel kurima🙌

#ሰይጣንን_መቃወም ከፍ ባለ ድምፅ አዳረሹን በቡጢ 😂 እያለን ሳይሆን በስረዎቹ አለመተባበር ፣አለመተግበር ነው። እውነቱ ይኸው ነው👆

ኤፌሶን 6 ¹⁰ በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ። ¹¹ የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። ¹² መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። ¹³ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። … ¹⁶ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ ¹⁷ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።

#ዲያብሎስን ተቃወሙት🙅 👇 "የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፤ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ" (ኤፌ. 6፡11፤ 6፡13)። 👆ይሄ በሁለትም ክፍሎች በአማርኛው ትርጉም “ትቃወሙ ዘንድ” እና “ለመቃወም” ተብሎ የተተረጎመው ቃል ፈጽሞ በተሳሳተ ሁኔታ የተረዳነው ቃል ነው። ብዙዎቻችን ዲያብሎስን መቃወም ሲባል ወደ አዕምሮአችን የሚመጣልን ነገር መገሠጽ የሚለው ነው። ስለዚህም በተመሳሳይ ሁኔታ “ዲያብሎስን .... ጸንታችሁ በእምነት ተቃወሙት” 1ጴጥ. 5፡9 እና “ዲያብሎስን ግን ተቃወሙት፤ ከእናንተም ይሸሻል” ያዕ. 4፡7 የሚሉትን ጥቅሶች ስናነብ ቶሎ ብሎ የሚገባን ክፍሎቹ ስለመገሠጽ እንደሚናገሩ ነው። ነገር ግን፤ ክፍሎቹ ጨርሶ ስለመገሠጽ የሚያወሩ አይደሉም። ጸሐፊዎቹ እነዚህን ክፍሎች ሲጽፉ አሁን በሀገራችን አማኞች ዘንድ ልማድ እንደሆነው “በኢየሱስ ስም” እያሉ ሰይጣንን ስለ መገሠጽ ለመናገር ፈልገው አይደለም። 🤔ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ትክክለኛውን አረዳድ መያዙ በመንፈሳዊ ትግል/ውጊያ ውስጥ ድል ለመንሣት ትልቅ አስተዋጽዖ አለው። በኤፌሶን መጽሐፍ “ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ” ተብሎ የተተረጎመው ቃል በግሪኩ histemi የሚል ቃል ነው። ይህም “ጸንቶ መቆም (steadfastness)” የሚል ትርጉም አለው። በጴጥሮስ እና በያዕቆብ መልዕክቶች ውስጥም በአማርኛው ትርጉም ስለ መቃወም የሚናገሩት ክፍሎችን በሙሉ ከግሪኩ anthistemi ከሚለው ቃል የተተረጎሙ ናቸው። ይህም anti እና histemi የሚሉ ቃላቶችን በአንድነት የያዘ ነው። እንደሚታወቀው anti “መጻረርን ወይም መቃወምን” የሚያመለክት ሲሆን histemi ደግሞ ከላይ እንዳየነው “ጸንቶ መቆምን” የሚያሳይ ነው። እንግዲህ፤ anthistemi የአንድ ነገር ተጻራሪ ወይም ተቀናቃኝ ሆኖ መቆምን የሚያመለክት ነው። በሌላ አገላለጽ፤ ለመጣል ከውጭ የሚመጣን ግፊትና ፈተና ተቋቁሞ ሳይወድቁ ጸንቶ መቆምን የሚያመለክት ነው። የአማኞች መንፈሳዊ ውጊያ የመጨረሻ ግብ ምን እንደሆነ የሚነግረን የኤፌሶን ክፍል “ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ” ይላል (ኤፌ. 6፡13)። አዲሱ መደበኛ ትርጉም “የዲያብሎስን ሥራ [ሽንገላ] መቋቋም ትችሉ ዘንድ” ኤፌ 6፡11 ብሎ የተረጉመውም ለዚህ ነው። ✍️የውጊያው ማዕከላዊ ነገር ያለው እንግዲህ መከላከል ላይ ነው። ልክ በዚያን ዘመን ይታወቅ እንደነበረው የትግል ውድድር (wrestling) በተጋጣሚው ተሸንፎ ላለመውደቅና ጸንቶ ለመቆም የሚደረግ ግብግብ ነው። ዲያብሎስ የሚያመጣውን የተንኮል ሀሳብና ዘዴ እንቢ ብሎ በጌታ መንገድ መጽናቱ ነው ዋናው ድል። ይሄ ሳይሆን ግን በጸሎት ጊዜ ብቻ በመገሠጽ ፈተናውን አሸናፊዎች ነን ማለት ራስን ማታለል ነው። ብዙ አማኞች ዲያብሎስ በሕይወታቸው የሚያመጣውን የኃጢአት ፈተና፤ ወንድምን የመጥላት ፈተና፤ የትዕቢት ፈተና፤ ሥጋዊ ክብርንና ዝናን የመፈለግ ፈተና፤ ገንዘብን የማምለክ ፈተና፤ ቂም የመያዝን ፈተና ሁሉ እንቢ ብለው በሕይወታቸው ሳይቋቋሙ በቤተክርስቲያን ፕሮግራም ላይ ግን ሰይጣንን በመገሠጽ አንደኛ ናቸው። ይህ መቃወም አይደለም። ሰይጣን ባመጣው የተንኮል ፈተና በተግባር እየተሸነፉ በፕሮግራም ላይ ብቻ መገሠጽ የመንፈሳዊ ውጊያ ምንነት ጨርሶ አለመረዳትን የሚያሳይ ነው። 👌ዲያብሎስን ተዋግተን ድል ለመንሣት መንፈሳዊ የጦር መሣሪያዎችን በአግባቡ መታጠቅን ይጠይቃል። ትጥቃችን ከዲያብሎስ ትጥቅ ካልበለጠ ልናሸንፈው አንችልም። በርግጥ ይህ እኛ በራሳችን ጥረት ቀጥቅጠን የምንሰራው የጦር መሣሪያ አይደለም። አስፈላጊው ሁሉ ትጥቅ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ተሟልቶልናል። ይሁን እንጂ፤ እነዚያን የጦር መሣሪያዎች በአግባቡ ታጥቆ መገኘት አሊያም ቸል ማለት በአማኞች መካከል ትልቅ ልዩነት ይፈጥራል። የጦር ዕቃዎቹ ምንድን ናቸው? ለነገሩ ትጥቆቹን በአግባቡ መታጠቅ የትጥቆቹን ምንነት ከመረዳት ይመጀምራል። የክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን!

#እርሱ_ግን_ስለኔ⤵️⤵️⤵️ 👉ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። — ኢሳይያስ 53፥7

#እኔ_በክርስቶስ🤍👇 ☞ ተመርጫለሁ   ኤፌ.1:14 ☞ ያለ ሁኔታ ተወድጃለሁ   ዮሐ.3:16 ☞ ይቅርታን አግኝቻለሁ   ኤፌ.1:7 ☞ ልጅ ተብያለሁ   ኤፌ.1:5 ☞ በቁስሉ ተፈውሻለሁ   1ኛ ጴጥ.2:24 ☞ ከእርግማን ተዋጅቻለሁ   ገላ.3:13 ☞ በደሙ ታጥቤአለሁ   ራዕ.1:5 ☞ ከጨለማ ወጥቻለሁ   ቆላ.1:13 ☞ ህያው ሆኛለሁ   ኤፌ.2:5 ☞ ኩነኔ የለብኝም   ሮሜ.8:1 ☞ በሰማይ ቦታ አግኝቻለሁ   ኤፌ.2:6 ☞ በነፃ ክብርን ተቀብያለሁ   ኤፌ.1:6 ☞ ዓለምን አሸንፌአለሁ   1ኛ ዮሐ.5:5 ☞ ድልን አግኝቻለሁ   1ኛ ቆሮ.15:57 ☞ ባርኮትን አግኝቻለሁ   ኤፌ.1:3 ☞ በመንፈስ ቅዱስ ታትሜአለሁ   ኤፌ.1:13 ሌላ የሚተረክ ታሪክም የሚነገር ድርሰትም የሚወራ ተረት ተረትም የለኝም!!! የማወራው አዲስ ነገርም ይሁን የማውጀው ሌላ የመዳን አዋጅም የለኝም!!! አንዱ የእግዚአብሔር ልጅ 👉 ኢየሱስ ክርስቶስ 👈 ከዘላለም ሞት ያድናል!!! ምስክርነቴ አንዲት ናት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ከአብ የተሰጠ ስጦታዬ በረከቴ 👇 ❤❤ ኢየሱስ ❤❤

           * #ክፍል_1**   #የቆላሲያስ_መልዕክት_መግቢያ ✍የቆላሲያስን ቤተክርስቲያን ማን እንደተከላት በእርግጡ ባይታወቅም እብዛኞቹ እንደሚስማሙት ከሆነ #ኤጳፍራ የሚባል ሰው እንደተከላት ወይንም #ጳውሉስ በኤፌሶን መቀመጫውን እርጎ  በኢስያ ለሚገኙ ሁሉ ለ 2 ዓመት ወንጌል በሰበከበት ጊዜያት ምናልባትም የቆላሲያስ ሰዎች ወንጌሉ ደርሷቸው ይሆናል ተብሎ ይታሰባል።   “ #በእስያም_የኖሩት_ሁሉ_አይሁድም_የግሪክ_ሰዎችም_የጌታን_ቃል_እስኪሰሙ_ድረስ_ሁለት_ዓመት_ያህል_እንዲህ_ሆነ።”   — ሐዋርያት 19፥10 ✍ሐዋርያው ጳውሎስ ምንም እንኳን በአይን ባያያትም እና በአካል እብዛኞቹን የቤተክርስቲያኒቱን ምዕመናን ባያውቃቸውም  #በኤጳፍራ አማካኝነት ስለነሱ ከሰማበት ቀን አንስቶ #እንደ_ሐዋርያነቱ_እና_እንደ_መጋቢነቱ_ስለነሱ_ያለማቋረጥ_በእስር_ቤት_ሆኖ_ይፀልይላቸው_እንደነበር_በመልዕክቱ_እናገኛለን።📨📨 ✅ እንዲህ አይነት የመማለድ አገልግሎት ና ለቅዱሳን የመቃተት አገልግሎት #ጌታ_ለኛም_እንደ_ፀጋው_ባለጠግነት እንዲያበዛልን ፀሎቴ ነው🙏            #የቆላሲያስ_ቤተክርስቲያን_ምን_ትመስላለች?         #ድክመቷ #1 ቤተክርስቲያኒቱ #በሐዋርያት ትምህርት ላይ አልተመሰረተችም፦  ለአንድ ቤተክርስቲያን መሰረት ከሚባሉት #አራቱ_ጉባኤዎች ውስጥ  የሐዋርያት ትምህርት አልነበራትም። #2   የግሪክ ፍልስፍና ቤተክርስቲያኒቱን በርዟታል። /Gnosticism #3 የአይሁድ ስርዓት ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ሰርጎ ገብቷል #4 የመንፈሳዊ ኃይለት አምልኮ ወይም መንፈሳዊ ኃይላትን ማምለክ እና ለእነሱ መገዛት የሚል የጣዎት አምልኮ በርዟታል   ✍ እነዚህን ድክመቶች በጥልቅ ምን እንደነበሩ በመፅሐፍ ውስጥ በቀጣይ የምናያቸው ይሆናሉ።              #ጥንካሬ #1 ምንም እንኳን ቤተ ክርስቲያኒቱ በእነዚህ የትምህርት ንፋስ ውስጥ ብትፍገመገምም ጳውሎስ ስለ እነርሱ ጥንካሬ እንዲህ እያለ እግዚአብሔርን ያመሰግናል👇 “ስለ እናንተ ስንጸልይ፥ #በሰማይ_ከተዘጋጀላችሁ_ተስፋ_የተነሣ በክርስቶስ ኢየሱስ ስለ #እምነታችሁ ...፥ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አባት እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እናመሰግናለን፤ ”   — ቆላስይስ 1፥3 🎤ሰዎቹ ምንም እንኳን ጠንካራ ባይሆኑም በወንጌል ከተሰበከላቸው #ተስፋ የተነሳ በክርስቶስ ላይ የነበራቸው እምነት የማይነቃነቅ እና የፀና እምነት ነበር።    አየሱስ እርሱ ጌታ ነው💪💪💪 ✍ ወንድሞቼ እና እሆቶቼ ዛሬ ከዚህ መልዕክ የምነግራችው ይህን ነው፦ በምንም ብትደክሙ ኑሮ እንዳሰባቹት ባይሆን ፣ ብዙ ጥያቄ ቢኖርባቹ ....  እናንተ #የምትጠብቁት ተስፋ ያላቹ ሰዎች ናችው። በወንጌል የተቀበላቸሀት ኢየሱስ እርሱ ለዘላለም ሊያሳርፋቹ እና ወደ አዲሲቷ ኢየሩሳሌም  ሊወስዳቹ #ተስፋ የገባላቹ እርሱ በቅብ ነው በእርግጥ ይመጣላቹዋል። ስለዚህ በጌታ ላይ ያላቹ እምነት ከመቼውም ይልቅ እንዲበረታ እጠይቃቹዋለው። እምነታቹን አበርቱ፣ ትጥቃቹ አይላላ፣ ጌታን ከፊት ይልቅ ተጠጉት ፤ ልክ እንደ ቆላሲያስ ሰዎች በብዙ ሁኔታ ውስጥ ሆነው በጌታ ላይ የፀና እምነትን እንደያዙ፥ ዛሬ እምነታችው እንዲበረታ እጠይቃቹዋለው፤ ምክንያቱም #ተስፋቹ_እርሱ_በቅርብ_ይመጣል። ፀንታችው እና ተደላድላችው ሲያገኛቹ ያኔ እንደ እናንተ የታደለ በምድር ላይ ሊኖር አይችልም🥰🥰     ከተስፋው የተነሳ የፀና እምነት ይኑራቹ🙏🙏🙏 ....ይቀጥላል.....

Repost from EGCI CHURCH TV
Amharic NIV ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ NIV ማብራርያ ነው፣ ዋጋው ገበያ ላይ እስከ 1000ብር ቢሆንም ዲጂታል አማራጩ ይሀው። መጽሐፍ ቅዱስ ለማጥናት ልትጠቀሙበት ትችላላችሁ። #Book #Pdf #Glory_Of_Christ_International_Church Follow Us On ▼▼▼ Telegram | YouTube  | Facebook

Coming soon

Coming soon 🔜

#በነፃ መጽሐፍ ቅዱስን ኦንላይን ለመማር አሁኑኑ ይመዝገቡ !! ሰላም የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሆሊስቲክ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ #በነጻ በኦንላይን የሰርተፍኬት ኮርሶችን መስጠት ከጀመረ ዓመታት እንደተቆጠረ
#በነፃ መጽሐፍ ቅዱስን ኦንላይን ለመማር አሁኑኑ ይመዝገቡ !! ሰላም የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሆሊስቲክ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ #በነጻ በኦንላይን የሰርተፍኬት ኮርሶችን መስጠት ከጀመረ ዓመታት እንደተቆጠረ ይታወቃል፡፡ ከ8 ሺ በላይ ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት አሰጣጥ መንገዶች (በቴሌግራም፣ በክላስ ሩም እና ኦንላይን ሌርኒንግ) ተምረው ጨርሰዋል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም ብዙዎችን በወንጌል እውቀት ለመድረስ የምዝገባ ስርዓቱን በሁለት መንገድ አድርገናል፡፡ 1ኛ የሚሰራ E-mail ያላቸው www.holisticbiblecollege.org ላይ በራሳቸው ተመዝግበው እንዲማሩ፤ 2ኛ ለመመዝገብ የተቸገሩ በ @infohbc ላይ በማናገር ተመዝግበው እንዲማሩ፡፡ E-Learning www.holisticbiblecollege.org የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ለሁሉም !               በኦንላይን ሁሌም ትምህርት ሁሌም ምዝገባ አለ! ለበለጠ መረጃ፦🤳 +251118206642                             +251919741700 ወይም @infohbc ያናግሩን። https://telegram.me/Living_word_of_GOD https://telegram.me/Living_word_of_GOD https://telegram.me/Living_word_of_GOD join #በማድረግ፦           🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 መማር ለሚፈልጉ ሁሉ #Share ያድርጉ!

‼️ ኢየሱስ የቅርብ ዘመደችን ወይም ወንድማችን አልነበረም ነገር ግን ሆነልን ከእርሱ በለይ የሚጠጋጋ የቅርብ ዘመድ የለም 🙅🙅 ኢየሱስ ዘመዴ አልነበረም ነገር ግን ሆነልኝ።🙏🤍 👇👇 እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም። — ኤፌሶን 2፥19 👇👇 Follow bamadirg yiketatalu https://www.facebook.com/teka.elias.7

መጽሐፍ ቅዱስ እና የቁርኣን ምንጮች አንወናበድ! አንሳት! ግር አይበለን! ቁርኣን ከመጽሐፍ ቅዱስ የወሰዳቸው የሚመስሉ ብዙ ታሪኮች አሉ። ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች በስም ተጠቅሰዋል፤ ስማቸው ተቆልምሞም ቢሆን ተጠቅሰዋል። ብዙ ታሪኮችም ተወስደዋል፤ ተዛብተውና ተበላሽተውም ቢሆን ተወስደዋል። የመቆልመማቸው፥ የመዛባታቸውና የመበላሸታቸው ምክንያት ምንድር ነው? ብለን ስንጠይቅ ትክክለኛውን መልስ እናገኛለን። ትክክለኛው መልስ፥ 1ኛ፥ ቁርኣን ታሪኮቹን የወሰደው በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ሳይሆን ከሌሎች፥ እነዚህ ሰዎች፥ ድርጊቶችና፥ ታሪኮች በከፊል፥ በትረካና በልብ ወለድ ድርሰቶች፥ በአጶቅሪፋ፥ በአዋልድ፥ በአይሁድ ሚድራሽ፥ በአይሁድ ታርግሞች (ትርጉሞች ወይም ማብራሪያዎች) እና ትርክቶች ውስጥ የተጻፉትን እና ከዚያ የተሰሙትን በመውሰድ ነው። 2ኛ፥ በጆሮ ስሚ የተነገሩትን በመስማት ብቻ መልሶ በመናገር ሌሎችም ያንን የተነገረ ቃል በመስማትና በመቅራት እየተላለፈ በመሄዱ ነው። በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተወሰዱ ቢሆኑ ኖሮ የተጻፈውን ታሪክ ሳይበላሽ እናገኘው ነበር። ነገር ግን ተበላሽተው የምናገኛቸው ከተበላሸ ምንጭ ስለተቀዱ ነው። በወንጌላት ውስጥ የተጻፈው የኢየሱስ ታሪክ ሳይሆን በኋላ የተጻፉ የኢየሱስ የልጅነት ተረቶች የተጻፉባቸው ሥራዎች ተወስደዋል። በወንጌል ውስጥ መሰቀሉ፥ መሞቱና ከሙታን መነሣቱ ሳይወሰድ ሌሎች ልብ ወለዶች ተወስደዋል። ይህ Protoevangelium of James the Less (የትንሹ ያዕቆብ መቅድመ ወንጌል) እና Infancy Gospels (የሕጻንነቱ ወንጌላት) የተባሉ ደኃራዊ ጽሑፋት ውስጥ የተወሰደ ነው። መርየም የዒሳ እናት እና መርየም የሙሳ እኅት አንድ የተደረጉበት ታሪክ ዛሬ አንዳንዶች፥ ‘አይሁድ የልጆቻቸውን ስሞች በቀደሙ አማኞች ስም ስለሚሰይሙ ነው የዒሳ እናት መርየም የሀሩን (አሮን) እኅት መርየም የተባለችው።’ ወይም፥ ‘መርየም ሌዋዊ ስለሆነች ነው በነሱ ስም የተጠራችው።’ ብለው ሊሸነግሉ እንደሚሞክሩት አይደለም። ብዙ ታሪኮች ከጀርባው አሉ። ከእጅ ወደ እጅ ከተላለፉ ሰልባጅ ታሪኮች አንሥቶ የሙሴ እኅት አልሞተችም እስከሚሉ የአይሁድ ተረቶች ድረስ ይገኛሉ። ያለዚያ የሐሩን እኅት እና የኢምራን ልጅ የተባለችው መርየም ከ1570 ዓመታት በኋላ የዒሳ እናት መርየም ልትሆን አትችልም። ቁርኣን በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቢኮርጅ ኖሮ እንዲያ የተምታታ ታሪክ አይኖርም ነበር። ይህ የሁለቱ መርየሞች ስሕተት አሁን የታወቀ ሳይሆን በኢስላም ነቢይ በሙሐመድ ዘመንም በናግራን (ነጀራን) ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖች የጠቆሙት ስሕተት ነበር። ከአይሁድ ትንቢቶች ውስጥ ስለ መሢሑ የተነገሩት ሳይወሰዱ ከተረቶቹ፥ ለምሳሌ ቃየን የአቤልን በድን እንዴት መቅበር እንደተማረ በሱራ 5፥310-32 የተጻፈው ተወስዷል። ቁርኣን አሳቦቹን የወሰደው ከመጽሐፍ ቅዱስ ቢሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተጻፉና አይሁድ ራሳቸውም እንደ መጽሐፍ የማይቀበሏቸው የተፈጠሩ ታሪኮች አይገቡም ነበር። በኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች በኖኅ ያላግጡበት እንደነበረ በሱራ 11፥38-40 የተጻፈው በአይሁድ ሚድራሽ (ሮሽ ሃሻናህ) የተጻፈና በመጽሐፍ ቅዱስ የማይገኝ ነው። አሮን የሠራው ጥጃ ማግሳቱ ወይ ድምጽ ማውጣቱ ሱራ 7፥148 በአይሁድ በረቢ ኤሊዔዘር የተጻፈው ነው። በአይሁድ ተረቶች ሰሎሞን አዕዋፍ ያናግር፥ ጅኒዎችን ያዝዝ፥ ለነፋሳት ትእዛዝን ይሰጥ፥ ወዘተ እንደነበር በቁርኣን የምናገኛቸው ታሪኮች የአይሁድ ሚድራሽ ተረቶች ናቸው። አብርሃም ጣዖታቱን ሰባብሮ በሕዝቡ ያፌዘበትና ሊያቃጥሉት ሲሉ እሳቱ ያላቃጠለው ታሪክ (ሱራ 21፥69-70) ከአይሁድ ታርጉም ታሪክ የተወሰደ ነው። የአብርሃም ታሪክ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ከሌላ መወሰዱ ግልጽ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ ቢሆን ትክክለኛው ታሪክ በቁርኣን ይገኝ ነበር። የዮሴፍ ቁንጅናና የግብጽ ሴቶች በውበቱ መውደቃቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ሳይሆን ከአይሁድ ተረት የተወሰደ ነው። አንዳንዶቹ ተረቶች አይሁድ ለልጆቻቸው ታሪካቸውን ለልጆች እንደሚመች አድርገው የፈጠሩት ፈጠራ ነው። ወደ ቁርኣን የገቡት የመጽሐፍ ቅዱሱ ታሪኮች ሳይሆኑ ተረቶቹ መሆናቸው እንዳይመሳሰል አድርጎታል። በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወስዶ ቢሆን እኮ ምን ችግር ነበረው? ወደ ክርስቶስ ስንመጣም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማናገኘውን ክርስቶስ አለመሰቀሉን፥ አለመሞቱን፥ ከሙታን አለመነሣቱን፥ ጌታ ወይም አምላክ አለመሆኑን በቁርኣን እናገኛለን። ኋላ የተፈጠሩ ትውፊቶች እና የስሕተት ትምህርቶች ውስጥ እነዚህን እናገኛቸዋለን። ለምሳሌ፥ ክርስቶስ በሥጋ አልተገለጠም የሚሉ ትምህርቶች ገና ዮሐንስ መልእክቶቹን በሚጽፍበት ጊዜም ነበረ። በሥጋ ካልመጣ ሥጋውም አልተሰቀለም ማለት ነው። ክርስቶስ ፍጡር ነው የሚሉ ትምህርቶች ኋላ አባቶች ጉባኤ የተቀመጡበትና ያወገዙት ስሕተትም ነበረ። ቁርኣን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተወሰዱ ለሆኑት ታሪኮች ዋናው ምንጩ መጽሐፍ ቅዱስ ቢሆን ኖሮ ከመጽሐፍ ቅዱሱ ታሪክ ጋር የተለያየ ትርክት ባላገኘንም ነበር። እንዲህ የተጋጩ ሆነውም ሙሐመድ የመጽሐፉ ሰዎች መጽሐፍ ትክክልና አረጋጋጭ መሆኑን መናገሩ ተጽፎአል። ይህ በራሱ ተቃርኖ ነው። ከርሱ በፊት ያሉትን መጻሕፍት የሚያረጋግጥ ሲሆን መጽሐፉን (ቁርአንን) ባንተ ላይ ከፋፍሎ በዉነት አወረደ። ተዉራትንና ኢንጅልንም (ኦሪትንና ወንጌልን) አውርዷል። ሱራ 3፥3። ከእርሱ በፊት ያሉት መጻሕፍት የአይሁድና የክርስቲያኖች መጻሕፍት ብቻ ናችው። ሌሎች መጽሐፎችም አሉ የሚሉ ካሉ ማቅረብ ይሞክሩ። ይህ ማለት ኋላ የወረደው (ቁርኣን) ቀድሞ የወረደው (የመጽሐፍ ቅዱስ) አረጋጋጭ እንጂ ተቃራኒ መሆን እንደሌለበት ነው። በቁርኣን የምናገኘው ደግሞ ተቃራኒው ነው።

#ጽድቅ_ተቆጥሮልናል‼️🙏🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ሮሜ 4 ¹ እንግዲህ በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን? ² አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም። ³ #መጽሐፍስ_ምን_አለ? አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት። ⁴ ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤ ⁵ ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል። ⁶ እንደዚህ ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቆጥርለት ስለ ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል፦ ⁷ ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤ ⁸ ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው። ⁹ እንግዲህ ይህ ብፅዕና ስለ መገረዝ ተነገረ? ወይስ ደግሞ ስለ አለመገረዝ? እምነቱ ለአብርሃም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት እንላለንና። ¹⁰ እንዴት ተቆጠረለት? ተገርዞ ሳለ ነውን? ወይስ ሳይገረዝ? ተገርዞስ አይደለም፥ ሳይገረዝ ነበር እንጂ። ¹¹ ሳይገረዝም በነበረው እምነት ያገኘው የጽድቅ ማኅተም የሆነ የመገረዝን ምልክት ተቀበለ፤ ይህም እነርሱ ደግሞ ጻድቃን ሆነው ይቆጠሩ ዘንድ ሳይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት እንዲሆን ነው፥ ¹² ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው። ¹³ የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም። ¹⁴ ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤ ¹⁵ ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም። ¹⁶-¹⁷ ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው። ¹⁸ ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ። ¹⁹ የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ ²⁰-²¹ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ²² ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። ²³ ነገር ግን፦ ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤ ²⁴-²⁵ ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

😭 አገር አለኝ 😭 በስጋ አህዛብ በእጅ ያልተገረዝኩ ከተስፋው ቃልኪዳን ከእስራኤል የራኩ በዚህ አለም ተስፋን ቆርጬ እየኖርኩ ኢየሱስ ወረደ ከሰማይ ሰማያት ሰላም ተሰበከ ሊድኑ ያመኑት ርቄ የነበርኩት ቀረብኩኝ በደሙ ምስራች ሆነልኝ ደረሰኝ ሰላሙ ወደ አብ እንድገባ እንድሆን በእርሱ መንፈስ ከቅዱሳኑ ጋር መንግስቱን እንድወርስ መፃተኛ እንዳልሆን ከእንግዲህ እንግዳ ባለአገር አረገኝ ከፍሎት የኔን እዳ                              ✍✍ በኤልሳ

እርሱ ነው ተስፋዬ ሊመጣ የቀጠረኝ ፈፅሞ አልተውህም አልረሳህም ያለኝ የማይችል አይደለም ያለውን ማያደርግ ሰው መሆን ችሎ አይደል የእኔን ነፍስ ሊታደግ። ተዉት የዙሪያዬን ግድ የለም አይሙላ የሰነፋም እምነት አይጥበቅ ይላላ አይመጣም ይበሉ አይናቸው ያልበራ ሀብት የሚያከማቹ በአለም ጎተራ ይሂዱ ለዘይት ሻማ የጠፋባቸው ቀድመው ያልገዙቱ ይዘገያል ብለው እኔ ግን ተስፋዬን- ውዴን ሙሽራዬን እጠብቀዋለው እርቃን ገላ ሆኖ የሞተልኝ ጌታ - በመልአክት ታጅቦ ይመጣል አምናለው። #beti fares