Ethio Universities Digital Network-EUDN
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ሁሉንም ትምህርታዊ ጉዳዮች በአንድ ላይ ያገኛሉ ✅ከሁሉንም ዩኒቨርስቲዎች የተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች ✅ከት/ሚኒስቴር ወቅታዊ መረጃዎች ✅የት/ት እድሎችን ✅ለ12ኞች እና ለአዲስ ግቢ ገቢ ተማሪዎች መረጃዎችን ✅Exit መረጃ ✅ለተመራቂያን እና ለሁሉም የሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎችን ♦️ሌሎችንም ፈጣን እና ጠቃሚ ጉዳዮች 👉ለጥቆማ እና Promotion👇👇 @EthioTag_Bot
Show more6 183
Subscribers
-924 hours
-517 days
-17830 days
Posts Archive
#Grade12
#NationalExam
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።
(ዝርዝሩን ከላይ ይመልከቱ)
@tikvahethiopia
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች፦
224,234 ➫ ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች
287 ➫ የቅድመ-ምረቃ የፈተና ዓይነቶች
47 ➫ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የፈተና ዓይነቶች
88 ➫ የፈተና ማዕከላት
>5000 ➫ የፈተና አስፈጻሚዎች
@tikvahuniversity
#ጥቆማ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡
አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
@tikvahuniversity
+1
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘገበ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ነበር።
@Addis_News
@Addis_News
ትናንት መሰጠት የጀመረው የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና በዛሬው ውሎ የማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ አድሚንስትሬሽን እንዲሁም ቢዝነስ ማኔጅመንትና ኢንተርፕሬነርሺፕ ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡
የመውጫ ፈተና የሁለተኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 05/2018 ዓ.ም)
ፈተናው በሦስት ክፍለ-ጊዜ ይሰጣል፦
✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ሰዓት
✅ ፈረቃ 2: ከሰዓት ከ7:30-10:00 ሰዓት
✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ10:15-12:45 ሰዓት
የመውጫ ፈተናው እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
@tikvahuniversity
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) መሰጠት ጀምሯል፡፡
ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን ይሰጣል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ እና በድጋሜ ለመውጫ ፈተናው የሚቀመጡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግሥት እና የግል ተፈታኞች ፈተናውን ይወስዳሉ፡፡
ተፈታኞች ስለፈተናው አጠቃላይ ገለጻ ዛሬ ጠዋት የተሰጣቸው ሲሆን፤ በዛሬው የመጀመሪያ ቀን የፈተና ውሎ በጠዋት እና ከሰዓት መርሐግብር (ከ5፡00-7፡00 እና ከ8፡30-11፡00) የ62 ትምህርት አይነት ፈተናዎች እንደሚሰጡ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የወጣው መርሐግብር ያሳያል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ፣ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
@tikvahuniversity
#ExitExamProtocols
የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡
➫ ተፈታኞች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል።
➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡
@tikvahuniversity
#AAU #GAT
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ለመውሰድ ይመዝገቡ!
የ GAT ማመልከቻ ጊዜ 👇
ከግንቦት 29 እስከ ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
➫ https://portal.aau.edu.et ይግቡ።
➫ 'Online Exams' የሚለውን ይጫኑ።
➫ Quick Links ከሚለው ስር 'Apply for GAT' የሚለውን ይጫኑ።
➫ 'Test Taker Registration' የሚለውን ቅፅ ይሙሉ።
➫ የፓስፖርት መጠን ያለው ፎቶ ያስገቡ።
➫ 'Submit' የሚለውን ይጫኑ።
➫ ሲስተሙ የሚሰጥዎን የመለያ ቁጥር ይያዙ።
➫ ቴሌብር በመጠቀም የምዝገባ ክፍያ ይፈፅሙ።
➫ አድሚሽን ቲኬትዎን በማውረድ ፕሪንት ብለው፡፡
የ GAT ፈተና በሁለት ዞሮች ይሰጣል፦ ከሐምሌ 20-24/2018 ዓ.ም እና ከነሐሴ 07-08/2018 ዓ.ም
@tikvahuniversity
Notice Exit Exam
ለሰኔ ወር exit-exam ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ በሚከተለው ሊንክ በመግባት ከዩኒቨርስቲያቹ ለመውጫ ፈተና ተብሎ በትምህርት ሚኒስትር በኩል የተሰጣቹን Username እና password በማስገባት Entrance tickey እንድታወርዱ እናሳስባለን።
ቲኬታቹን ለማውረድ https://verify.ethernet.edu.et.
https://verify.ethernet.edu.et.
https://verify.ethernet.edu.et.
Download ለማድረግ የተቸገራቹ ቤተሰቦቻችን ብቻ በ @rule_omerta ላይ Username and password ላኩልን አውረድን እንልክላቹኋለን!
NB: 1) ወደ ፈተና ስትገቡ entrance ticket print አድርጋቹ መያዝ ግዴታ ነው። በተጨማሪም የዩኒቨርስቲ መታወቂያቹ እና National ID mandatory ነው።
2) Username እና password ከልደረሳቹ ዲኖቻቹ ወይም ሬጅስትራር እንዲሰጧቹ ጠይቁ::
ለተጨማሪ መረጃ ✅Share Share🇪🇹
🛜JOIN👉ETHIO UNIVERSITIES DIGITAL NETWORK
የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) (Tentative)
የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።
@tikvahuniversity
#ExitExam
ከሰኔ 4 እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች በአስቸኳይ መረጃቸውን እንዲያረጋግጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው ተብሏል።
በመሆኑም ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞች የFAN ቁጥራቸውን በመጠቀምና የግል መረጃ በማሟላት የራሳቸውን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።
ተፈታኞች https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ በመግባት ወደ Exit Examination በመቀጠልም Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት እንዲያረጋግጡ ጥሪ ቀርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ/ም
Via @tikvahuniversity
+1
#RemedialExam
የ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ዛሬ መሠጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው ከዛሬ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ5 ተከታታይ ቀናት ይሰጣል።
Via @tikvahuniversity
#RemedialExamProtocols
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከነገ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል።
የሪሚዲያል ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦
➫ ተፈታኞች የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡
➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል።
➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡
@tikvahuniversity
#ExitExamSelfVerification
የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ተብሏል።
የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው።
በመሆኑም ብሔራዊ መታወቂያዎን በመጠቀም፣ የ FAN ቁጥር እና የግል መረጃ በማማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል።
https://verify.ethernet.edu.et/ ከተጫኑ በኋላ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።
የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዐሥራ ስምንተኛውን ዓመታዊ የመጻሕፍት ዓውደ ርእይ ከሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያከናውናል።
በዓውደ ርዩ ላይ ታላላቅ የመጻሕፍት አሳታሚዎች እና አከፋፋዮች ይሳተፋሉ።
በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ላይ የሚያተኩሩ በርካታ ነባርና አዳዲስ መጻሕፍት በቅናሽ ዋጋ ይቀርባሉ፤ በቅርቡ የታተሙ መጻሕፍትም ይመረቃሉ።
የመጻሕፍት አፍቃርያን በሙሉ ስድስት ኪሎ ዋናው ግቢ ተገኝታችሁ ከእውቀት ገበያ እንድትሸምቱ ጥሪ እናስተላልፋለን።
መግቢያ፦ በነጻ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ
+1
#AREB
በአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ
የ6ኛ ክፍል ፈተና
➫ ሰኔ 8 እና 09/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
የ8ኛ ክፍል ፈተና
➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
@tikvahuniversity
#RemedialExam
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከሐሙስ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
የሪሚዲያል ፈተና የመግቢያ ትኬትዎን (Entrance Ticket) ያውርዱ!
➫ https://verify.ethernet.edu.et ላይ ይግቡ
➫ 'Get your entrance ticket here' የሚለውን ይጫኑ
➫ የመለያ ስምዎን (Username) እና የይለፍ ኮድዎን (Password) ያስገቡ
➫ 'Download Entrance Ticket' የሚለውን ይጫኑ
@Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library
#ጥቆማ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ የውሀ ሀብት ማኔጅመንት የልህቀት ማዕከል በ2026/27 በውሀ ማኔጅመንት የ2ኛ (MSc) እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ለመማር ያመልክቱ!
PhD programs:
➫ PhD in Water Management with three specialization tracks
➫ PhD in Aquatic Ecosystems Management
➫ PhD in Water and Health program with two specialization tracks
MSc Programs:
➫ MSc in Water Management with three tracks
➫ MSc in Water, Sanitation and Health
➫ MSc in Wastewater Management
➫ MSc in Aquatic Ecosystems Management
ለፕሮግራሞቹ ብቁ መሆንዎን ለማወቅና የማመልከቻ ሒደቱን ለማየት 👇
https://acewm-aau.org/archives/9318
የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም
@tikvahuniversity
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
