en
Feedback
የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads

የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads

Open in Telegram

እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads

Channel የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads (@janyared_2) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 46 572 subscribers, ranking 1 201 in the Religion & Spirituality category and 733 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 46 572 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -322 over the last 30 days and by -16 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.73%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 862 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 132.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

46 572
Subscribers
-1624 hours
-237 days
-32230 days
Posts Archive
ጳጕሜን
+9
ጳጕሜን

እንኳን ለደብረታቦር በዓል አደረሳችሁ።

ጃን ቂርቆስ በጃን ቂርቆስ ፕሮጀክት ሥር ድጋፍ እየተደረገላቸው ከሚገኙ 700 ከሚሆኑ ሕፃናት/ታዳጊዎች እና 370 ከሚሆኑት እናቶች በተጨማሪ 150 ለሚሆኑ ሕፃናት እና ታዳጊዎች ከመስከረም 2019 ዓ
+1
ጃን ቂርቆስ በጃን ቂርቆስ ፕሮጀክት ሥር ድጋፍ እየተደረገላቸው ከሚገኙ 700 ከሚሆኑ ሕፃናት/ታዳጊዎች እና 370 ከሚሆኑት እናቶች በተጨማሪ 150 ለሚሆኑ ሕፃናት እና ታዳጊዎች ከመስከረም 2019 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ዓመታት የሚቆይ ወርኃዊ የገንዘብ፣ የተከታታይ ሥልጠና፣ የሕክምና እንዲኹም ሌሎች ድጋፍ ለማድረግ ነሐሴ 2 2018 ዓ.ም. ኢጃት ከጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ትምህር ቤት ጋር የስምምነት ውል ተፈራርሟል። ከልጆቹ ድጋፍ በተጨማሪ እናቶቻቸው አነስተኛ የንግድ ሥራ ሠርተው በኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ የንግድ ሥራ ሥልጠና እና የሥራ ማስጀመርያ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው ይሆናል።

የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ሐረር ቅንርጫፍ የመጀመርያውን ጉዞ ባስልዮስ አካሄደ። በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ፕሮጀክቶች ሥር የሚገኘው ጉዞ ባስልዮስ፤ በሐረር መቄዶንያ ለሚገኙ አረጋውያን ነጻ
+5
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ሐረር ቅንርጫፍ የመጀመርያውን ጉዞ ባስልዮስ አካሄደ። በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ፕሮጀክቶች ሥር የሚገኘው ጉዞ ባስልዮስ፤ በሐረር መቄዶንያ ለሚገኙ አረጋውያን ነጻ ሕክምና እንዲያገኙ የሚያደርግበት የሕክምና ጉዞ በነሐሴ 3 2018 ዓ.ም. አድርጓል። በተካሄደው በዚህ ጉዞ ስድስት የሚሆኑ ልዩ ልዩ የጤና ባለሙያዎችን የያዘው የሕክምና ቡድን 200 ለሚሆኑ አረጋውያን አስፈላጊውን ምርመራና ሕክምና ያደረገ እና የመድኃኒት ስርጭትም ያከናወነ ሲሆን አረጋውያኑ በተደረገላቸው ሕክምና ተደስተው ምርቃታቸውንም ለሕክምና ቡድኑ ሰጥተው ሸኝተዋል።

4ኛ ትውልድ ሱባዔ ጉባኤ ስልጠና መካፍል የምትፈልጉ በድሬዳዋ እና አቅራቢያ የምትገኙ በሙሉ ከዚህ በታች ባለው መስፈንጠሪያ(ሊንክ) ይመዝገቡ። https://forms.gle/nf1UEjzps8VbSMDY7
4ኛ ትውልድ ሱባዔ ጉባኤ ስልጠና መካፍል የምትፈልጉ በድሬዳዋ እና አቅራቢያ የምትገኙ በሙሉ ከዚህ በታች ባለው መስፈንጠሪያ(ሊንክ) ይመዝገቡ። https://forms.gle/nf1UEjzps8VbSMDY7

የማደጎ ልጆች አስተዳደግ ሴሚናር ተካሄደ! ከኢጃት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው በጃን ቂርቆስ አዘጋጅነት የተሰናዳ በማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆች አስተዳደግ ላይ ያተኮረ ሴሚናር ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 201
+4
የማደጎ ልጆች አስተዳደግ ሴሚናር  ተካሄደ! ከኢጃት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው በጃን ቂርቆስ  አዘጋጅነት የተሰናዳ በማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆች  አስተዳደግ ላይ ያተኮረ ሴሚናር ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.  በአፍሪክ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ካቴድራል ሰ/ት/ ቤት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።  300 የሚሆኑ ታዳሚዎች  በተሳተፉበት በዚህ መድረክ ላይ፣ የማደጎ ልጆች አስተዳደግ መንፈሳዊ፣ ስነ ልቡናዊና ማሕበራዊ ገፅታ  ሁለንተናዊ እይታን በገነባ መልኩ ተዳሷል። በመርሐ ግብሩ ላይም "የማደጎ/ጉዲፈቻ ወላጅነት በመንፈሳዊ ዕይታ" በሚል ርዕስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን  "የልብ ምጥ" በሚል ርዕስ የማደጎ/ጉዲፈቻ ወላጅነት ሥነ-ልቦናዊና ማኅበራዊ ገፅታን በተመለከተ ሙያዊ ገለፃ በሥነ-ልቦና ባለሙያ ተሰጥቷል። ከትምህርታዊ ገለፃዎቹ በተጨማሪም የማደጎ/ ጉዲፈቻ ልጆችን ወስደዉ እያሳደጉ ያሉ ወላጆች የማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆች አስተዳደግን በተመለከተ  የህይወት ተሞክሯቸውን አጋርተዋል። ይህ የልምድ ማካፈል መድረክ ታዳሚው ስለ ማደጎ ልጆች አስተዳደግ ተግባራዊ  ግንዛቤን እንዲጨብጥና አዳዲስ እውቀቶችን እንዲቀስም ትልቅ በር የከፈተ ነበር። መድረኩ በርካታ  ጉዳዮች የተዳሰሱበትና ስኬታማ የነበረ ሲሆን፣ ከተሳታፊዎችና ከተመልካቾች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል።  በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት ጥቂት የማይባሉ ታዳሚዎችም የማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆችን ለመውሰድ ያላቸውን ከፍተኛ ፍላጎት የገለጹ ሲሆን፣ ይህንን በጎ ምኞታቸውን ወደ ተግባር ለመቀየርም በቀጣይነት ያለው የስልጠና አና የማማከር አገልግሎት የሚያገኙ ይሆናል።

በኢጃት ጃን አግናጥዮስ የሚዘጋጀው ጉባኤ አግናጥዮስ የአዳጊ ልጆች የክረምት ትምህርት ላይ ለመሳተፍ የተቀመጠውን ቅጽ በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ። https://forms.gle/Lwf67YChbYwSj
+5
በኢጃት ጃን አግናጥዮስ የሚዘጋጀው ጉባኤ አግናጥዮስ የአዳጊ ልጆች የክረምት ትምህርት ላይ ለመሳተፍ የተቀመጠውን ቅጽ በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ። https://forms.gle/Lwf67YChbYwSjxDT7 ማሳሰቢያ፦ የ12ተኛ ክፍል የመውጫ ፈተና እና የ11ኛ ክፍልን የክረምት ትምህርት በማስመልከት፡ ተማሪዎችን ከመርሐግብሩ መሳተፍ ይችሉ ዘንድ 1ሳምንት ተራዝሟል። የተሳታፊዎች ዕድሜም ከ14-19 ዓመት ላሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። ሐምሌ 6 ሊጀምር የነበረው የጉባኤ አግናጥዮስ የክረምት መርሐግብር በ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን ትምህርቱ የሚጀመርበትን ቀን በዚሁ
ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። ሐምሌ 6 ሊጀምር የነበረው የጉባኤ አግናጥዮስ የክረምት መርሐግብር በ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን ትምህርቱ የሚጀመርበትን ቀን በዚሁ ገጽ የምናሳውቅ ይሆናል።

በኢጃት ጃን አግናጥዮስ የሚዘጋጀው ጉባኤ አግናጥዮስ የአዳጊ ልጆች የክረምት ትምህርት ላይ ለመሳተፍ ከስር የተቀመጠውን ቅጽ በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ። https://forms.gle/AdLs7RHSq
+4
በኢጃት ጃን አግናጥዮስ የሚዘጋጀው ጉባኤ አግናጥዮስ የአዳጊ ልጆች የክረምት ትምህርት ላይ ለመሳተፍ ከስር የተቀመጠውን ቅጽ በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ። https://forms.gle/AdLs7RHSqPhVvfjD9

ዘመነ ክረምት (ከሰኔ 25 - መስከረም 25)

በማደጎ ልጅ አስተዳደግ ዙሪያ የተዘጋጀ ልዩ የግንዛቤ መፍጠሪያና የልምድ ልውውጥ መርሐግብር ሐምሌ 04፣ 2018 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 በአፍሪካ ኅብረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አዳራሽ
+2
በማደጎ ልጅ አስተዳደግ ዙሪያ የተዘጋጀ ልዩ የግንዛቤ መፍጠሪያና የልምድ ልውውጥ መርሐግብር ሐምሌ 04፣ 2018 ዓ/ም ከቀኑ 7:00 በአፍሪካ ኅብረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አዳራሽ

የማደጎ ልጆች አስተዳደግ (Adoption)ላይ ያተኮረ ሴሚናር ለመመዝገብ ከታች የተቀመጠውን ሊንክ ይጠቀሙ። https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSd0v3vXzgHbmGiO10eQoe5teXkZJID5-7BMkRKBWMLYvSjuQQ/viewform 🗓️ቅዳሜ ሐምሌ 4 ⏱️ከቀኑ 7:00 ጀምሮ 📍በአፍሪካ ሕብረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ

"አሕዛብ፡— “አምላካቸው ወዴት ነው?” እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል፡ በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ይወቁ፤ የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት ሊገደሉ የተፈረ
+5
"አሕዛብ፡— “አምላካቸው ወዴት ነው?” እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል፡ በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ይወቁ፤ የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት ሊገደሉ የተፈረደባቸውን አድን" መዝ. 79:10-11 የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በምሥራቅ አርሲ በግፍ ለተገደሉ ሰማዕታት ጸሎተ ምሕላና ዝክረ ሰማዕታት አርብ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም አካሔደ:: ሐዋርያው "አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል" በማለት እንደተናገረ በየትኛውም ሥፍራ የሚፈጸም ግድያ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ኀዘን ነው:: 1 ቆሮንቶስ 12:26 በዚህም ምክንያት የምእመናን ድምፅ ለሚሰማና ዕንባ ለሚቀበል ፣ ለተገፉት ለሚፈርደው አምላክ ስለ ሰማዕታቱ ሞት በእግዚኦታና በጸሎት በመማፀን እንዲሁም በሻማ ማብራት መታሰቢያ ተከናውኖአል:: ጸሎተ ምሕላው በጾመ ሐዋርያት ያለማቋረጥ እንደሚከናወን የተገለጸ ሲሆን ከጸሎትና ዝክረ ሰማዕታቱ ጎን ለጎን በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተጠራው የማኅበራት ኅብረት ውስጥ ኢጃት በአባልነት እየሠራ እንደሆነና ዝርዝር ሁኔታዎች በሒደት የሚገለጹ መሆኑን በጉባኤው ላይ ተገልጾአል:: "በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ" ዕብ. 10:25

"አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ለምን ይላሉ? የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል ዓይኖቻችን እያዩ አሕዛብ ይወቁት።" መዝሙር 79:10

መጪውን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል (ግንቦት ልደታ) ለምን፣ እንዴት እና በምን አይነት የአከባበር ስርዓት ማክበር እንዳለብን የሚያሳይ የኦንላይን ስልጠና በኢትዮጲያዊው ጃንደ
መጪውን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል (ግንቦት ልደታ) ለምን፣ እንዴት እና በምን አይነት የአከባበር ስርዓት ማክበር እንዳለብን የሚያሳይ የኦንላይን ስልጠና በኢትዮጲያዊው ጃንደርባ ትውልድ የጃን ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ፕሮጀክት አዘጋጅቷል። የዚህ ስልጠና ተሳታፊ መሆን የምትፈልጉ ወጣቶች ከታች በተያያዘው ሊንክ በመመዝገብ ስልጠናውን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeRvipiuCXKfIrOIPZfzTKJUT3DwXCcKaVPiUz9tXV-Sg3vRQ/viewform?usp=publish-editor

በግፍ የሰቀሉት ያማረ በግ እናቱ ፣የሐዋርያው ዻውሎስም የምስክርነቱ ድንኳን የምትሆኚ የተድላና የደስታ ዘመን እመቤታችን ሆይ ሰላምታ ይገባሻል። እመ ቅድው በግዕ ዘሰቀልዎ በግፍዕ ወደብተራ ስምዕ ዘዻ
+1
በግፍ የሰቀሉት ያማረ በግ እናቱ ፣የሐዋርያው ዻውሎስም የምስክርነቱ ድንኳን የምትሆኚ የተድላና የደስታ ዘመን እመቤታችን ሆይ ሰላምታ ይገባሻል። እመ ቅድው በግዕ ዘሰቀልዎ በግፍዕ ወደብተራ ስምዕ ዘዻውሎስ ረድዕ ማርያም ዘመነ ፍግዕ ሰላም ለኪ።

የስቅለት ምንባባት - በሦስት ሰዓት ፣ በስድስት ሰዓት ፣በዘጠኝ ሰዓት
+7
የስቅለት ምንባባት - በሦስት ሰዓት ፣ በስድስት ሰዓት ፣በዘጠኝ ሰዓት