ተዋሕዶን እንወቅ።
Open in Telegram
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
Show more2 372
Subscribers
-124 hours
-117 days
+330 days
Posts Archive
2 371
Repost from Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
ጥላ ኃጥያታችን እየተከተለ ሰለም የሚነሳን ብኩን ፍጥረቶች እኮ ነን!😢
ንስሐ በራሱ ሰላም ነው።
pls ንስሐ እንግባ🙏
@i_panagia
2 371
❝#ቅድስት_ሆይ_ደስ_ይበልሽ?❞
የልጄ የወዳጄ መቅደስ ማደሪያ የሆነ ሰውነታችሁን በኃጢአት እያነደዳችሁት እያፈረሳችሁት ልጄንም ዳግም እየሰቀላችሁብኝ አይደለምን? ታዲያ ስለምን ደስ ይበልሽ ትሉኛላችሁ?
የልጄን ሕማም፥ የልጄን ዋጋ ሁሉ ትታችሁ ረስታችሁ ስለምን ደስ ይበልሽ ትሉኛላችሁ? ከአይሁድ ይልቅ በልጄ ላይ እጅግ ከፍታቹበት የለምን? እነርሱስ አንዴ ሰቀሉት እናንተ ግን ልጄ ወዳጄን የገረፋችሁብኝ የሰቀላችሁብኝ ቀናት ስፍር ቁጥር የላቸውም!
ታዲያ ስለምን ደስ ይበልሽ ትሉኛላችሁ? በልጄ በወዳጄ ላይ ስለምን ይህን ያህል ከፋችሁበት? ስለእናንተ ብሎ በመስቀል ስለተሰቀለ ነውን? ደሙንስ ስለናንተ ፍቅር እንደ እህል ስለዘራ ነውን? ቅዱስ ሥጋውን ሳይሳሳ ስለቆረሰ ነውን?
ታዲያ ስለምን ደስ ይበልሽ ትሉኛላችሁ? ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ ስትሉኝ ከልቤ ደስ ይለኝ ዘንድ ልጄን ዳግም አታቁስሉብኝ፤ አታድሙብኝ።
2 371
“ከማሃ ሃዘን ወተሰዶ ሶበ በኵለሄ ረከቦ፤
ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ።”
"እንደሷ [እንደ እመቤታችን] ኀዘንና መሰደድ ባጋጠው ጊዜ ፥ ዓይነ ልቡና [ማስተዋል] ያለው ሁሉ ማልቀስሽን አይቶ ወየው ወየው እያለ ሊያዝንና ሊያለቅስ ይገባዋል" ሰቆቃወ ድንግል
የተቻለን ከማህሌተ ጽጌው እያደርን ከምስጋናው ማዕድ እየተካፈልን ድንግል እመቤታችንን ደጅ እንጥናት !!
ከስር ባስቀመጥላችሁ link ተጠቅማችሁ በMilky animate የተሰራው አጭር animation ይመልከቱ !!
https://youtu.be/NxzRnIy4ZCA
2 371
Repost from Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
ክርስቶስን ብታገኘው ምን ትለዋለህ?
የምንናፍቀውን ክርስቶስን ፊት ለፊት በአካል ተገልጦ ብንመለከተው ብዙ የምንለምነው፣ የምንማጸነው ነገር እንዳለ ጥያቄ የለውም።
እኔ ዛሬ ይኽ ምኞታችንን እውን የሚያደርግ ብዙዎቻችን ያላስተዋልነው ነገር ግን ቅርባችን የነበረን ክርስቶስን በአካል የምናነጋግርበት ሥፍራ ልጠቁማችሁ።
ይኽም ስፍራ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ነው — የዕለተ አርቡ አማናዊ በግ ኢየሱስ ክርስቶስ በአካል ከፊት ለፊትህ ሆኖ ጸሎት የምታደርስበት በጎ እድል። ከእግረ መስቀሉ ስር ሆነህ ከጌታ ይቅርታን የምትለምንበት፣ ከንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ዙፋኑ ሥር ተንበርክከህ በሕይወትህ ያታከተህን ቀንበር የምታቀልበት ፣ ድንግል እንድትሰጥህ ደጅ ምትጠናበት የሚናፈቅ ጊዜ ይኸውም ቅዳሴ ነው።
ቅዳሴ ማለት "የሰማያዊ ሰርግ ጥሪ ነው" ይላሉ ቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ። እኔም ዛሬ ወደዚህ ሰማያዊ ሰርግ ጥሪ የጌታ ቀን በሆነችው በዕለተ ሰንበት በምድር በምትገኘው ኢየሩሳሌም ሰማያዊት እንድንሳተፍ ሙሽራው ክርስቶስ የጋበዘንን ግብዣ ላስታውሳችሁ ወደድሁ።
እግዚአብሔር ቢፈቅድና ቢወድ ከጥቅምት ወር ጀምሮ እሑድ እሑድ ሁላችንም የምንናፍቀውን ክርስቶስን ለማናገር ወደ መቅደስ እንገሰግሳለን።
ይኽንንም ለማገዝ በሚል በየሰንበታቱ የሚነበቡትን ምንባባት፣ የሚሰበከውን ምስባክ፣ የሚቀደሰውን ቅዳሴ የያዘ ሁላችንም እንድንጠቀመው በሚል አንድ ቅጽ ተዘጋጅቷል። ይኽንን ከታች የምታገኙትን ቅጽ ፕሪንት በማድረግ ቅዳሜ ምሽት አስቀድመን በነጋታው የሚነበቡትን ምንባባት ከቅጹ ተመልክተን ክፍሎቹን በማንበብ ቀድመን እንዘጋጃለን። ከዚያም ቅዳሴውን ከመነሻው ጀምሮ በመካፈል እሑዳችንን ሰንበት ሰንበት በመሽተት እንባርከው።
ይኽንንም ለማሰላሰል እንዲመች የተገኘንበትን ሰዓት ላይ ✅ ካልሔድን ደግሞ ❌ እያደረግን መሻሻላችንን እንድንገመግምና ለቀጣይ ደግሞ በርትተን ሁሉንም ለመካፈል እንድንችል በሚል ቅጹ ተዘጋጅቷል። ከምንባባቱና ከቅዳሴው ክፍልም የወደድናቸው ጥቅሶችና ሀሳቦችንም የምናሰፍርበት ቦታ ተካቷል።
ቅጹን በመጠቀም በግል፣ ከቤተሰቦቻችን፣ ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን እየተቀሳቀስን ወደ ቀራንዮ አደባባይ አብረን እንገስግስ (ቅዳሴ ማለት ዕለተ አርብ ነውና)። መሰባሰባችንን ለዚህ በጎ ዓላማ እናድርገውና አባታችን እግዚአብሔርን እናስደስተው።
በጌታ ቀን በበጉ ሰርግ እንገናኝ!
የጥቅምት ወር ይሞክሩኝ (challenge) 5ቱንም ሰንበታት ማስቀደስ።
ዲ/ን ዘለዓለም ዓለማየሁ ጥቅምት 1 : 2018@i_panagia
2 371
Repost from Milkyanimates
ከማሃ ሃዘን ወተሰዶ ሶበ በኵለሄ ረከቦ፤
ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ።
እንኳን ለጾመ ጽጌ እና ማሕሌተ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ።
በሚመጡት ሳምንታት ደግሞ የሥዕላቶቹን ታሪክ ሥዕሉን ከሚገልጹ የሰቆቃወ ድንግል ዜማው ስለምለቅ እንድትከታተሉኝ ሼርም በማድረግ እንድታግዙኝ ስል እጠይቃለሁ
ቶሎ እንዲከፍት በሚል ሳይዙ ተቀንሷል...instagram ina tik tok ላይ በሙሉ ጥራቱ ማየት ይቻላል
👇🏾👇🏾👇🏾Social media👇🏾👇🏾👇🏾👇🏾
Instagram Tiktok You Tube
2 371
Repost from Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
ፍቅር እና ጥላቻ አንድ የሚያመሳስላቸው ነገር ቢኖር ሁለቱም ያ ስሜት ከሚሰሙን አካላት ጋር ያጣብቁናል። ልዩነቱ ፍቅር ያንን አካል ያለማቋረጥ በደስታ እንድናስበው ሲያደርገን፤ ጥላቻ ግን አንጀታችን እያረረ ያንን አካል እንዴት አድርገን እንደምንበቀለው ያሳስበናል።
ለዛ ነው ጌታ ጠላቶቻችሁን ውደዱ ያለው።አይገርምም ለራሳችን አስቦ እኮ ነው፤ እነዛ ሰዎች ከፈጸሙብን ክፋት በላይ ያንን ቁስል እየነካካን የምናመረቅዘው ራሳችን ስለሆን ከዚህ ጠባሳ ለማምለጥ የወጉህን ውደዳቸውና የተወጋውን ጎንህን በፍቅር ጠግነው ብሎ ተግብሮ ያሳየን - መፍቀሬ አይሁድ ክርስቶስ።
ዲ/ን ዘለዓለም ዓለማየሁ
መስከረም 15 2018 ዓ.ም
2 371
Repost from Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
ፍሬ ማፍራት የተሳነው ዕፅ ጸሎት
ጌታዬ ፀሐይን በመሞቄ እኔ እልፍ የሆነ ጥቅም ባገኝም ለፀሀይ ግን አንዳች የምጨምርላት ነገር እንደ ሌለ ሁሉ ምስራቅ ከሆነች ድንግል የተወለድከው ፀሐይ ክርስቶስ ሆይ እኔ ታናሹ እፅ በአንተ ምድር የተተከልኩ በመሆኔ የአንተ ብርሃን ለኔ ልምላሜ ያስፈልጋል እንጂ የኔ መኖር አንዳች ክብር አይጨምርልህም።
ነገር ግን የጠፋሁትን በግ እኔን ፍለጋ ወደዚህ ምድር መጥተኃልና ስለ ወላዲትህ ብለህ ይችን ጸሎቴን አድምጠኝ።
ቅዱስ ዳዊት የለመነህን አንዲት ነገር እኔም ዛሬ እለምንሃለው፤ እርሷም "ከመ እሕድር ቤቶ ለእግዚአብሔር በኩሉ መዋዕለ ህይወትየ ፡ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ" ነው። ይህን ምለምንህ ከአፀድህ ተነቅሎ ወደሜዳ የወጣ መጨረሻው እንዳላማረ ስላየሁ ብቻ አይደለም በአፀድህ ያሉት እንደ ዝግባ ያሸበረቁ ቅዱሳን እውነተኛ ገፅህን እንድመለከት መስታውት ስለሆኑኝ ጭምር እንጂ::
በአንተ ቤት መተከል ማለት እኮ ከህይወት ውሃ ምንጭ ከሚፈልቁት 4ቱ አፍላጋት ይልቅ ነፍስ የሚዘራውን ቅዱሱን ደምህን ዘወትር መጠጣት፤ ምስራቀ ምስራቃት ከተባለች ቅድስቲቱ እመቤት የወጣውን ያንተ ቅዱስ ስጋ ወቅት ሳያፈራርቁ መመገብ:: እንደ ደመና ከበውን ካሉት ምስክሮቻችን በሚወጣው የዝናብ ጠለ ምህረት ዕለት ዕለት መረስረስ ነው::
እኔ ፍሬ አልባውን ዕፅ በቤትህ ትከለኝና የአረም መጫወቻ የነፍሳት መዘባበቻ መሆኔን በቃ በልልኝ:: ይኼ እንኳን ፍሬ ማፍራት ቀርቶ ተጣምሜ እንድቆም ያደረገኝን አጭሩን ስሬን መሰረት እንዲይዝ በፍቅር እንዲጸና አድርግልኝ:: ስሬ አጭር ባይሆን ኖሮ አኮ እንደ ውሃ የጠራውን ቃለ እግዚአብሔር ለመስማት አልፎም ለመተግበር ባለገምሁ ነበር፤ ግልበኛ መሆኔ ቀርቶ አጥልቆ መመርመርን ገንዘብ አደርግ ነበር::
ፀሐይ መከራ ሲመጣ ቶሎ ምጠወልገው፣ አላውቅህም ብዬ የምክድህ ስሬ በወንጌል "ቤቱን በአሸዋ ላይ የሠራ ሰነፍ ሰውን ይመስላል።" እንዳልከው ሆኖ ነውና 'እንደምወድህ አንተ ታውቃህ' ብዬ እንድመሰክር በአለቱ ጴጥሮስ ላይ አጽናኝ።
እሾህ ኃጥያቴ ጠፍንጎኝ በጽድቅ ማደግ አቅቶኛልና ደቀ መዛሙርትህን ልጄ ደካማ ነውና እርሱ እስኪመጣ አትጠብቁት ሂዱና የታሰረበትን የኃጥያት በፍታ ፍቱለት ብለህ ወደ ዳግማዊው አልዓዛር ወደኔ ላካቸውና ትንሣኤ ልቡና ይሁንልኝ።
ጌታዬ ሆይ እባከህን ህይወት ዘመኔን ካንተ ጋር እንድኖር በቅዱሱ መሬትህ ትከለኝ።
ዲ/ን ዘለዓለም ዓለማየሁ
ጥቅምት 18 : 2017 ዓ.ም
@i_panagia
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
እንኳን ለዘመነ ጽጌ አደረሳችሁ።
❝ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ፤ እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ፤ መላእክት ይትለአኩኪ። ፃዒ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት። — ርግቤ ሆይ ነዪ፤ ሐዋርያት የሚያመሰግኑሽ መላእክትም የሚላላኩልሽ መልካሜ ሆይ ነዪ። የሕይወት ውበት ከሊባኖስ ውጥተሽ ነዪ።❞
#ከመጽሐፍ_ቅዱስ_ገጾች
2 371
አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከኛ አስቀድመው የሞቱትን አሳርፋቸው። የታመሙትንም ፈጥነህ አድናቸው። የሁላችን ሕይወት የሁላችንም ተስፋ የሁላችንም አዳኝ የሁላችንም አስነሽ አንተ ነህና። ላንተ ምስጋናን እስከ አርያም ድረስ እንልካለን። ለዘለዓለሙ አሜን።
ሥርዓተ ቅዳሴ
@i_panagia
@i_panagia
@i_panagia
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
“ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክሕት ከእኔ ይራቅ።” (ገላ. 6፥14)በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ዛሬ ‛ስለምን መስቀልን እናከብራለን?’ በሚል አጠር ያለች ጽሑፍ አዘጋጅተንላችኋል አብራችሁን ቆዩን። ስለ ምን መስቀልን እናከብራለን? 1ኛ. ኃይላችን ስለሆነ ነው፤ ጠላትን የምናስበረግግበት ድል የምንነሳበት ስለሆነ፦ “የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።” (1ኛ ቆሮ. 1፥18) 2ኛ. የዳንበት፥ ጠላት ዲያቢሎስ የተቀጠቀጠበት፥ የዘመናት የጥል ግድግዳ የፈረሰበት ስለሆነ፦ “ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው።” (ኤፌ. 2፥16) 3ኛ. በእኛ የነበረውን መርገም በመስቀሉ ያስወገደልን ስለሆነ፦ “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።” (ቆላስ. 2፥14) በጥቅሉ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በገላትያ መልዕክቱ እንዳለን እኛ ክርስቲያኖች ከክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ መመኪያ ሊኖረን አይገባም። ክርስቶስ የኃጢአታችንን የዕዳ ደብዳቤ የሻረው በመስቀሉ ነው። መስቀል ምልክታችን ብቻ ሳይሆን ሕይወታችንም ነው። ክርስትና ያለ ክርስቶስ መስቀል ነፍስ የተለየው ሥጋ ማለት ነው። የክርስትና መሠረቱም፥ ማዕከሉም፥ ጉልላቱም የክርስቶስ መስቀል ነው።
❝ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአይሁድ እመኑ ብየ፤ ወእመኑ በአቡየ፤ ዮምሰ ለእሊአየ፤ አበርሕ በመስቀልየ። — ኢየሱስ አይሁድን “በኔ እመኑ፤ በአባቴም እመኑ” አላቸው፤ “ዛሬ ለእኔዎቹ በመስቀሌ አበራላቸዋለሁ።”❞መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ!
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
ሁል ጊዜ እንደዚህ አይነት ሁኔታዎች ላይ ስሆን ነብየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ የተናገረው ቃል ትዝ ይለኛል።
“ዐሳቤ እንደ ዐሳባችሁ፥ መንገዴም እንደ መንገዳችሁ አይደለምና፥ ይላል እግዚአብሔር።” ከዚያም ይቀጥልና “ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ፥ ሀሳቤም ከሀሳባችሁ የራቀ ነው።“ ፈጣን የፊዚክስ(ለሶሻሎች የጂኦግራፊ) ጥያቄ 'ሰማይ ከምድር ምን ያህል ኪሎ ሜትር ይርቃል?' አይ እንግዲህ እንዳላችሁ አልጠራጠርም።
እግዚአብሔር ያሳያችሁ የኛ ሀሳብና የሱ ሀሳብ ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ የራቀ ነው። እኛ “እንደዚህ አምጥቼ በዚህ ወጥቼ በዚህ ወርጄ” ካልነው መንገድ እግዚአብሔር ያዘጋጀልን መንገድ እጅግ የራቀና የላቀ ነው።
ለነገሩ እስከዛሬ ያሳለፍነው ሕይወት ለዚህ ሁነኛ ማስረጃ ነው። በሕይወታችን ስንቴ ነው እግዚአብሔርን ይህንን ወይም ያንን ካልሰጠኸን ብለን ደም እንባ አልቅሰን፥ ስላልሰማን ካኮረፍን ከጥቂት ቀናት በኋላ “እንኳንም አልሰጠኸኝ” ብለን ስላልሰጠን በደስታ የተፍነከነክነው⁈ የለመነውን ጸሎት የሻትነውን ነገር ስላላገኘንን ምን ያህል ደስተኛ እንደሆንን ሁላችን እናውቀዋለን።
የኛ ሐሳብና የእግዚአብሔር ሀሳብ ምን ያህል ሩቅ እንደሆነ ከመጸሐፍት እየጠቀስኩኝ አላለፋችሁም፤ ያንተ ሕይወት ያንቺ ሕይወት ምስክር ነው። ዞር ብለህ ወደ ኋላ መንገድህን ስትመለከተው እግዚአብሔር እንዴት አድርጎ የሕይወትህን ስብራት ጠግኖ እንዳስዋበህ አልረሳኸውማ መቼም⁈ ከእርሱ የራቀውን የሀሳብ መንገድህን አፍርሶ እንዴት ባለ ፍቅር ከእቅፉ እንዳኖረህ የምትዘነጋ አይመስለኝም።
አንተ ‘ይህ ውጤት እንደ ዮናስ ወደሻትኩበት ሀገር የምሄድበት መርከቤ ነው’ ብለህ እያሰብክ ይሆናል። እግዚአብሔር ግን አንተ ከምትሸሽበት ከተማ ይልቅ እርሱ ያዘጋጀልህ ነነዌ ስላለ መርከብ ውጤትህን ያናውጠዋል፤ ዙርያህ ያሉ ሰዎች በጭንቀት ማዕበል ሲናወጹ ቆመህ እንድታይ ያደርግሀል፤ ተጨንቀው ተጨንቀው የሚያደርጉት ጠፍቷቸው ርግፍ አድርገው ትተውህ ወደ ባህር እንዲወረውሩህ ያደርጋቸዋል። በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን እግዚአብሔርን ምን በድዬው ነው ያልክ እያማረርክ ይሆናል። እርሱ ዝም የሚለው ባህር ውስጥ ያዘጋጀልህን ስፍራ፥ በማዕበል ውስጥ ያኖረልህን አሳ አንበሪ ስለሚያውቅ ነው።
በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እንደ ቅዱስ ዳዊት “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝ የለም” እያልክ የማያንቀላፋውን ጠባቂህን አመስግነው።
“አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን ነው፤ ባገኘን በታላቅ መከራም ጊዜ ረዳታችን ነው። ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ፥ ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢፈልሱ አንፈራም።” እያልክ ከባለ በገናው ጋር ዘምር። ለምን? ትል እንደሆነ “እንዳትታወክም እግዚአብሔር በመካከልዋ ነው፥ እግዚአብሔርም ፊት ለፊት ይረዳታል።” ይልሃል እንደልቤ የተሰኘው ዳዊት።ከዚህ ሁሉ የምንረዳው የፈተናህ ውጤት ምድር እስክትናወጥብህ እንኳን ቢያሳዝን ምንም ልትፈራ እንደማይገባ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንደሆነ ነው።
በዚህ መሀል ደግሞ የራስን ስሜት ከማስተናገድ አልፈን ከአጠገባችን ስላሉት ሰዎች መጨነቅ አይቀሬ ነው። መቼስ ልጁ ዳቦ ቢጠይቀው ድንጋይ የሚሰጥ ወላጅ እንደሌለ ከራሳቸው በላይ የሚወዱን ቤተሰቦቻችን እኛን ስላልሆኑ የምናልፍበትን የስሜት መዋዠቅ ሳይረዱት ብዙ ነገር ሊሉን፤ ከእኛም ብዙ እንደሚጠብቁ ሊያሳዩን ቢሞክሩ የወላጅነት ተፈጥሯቸው ነውና ልንታዘባቸው አያሻም። እንደማኅበረሰብ የተቀመጠልንን የጉብዝናን መስፈርት ተንተርሰው ለኩራታቸው ወይም ለውርደታቸው ምክንያት ቢያደርጉን ሊደንቀን አይገባም። አንዳንዴም ከራሳችን ይልቅ እነርሱን ማበርታት የእኛ ድርሻ መሆኑ ስለማይቀር የመንፈስ ጥንካሬ ሊኖረን ይገባል። ይህ የመንፈስ ጥንካሬ የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእግዚአብሔር ብቻ ነው። ከፈተናው ጋር መውጫውን የሚያዘጋጅ ጌታ ለእነሱ መከፋት መጽናናት እንድሆን አበርታኝ ብሎ መማጸን የልጅነት ግዴታችን ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ያሰብከው ውጤት ቢመጣልህ ከውጤቱ በኋላ እነዚያ እግዚአብሔርን የለመንካቸው ልመናዎች፣ ለእርሱ የገባህለትን ቃልኪዳኖች ሳይታጎሉ ይፈጸሙ ይሆን? “ወይስ ታሞ የተነሳ እግዚአብሔርን ረሳ” እንደሚባለው ችግሮችህን፣ እረፍት የሌላቸውን እንባዎችህን ሳይዘነጋ የለመንከውን የሰጠህን ጌታ በወንጌል ”ያዳነው ማን እንደሆነ አላወቀም” እንደ ተባለው መጻጉዕ በመካድ ነው ብድራትህን የምትከፍለው? ወይስ በልግስና ሳይሰስት የቸረህንስ አምላክ ምንም እንዳላደረገልህ፣ የድርሻህን እንደሰጠህ አድርገህ ትተህው ከደጁ ትጠፋለህ? አደራህን ወዳጄ 'እግዚአብሔር ባይሰጠው ኖሮ እኮ ከደጁ አይጠፋም ነበር' የሚባልልህ እንዳትሆን። ምክንያቱም እግዚአብሔር ሲጎልብህ እየመጣህ የምትነዘንዘው ጌታ ብቻ ሳይሆን ነፍስህ እስካትቀርልህ ደስ የምትሰኝ ሁል ጊዜም መጥተህ የምታመሰግነው ልዑል ነው።ነገር ግን ውጤቱ እንዳሰብከው ባይመጣ ደግሞ ፊትህን ከእግዚአብሔር ፊት ካዞርክ ጌታን ምትከተለው እንደ አይሁዳውያን ምግብ አበርክቶ ሲመግብ ተአምር ሲሰራ በአጭሩ ሲሰጥህ ብቻ ነው። እንደሻትከው ስላልሆነልህ ፊትህን እንደ ቃኤል የምታጠቁር ከሆነ ያቀረብከውን መስዋዕት ጎዶሎነት ረስተህ እርሱ ስለማይወደኝ ነው እያልክ አምላክህን ትወቅሳለህ። ስለሁሉ ግን እግዚአብሔር ሲሰጥ የሚመለክ ሲነፍግ ደግሞ ፊት የሚዞሮበት አምላክ አይደለም። ኢዮብ እንደተናገረው፥ የተናገረውን ኖሮ እንዳሳየን እግዚአብሔር ቢሰጠንም ቢነሳንም እርሱን ማምለክ ልናስታጉል አይገባም። ቅዳሴያችን እንደዚህ ይላል፦
ባለጸጋውን ይጠብቃል ከደሀ ጋርም ይኖራል፤ ትሁቱን ሰው ይወዳል። ትዕቢተኛውን ግን ቸል ይላል፤ ቢፈቅድ ያጸድቃል፤ ሲወድም ያድናል። እንደማይሰማ ቸል ይላል። እንደማያይ ዝም ይላል፤ እንደማያውቅ ይታገሳል፤ እንደማይሰጥ ያዘገያል።— ቅዳሴ ሠለስቱ ምዕት ቁጥር 60 ዲ/ን ዘለዓለም ዓለማየሁ ጳጉሜን 4 : 2017 ዓ.ም
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
"ጌታ በእኔ አጠገብ ቆሞ አበረታኝ።" (2ተኛ ጢሞ 4፡17)
[ጥቂት ዘለግ ያለ ጽሑፍ ቢሆንም በትዕግስት አንብቡት..በተለይ የ12 ክፍል ውጤት እየጠበቃችሁ ያላችሁ ግድ ነው!]
እያንዳንዳችን በሕይወት ዘመናችን የተጓዝናቸውን ጉዞዎች ፍጻሜ ማየት፥ የለፋናቸው ልፋቶች ተገባደው መመልከት እጅግ የምንጓጓለት ነገር ነው። ግን አብዛኛውን ጊዜ ወቅቱ እየተቃረበ በመጣ ቁጥር ጭንቀት እኛነታችንን ወርሶ አቅላችንን ያሳጣናል “እንዳሰብኩት ይጠናቀቅ ይሆን?” “እንደዚህ ቢሆብኝ ምን እሆናለሁ?” “እንደዚህማ አይሆንም!” በማለት ጉዳዩ ላይ ካፈሰስነው ጉልበት በላይ ራሳችንን በሀሳብ ባህር አጥለቅልቀን ምንሆነውን እናጣለን። ፍጻሜውን አግኝቶ ቁርጣችንን ያወቅን ዕለት አንዳንዶቻችን በጸጸት አለንጋ ራሳችንን እንቀጣለን። አንዳንዶቻችን ደግሞ ውጤቱን መቀበል ተስኖን በመኖር ተስፋ እንቆርጣለን - ከዚያ ወዲያ ሕይወት የሚያበቃ ይመስል።
ምንድነው ዙርያ ጥምጥም የሚያስኬድህ ወደ ጉዳይህ አትገባም እያላችሁኝ ይሆናል። ከቀናት በኋላ አልያም ዛሬ ስለሚወጣው የ12 ክፍሎች Entrance exam ጥቂት ሀሳብ ልላችሁ ወደድሁ። እርግጠኛ ነኝ እያንዳንዳችሁ ለራሳችሁ “ከእዚህ በላይ ካላመጣሁ” ብላችሁ የያዛችሁን ነጥብ አለ አንዳንዶቻችሁ ደግሞ “የመጣው ይምጣ ዋናው ማለፌ ነው” ብላችሁ የተቀመጣችሁም ትኖራላችሁ፤ ሌላው ደግሞ “የመጣው ይምጣ በጸጋ መቀበል ነው” እያሉ ለሰዎች የሚያወሩ ነገር ግን ለራሳቸው እንደዚህ ካልመጣ ተስፋ የለኝም በማለት የሚጨነቁትን ቤት ይቁጠራቸው። ደጀ ሰላሟን ረግጦ ድንግል ይህንን ያህል እንዳመጣ ከረዳሺኝ እንደዚህ አደርጋለሁ ብሎ ለእግዚአብሔር፥ ለቅዱሳኑ የተሳለም ጥቂት አይደለም።ይህም ሆነ ያ እያንዳንዳችን ካሰብነው ነገር ጋር ውጤቱ ባይገጥምስ? ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን እኛ እንዳሰብነው ባይሆንስ?
2 371
Repost from Gracious ✝
ጌታ ሆይ በኢያሪኮው መንገደኛ በኩል እንዳለፍህ ይህች ዐመት ከማለቋ በፊት እባክህን በእኔም በኩል እለፍ። የጠፋውን በግ አዳምን የፈለግኸው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ እኔንም ፈልገኝ፤ ባገኘኸውም ጊዜ እንደተሸከምኸው እኔንም ተሸከመኝ። የቀደመ ፍጥረትህን አዳምን ቸል እንዳላልከው ከእርሱ አብራክ የተገኘሁ እኔ ደካማ ልጁንም ቸል አትበለኝ። ይልቁንም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንድ ሰው የተባለ አዳምን እንደተሸከምከው እኔንም ተሸከመኝ።
አዎን ጌታ ሆይ በመንገድ ላይ የወደቀው ስም የለሽ አንድ ሰው እኔ እንደሆንኩ አውቂያለሁ። ከኢየሩሳሌም ልዕልና ነፍስ ወደ ኢያሪኮ የኃጢአት ቁልቁለት የወረድሁት እኔ እንደሆንኩ ገብቶኛል። አንተ ለእኔ ድኅነት የሠራኸውን አሸቀንጥሬ ጥዬ እኔን ካስቀመጥክበት ከፍታ ተንደርድሬ ለእኔ ፍላጎት ወደሚስማማው ቁልቁለት የወረድሁት በወንበዴዎች እጅም የወደቅሁት የኢያሪኮው መንገደኛ እኔ ነኝ።
የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።” (1ኛ ጴጥ. 4፥3)
#መልካም_የጸጸት_ዘመን_ይሁንልን
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
አዲሱን ዐመት እንዴት እንቀበለው? — #ከቅዱሳን_አንደበት “የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል።” (1ኛ ጴጥ. 4፥3) እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን፤ አሸጋገራችሁ።
2 371
Repost from ኪዳን ዘኢየሱስ
አዲሱን ዓመት በክርስቶስ!
ያለፈው ዓመት ክፉም ሆነ መልካም ብዙ ነገሮችን ይዞልን የመጨረሻው ቀን ደርሰናል። ስላለፈው ዓመት እና ስላደለን በረከት ሁሉ ጌታችንን እናመስግነው ካለመኖር ሁሉ መኖር መልካም ነውና በመኖራችንም ከእርሱ መኖር መልካምነት ተሳትፈናልና ፤ በችግር እና በፈተናዎች ያሳለፍንም ስለ ፈተናዎቹ ጌታችንን እናመስግነው በፈተናዎቹ ውስጥ ሠርቶናልና ከመስቀሉ በረከትም አካፍሎናልና። በሁሉም ነገር ፣ ለሁሉም ነገር ፣ ስለ ሁሉም ነገር እናመስግነው ለተመረጡት ሁሉ ለበጎ ነውና!
የሚመጣውን አዲሱን ዓመትም በክርስቶስ እንደ ክርስቲያን እንቀበለው ፣ ባሕላዊ ክርስቲያኖች ብቻ አንሁን በእውነትም ክርስቲያኖች እንሁን እንጂ ፤ አብሮ ተሰብስቦ መብላት ፣ መጠጣት ፣ መደሰት መልካም ነው ነገር ግን ክርስቲያንነት ከዚህም የላቀ ነው ለእኛ ምግባችን ፣ መጠጣችን ፣ ደስታችን ፣ አባታችን ፣ እናታችን ሁሉ ነገራችን ክርስቶስ ነው! ክርስቶስን የያዘ ሁሉን ያተርፋል ፤ ክርስቶስን ያጣ ግን ዓለምን ሁሉ እንኳን ቢያተርፍ የከሰረ ነው ስለዚህም አዲሱን ዓመት በክርስቶስ ተባርከን እንድንጀምር በቁርባን ከእርሱ ጋር እንዋሐድ በክርስትና አንድነት አንዱን ክርስቶስ በመቀበል እንጀምር ከዚያም የተቀበልነውን ክርስቶስ ለዓለም እንመስክር። የዓለሙን እውነተኛ ብርሃን ክርስቶስ ተቀብለን እኛም ለዓለም የክርስቶስን ብርሃን የምናበራ በተራራ ላይ ያለች ከተማ እንሁን ልንሠወር አይቻልንምና።
በአዲሱ ዓመት ቁርባናዊ ሕይወት እንኑር የተሰጠንን ክርስቶስ ተቀብለን እኛም ለቤተክርስቲያናችን ፣ ለቤተሰባችን ፣ ለማኅበረሰባችን ፣ እንዲሁም ለሀገራችን እራሳችንን እንስጥ የመሰጠት ሕይወትን እንኑር ፤ በሕይወታችን የክርስቶስ ክብር ይገለጥ "አቤት ክርስቲያኖች እንዲህ ናቸው እንዴ የመምህራቸው የክርስቶስ ልጆች ናቸው" ተብለን ዓለም እስኪደነቅ ድረስ ክርስቲያን እንሁን ፤ ነገር ግን በሥራዎቻችን እኛ አንክበርበት ክርስቶስ ይክበርበት እንጂ መልካሙን ሥራችንን አይተው ሰማያዊ አባታችንን ያከብሩ ዘንድ!
መልካም አዲስ ዓመት!
2 371
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
❝ከገቢረ ኃጢኣት ሳይወጡ አዲስ ዓመት ሲመጣ መደሰት፥ ብዙ መብልና መጠጥ ማዘጋጀት፥ አዲስ ልብስም መልበስ ጥቅም የለውም። ... እንዲኽ ከገቢረ ኃጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመትን ማክበር ማለት ለኔ እንደ ልጆች የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ነው።❞ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
“በዚያም ወራት መጥምቁ ዮሐንስ፦ ‛መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ’ ብሎ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ።” (ማቴ. 3፥2)
