Ethio Universities Digital Network-EUDN
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ሁሉንም ትምህርታዊ ጉዳዮች በአንድ ላይ ያገኛሉ ✅ከሁሉንም ዩኒቨርስቲዎች የተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች ✅ከት/ሚኒስቴር ወቅታዊ መረጃዎች ✅የት/ት እድሎችን ✅ለ12ኞች እና ለአዲስ ግቢ ገቢ ተማሪዎች መረጃዎችን ✅Exit መረጃ ✅ለተመራቂያን እና ለሁሉም የሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎችን ♦️ሌሎችንም ፈጣን እና ጠቃሚ ጉዳዮች 👉ለጥቆማ እና Promotion👇👇 @EthioTag_Bot
Show more6 191
Subscribers
-1124 hours
+27 days
+18930 days
Posts Archive
❤️ ከ 6-12ኛ ክፍል ያሉትን አዲሱን curriculum መጽሐፎችን📚 በነዝህ ቻናሎች መግኘት ትችላላቹ👇
ለ Remedial ለምገቡ ተማርዎች መልካም ዜና!
ትኩስ የመቁረጫ ነጥብ ጋር የተገናኘ ዜና የምታገኙበትን ምርጥ ቻናሎች ልጋብዛቹ ትወዳላቹ።
ተማሪ ላይመደብ ይችላል‼️
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሰሰሰበ።
ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግቢ ውስጥ የሚገኙ የጦር ቄስፎች እና ታጣቂዎች በአስቸኳይ እንዲነሱና ግቢዎቹ ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲደረጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።
ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች በላኩት ደብዳቤ፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ ኃይሎችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው የተማሪዎችን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር-ማስተማር ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ አክሎም፣ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው በበቂ ሁኔታ ካልተረጋገጠ ሚኒስቴሩ ወደ ተቋማቱ ተማሪዎችን እንደማይመድብ አስታውቋል።
በጦርነቱ የተጎዱ እና የቆሰሉ ታጣቂዎች ሰሞኑን ወደ አዲግራት፣አክሱምና መቀሌ ዩኒቨርስቲ ሲገቡ እንደነበር አዩዘሀበሻ መዘገቡ ይታወሳል።
+2
#ጥቆማ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ2019 የትምህርት ዘመን በመደበኛ የቅድመ-ምረቃ መርሐግብር ለመማር የሚፈልጉ አመልካቾችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡
ኢንስቲትዩቱ በ24 የመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ፕሮግራሞች አመልካቾችን እየተቀበለ ነው።
መስፈርቶች
➻ አመልካቾች ከተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ መሆን አለባቸው
➻ በ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ቢያንስ 50% ውጤት ያመጡ
➻ የሪሚዲያል ፕሮግራም ከሆኑ በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ያስመዘገቡ
➻ ደረጃ 4 ያጠናቀቁ ከሆኑ COC ያለፉ መሆን አለባቸው።
የማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇
መስከረም 20/2019 ዓ.ም
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ይገለጻል ተብሏል፡፡
ኢንስቲትዩቱ የዶርሚተሪ እና የምግብ አገልግሎት ያቀርባል። ተጨማሪ የቻይንኛ እና የኮሪያኛ ቋንቋዎች ስልጠና ይሰጣል፡፡
(ለቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ዝርዝር ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።)
አድራሻ፦
አዲስ አበባ፣ ከላምበርት መናኸሪያ በወሰን መስመር 500 ሜትር እንደሄዱ
@Qesemacademy ✔️
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች፣ ሰኞ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
የጥሪ ማስታወቂያ ለነባር ተማሪዎች
#Mettu_University
የምዝገባ ጊዜ መስከረም 7 እና 8 2019ዓ/ም
ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 11/2019
በ 2019 አዲስ ለምትመደቡ የ 12ኛ ክፍልና በመቱ ዩኒቨርስቲ ሬሜዲያል ተከታትላችሁ ላለፋችሁ ተማሪዎች በቅርቡ ጥሪ ይደረጋል።
@Ethio_Students
