🧕WeeMuslims👳♀
⚫️ የስኬቶች ሁሉ መሠረት አላህን ማስታወስ ሲሆን የውድቀቶች ሁሉ ሰበብ አላህን መርሳት ነው። Join 👇👇
Show more217
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Repost from Abdul Halim Al Letemiy
የመፈተንህ ግቡ!!
=============
ኢብኑል ቀዪም_የአሏህ እዝነት በርሱ ላይ ይሁንና_ እንዲህ ይላል ፦
"አሏህ ባሪያው ወደ እርሱ መዋደቁን፤ መተናነሱን፤ ማሰሞቱን፤ እርሱን መለመኑን ሊሰማ ሲል ይፈትነዋል። አሏህም በችግር ግዜ ወደ እርሱ ማይተናነሱትንና ማይዋደቁትን አውግዞዋ ። አሏህﷻ እንዳለው ፦ "በእርግጥም በቅጣት ያዝናቸው፡፡ ታዲያ ለጌታቸው አልተናነሱም፡፡ አይዋደቁምም፡፡"
ባሪያው በጌታው መጠንከር (እርሱን ከመለመን የተብቃቃ ከመምሰል) ደካማ ነው!!
አሏህ ከባሪያ የፈለገው እንዲተናነስለትና እንዲዋደቅለት እንጂ ከረሱ የተብቀቃ ጠንካራ እንዲመስል አይደለም። "
•-قَالَ الْإِمَامُ ابْنُ الْقَيِّمِ -رَحِمَهُ اللَّهُ تَعَالَى-:
اللَّهُ تَعَالَى يُبْتَلَى عَبْدِه لِيَسْمَع شَكْوَاه وَتَضَرُّعِه ودعاءه ، وَقَدْ ذَمَّ سُبْحَانَهُ مِنْ لَمْ يَتَضَرَّعُ إلَيْهِ وَلَمْ يَسْتَكِن لَهُ وَقْتٌ الْبَلَاء ، كَمَا قَالَ تَعَالَى:
﴿ وَلَقَدْ أَخَذْنَاهُم بِالْعَذَابِ فَمَا اسْتَكَانُوا لِرَبِّهِمْ وَمَا يَتَضَرَّعُونَ ﴾ والعبد أَضْعَفُ مِنْ أَنَّ يَتَجَلَّدُ عَلَى رَبِّهِ ، وَالرَّبُّ تَعَالَى لَمْ يَرِدْ مِنْ عَبْدِهِ أَنْ يَتَجَلَّد عَلَيْه ، بَلْ أَرَادَ مِنْهُ أَنَّ يَسْتَكِينَ لَه ، وَيَتَضَرَّعْ إلَيْهِ
📘| عُدَّةِ الصَّابِرِينَ (ص٣٦).
https://t.me/Abdul_halim_ibnu_shayk
Abdul Halim Al Letemiy
``በድምፅ ብልጫ ሳይሆን በእውነት ላይ የተመረኮዘ አካሄድ ተጓዝ፤ብቻህንም ቢሆን በሐቅ ላይ ፅና!!``
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
እውነታ!
«ሶላት ባለመስገድህ የሚጠብቅህን ቅጣት ተወውና አለመስገድህ ራሱ ከአላህ የሆነ ቅጣት መሆኑን ተገንዘብ።
የውዱ ነቢይ ﷺ የመጨረሻው ምክር « ሶላትን አደራ!» የሚል ነበር።» አደራቸውን መብላት በራሱ ለሌላ የከፋ ቅጣት የሚዳርግ ቅጣት አይደለም ትላለህን?
👆👆
አንድ ሰው በሚሰራው ወንጀል ምክንያት እዚሁ ዱንያ ላይ ከሚቀጣባቸው ቅጣቶች መካከል ከባድ የሚባሉት 4 ነገሮች ናቸው
አላህ ይጠብቀን
https://t.me/bin_Husseynfurii
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ይህንን ጠቃሚ ገጠመኝ አዳምጡት።
||
t.me/MuradTadesse
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ገራሚ ታሪክ‼
==========
(በተለይ ወላጆች ይህን ሸይኽ ፕሮፌሰር ዐብዱ-ር'ረዛቅ አል-በድር የሚነግሩንን ታሪክ በደንብ አዳምጡት!)
||
✍ ከሆነ ሃገር ለዑምራ የመጣ አንድ ሰው ጠዋፉን ጨርሶ በካዕባ ዙሪያ ሐጀረ-ል-አስወድ አካባቢ ዱዓእ እያደረገ ነበር። አስተውላችሁ ከሆነ ሐጀረ-ል-አስወድ ጋር ከፍተኛ የህዝብ መገፋፋት ስላለ እጃቸውን በሆነ መያዣ ላይ አስደግፈው የሚቆሙ ወታደሮች አሉ። በዚያ አጋጣሚ እዛ ጋ ቆሞ የነበረው ወታደር ገጠመኙን እንዲህ ይተርከዋል። "በጣም ለቅሶው የበረታ ሰው ድምፅ ሰማሁ። ምንድን ነው ብዬ ዘወር ሲል አንድ ሰው ከባድ ለቅሶ እያለቀሰ አላህን ይለምናል። ለቅሶው ስለሳበኝ ምን እያለ ይሆን ብዬ ሳዳምጠው በዱዓቅ መሃል «ያ ረብ! (ጌታዬ ሆይ!) ሰዎች ልጆች አሏቸው። እኔ ልጅ የለኝም!» ይህን ቃል እየደጋገመ በጣም በብርቱው ያለቅሳል። ሲደጋግመው ስለነበር በጆሮዬ ይህንን ድምፁን ሸምደጀዋለሁ።
ከዚያም ከ18 ወይም 20 አመታት በኋላ በዚሁ በሐጀረ-ል-አስወድ ቦታ ሳለሁ፤ ራሱኑ ያኔ የሰማሁትን ድምፅ ሰማሁ። ግለሰቡን አስታወስኩና ፊቱን ለመመልከት ዞርኩ። ራሱ የያኔው ሰውዬ ነበር። ልክ እንደዛው በብርቱው እያለቀሰ አላህን ይለምናል። ምንድን ይሆን የሚለምነው ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። "ያ ረቢ! (ጌታዬ ሆይ!) ይህንን ልጅ አጥፋልኝ!" ይላል። እዛ ዱዓእ ማድረጊያው ዘንድ ሆኖ ልጄን አጥፋልኝ እያለ አላህን ይማፀናል። ከቆምኩበት ቦታ ወረድኩና ከዚያ ከካዕባው ዙሪያ ይዠው ወደ ውጭ (ወደ ዳር) ወጣን። እንዲህም አልኩት፦ «ከዛሬ 18 አመታት በፊት በዚሁ ቦታ አላህ ልጅ እንዲሰጥህ ስትለምን የነበርከው ሰው አይደለህምን?»
«አዎ!» አለኝ። እኔም «አንተ በዚህ ቦታ ልጅህን ሁለት ጊዜ በድለኸዋል። የመጀመሪያው በደልህ፤ እኔ ያኔ ሰምቸሃለሁ፣ ዱዓህን ሐፍዤዋለሁ፣ ዝም ብለህ "ልጅ ስጠኝ!" ነበር እንጂ ስትል የነበረው "መልካም ልጅ ስጠኝ!" አልነበረም ያልከው። አሁን ደግሞ ሁለተኛው በደልህ ራሱ ቦታ መጥተህ አላህ እንዲያጠፋው ትለምናለህ። በመጀመሪያውም በመጨረሻውም አላሳመርክለትም። አሁንም ወደዛው ቦታ ተመለስና አላህ እንዲመራው ዱዓእ አድርግለት። ልክ እንደበፊቱ ራሱኑ ለቅሶ እያለቀስክ ቀልቡን እንዲመራለት ዱዓእ አድርግለት። ይህን አስረዳሁትና ይዤው መልሼ ወደዛው ቦታ ወሰድኩት። ከዚያም ለቅሶውን ጀመረና ለልጁ ሂዳያ እንዲሰጠው አላህን መለመን ጀመረ።
ከዚያም ከአንድ አመት በኋላ ከልጁ ጋር መጣ። ሰላምታ አቀረቡልኝና ለልጁ ታሪክህን ንገረው አለው። ከዚያም ልጁ መሃላ እየማለ፤ ያኔ አባቴ በዚያ ቦታ እያለቀሰ አላህ ሂዳያ እንዲሰጠኝ በሚማፀንበት ሰዓት ተነስቼ ውዱእ አድርጌ ሶላት ጀመርኩ። ከዚያም በኋላ ሁኔታዬ ተስተካከለ።
በብዙ መልኩ ወላጆቹን አዛ የሚያደርግና በሐራም ነገሮች ላይ ሲያሳልፍ የነበረ ልጅ ነው።»
ከዚህ የምንማረው፤ ወላጆች አላህ ልጅ እንዲሰጣችሁ ስትፈልጉ፣ ልጅ ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም ነገር ስትጠይቁት መልካሙን (ሷሊሑን) ጠይቁት። አንዳንዱ ፊትና ይሆናል። አይበለውና መጥፎ ካጋጠማችሁ ለውሳኔ ቸኩላችሁ በንደት አትራገሙ፤ በምትራገሙበት ምትክ አላህ እንዲያስተካክለው ዱዓእ ብታደርጉበት የበለጠ ነው። አላህ መልካምን ሁሉ ይወፍቀን።
||
t.me/MuradTadesse
RUQYAH - POWERFUL - Remove Sihr, Magic, Jinn. القارئ عمر هشام العربي - رقية قرءا
👇👇👇👇👇
@UMARHISHAM
Repost from አል-ሙተሀቢን(المتحابين)
☀️ከወንድሜ ጋር በሀይለኛው ተጣላን አስለቀሰኝ
ለአባቴ እንደምናገር አስፈራራሁት....!
አባቴ ሲመጣ ሳልናገር ቀረሁ
እናቴ ግን የተፈጠረውን ነገረቺው ለአባቴ...
ሳላስበው አባቴ ክፍላችን ገብቶ
ወንድሜን እንዲህ ሲል ተናገረው ....
እህትህ ጋር ለምንድን የተጣላችሁት..?
ወንድሜም እየተነጫነጨ እሷ ነች የጀመረቺው አባቴ..!
አባቴም እጁን ይዞ ከክፍሉ ወጣ
የምትናገረውን ልብ ብለሀል ታውቆሀል ወይ አለው..? እሷ ነች የጀመረቺው ማለት ምን ማለት ነው!
ይህ እኮ ቤተመንግስቶ ነው
እዚህ ከተዋረደች የት ነው የምትከበረው!
አንተ እኮ ከኔ ቀጥሎ መከታዋ ነህ.. ምርኩዞ ነህ..አንተ ከሰበርካት ወደየት ትጠጋለች!
ልጄ እህት አለህ ማለት እኮ
የዱንያን ጀነት ከነ ፀጋው አገኘህ ማለት ነው!
አደራህን ልጄ
'ባንተ ልቧ እንዲሰበር አታድርግ'
#Join_Share
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
@almutehabin
@almutehabin