en
Feedback
꧁༒꧂ አዕማድ ꧁༒꧂

꧁༒꧂ አዕማድ ꧁༒꧂

Open in Telegram

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የወልድ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት በክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት ያለ ጥርጥር በፍጹም ልባችን ከምናምን ምእመናን ጋር ይኹን! [፪ኛቆሮ.፲፫፥፲፬] https://www.facebook.com/share/1BKZDTmdeH/ https://www.tiktok.com/@eyuel.solomon18?_t=ZN-90PXVwTr5aZ&_r=1 https://youtube.com/@eyuel-solomon?

Show more
1 705
Subscribers
-124 hours
-87 days
-1530 days
Posts Archive
የሰማዕታትና የጻድቃን የድል አክሊል መቀበያ ሰዓት፦ በሰማዕታት መጻሕፍትና በሪክሾ መዝገቦች እንደሚታወቀው፣ ጳጕሜን በዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆኗ የዘመናት ሁሉ መቋጫ ብቻ ሳይሆን፣ ዓመቱን ሙሉ ሲጋደሉ፣ ሲሰደዱ፣ ስሙን ሲጠሩ እና በሃይማኖት ጸንተው የኖሩ ቅዱሳንና ጻድቃን ዋጋቸውን የሚቀበሉበት የክብር ምሳሌ ናት። ልክ በእርሻ ዘመን መጀመሪያ የሚዘራው እህል በክረምት አልቆ በመስከረም ወር ማሳ ላይ እንደሚሰበሰብ ሁሉ፤ የዘመኑም ፍሬ (የሰው ልጅ መልካም ሥራና ጸሎት) በጳጕሜን መዝጊያ ተመዝኖ ለአዲሱ ዘመን በረከት መሠረት ይሆናል በመሆኑም ጳጕሜን የጸጸት፣ የዕጥበት፣ እና የዘላለም ሕይወት ዋጋችንን የምንመረምርባት «የሕሊና መስተዋት» ናት። ​፬. የቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ እና የአባ ሕርያቆስ ምስጋና (የዘመን ማኅተም)፦ በሊቃውንት መዛግብት እንደሰፈረው፣ ጳጕሜን የቃልኪዳን እና የሰማያዊ ምስጋና ማኅተም ናት። አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ላይ «አንቲ የሆድ ፍሬ...» እያለ እንዳመሰገነ፣ በዚች ወር ማጠቃለያ ላይ ቅዱሳን መላእክት የሰውን ልጅ ድካም እያዩ ከፈጣሪ ፊት የሚቆሙበት እና የምሕረት ጽዋ የሚሞላበት ሰዓት ነው። ዘመነ በርዮድ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቅባት፣ መላእክትም በምድርና በሰማይ መካከል ሐሴት የሚያደርጉባት የንጽህና ማማ ናት [ትርጓሜ ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ]። ​፭. የዘመናት መቋጫ እና የ«አዲስ ፍጥረት» (በክርስቶስ ዳግም መታደስ) ምስጢር በሐዲስ ኪዳን መለኮታዊ ሐተታ መሠረት፣ አሮጌው ዓመት ተፈጽሞ አዲሱ ዓመት እስኪተካ ድረስ ያለው ይህ አጭር ልዩ ጊዜ የሰው ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት የመሆኑ ትክክለኛ ምሳሌ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ሰው በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል፣ እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኗል» ብሏል [2ኛቆሮንቶስ 5፥17]። ጳጕሜን የኃጢአት አሮጌ ልብስ ተገፎ የጽድቅ ነጭ ካባ የሚደረብባት፣ የሰው ልጅ ሕሊና ከቀድሞው ውድቀት ተነሥቶ ከእግዚአብሔር ጋር ሐዲስ ኪዳን የሚመሠርትባት ሰማያዊ የዕድሳት ማዕድ ናት። ​«እነሆ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ፤ ዘመናችንን በሰላም ጀምረን በሰላም እንድንፈጽም የፈጣሪ ቸርነትና ጸጋ ከእኛ ጋር ይሁን።» ​ዋቢ መጻሕፍት እና የምንጭ መዛግብት • ​መጽሐፍ ቅዱስ (ቅዱስ መጽሐፍ) ◦ ​መጽሐፈ ሲራክ 17፥2 (ስለ ዘመንና ቀን አቆጣጠር) ◦ ​መጽሐፈ ኢዮብ 38፥7 (ስለ መላእክት ዝማሬ እና ፍጥረት) ◦ ​መጽሐፈ ሕዝቅኤል 36፥25 (ስለ ንጽሕና እና የውኃ ግርማ) ◦ ​መጽሐፈ ዘፍጥረት 2፥2 (ስለ ሰባተኛው ቀን ዕረፍተ እግዚአብሔር) ◦ ​2ኛ መጽሐፈ ቆሮንቶስ 5፥17 (ስለ ዐዲስ ፍጥረት እና የዘመን መታደስ) • ​መጽሐፈ ዮዲት (የብሉይ ኪዳን አዋልድ መጽሐፍ) ◦ ​ምዕራፍ 2፥2-7 (ስለ ናቡከደነጾር ትእዛዝ እና የሆሎፎርኒስ ዘመቻ) ◦ ​ምዕራፍ 8፥2-6 (ስለ ዮዲት ሱባኤ፣ ንጽሕና እና ጸሎት) • ​ቅዱስ ያሬድ ድጓ እና የዜማ መዛግብት ◦ ​የዘመነ በርዮድ እና የዕለቱ ዑደት (ጎሕ፣ ነግህ፣ ጽባሕ፣ ብርሃን፣ መዓልት፣ ጌና) መግለጫዎች የሚገኙባቸው የሰዓታትና የድጓ መዛግብት። • ​ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የትርጓሜ መጻሕፍት እና ጠቃሚ ጽሑፎች ◦ ​አምስቱ አዕማደ ምስጢር ማብራሪያ መጻሕፍት (ምስጢረ ሥላሴ፣ ትስብእት፣ ጥምቀት፣ ሥጋዌ፣ ትንሣኤ)። ◦ ​የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዓታት አቆጣጠር እና የበዓላትና አጽዋማት ሥርዓተ መመሪያ መጻሕፍት። ◦ ​ቅዳሴ ማርያም እና ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ (የአባ ሕርያቆስ እና የቅዱስ ኤፍሬም ሐተታዎች)። በቀሲስ ኢዩኤል ሰሎሞን ዘደብረ ብሥራት 2018 ዓ.ም

[የዘመነ በርዮድ እና የጳጕሜን መንፈሳዊ ምስጢር ከታሪክ እስከ ዘላለማዊ ድኅነት] ​ዓመትን በዘመናት ስንከፋፍለው በአራት ወቅቶች ይታደላል። ከእነዚህም መካከል ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ያለው ዘመነ ክረምት አንዱ ነው። በዚህ የክረምት ወቅት ማጠናቀቂያ ላይ ከነሐሴ 28 እስከ ጳጕሜን ፭ (በሠግር ዓመት ፮) ያለው ጊዜ ዘመነ በርዮድ በመባል ይጠራል። «በርዮድ» የሚለው ቃል የሽግግር ወይም የመሻገር ትርጉም አለው፤ ይህም አሮጌውን ዓመት አስረክቦ ወደ አዲስ ዓመት የሚያሻግረን ወሳኝ የሰዓታት ምዕራፍ መሆኑን ያሳያል። ​በቅዱስ ያሬድ ድጓ መሠረት ይህ የሽግግር ወቅትና የዕለቱ ዑደት በስድስት ክፍሎች ይገለጻል፦ • ​ጎሕ (ውጋገን)፦ የጨለማው መደምደሚያና የብርሃን አበደ መጀመሪያ። • ​ነግህ (ንጋት)፦ ብርሃን እየሰፋ የሚሄድበት። • ​ጽባሕ (ጥዋት)፦ ሐፀር (የቀኑ አጭር ክፍል) አልፎ ፀሐይ የምትወጣበት። • ​ብርሃን፦ ፍጹም ቀን የሚታይበት። • ​መዓልት (ዕለት)፦ ሙሉው የቀን ሰዓት። • ​ጌና (ልደት)፦ ከዘመነ በርዮድ ጋር ተያይዞ የፍጻሜና የጅምር ምሳሌ ሆኖ የሚነሣበት። ​መጽሐፍ ቅዱስም ሰዓቱንና ወቅቱን በተመለከተ፦ «ዘመንን ቀንን በቊጥር ሰጣቸው፣ በውስጧም ያለውን ፍጥረት አስገዛቸው» ይላል [ሲራክ 17፥2]። ይህ የሚያሳየው የጊዜ ባለቤት እግዚአብሔር መሆኑንና እያንዳንዱ ወቅት የራሱ አጽናፈ ሰማያዊ ዓላማ እንዳለው ነው። ​«ጳጕሜን» የሚለው ቃል የግሪክ መሠረት ያለው ሲሆን ትርጉሙም «ጭማሪ» ማለት ነው። የወቅቱ ርዝማኔ በመደበኛ ዓመት ፭ ቀናት፣ በሠግር (በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ) ደግሞ ፮ ቀናት ሲሆኑ፣ በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ሰባት ቀን ሆኖ የምትመጣበት ልዩ ወር ናት። በዚህም የተነሣ ሀገራችን ኢትዮጵያ የዐሥራ ሦስት ወራት ጸጋ /13 በመባል በዓለም ታውቃለች። ​በቀዳሚው ፍጥረት መሠረት እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን፣ ሐመልማልንና ፀሐይን ጨረቃን ሲፈጥር አምስቱ ቀን አልቀዋል፤ ስድስተኛው ቀን ደግሞ አዳም የተፈጠረበትና እንስሳት የተገኙበት ነው። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስተምሩት፣ ጳጕሜን በዓመቱ መጨረሻ ላይ ስትመጣ «የዓለም ፍጻሜና የትንሣኤ ምሳሌ» ናት። በመላእክት ዝማሬ የተከበረችው ይህች ወር አሮጌው ዓመት ተፈጽሞ አዲሱ ሳይገባ በመካከከል የምትገኝ የ«ምስጋና እና የእረፍት ሰዓት» ናት፤ መጽሐፍ ቅዱስም፦ «የጠዋት ከዋክብት በአንድነት ዘመሩ፤ የእግዚአብሔር ልጆችም ሁሉ እልል አሉ።» በማለት ይመሰክራል [ኢዮብ 38፥7]። ​በቁጥር ጥናት መሠረት የጳጕሜን ቀናት ፭ መሆናቸው በአምስቱ አዕማደ ምስጢር (ምሥጢረ ሥላሴ፣ ምሥጢረ ትስብእት፣ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ሥጋዌ፣ እና ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን) ይመሰላል። በዘመነ ሉቃስ ስድስት ቀን ስትሆን፣ ስድስተኛው ቀን እግዚአብሔር አዳምን የፈጠረበት ዕለት በመሆኑ «ሰው ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቅበትና አዲስ ሕይወት የሚጀምርበት» ታላቅ ምሳሌ ሆኖ ይታያል። ​በተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ከሚገኙ ሁለት የፈቃድ አጽዋማት አንዱ በጳጕሜን ወር የሚጾመው ጾመ ዮዲት ነው። ይህ ጾም እንደ ጾመ ጽጌ በውዴታ እንጂ በግዴታ የተጣለ አይደለም። እዚህ ላይ መገንዘብ የሚገባው ታላቁ ሐቅ፦ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በመጽሐፈ ዮዲት የተገለጸችው ጀግናዋ መበለት ናት እንጂ በታሪክ ትምህርት በጥፋት ሥራ የምትታወቀው «ዮዲት ጉዲት» አይደለችም። የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር ጦር አበጋዙን ሆሎፎርኒስን ልኮ እስራኤልን በወረረ ጊዜ፣ ሕዝቡ ታላቅ መከራና ስቅየት ደረሰባቸው። በዚህ ጊዜ ባሏ ሞቶባት ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም፣ በቀኖናና በሐዘን ተወስና የምትኖር ዮዲት ማቅ ለብሳ፣ በራሷ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች። የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ አምላክ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ተገለጠላት [ዮዲት 8፥2]፤ እስራኤላውያንም ጠላታቸውን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጠፉት። ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንንና ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ ጳጕሜንን በፈቃድ እንጾማለን። ​ይህቺ ወር የዕለተ ምጽአት መታሰቢያም ናት። የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነ ሁሉ፤ ምጽአትም ከጊዜያዊው ዓለም ወደ ዘላለማዊው፣ ከምድራዊው መኖሪያ ወደ ሰማያዊው መንግሥት መሸጋገሪያ ነጥብ ነውና። ​ክርስቲያኖች በየዓመቱ በጳጕሜን ወር ተሰብስበው ከሌሊት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን በመገኘት ጠበል ይጠመቃሉ። እግዚአብሔር የተባረከ ዐዲስ ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሠራነውን ኃጢአት በንስሐ ታጥበን ይቅርታን እንድንቀበል ነው። በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጠበል ከሥጋዊና ከመንፈሳዊ በሽታ ያድነናል፤ የተቀደሰ ሕይወት እንዲኖረን በማድረግ መጪውን ዘመን የተባረከ ያደርግልናል። ​ከዚህም ባሻገር፣ የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት፣ ድጓዎች እና ሰማያዊ መዛግብት ሲመረመሩ የጳጕሜን እና የዘመነ በርዮድ ምሥጢር ከዚህ በላይ የሰላም ልብን የሚያለመልም እና የሰውን ልጅ መዳን ከዘላለም እስከ ዘላለም የሚያሳይ ጥልቅ ሰማያዊ ገጽታ አለው፦ ​፩. የጳጕሜን ወር እና የ«ሰባተኛው ሺህ» (የዕረፍተ እግዚአብሔር) ምስጢር በቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜ (እንደ ጸሐፍተ ሕግና ሊቃውንት ትውፊት) መሠረት አንድ ሺህ ዓመት በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ አንድ ቀን ነው። አምላካችን ሰማይንና ምድርን በስድስት ቀን ፈጥሮ በስድተኛው ቀን ፍጥረቱን ከፈጸመ በኋላ በሰባተኛው ቀን አርፏል [ዘፍጥረት 2፥2]። የመጀመሪያው ሺህ እስከ ስድስተኛው ሺህ ዓመት ድረስ ያለው ዘመን የደካማው ሥጋ፣ የውጊያ፣ የድካም እና የፈተና ዘመን (የክረምት ምሳሌ) ነው። በዘመናት አቆጣጠር ጳጕሜን ከስድስቱ ወራት (ወይም ከዓመቱ ፍጻሜ) በኋላ ስትመጣ፣ የዚህች ምድር ሠርቶ መከራን ተቀብሎ ማለፍ ፍጻሜ ሆና የምትታወቀው «የሰባተኛው ቀን ዕረፍት» ነጸብራቅ ናት። አሮጌው ዓመት ተፈጽሞ ጳጕሜን ስትገባ፣ አማኝ ከዚህ ዓመት ድካም አርፎ ወደ አዲሱ ብርሃን (ወደ መንግሥተ ሰማያት) የሚገባበትን የዘላለም ዕረፍት ምሥጢር ያሳያል። ​፪. በዘመነ በርዮድ የሚደረገው «የመጋረጃ መከፈት» (የምስጢር መገለጥ)፦ በጥንታዊው የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ትውፊት መሠረት (በተለይም በቅዱስ ያሬድ መጻሕፍትና በቅዳሴ ሃይማኖት ትርጓሜዎች)፣ በዘመነ በርዮድ ሰዓታት ውስጥ የሰማይ መጋረጃዎች ተከፍተው የእግዚአብሔር ቸርነትና የቅዱሳን መላእክት ሠራዊት ከምድር ጋር የሚቀራረቡበት ሰዓት ነው። «በርዮድ» ማለት ድንበር ማቋረጥ እንደሆነ ሁሉ፤ በዚህች ወር አማኝ ከሰዎች ግርግር ራሱን አግልሎ በጸሎት ወደ ፈጣሪው ሲቀርብ፣ በነፍሱና በሥጋው መካከል የነበረው የኃጢአት መጋረጃ ተቀዶ የእግዚአብሔር ሰላም በልቡ ላይ የሚሰፍንበት ልዩ ጸጋ አለው። መላእክት የዓመቱን ፍጻሜ እያመሰገኑ፣ የሐዲሱን ዓመት በረከት ወደ ምድር የሚያመጡበት ሰማያዊ ሠልፍ የሚከናወንበት ወቅት በመሆኑ አባቶች ይህንን ጊዜ በንቃት፣ በጾምና በስግደት ሊያሳልፉት ይገባል ይላሉ። ​፫.

*እነሆ የትንሣኤ እና የዕርገት ብርሃን በሰማይና በምድር ላይ አበራ!* ​የእናቶች እናት፣ የዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነችው ንጽህት ድንግል ማርያም ከዕረፍት በኋላ በክብር ወደ ሰማይ ማረጓን የሚያበስረው ይህ ዕለት የሰላም፣ የፍቅር እና የተስፋ በዓል ይሁንልን። ​እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእናትነት ጽንፍ የቆመችበት፣ የሰው ልጅ ትንሣኤ መጀመሪያ የሆነው ይህ ድንቅ ቀን፤ በቤታችሁ ሰላምን፣ በልባችሁ ዕረፍትን፣ በኑሮአችሁም በረከትን አብዝቶ ያኑርልን። ​እንኳን አደረሳችሁ! መልካም የዕርገት በዓል ይሁንልን! 🌸

ደብረ ታቦር የተባለው ጌታ ክብሩን የገለጠበት ስፍራ ደብረ ታቦር ስለሆነ በዚሁ በዓሉ ስያሜውን አግኝቷል፡፡ ቡሔ ይባላል ፡- ቡሄ ብርሃን ማለት ነው በደብረ ታቦር ቧ ብሎ የተገለጠውን የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል፤ የልብሱንም እንደ ነጭ በረዶ ጸዓዳ መሆን ያስረዳል፡፡ ♰ • አንድም፡- ቡሔ ማለት መላጣ (ገላጣ) ማለት ነው፡፡ ይኸውም በበዓሉ ዋዜማ ልጆች ‹‹ ቡሔ በሉ፤ ቡሔ መጣ ፣ ያ መላጣ፣ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ›› ይላሉ እዚህ ላይ ቡሄ ያለው ዳቦውን ነው፡፡ ♰ • አንድም፡- ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንደሚባል ወቅቱ በሃገራችን የጸዓተ ክረምት ዋዜማ ስለሆነ የክረምቱ አፈናው ተወግዶ /ተጋምሶ/ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት ፤ በዶፉና በጎርፉ ተሸፍና የነበረች መሬት የምትገለጥበት በመሆኑ ነው፡፡ ♰ • አንድም፡- ቡሔ (ቡሔእየ) ተብሎ ይተረጎማል ይኸውም የደብረታቦር እለት እርሾ ሳይገባበት ተቦክቶ የሚጋገረውን ኅብስት ያሳያል፡፡ → ችቦ የመብራቱ ፣ የሙልሙል ዳቦ የመጋገሩና የጅራፍ ማጮኽ ምክንያት፡- ♰ • የጌታችን ክብሩ በተገለጠበት ጊዜ ብርሃኑ የሌሊቱን ጨለማ ገፍቶት እስከ አርሞንዔም ደርሶ ነበርና በዚያ አካባቢ የነበሩ እረኞች በኹኔታው ተገርመው ቀንም መስሎአቸው ሌሊቱም ተዘንግቷቸው በዚያው ቆይተው ነበርና ቤተሰዎቻቸው ምን አግኝቷቸው ይሆን በማለት መብራት አብርተው (ችቦ ይዘው)፣ የሚመገቡትን ይዘው ወገኖቻቸውን ፍለጋ ወጥተዋል እረኞችም ያሉበትን ቦታ ለቤተሰዎቻቸው ጅራፍን በማጮኸ አመልክተዋቸዋልና ይህን ለማሰብ ነው፡፡ ♰ • ዋናው ምስጢሩ ግን፡- የችቦው ብርሃን የጌታ ክብር መገለጡን፣ የጅራፋ ጩኸት ሐዋርያትን ያስደነገጣቸው የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ሲሆን፣ ኅብስቱ ጌታችን በመስቀል ላይ መሥዋዕት የመሆኑ (የሥጋ ወደሙ) ምሳሌ ነው፡፡ ♰ • ማስታወሻ፡- ከላይ እናዳየነው ጅራፋ መጮኹ የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ነው ይኸውም በታቦር ተራራ ላይ እንደሆነም ተገልጧል ስለዚህ ዛሬም ምሳሌነቱን ለማጉላት ጅራፍ የማጮኹን ሥርዓት በተራራ ማድረግ የተሻለ ነው፡፡ መልካም በዓል ይሁንላችሁ።

♰ ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚኣከ ይትፌስሑ [መዝ.88÷12] → ይህ በዓል ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ሲሆን የሚከበረው ጌታችን የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅነቱን ያስመሰከረበት፣ ጌትነቱን እና ክብሩን የገለጠበት በመሆኑ ነው፡፡ [ማቴ.17:1፣ ማር.9:2፣ ሉቃ.9:28፣ 2ጴጥ.1:16-18]፡፡ ♰ → ጌታችን ሐዋርያትን ‹‹ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ብለው ይሉታል? ›› ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ቅድስናህን ዓይተው ሙሴ ነህ ይሉሃል፤ የኃይል ሥራህን ድንግልናውንም ዓይተው ኤልያስ ነህ የሚሉህ አሉ ……… ብለውት ነበረና እግዚኣ ሙሴ ወኤልያስ (የነቢያት ጌታ) መሆንኑን ለመግለጥ፤ አንድም ጌታችንም መልሶ ‹‹ እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ? ›› አላቸው ቅዱስ ጴጥሮስም እስከ ክርስቶስ ተብሎ የተነገረልህ ‹‹ አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ ›› አለው [ማቴ.16:13-20/ ዳን.9:25] ይህን በፍጡር አንደበት የተመሰከረውን ጌትነቱን በአብ ምስክርነት ለማጽናት እና በተግባር ለመግለጥ የሐዋርያትንም እምነታቸውን ለማጽናት አዕማደ ሐዋርያት የሆኑትን ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ቅዱስ ያዕቆብ እና ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ ወደ ቅዱሱ ተራራ አወጣቸው፡፡ ስለምን እነዚህን ብቻ አወጣቸው ቢሉ ለፍቅሩ ይሳሳሉና በፍቅሩ ይናደዳሉና ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታ እሞታለሁ ቢለው " አንተስ አትሞትም እኔ እሞታለሁ እንጂ " ማለቱ እኒም እኔ የምጠጣውን ጽዋ (ሞት) ልትጠጡ ትችላላችሁን? ቢላቸው " አዎ እንችላለን " (ስለ አንተ እንሞታለን) ማለታቸው እጅግ ቢወዱት ነው ስለዚህ ሦስቱን መረጣቸው፡፡ ♰ → ቀሪዎችን ስምንቱ ሐዋርያትንና ይሁዳን ከእግረ ደብር አቆይቷቸዋል ከይሁዳም በስተቀር ከላይ ላሉት የተገለጠ ምስጢር ከሥር ላሉትም ተገልጦላቸዋል፡፡ ይሁዳን ‹‹ያእትትዋ ለኃጥእ ከመ ኢይርአይ ስብሓተ እግዚአብሔር›› (የእግዚአብሔርን ክብር እንዳያይ ኃጢአተኛው ያስወግዱታል፡፡) [ኢሳ.26:10] እንዲል ኋላ የሚሠራት ኃጢአት ይህን ምስጢር እንዳያይ አድርጋዋለች ምስጢር የማይገልጥለት ከሆነ ከሌሎች ሐዋርያት ጋር አብሮ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ቢሉ ከእነርሱ ቢለየኝ በሞቱ ገባሁበት ብሎ ምክንያት እንዳያገኝ ነው፡፡ ♰ → መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ፊቱም ከፀሓይ ይልቅ አበራ፤ ልብሱም ልብስ አጣቢ ከሚያነጻው ይልቅ እንደ በረድ ፀዓዳ ሆነ፡፡ ‹‹ እነሆ ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው›› ቅዱስ ጴጥሮስም ጌታን ‹‹ አቤቱ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ ሦስት ቤቶችን በዚህ እንሥራ፤ አንዱን ለአንተ÷ አንዱንም ለሙሴ÷ አንዱንም ለኤልያስ አለው›› በዚህ ቃል የትህትና እና የደካማነት ምልክት አለበት፡፡ ትህትና ያልነው ቅዱስ ጴጥሮስ ለራሱና ለባልንጀሮቹ ሐዋርያት ቤት ይሠራ ዘንድ ስለ አላሰበ ነው ራሱንና ባልንጀሮቹን እንደ ባሮች፤ ነቢያትን ደግሞ እንደ ጌቶች (የጌታ ባለማሎች) አድርጎ አስቧልና፡፡ ደካማነት የተባለው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችን ከሰማይ የወረደበትን (ሰው የሆነበት) ሥራ ትቶ በተራራ ላይ ይኖር ዘንድና ራሱን የሚሰውርበትን ቤት ይሠራለት ዘንድ የተናገረው ነው፡፡ ስለዚህም ጌታችን ምድራዊ ቤት እንደማያስፈልገው ያስረዳው ዘንድ የክብሩ መገለጫ የሆነ ብሩህ ደመና መጥቶ እንደቤት ሁኖ ጋረዳቸው፡፡ ‹‹እነሆ በደመናው ውስጥም የምወደው በእርሱም ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል ቃል መጣ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው ደንግጠው በግንባራቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸው ተነሡ አትፍሩም አላቸው፡፡ ዓይናቸውንም አቅንተው ዓዩ ነገር ግን ከጌታችን ከኢየሱስ ብቻ በቀር ያዩት ማንም አልነበረም፡፡›› ከነቢያት ሁሉ ለይቶ ሙሴና ኤልያስ እንዲገለጡ ማድረጉ ስለምንድን ነው ቢሉ ሙሴ ከአምላክ ጋር 570 ጊዜ ያህል ቃል ለቃል ተነጋግሮት ነበርና ባለማልነቴ ይገለጥ ዘንድ ባይህ እወዳለው አለው፡፡ አምላክም ፊቴን ዓይቶ አንድ ሰዓት ስንኳ መቆም የሚቻለው የለም ብሎ መለሰለት ሙሴም ይህ ካልሆነማ ባለሟልህ መባሌ ምኑ ላይ ነው በቃልማ ሌሎቹንስ ታናግር የለምን ቢለው አምላክም " ድኅረሰ ትሬኢ ገጽየ " መሥዋዕት ሁኜ በምቀርብበት ጊዜ (በዘመነ ሥጋዌ) እታይሃለሁ ብሎት ነበርና ይህ እንዲፈጸም፡፡ [ዘጸ.33÷18-23]፤ ኤልያስ ስለአምላክ እጅግ በመቅናቱ ተስፋ ተሰጥቶት ነበርና፡፡ ክብሩ በተገለጠ ጊዜ ግን ሙሴ ‹‹ትኄይሰኒ መቃብርየ›› (መቃብሬ ትሻለኛለች ብሏል)፤ ኤልያስም ወደ እሳት ሠረገላው ተመልሷል፡፡ ♰ • አንድም፡- ሙሴ ኤልያስ ይሉሃል ብለውት ነበረና እግዚኣ ሙሴ ወኤልያስ መሆኑን በራሳቸው አንደበት ለማስመስከር፡፡ ♰ • አንድም፡- የሕያዋን (ሞት ያላገኛቸው) የሙታን (ሞት ያገኛቸው) አምላክ መሆኑ ለማጠየቅ ነው ከእርሱ በቀር የሙሴን መቃብር (ይሁ.ቍጥ.9)፤ ኤልያስም የተሰወረባት (ብሔረ ሕያዋንን) የሚያውቅ የለምና፡፡ ♰ • ፍጻሜው ግን፡- ደብረ ታቦር የቤተክርስቲያንና የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ እንድትሆን ነው፡፡ → ደብረ ታቦር የተመረጠበት ምክንያትና ምሳሌነቱ፡- ♰ • ደብረ ታቦር ማለት ደብር ተራራ ሲሆን ታቦር የቦታው ስም ነው ከኢያቦር ወገን የነበረ ቦር የሚባል ሰው ነበረና በሱ ስም ታቦር አሉት "ቦር" ማለት ትልቅ ማለት ሲሆን "ታ" ን ጨምረው ታቦር ብለውታል። በደብረ ታቦር ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለም ነው ቢሉ ትንቢቱ ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ ነው፡፡ ትንቢቱ ‹‹ ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ ›› [መዝ 88:12] ያለው ነው። ምነው ክብሩን የገለጠ በታቦር አይደለምን አርሞንዔምንም አነሳ ቢሉ ብርሃኑ እስከ አርሞንዔም ደርሷልና ነው፡፡ ምሳሌው ፡- በዚህ ተራራ ላይ ነቢያቱ ዲቦራ ከባርቅ ጋር በመሆን የከነዓናውያን ንጉሥና የጦር መሪ ሲሳራንና ኢያቡስን በጦርነት ድል አድርገውበታል [መሳፍንት 4:5–24] ጌታም በልበ ሐዋርያት ያደረ ሰይጣንን ድል ነሥቶበታልና፡፡ ♰ • ደብረ ታቦር የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው፡፡ በዚህ ተራራ ላይ ብሉይን የሚወክሉ ነቢያት፤ ሐዲስንም የሚወክሉ ሐዋርያት እንዲሁም ሐጋጌ ሕግ የሆነም ጌታ እንደተገኙ በእግዚአብሔር ቤትም ብሉይና ሓዲስ እንደሚነገሩ ምእመናንም በእነዚህ ሕግ እንደሚመሩ ያስረዳል፡፡ መምህር ጳውሎስም ስለዚህ ነገር ሲያስረዳ ‹‹በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋልና፤ የሕንጻው የማዕዘን ራስ ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ እርሱም ሕንጻ ሁሉ የሚያያዝበት÷ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግንብ የሚያድግበት ነው፡፡ እናነተ በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ልትሆኑ በእርሱ ታነጻችሁ፡፡›› አለ፡፡ [ኤፌ.2:20-21] ♰ • አንድም፡- የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ናት ነቢያትም ሐዋርያት አንድ ሁነው እንዲወርሷት፤ ከመዓስባን ሙሴን ከደናግላን ኤልያስን አመጣ መዓስባንና ደናግላን አንድ ሁነው እንደሚወርሷት፤ ከምዉታን ሙሴን ከሕያዋን ኤልያስ አመጣ ሁሉም በትንሣኤ እንደሚወርሷት ለማጠየቅ፡፡ → የበዓሉ መጠሪያ ስሞች (ደብረ ታቦር / ቡሄ/ ቡሔ መባሉ ስለምንድ ነው?)

Please join and share this link to anyone who you think will benefit. Thank you https://t.me/official_kesishibret

#መሠረተ_ሃይማኖት_ዘኦርቶዶክስ_ተዋህዶ በቀሲስ እዩኤል ሰሎሞን ተዘጋጅተዋል። ነገ በአርጋኖን መጻሕፍት መደብር ይከፋፈላል። #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግ
+2
#መሠረተ_ሃይማኖት_ዘኦርቶዶክስ_ተዋህዶ በቀሲስ እዩኤል ሰሎሞን ተዘጋጅተዋል። ነገ በአርጋኖን መጻሕፍት መደብር ይከፋፈላል። #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0925421700_ይውሰዱ!

«[ማርያም ሆይ] አንቺ ምሥራቅ ነሽ፤ ልጅሽ ደግሞ የጽድቅ ፀሐይ ነው።» ​ለዘመናት በድንግልናዋ ክብር፣ በንጽህናዋ ልዕልናና በመለኮታዊ ማደሪያነቷ ተደንቆ የማይጠገበው የሰማይና የምድር ድንቅ ምሥጢር ይህ ነው። እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ፣ የብርሃን መውጫ በር፣ የሰማያዊቱ ርስት መተላለፊያ ምሥራቅ ናት። ከእርስዋ ማኅፀን የፈነጠቀው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የጨለማውን ዘመን ገፎ፣ የሞትን አገዛዝ ሰብሮ ሕይወትን የሰጠ የባሕርይ አምላክ የጽድቅ ፀሐይ ነው። ​ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን (እንደ ቅዱስ ያሬድ፣ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩክ፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እና አባ ሔርያቆስ) ይህንን ቃል ሲያብራሩት፤ ምሥራቅ ፀሐይን ስትወልድ ተከፍታና ቆስላ አትወጣም፤ ፀሐይም ከምሥራቅ ስትወጣ ምሥራቁን አታጎድፈውም፣ ውብ መልኩን አታጠፋውም። እንዲሁም መለኮት በድንግል ማርያም ማኅፀን ሲያድር የድንግልናዋ ማኅተም ከቶ አልተለወጠም፤ ድንግልናዋ እንደታተመ ኖረ እንጂ። ​ሙሴ በሲና ተራራ ያያት እሳት ያልቃጠላት የሰንሰል ሐመልማል ምሳሌ እርስዋ ናት፤ መለኮታዊውን እሳት በማኅፀኗ ተሸክማ ሳትቃጠል፣ መለኮትም ከእርስዋ ሰው ሆኖ ተወልዶ ለዓለም የዘላለም ሕይወትን አብርቷል። ይህችውም ድንግል መለኮታዊ ፀሐይ የታቀፈባት ሕያዊት ሰማይ ናትና፤ ይህ ጥልቅ፣ የረቀቀና አዕምሮ የማይመረምረው መለኮታዊ ምሥጢር በልቦናችን ታትሞ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ በሰማያዊ ዝማሬና በአንደበት ምስጋና እስከ ዘላለም ይኖራል። ቀሲስ ኢዩኤል ሰሎሞን

የዕንቁ መዋዕል፡ የድንግል ማርያም የፍልሰታ ጾም ማኅተም እና የልብ ሱባኤ ​ሰላም ለኪ እግዝእትነ ወመድኃኒትነ ማርያም! ​ወገኖቼ ሆይ፤ እንሆ ሰማያዊው መዐዛ የሚረጭባት፣ መላእክት በግርማ የሚከቡባት፣ የምድር ሰዎች ደግሞ ከሐዘን ወደ ሐሴት የሚሸጋገሩባት ቅድስተ ቅዱሳን የዕንቁ ወራት—የእመቤታችን የድንግል ማርያም የፍልሰታ ጾም ደርሳለች። ሐዋርያት በዕለተ ዕረፍቷ ጊዜ ሐዘንና ልቅሶን ችለው፣ መዐዛውን ተቀብለው፣ የተቀደሰችውን ሥጋዋን በገነት መካነ ዕረፍት በክብር ከደብረ ዘይት አግኝተው መልሰው በጌቴሴማኒ ዳግም የቀበሩበትና የልጇን ትንሣኤ ምሳሌ ያዩበት ያ ምስጢረ ፍልሰታ ዛሬም በኛ ሕይወት እየታደሰ ይገኛል። ​ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ “የብርሃን አጽራር” እያለ እንዳመሰገናት፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጸሐፈ ሰዓታት እንዳሰማው፣ ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሱሩግ በግጥም ሐመልማለ ጽጌ እያለ እንዳነጻጸራት፣ እንዲሁም አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው “እመቤታችን ሆይ፤ ከሰማያት በላይ የረቀቅሽ፣ ከኪሩቤል የከበርሽ አንቺ ነሽ” እያለ እንዳቀረበው ምስጋና፣ የዚህች እመቤት ጾም የሰማይና የምድር መገናኛ ድልድይ ነው። ​፩. የሕዋሳት ሰንሰለት ሲፈታ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን አስቦ)፦ ​ጾም ከሆድ ዕቃ ጥጋብ መከልከል ብቻ አይደለም፤ ሐዋርያውና ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚያስተምረን ጾም የጠቅላላው ሰውነት መንጻት ነው። • ​ዐይናችን ከንቱ ዓለማዊ መጫወቻዎችን ከመመልከት ታቅቦ፣ የእግዚአብሔርን ተአምራትና የተቸገሩ ወንድሞቹን እየተመለከተ ወደ ሰማይ ከፍ እንዲል፣ • ​ጆሯችን ከሐሜት፣ ከክፉ ወሬና ከከንቱ ነገሮች ራቁቱን ቀርቶ የምስራች ቃላትን እና የእግዚአብሔርን ቃል ብቻ እንዲሰማ፣ • ​እግራችን ወደ በጎ መድረኮች እንጂ ወደ ጥፋት ጎዳና እንዳይቸኩል፣ በንጹህ አቋም መገደድ አለበት። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዜማው እንደሚያሰማው፣ መላእክት የሚሰግዱላት ንጽህት እመቤት ስትታሰብ ሕዋሳቶቻችን በቅድስና ሊቀደሱ ይገነው። ​፪. የንስሐ ሐመልማልና የልብ መታደስ (የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሐዋርያዊ ጥሪ)፦ ​በዚህ በረከቱ እጅግ በረቀቀ ወራት፣ ከፈጣሪ ጋር ያለንን ግንኙነት በጥልቀት እንመርምር። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር እንደመከረን፣ ንስሐ የሰማይ መዝገብ መክፈቻ ቁልፍ ናት። ቆሻሻን ይዞ ንጹህ ንብረት እንዳይቀመጥ፣ የሕይወታችንን ቍስል ለሐኪሙ ለክርስቶስና ለንስሐ አባታችን በመግለጥ ከእመቤታችን አማላጅነት በታች እንበርከክ። የፍልሰታ ጾም የዕርቅ፣ የሰላም እና የድንግል እናት አፍንጫ የምትሸጥበት የይቅርታ አውደ ምህረት ነው። ​፫. ሰማያዊው ሰልፍ፡ ቅዳሴና የሊቃውንቱ መዐዛ (የቅዱስ ያሬድ ዜማ)፦ ​ቅዳሴ በምድር ላይ ያለ ሰማያዊ አገልግሎት ነው። በቅዱስ ያሬድ ዜማ ድምፅ፣ “ኪሩቤል ይሰግዱ ለኪ፣ ወሱራፌል ይትኤአዩ ለኪ” (ኪሩቤል ይሰግዱልሻል፣ ሱራፌልም በአክብሮት ይመለከቱሻል) እየተባለ የውዳሴ ማሕሌት ሲቆም፣ እኛም በዚያ ሰማያዊ ማዕድ እንገኛለን። ዕለት ዕለት የሚተረጎመውን የእመቤታችንን ውዳሴዋን፣ የሊቃውንቱን መጻሕፍት ትርጓሜ መስማት መንፈሳችንን ከማልማቱም በላይ፣ የድንግልን ስደት እና ሐዘን አስበን ከእርሷ ጋር እንድንባትን ያደርገናል። ​፬. የመንፈስ ርቀትና የንባብ ብርሃን (በቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ጥበብ)፦ ​አእምሮአችን ከዓለማዊ ጩኸት ርቆ ጸጥ ባለበት በዚህ ሰዓት፣ ከነገረ ማርያም ጋር የተያያዙ ውብ መጻሕፍትን እንክፈት። የቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ድርሰቶች፣ የውዳሴ ማርያም ጥልቅ ምሥጢራት ሲነበቡ የልብ መጋረጃ ተገልጦ የብርሃን ጸዳል ይፈስበታል። ንባብ የነፍስ ምግብ ነውና ቃሉን እናጥናው፤ በዕለታት የሚነገሩትን መጻሕፍትም ልብ ብሎ ማስተዋል ትልቅ ማስተዋልን ያስጨብጣል። ​፭. የሐዋርያት ሐዘን የተለወጠበት መዐዛ (የፍልሰታው ጥልቅ ምስጢር)፦ ​ሐዋርያት የእመቤታችንን ዕረፍት ሰምተው በሰንሰለታማ ሐዘን ተውጠው ሳለ፣ ጾሙን በመያዛቸውና ጸሎታቸውን ወደ ሰማይ በማሳረጋቸው ብቻ ከዕንባ ወደ ሐሴት ተሸጋገሩ። ቅዱስ ዮሐንስ የእናቱን ሥጋ በክንፈ መላእክት ታጅቦ ሲወጣና መዐዛው ሲረጭ ዐይቷልና፤ ሐዋርያትም ዮሐንስ የያዘውን የእመቤታችንን ንጹሕ ሥጋ ከገነት መልሰው አግኝተው በጌቴሴማኒ ሲቀብሩት ልባቸው በሰማያዊ ሰላም ተሞልቷል። እኛም ዛሬ ይህንን ጾም ስንጾም፣ የሐዋርያትን ያንን የድል አክሊል እና የሰማይ መዐዛ በመንፈስ እየተካፈልን፣ ከፍጥረታት ሁሉ በላይ የከበረችውን እናት ርኅራኄ በልባችን እንጨብጣለን። ​፮. የሕይወት ሰንሰለት፡ የቅዱስ ቊርባኑ ማኅተም (በአባ ሕርያቆስ ቅዳሴ)፦ ​ጾሙ፣ ጸሎቱ፣ ስግደቱ ሁሉ ማረፊያው ወደ ሕያው ቅዱስ ቊርባን ሲደርስ ነው። አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው “እመቤታችን ሆይ፤ ሕብስት የምትባል የሕይወት እንጀራ ከሥጋሽ ተገኘች” ብሎ እንዳመሰገነው፣ እኛም ንስሐ ገብተን፣ ቀኖናችንን ፈጽመን፣ የክርስቶስን ሥጋና ደም በመቀበል ይህንን ጾም የድል አክሊል እናድርገው። ያለ ቅዱስ ቊርባን የሚደረግ ጾም ፍሬው አይሞላምምና ማኅተሙን በንጹሕ ሕሊና እንቀበል። ​ወገኖቼ! ይህንን የፍልሰታ ጾም እንደ ተራ ልማድ ሳይሆን፣ እንደ ሕይወት መለወጫ ዕድል እንያዘው። እመቤታችን ድንግል ማርያም የልመናችንን ቃላት ወደ ልጇ ዙፋን አሳርጋ፣ የዕንባችንን ጥያቄ በምልጃዋ መልሰህ የምንልበት ጸጋ ይብዛልን። ​ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የዚህ በረከት ተካፋይ ያድርጓቸው! ቀሲስ ኢዩኤል ሰሎሞን ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም

✞ የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፣ ያድናቸውማል [መዝ 33፥7]. ቅዱስ ቂርቆስ (በእንግሊዘኛ :Cyricus) (በአራማይክ : ܡܪܝ ܩܘܪܝܩܘܣ ܣܗܕܐ‎ Mar Quriaqos Sahada ፤ በተጨማሪ Quiricus Cyriacus Quiriac) ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው። አባቱ ቆዝሞስ ይባላል። እናቱ ቅድስት እያሉጣ (በእንግሊዘኛ : Julitta) (በግሪክ: ουλίττα) (በአራማይክ ܝܘܠܝܛܐ‎, : Yolitha) በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች። እኒህ ኹለት ሰማዕታት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናቸው። በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል ተርከውታል፡፡ እንኩዋን አደረሳችሁ!

የምስጢረ ሥጋዌ እና የቅድስት ድንግል ማርያም «በዓተ» እና «በዓታ»፡ የነገረ መለኮት ጥልቀት ​በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ትርጓሜ መሠረት፣ «በዓተ» እና «በዓታ» የሚሉት ቃላት የክርስትና እምነት መሰረት የኾኑትን ታላላቅ ምስጢራት ይገልጣሉ። እነዚህ ቃላት በግእዝ ቋንቋ «መግባት» የሚለውን ትርጉም ቢይዙም፣ በነገረ መለኮት አውድ ግን እንደ ውቅያኖስ ጥልቅ ምስጢር አላቸው። ​፩. «በዓተ» (የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋዌ) ​«በዓተ» (Bae’a) ማለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የባሕርይ አምላክ ሆኖ ሳለ፣ የሰውነትን ባሕርይ (ሥጋንና ነፍስን) ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ነሥቶ በሰውነት ውስጥ መገለጡ ነው። • ​የሊቃውንቱ ትንታኔ፦ አበው «በዓተ» ሲሉ እንደ ሰው ወደ አንድ ክፍል መግባት አያስተምሩም። ይልቁን «መለኮት በሥጋዊ ባሕርያችን መገለጥ» ብለው ይተረጉሙታል። ◦ ​እንደ እሳትና ብረት፦ ጌታ በድንግል ማሕፀን ሲገባ (በዓተ)፣ ብረቱ እሳቱን እንደሚዋሐድ፣ እሳቱም ብረቱን እንደሚቀድስ፣ የድንግልን ማኅተመ ድንግልና ሳይለውጥ በምስጢር ገባ። ◦ ​የባሕርይ አንድነት፦ ይህ መግባት «ተዋሕዶ» ይባላል። መለኮት ትስብእትን፣ ትስብእትም መለኮትን ተዋሕዶ በአንድ አካል መገኘታቸው የ«በዓተ» ምስጢር ቁልፍ ነው። • ​መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ «ቃልም ሥጋ ሆነ፥ በእኛም አደረ (በግእዙ፦ ወበዓተ ማእከሌነ)፤ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሚሆን ክብርን አየን፤ ጸጋንና እውነትንም ተሞልቶ ነበር።» (ዮሐንስ 1፡14)። ◦ ​ትርጓሜ፦ እዚህ ላይ «በዓተ» መባሉ፣ መለኮት በሰውነት ውስጥ መኖሪያውን እንደመሰረተ ያመለክታል። ​፪. «በዓታ» (የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቤተ መቅደስ መግባት) ​«በዓታ» (Be’ata) የሚያመለክተው እመቤታችን በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ምስጢራዊ ጉዞ ነው። • ​የሊቃውንቱ ትንታኔ፦ እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ ስትገባ (በዓታ)፣ «ለሕያው አምላክ ማደሪያ» ለመሆን ራሷን አዘጋጀች። ሊቃውንቱ «እርሷ በዓታ (ስታደርግ)፣ የቤተ መቅደሱ ጌታም ወደ እርሷ በዓተ (ሊገባ) ተዘጋጀ» ይላሉ። ◦ ​መስተጋብሩ፦ እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ በገባች ጊዜ (በዓታ)፣ ራሷ ቤተ መቅደስ ሆነች። በውስጧም የዓለሙ ሁሉ ፈጣሪ ገባ (በዓተ)። ይህ የኹለቱ ቃላት መስተጋብር ነው የነገረ ማርያም የልብ ምት። • ​መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ «አንቺ ልጅ ሆይ፥ ስሚ እይ ጆሮሽንም አዘንብዪ፥ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።» (መዝሙረ ዳዊት 44፡10-11)። ◦ ​ትርጓሜ፦ ሊቃውንቱ «ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ» የሚለውን፣ እመቤታችን ምድራዊውን ቤቷን ትታ ወደ ቤተ መቅደስ በዓታ (መግባት) ያደረገችበትን ምስጢር ይገልጻሉ ይላሉ። ​፫. የቋንቋ ትክክለኛነት፡ ለምን «በዓተ» እና «በዓታ» ተለያዩ? • ​የ«በዓተ» ረቂቅነት፦ በዓተ (በ አ ዐ ተ) ሲባል፣ የአይኑ (ዐ) መኖር በውስጡ «የመለኮትን መደበቅ» ያመለክታል። አምላክ ክብሩን በሥጋ ውስጥ ደበቀ። «በዓተ» ማለት «ምስጢሩን በውስጡ አዝሎ መግባት» ማለት ነው። • ​የ«በዓታ» ግልጽነት፦ በዓታ (በ አ ተ) ሲባል፣ ወደ ተቀደሰ ሥፍራ የሚደረግ «ምድራዊ የቅድስና ጉዞ» ነው። እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ የገባችው ለራሷና ለዓለሙ ሁሉ «መቅደስ ሆና ለመገኘት» ነው። • ​የመደምደሚያው ማሳሰቢያ፦ «በዓተ» የፈጣሪ ወደ ፍጥረት የሚደረግ «መውረድ» ሲሆን፣ «በዓታ» የፍጥረት ወደ ፈጣሪ የሚደረግ «መውጣት/መቅረብ» ነው። ​፬. የጊዜ፣ የታሪክ እና የነገረ ማርያም አውራነት • ​የጊዜ ምስጢር፦ ጌታ በዓተ (ሲገባ)፣ ጊዜንና ዘመንን ፈጣሪ ስለሆነ፣ በጊዜ ውስጥ መታሰር ሳይሆን «ጊዜን ወደ ራሱ አቅፎ መለወጡ» ነው። • ​የነገረ ማርያም እና የነገረ ክርስቶስ ውህደት፦ እመቤታችን «በዓታ» ባታደርግ ኖሮ፣ ለጌታ መቅደስ አልተገኘም ነበር፤ ጌታ «በዓተ» ባያደርግ ኖሮ፣ መቅደሱ ባዶ በሆነ ነበር። ስለዚህ «በዓታ» ያለ «በዓተ» ታሪክ የለበትም፤ «በዓተ» ያለ «በዓታ» መግቢያ የለበትም። ​፭. የሊቃውንት አስተምህሮ • ​ቅዱስ ያሬድ፦ በዜማው «መለኮት ሥጋን ለበሰ፣ ሥጋም መለኮትን ተዋሐደ» ሲል የ«በዓተ»ን ምስጢር ያበራል። • ​ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ፦ «በዓተ ማለት የእግዚአብሔር ቃል በሰውነት ውስጥ መኖሪያውን መመሥረት ነው።» • ​አባ ባሕሪ፦ ቃላትን በምስጢር መነጽር በመመልከት፣ በዓተን ለጌታ፣ በዓታን ለእመቤታችን በመለየት የሥነ-ጽሑፍ ግርማን ይገልጣሉ። ​፮. ዋቢ መጻሕፍት (የማይሻር ማስረጃ) 1. ​መጽሐፍ ቅዱስ (81ዱ): ዮሐንስ 1፡14, መዝሙረ ዳዊት 44፡10, ሕዝቅኤል 44፡2። 2. ​መጽሐፈ ቅዳሴ (ቅዳሴ ማርያም): «በዓተ ውስተ ማኅፀና ወአልቦ መለወጥ»። 3. ​ድርሳነ ማርያም (ዘሰኔ ጎልጎታ): የኹለቱን ቃላት ምስጢር አጣምሮ የሚተነትን። 4. ​ሃይማኖተ አበው: የሥጋዌ ዶግማ መሠረት። 5. ​መጽሐፈ ፊልክስዮስ: ስለ ሥጋዌ ምስጢር የቃላት ትንታኔ። 6. ​ገድለ ማርያም: የእመቤታችን የቤተ መቅደስ መግባት (በዓታ) ታሪክና ትርጓሜ። 7. ​የሊቃውንት መዝገበ ቃላት (ግእዝ): «በዓተ» (ለፈጣሪ), «በዓታ» (ለቅዱሳን)። ​፯. ማጠቃለያ (አምስቱ አጥራራ) 1. ​የድነት ድልድይ፦ «በዓታ» ለፈጣሪ ማደሪያነት መዘጋጀት፣ «በዓተ» የፈጣሪ መገለጥ ነው። 2. ​የሥጋዌ ጥልቀት፦ ጌታ በድንግል ማርያም ማኅፀን መግባቱ የዘለዓለም ሕይወት መክፈቻ በር ነው። 3. ​የድንግልና ማኅተም፦ ጌታ በ«በዓተ» ምስጢር የድንግል ማርያምን ማኅተመ ድንግልና ሳይለውጥ ገባ። 4. ​የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፦ ከቅዳሴ እስከ ድርሳን፣ ይህ ትምህርት የክርስትና እምነት አምድ ነው። 5. ​የመንፈሳዊ አንድነት፦ መግባት (በዓተ/በዓታ) የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር የተገናኘበት፣ የሰማይና የምድር ድልድይ ነው። ​መደምደሚያ፡ «በዓታ» የቅድስና ጉዞ፣ «በዓተ» የድነት ኃይል ነው። ክርስቶስ በሥጋዊ ባሕርያችን ውስጥ «በዓተ» (ገባ)፤ በዚህም እኛን ወደ ክብር አወጣን። ይህ ምስጢር የሰው ልጅ ከፈጣሪ ጋር የተገናኘበት ረቂቅ የነገረ መለኮት ባሕር ወጀብ ነው። በቀሲስ ኢዩኤል ሰሎሞን ዘደብረ ብሥራት ሐምሌ 5/2018ዓ.ም ​#ተዋሕዶ #በዓተ #በዓታ #ምስጢረሥጋዌ #ኦርቶዶክስ #የሊቃውንትትርጓሜ