cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አንቀጸ ብጹዓን ሰንበት ትምሕርት ቤት አባላት ሕብረት

ይሕ ቻናል በሰንበት ትምሕርት ቤቱ ጽ/ቤት እውቅና ያለው ለትምሕርት የተዘጋጀ ነው

Show more
Advertising posts
244
Subscribers
No data24 hours
-17 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailable
ምዝገባ ተጀምሯል‼ አንቀጸ ብጹዓን ሰንበት ትምህርት ቤታችን የክረምት መንፈሳዊ  የተከታታይ ትምህርት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እናበሥራለን! መሰረታዊ የቤተክርቲያናችንን ትምህርቶች በዘርፉ ልምድን ባካበቱ መምህራኖቻችን ይማሩ ዘንድ ግብዣችን ነው። የምዝገባ ቀን ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከ11:00— 1:00 እሁድ ሙሉ ቀን የምዝገባ ቦታ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት  በቤተ አብርሐም ክፍል በሰንበት ትምህርት ቤቱ ልማት ሱቅ ትምህርቱ የሚሰጥበት ቀን በሳምንት ሦስት ቀን ከ12:00— 1:30 ትምህርቱ የሚጀምርበት ቀን ሰኔ 14/2016 ዓም ለበለጠ መረጃ +251954905316 +251940191952 +251919827915 በመደወል መጠየቅ ይቻላል! መሰረታዊ የሃይማኖት ትምህርቶችን እንማር!!
Show all...
እነሆ የጌታን   ትንሣኤ  ካየን ዛሬ  ፵ኛ  ቀን ተቆጠረ ፤ ዕርገቱም  ደረሰ ወደ ደብረ ዘይት እንድንወጣ  ዓይኖቻችንም  የእርሱን  ከፍታ  የእርሱን  ፍቅር  ብቻ  እንዲመለከቱ  ይሁንልን ለጆሮዎቻችንም ' ወደ ሰማይ ሲሔድ እንዳያችሁት፤ እንዲሁ ይመጣል' የሚለውን  ቃሉን   ' እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ኹልጊዜ ከእናንተ  ጋር ነኝ ' የሚለውን  ከዓለም ጭካኔ  ከሚደርስብን  እንግልት  ሁሉ  የምንጠለልበትን  የምንጠጋበትን  ህያው  ቃሉን  መስማትን  ይሁንልን! ለልቡናችንም  በአመጽ  እንኳን  የሻትነውን  አምላክነት  በፍቅር በትህትና  ዝቅ  ብሎ  የተጣለውን  ሥጋችንን  ከፍ ከፍ እንዳደረገ  ለአፍታም  ባለመዘንጋት  ማሰብን ፤ ሰማያዊውን  ብቻ  በማስብ  ልቡናችንን  ከፍ ከፍ  ማድረገን  ይሁንልን! በ'እኛ'ነታችን  መስታወት  በህይወታችን  በኑሯችን  በጉዟችን  ሁሉ 'እርሱን  መምሰልን' ፣ በእርሱ  መኖርን ፣ ለእርሱ መኖርን  ያድርግልን! ከዚህ  በኋላ  መነጠልም  ቢሆን  መለየትም  ቢሆን  በሌለበት  ፍጹም  ተዋህዶ  በፍቅሩ  ተሳታፊ  አድርጎናልና  ከእርሱ የሚለይ  እንግዳ  ትምህርትም  ሃሳብም  አይሁንልን! 'ዓለምን  ከፈጠረበት ፡ ያዳነበት ጥበቡ  ይበልጣል' እንዳሉ  አባቶቻችን  እስከ  ዘለዓለም  ድንቅ በሆነው  በአምላካችን ሥራ  በተደሞ   መኖርን  ይሁንልን! ደግሞም  በተወደደው  መቅደሱ  እንዳስተማሩን 'እስከ  መጨረሻው  ህቅታ  ልዩ  ሦስትነቱን  ማመንን  ይፈጽምልን'! መዝ ፵፮÷፭ ' አምላክ በእልልታ ፣ እግዚአብሔር  በመለከት ድምጽ ዐረገ' አምላክ  ሰው  ሆነ ፤ ሰው  አምላክ ሆነ ! 'ስላደረገልን ሁሉ  ለእግዚአብሔር  ምንን  እንመልሳለን ?! ' በዓለ  ዕረገቱ  ለእግዚእነ  ወአምላክነ  ወመድኃኒነ  ኢየሱስ  ክርስቶስ                                          መልካም በዓል!
Show all...
Photo unavailable
ምዝገባ ተጀምሯል‼ አንቀጸ ብጹዓን ሰንበት ትምህርት ቤታችን የክረምት መንፈሳዊ  የተከታታይ ትምህርት ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እናበሥራለን! መሰረታዊ የቤተክርቲያናችንን ትምህርቶች በዘርፉ ልምድን ባካበቱ መምህራኖቻችን ይማሩ ዘንድ ግብዣችን ነው። የምዝገባ ቀን ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከ11:00— 1:00 እሁድ ሙሉ ቀን የምዝገባ ቦታ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት  በቤተ አብርሐም ክፍል በሰንበት ትምህርት ቤቱ ልማት ሱቅ ትምህርቱ የሚሰጥበት ቀን በሳምንት ሦስት ቀን ከ12:00— 1:30 ትምህርቱ የሚጀምርበት ቀን ሰኔ 14/2016 ዓም ለበለጠ መረጃ +251954905316 +251940191952 +251919827915 በመደወል መጠየቅ ይቻላል! መሰረታዊ የሃይማኖት ትምህርቶችን እንማር!!
Show all...
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ የምልዓተ ጉባኤ መግለጫ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱሳን አበው ሐዋርያት ትውፊት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በርካታ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ውይይት ሲያካሄድ ሰንብቷል፡፡ ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚሁ መሠረት፡- 1.በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤ 2.በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን ያቀርባል፤    3.በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያናችን ይዞታዎች የከተማ አስተዳደሩ ምትክ ቦታ በመስጠትና ቤተ ክርስቲያናችን ወደ መልሶ ማልማት እንድትገባ ድጋፍ በማድረግ፤ በተለይም ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በፈረሰው የጽርሐ ምኒልክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃ ምትክ በከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጭ ተጨማሪ ምድር ቤትና የቦታ ስፋት ያለው B+G+4 ሕንፃ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል በመግባትና የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ኃላፊ አባቶች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ እንዲጣል ማድርጋቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ከምስጋና ጋር የተቀበለው ሲሆን በተሰጠን ምትክ ቦታ ላይም የከተማው ፕላን በሚፈቅደው መሠረት የመልሶ ማልማት ሥራው እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 4.የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ መረዳት እንደሚቻለው ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው እናት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ 5.የብፁዓን አባቶች የዝውውርና የአህጉረ ስብከት ሥያሜን አስምልክቶ የቀረቡ ጥያቄዎችን ምልዐተ ጉበኤው ተመልክቶ ተገቢውን ውሳኔ አሳልፏል፤ 6.የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በረቂቅ አዋጁ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ያመነባቸውን የማሻሻያ ሐሳቦች በማዘጋጀት ለሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም እንዲላክና ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተሰጡት የማሻሻያ ሐሳቦች በረቂቁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ 7.በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑ ቢታወቅም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተከሰቱትን ወቅታዊ ችግሮች አስመልክቶ እየተላለፉ ያሉ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ መልእክቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸውና በጥብቅ የሚቃወማቸው መሆኑን እየገለጸ ወደፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ለማድረግ ይቻል ዘንድ ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ 8.ግብረ ሰዶማዊነትና የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ እያወገዘ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና የግብረ ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ 9.በደቡብ የሀገራችን ክፍል የቤተ ክርስቲያኒቱን አብነት ትምህርት ከማስፋፋትና ከፍ ያለ መዐርግ ከመስጠት አንፃር የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዝጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት ማስመስከሪያ ትምህርት ቤት እንዲሆን በቀረበው ጥናት መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ለምሥክር ጉባኤ ቤቱ ዕውቅና በመስጠት ወደ ትግበራ እንዲገባ ወስኗል፡፡ 10.ከሀገራችን ውጭ ባሉ አህጉረ ሰብከት መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚላኩ አገልጋዮች በክፍሉ ሊቀጳጳስ ሲጠየቅ በሙያ ብቃታቸው፣ በምግባራቸውና በመንፈሳዊነታቸው የተመሰከረላቸው አገልጋዮች ከሁሉም አህጉረ ስብከት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አቅራቢነት በውድድር እየተለዩ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 11.የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚሁም መሠረት ለአፈጻጸሙ ያመች ዘንድ በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን መዋቅራዊ አደረጃጀት በማጽደቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 12.በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ2017 ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡  በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት ፳፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
Show all...