cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወንጭፍ ሚዲያ

ነፃነት፥ፍትህ፥እኩልነት=ዴሞክራሲ We are Fano!

Show more
Advertising posts
509
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from ሚኒሊክ TV
በአጣዬ ከተማ ፋሽስቱ መከላከያ በባጃጅ ይጓዙ የነበሩ 3 ንፁሃንን ረሽኗል። ከዚህ በፊት በደብረ ማርቆስ አንድ ወጣት ዶ/ር በአሰቃቃ ሁኔታ በባጃጅ ጉዞ ላይ እያለች መግደላቸው ሲታወስ፣ በሳምንቱ በደንበጫ ከተማ የሚሰራን ምስኪን ባጃጅ ሹፌር ከነባጃጁ አስገድደው በመውሰድ ፍ/ሰላም ልዩ ስሙ #ገውቻ በተባለ ስፍራ ቆራርጠው ገድለው ጥለውት ተገኝቷል። #ዛሬም፣ በአጣዬ ከተማ አደባባይ ላይ በባጃጅ ተሳፍረው ይጓዙ የነበሩ ተጓዦችን ጨምሮ ከነ ሹፌሩ ፋሽስቱ መከላከያ እሩምታ ተኩስ በመክፈት ሁሉንም ከባጃጅ ሳይወርዱ ገድለዋቸዋል። የሟቾችን ስም ዝርዝርና ሌሎች ተጨማሪ መረጃዎችን አጣርተን እንመለሳለን። #ድል፣ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/minilikcom
Show all...
ሚኒሊክ TV

Still he is our Hero!

የአምሓራዊ ትንሳኤያችን ምልክት፣ የታሪካችን እድሳት ብስራት ነጋሪው ድምፅ፣ ለጠላቶቻችን አስደንባሪ ባለግርማ ነጎድጓድ… ከነፍጣችን አፈሙዝ ጫፍ የሚገኘው ይህ ኢላመኛ ጠላትን ቀባሪ የሆነው ድምፅ ነው። ነፍጠኞቹ፣ እንኳን ለትንሳኤ በዐል አደረሳቹ!!! @#ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ‼️ https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
Repost from ሚኒሊክ TV
🇰🇪 #Kenya ‼️ በጎረቤት ኬንያ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 188 ደርሷል። ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በደረሰው አውዳሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 188 መድረሱን የሀገር አስተዳደር ሚኒስቴር አሳውቋል። እስካሁን ያልተገኙ በርካታ ሰዎች መኖራቸውም ተገልጿል። በኬንያና ሌሎች የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች በተከታታይ እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ የብዙ ሰዎች ህይወት እየጠፋ ሲሆን የከፍታ ቦታዎች መናድም ነዋሪዎችን ካለመጠጊያ አስቀርቷል፡፡ መንገዶችን ድልድዮችን እና ሌላም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ውድሟል። ምንጭ #VOA https://t.me/minilikcom
Show all...
👍 2
በዐንድ ራስ ፣ሁለት ምላስ ወይስ…⁉️ "#በአንድ ራስ ሁለት ምላስ" ሌላ ትርጉም የለውም። ኤርሚያስ ዋቅጅራ ማለት ነው። ባጎረሱት የሚተፋ ጆተኔ ማለት የወይራ ሰፈር ልጁ ኤርሚ ነው። በቀጣይ ኤርትራ ትከፍለዋለች ተብሎ ይገመታል። ያኔ "#ወልቃይት የኤርትራ ግዛት ነበረች" ይላል። በከፋዩ ኪስ ልኬት የጭንቅላቱ ሆርሞን የሚንቀሳቀስ የፖለቲካ ጋለሞታ… ይሄን ሰው መሳይ ዳግም የማይ አይመስለኝም። ኤርሚ፣ አባ ቀፋይ…በርታ!!! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
የዘመዴ #የሕማማት ሀሜት ለምን⁉️ ሐብታሙ አያሌው ኦሮምኛ መዝፈኑ ለዘመዴ እንደምን አበሳጨ፣ እየቆራረጠ ማሳበቁስ ለምን? የሀብትሽ ደሞዝ 6ሺህ መሆኑ፣ ስለምን ለዘመዴ አንገብጋቢ ጉዳዩ ሆነ? ሀብታሙ ኦሮምኛ መዝፈኑና መተዳደሪያውን ደሞዝ መቀበሉስ ወንጀል ሆኖ ተቆጥሮበት ዘመዴ በገፁ እያብጠለጠለ ለምን ለጠፈው? ሀብትሽ ስለሚከፈለው ደሞዝ መተንተንስ ለዘመዴ ስለምን አስፈለገው? #ኦሮምኛ ለመራታው ብቻ የተፈቀደ፣ ለሌላው ንግረ ፅዩፍ ነውዴ? በፅሁፉ፣ ሀብትሽ ስለሚከፈለው ደሞዝ ትኩረት መደረጉ ብቻ፣ የጥቅም ግጭት በመካከላቸው ያለና ቅናቱን አሳብቋል። የሆነው ሆኖ… ዘመዴም ሆነ ሀብትሽ ለአማራ ህዝብ ትግል ትልቅ አስተዋፅኦ፣ ውለታም አድርገዋል። ሆኖም፦ ሁለቱም የአምሓራ ብሔርተኛ አይደሉም። ከዐማራ፣ ለዐማራ፣ የዐማራ የሆነ አውደ ዋና የፖለቲካም ሆነ ህልውናዊ ግብ የላቸውም። ያለ ኢትዮጵያ አማራን ሆነ ኦርቶዶክስን ለማየት አይችሉም። አንደኛው ሀይማኖቱን በአማራ፣ ሌላኛው ኢትዮጵያውን በአማራው ለማትረፍ… አማራውን ያታግሉታል። ፣ ኢትዮጵያ ባትቀልጥል አማራ ራሱን ችሎ ቆሞ ሲቀጥል… ከማየት የሚነሳ ፖለቲካ ይነስራቸዋል። በአጭሩ  የአምሓራው፣ ለአምሓራው፣ ከአምሓራው ለሆነው የራሱ ፖለቲካ ስሪትና ትልም ደንቃራ ናቸው። የራሱ ፖለቲካ የሌለው ህዝብ ደግሞ… በር አልባ #ጎጆ ማለት ነው። ካስተዋላችኋቸው፣ አማራውን በአውራጃ ሸንሽኖ መጥራት የሚቀናቸው ታጋዮች ናቸው። ዘመዴ፦ "ቆቱ ኦሮሞ ነኝ፣ ለአማራና ኦርቶዶክስ እታገላለሁ" ብሎ ዋጋ ሲከፍል የባጀ፣ ኦርቶዶክስና አምሓራ ህዝብን አጃምሎና ቀይጦ እጣፋንታቸውን የሚያይ…  መነጠል ላይችል አምኖ እየለፋም ያለ ባለ ግዙፍ ሚና ወንድማችን ነው። አማራ የራሱን አታጋይ መስመረኛ ድርጅትና  አምሓራዊ ሚዲያውን ቃኝቶና ሞርዶ ለአየር  ለምድር እስኪያበቃ በነዚህ እያነከሰ መጠበቅ ግዱ ሆኖ ሰንብቷል፣ገናም ይቆያል። የአምሓራን ትግል ግለሰብ የሚያንገዳግደው ትግል ከመሆን ታድገን በመስመረ ርዕይ እስክናሻግረው ይሁና ! ብለናል… ኢጎኛ እና ቅናተኛ ይንቦራጨቅበት። ሐብትሽ፦  ኢትዮጵያዊ ብሄርተኛ፣ ደመ አምሓራ ታጋይ ነው። በአምሓራ ደም ቤዛነት ኢትዮጵያን መታደግን ቁርጥ አላማ ያደረገ ከዚያ መለስ ያለን የአምሓራ እጣ ፋንታ ለማየት ያልደፈረ… ለዚህም ግበ ኣላማ ዳር መረድስ ሲል…የዘመኑን ዋና የገበረ፣ ከዘመዴ አንፃር ሲታይ አውራ ታጋይ ልምደኛ ጀግናም ሰው ነው። ሁለቱም በትግል አየር ምድሩ ላይ መኖራቸው የግድ ሆኖ እንዲቆዩ የድክመታችን እጣ ፋንታ ናቸውና ጎንዮሻዊ ውጊያ ለአማራ ትግል አደጋ መሆኑን ለመገንዘብ ጊዜ አላቸው። በተለይ በዘመዴ በኩል ያለ ተንኳሽ አጀንዳን ፈጣሪ፣ የትግል ረባሽ ሰው፣ ትግሉን ከፋፋይ የሆኑ ዋን አማራ መሳዮችን በማሞገስና ምስክርነት በመስጠት በድለላ አቅራቢነት መሳተፉ… ተሳዳቢን፣ ትግልን ከፋፋይን መልምሎ ከማቅረብ አልፎ… ራሱም ከፋፋይ ሚነኛ ሆኖ መጥቷል። ዘመድኩን በቀለ፣ እየተጓዘበት ላለው መንጋን እና ጭፍራን ተመክቶ ያሻውን ታጋይ ስም የማጠልሸት፣ መንገድ እጅግ አደገኛና ሀይ ባይ ጠሪ ነው። በተቃራኒው፣ በጋራ በህዝባዊ ግንባሩ ስም ለተሰበሰበ የህዝብ ሀብት ግልፅ ተጠያቂነት በሚያሳይ ከሀሜት ነፃ አውጭ መንገድ አለመመረጡ አደጋ አለው። ከግንባሩ ጋር የነበራችሁና ፋይናስና ስትራቴጅካል ሚና ላይ የነበራችሁ ሁሉ በግልፅ ጉዳዩን በማስረዳት፣ ከሀሜት እና ትግሉን ጎጅ አሉባልታ ነፃ ውጡ። መሬት ላይ ባለው የትግል አደረጃጀት ላይ በተደጋጋሚ የምትባሉበትን ጉዳዬ ሀሜት አጥሩ። አጥሩ!!! የበዛው ዝምታ አሉታዊ ትርጉም ይዟል። በተረፈ…  የብሄርተኝነት ለጋ ጅምር የሚያጋጥመውን ተለማጅ ችግር መጋፈጣችን ግድ ነው። መራር፣ ብሄርተኞች በሆንን ማግስት፣ በመካከላችን፣ እንኳን ሰው፣ ነፋስ… እንኳን አሉባልታ፣ ሴራ አይበግረንም!!! ድል፣ ከዚያ መለስ ነው!!! #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ!!! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

Show all...
አሻራ ለማስቀመጥ ዋጋ መክፈል አለብን!

‹‹አሻራ ለማስቀመጥ ዋጋ መክፈል አለብን››………………………………………………….ሞገድ እጅጉብዙ ልብ ያልተባሉ ነገሮች አሉ፡፡ አብይ አህመድ እያንዳንዱን ጥፋት ያደረሰው በረቀቀ ሴራ ሳይሆን በግልጽ እየተናገረ ነው፡፡ ጦርነቱን እንደሚያደርግ በግልጽ ሲናገር ነበር፡፡ የሚረዳው በመጥፋቱ ግን ያሰበውን ማሳካት ችሏል፡፡አሁ…

👍 3
በራስ ሀብት አንውደም‼️ ቢሊዮን ብሮች መድቦ የዜጎችን ቤት የሚያፈርሰው፣ በማንነታቸው ኪራይ እንዳያገኙ ከልክሎ፣ አከራይቶ የተገኘን የሚቀጣው አፖርታይዱ ስርዓት ጨዋታው አይጠገብም። "እኔ የሀገሪቱን በጀት ለድሮን ቦንብ እና አማራን እና የአማራ የሆነን ሁለ ነገር ለማፍረስ እና ለማውደም ልጠቀምበት እናንተ ደግሞ በአዲስ አበባ መፀዳጃ ቤት ገንቡ እያለን ነው። በእርግጥ በመፀዳጃ ቤት መገንባት ስም፣ በግል ተቋማት ጭንብል ተከልሎ የሚሰበስበውንም፣ ማንኛውንም ሀብት ለአምሓራ ማጥፊያ ከማድረግ አይቆጠብም። የአምሓራ ልጆች በእጅ ስልክ ላይ በደረሰዎ መልዕክት በገንዘብ ከመሳተፍ ይቆጠቡ። ይልቅ ፋኖ እና የራያ 100 ሺህ ተፈናቃዮች በእኛ ተስፋ ጥለዋል። #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
👍 1
የፋኖ አዱኛ ምትኩ አነቃቂ ሙዚቃ ከግምባር‼️ ጓዶቻችን፣ በየጥሻ እና ጉድባው ጠላትን እያርበደበዱም፣ የጥበብ መክሊታቸውንም ከመጠቀም ወደ ኋላ አላሉም። ፋኖ አዱኛ፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ ነበልባል ተወርዋሪ ፋኖ ነው። በዛሬው እለት፣ ፋኖ ጓዶቹን ያበረታታበትን የድምፅ ሙዚቃ አድምጡልኝ ብሏል። ዛሬ… የፋኖ አዱኛ ምትኩ ሙዚቃ በሞዐ ሚዲያ ቻናል ላይ ተለቋል። ቲክቶክ ላይ በተንቀሳቃሽ ምስል አየሰራችሁ አበርቱት‼️ https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ፋሽስታዊ አገዛዙ፣ ክፉ ነው። "#አትሄዱም፣ አትኖሩም፣ ነው" አቋሙ። "መረጃን በማሳለጥ ጉዳይ ከመንግስት በቂ ትብብር በማጣቴ ለኢትዮጵያውያን ቪዛ መስጠት አቁሚያለሁ" ብሏል አውሮፓ ህብረት #የአውሮፓ ህብረት #ለኢትዮጵያውያን በጊዜያዊነት ወደ አውሮፓ የመግቢያ ቪዛ ፈቃድ መከከሉን አስታወቀ፣ ከመንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ የሚል ምክንያት ጠቅሷል የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ለኢትዮጵያውያን በጊዜያዊነት ወደ አውሮፓ የመግቢያ ቪዛ ፈቃድ መስጠት የሚከልክል ውሳኔ አሳለፈ። ለክልከላው የሰጠው ምክንያት ከኢትዮጵያ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው በህብረቱ ሀገራት በህገወጥነት በሚቆዩ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ዙሪያ ከሀገሪቱ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። ውሳኔው ለምን ያክል ግዜ እንደሚቆይ ያለው ነገር የለም፤ መደበኛው ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን አራዝሞታል። https://t.me/Moamediamoresh
Show all...