en
Feedback
EBC Ethics Department

EBC Ethics Department

Open in Telegram

Integrity is our currency to fight corruption

Show more
351
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+6630 days
Posts Archive
የማይሰራ አይብላ 👆!! መታሰቢያነቱ ፡- በሚሰሩ ሰዎች ስር ተሸፍነው ለሚኖሩ . . . መስራት የምትችለውን ሁሉ የምትሰራ ሰው ሁን፤ እና የቀጣሪህን እጣ ፈንታ ከአንተ ጋር በማያያዝ ሊያስወግዱህ እንዳይችሉ አድርጋቸው። ነገር በምሳሌ 1 ሁልጊዜ ሸክም የሚጫንባቸው ሁለት ፈረሶች ነበሩ። የፊተኛው ፈረስ ሸክሙን እንደያዘ በጥሩ ሁኔታ የሚሄድ ሲሆን፣ የኋለኛው ፈረስ ግን ሰነፍ ነበር። በዚህም ምክንያት ሰዎች የኋለኛውን ፈረስ ሸክም በፊተኛው ፈረስ ላይ ደርበው ለመጫን ይገደዱ ነበር፤ የኋለኛው ፈረስም ሸክሙ ስለቀለለለት ተደስቶ፣ ፊተኛውን ፈረስ “ድከም ያለህ ነህ! የበለጠ ለመስራት በሞከርክ መጠን ብዙ ትሰቃያለህ 😜 ።” አለው። ወደሚያርፉበት ስፍራ ሲደርሱ የፈረሶቹ ባለቤት፡- “ሁሉንም ጭነቴን በአንድ ፈረስ ላይ መጫን እየቻልኩ ሁለት ፈረሶች የምቀልበው ለምንድነው ? ከዚህ ሁሉ ለአንደኛው የሚያስፈልገውን ያህል ብመግበውና ሌላኛውን ባርደው ይሻላል፤ ቢያንስ ቆዳው ይጠቅመኛል” አለ። እንዳለውም አደረገ። ይህ ካልሆነ አንድ ቀን የራስህን ለቅሶ እንድትደርስ ትገደዳለህ 😭፡፡ ሊዮ ቶልስቶይ፣ 1828-1910

photo content

• "ሙስናን ለመከላከል እና ለመቀነስ በሚደረጉ ሂደቶች ውስጥ በድርጊቱ የተዘፈቁ አካላትን አካታች ማድረግ መፍትሄው እንዳይገኝ እያደረገ ነው" - ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ • "በ2016 በጀት ዓ
• "ሙስናን ለመከላከል እና ለመቀነስ በሚደረጉ ሂደቶች ውስጥ በድርጊቱ የተዘፈቁ አካላትን አካታች ማድረግ መፍትሄው እንዳይገኝ እያደረገ ነው" - ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ • "በ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም በሙስና ሊመዘበር የነበረ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ሐብት ማዳን ተችሏል"- የፌደራል የስነምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ***************** ዜጎች በተለያዩ የመንግስት ተቋማት በሚገለገሉበት ወቅት ለሚገጥሟቸው ብልሹ አሰራሮች መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባ በተለያዩ ጊዜያት ተገልጋዮች ሲያነሱ ይስተዋላል፡፡ "አገልግሎት ለማግኘት ወደ አንድ ተቋም ስሄድ 'እጅ መንሻ' እንደምጠየቅ እርግጠኛ ሆኜ ነው የምንቀሳቀሰው" የሚሉት አቶ በቀለ አንዳርጌ (ለዚህ ዘገባ ስማቸው የተቀየረ) የተባሉ የአዲስ አበባ ነዋሪ በቅርቡ ወደ አንድ ተቋም አገልግሎት ለማግኘት በሄዱበት ወቅት የገጠማቸውን እንዲህ ያነሳሉ፡፡ አገልግሎት ለማግኘት በርካታ ሰዎች ጠዋት ጀምሮ በተቋሙ በመገኘት በወረፋ እየጠበቁ የነበረ ቢሆንም፤ ከኋላ ለመጡ እና በወረፋው ውስጥ ያልነበሩ ግለሰቦች በትውውቅ እንዲሁም ጥቅማ ጥቅም በማቀበል ሲስተናገዱ ማስተዋላቸውን ይናገራሉ፡፡ አክለውም፤አሁን ላይ አግባብ ያልሆነ ጥቅማ ጥቅም እጠየቃለሁ? ወይስ አልጠየቅም የሚለው ሳይሆን የሚያሳስበው፤ ምን ያህል እጠየቅ ይሆን? የሚለው እንደሆነ ያነሳሉ፡፡https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0vsk8k4tJ97ap29yysp3MAD6rqn8KWnP25NxXcVjqRXJFvhep1mjSuf5tHjpb4AT1l

photo content

እንኳን 1445ኛ ለዒድ አል ፊጥር በዓል አደረሳችሁ በአሉ የሰላም ፣ የጤና ፣የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን እንመኛለን። Eid Mubarek !!!
እንኳን 1445ኛ ለዒድ አል ፊጥር በዓል አደረሳችሁ በአሉ የሰላም ፣ የጤና ፣የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን እንመኛለን። Eid Mubarek !!!

በዘር፣በጉቦ፣ በወንዝ ልጅ፣ በስጋ ዝምድና፣ በሀይማኖት፣ በጓደኝነት መስፈርት በየተቋሙ ተሰብስበው ሲያበቁ ውጤት የሚባል ነገር ሲርቃቸው ሰራተኛውን ያስጨንቃሉ። የአንድ ተቋም ውጤት የሚመስለው የሰበሰ
በዘር፣በጉቦ፣ በወንዝ ልጅ፣ በስጋ ዝምድና፣ በሀይማኖት፣ በጓደኝነት መስፈርት በየተቋሙ ተሰብስበው ሲያበቁ ውጤት የሚባል ነገር ሲርቃቸው ሰራተኛውን ያስጨንቃሉ። የአንድ ተቋም ውጤት የሚመስለው የሰበሰበውን የሰው ኃይል ነው፣ በዘርና በትውውቅ አለፍ ሲልም በጉቦ የሰው ኃይል የሰበሰበ የመንግስት ተቋም በምንም ተአምር ውጤታማ ሊሆንና የህብረተሰብ ችግር ሊቀርፍ አይችልም።

የሙስና ወንጀልን በቀላሉ ይጠቁሙ! *************** በተለያዩ አካላት የሚፈጸሙትን ብልሹ አሰራሮች እና ሙስና ከመረጃ በተጨማሪ በድምጽ፣ በቪድዮ፣ በሰነድ ወይም በፎቶ የተደገፈ ማስረጃ በማካተት ጥቆማ ለማቅረብ የሚያስችል የዲጂታል አማራጭን በመጠቀም ባሉበት ቦታ ሁነው የእጅ ስልኮዎን በመጠቀም በተዘጋጀው የጥቆማ ሶፍትዌር፡- https://www.epfs.gov.et/ አሁኑኑ ይጠቁሙ።

photo content

photo content

photo content

ሙስና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጎዳ ነቀርሳ ቢሆንም ችግሩ የሚያደርሰው አደጋ በሴት እህቶቻችን ላይ ድርብርብ ነው።ሴቶች መንግስታዊ አገልግሎቶችን ፍለጋ ወደ መንግስት ተቋማት ጎራ ሲሊ ከጉቦና መ
ሙስና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጎዳ ነቀርሳ ቢሆንም ችግሩ የሚያደርሰው አደጋ በሴት እህቶቻችን ላይ ድርብርብ ነው።ሴቶች መንግስታዊ አገልግሎቶችን ፍለጋ ወደ መንግስት ተቋማት ጎራ ሲሊ ከጉቦና መማለጃ በተጨማሪ ስነምግባር ከጎደላቸው የመንግስት ባለስልጣናት ፆታዊ ትንኮሳ ይደርስባቸዋል ። ይህን ችግር ለመቀነስ ሴቶች ባሏቸው የተለያዩ አደረጃጀቶች ሊታገሉ ይገባል፣ በተጨማሪም ትውልድ በማነፁም ግንባር ቀደም ሚና መጫወት አለባቸው። ሙሰኞች የሚፈፅሙት ወንጀል ጉቦና መማለጃ ከመቀበል ባለፈ የሚያደርሱትን ፆታዊ ጥቃትንም የሚጨምር ነው። የብዙዎቻችን ትኩረት በሚያደርሰት የገንዘብ ሀብት ብክነት ላይ ሆነና በሴት እህቶቻችን ላይ የሚፈፅሙትን ፆታዊ ጥቃት ዘንግተነዋል።

ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው !! ****************************** በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በድህነት ውስጥ እንዲኖሩ ያደረገው ዋነኛው ምክንያት ሙስና ነው። የተለያዩ ጥናቶች እ
ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው !! ****************************** በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በድህነት ውስጥ እንዲኖሩ ያደረገው ዋነኛው ምክንያት ሙስና ነው። የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ ሀገራት ኢኮኖሚ ተጋላጭ ካልሆኑ ሀገራት ጋር ሲነጻጸር በአማካኝ በሳስት እጥፍ ያነሰ ነው። ይህ የሚያሳየው ሀገራት የቱንም ያክል የተትረፈረፈ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሀብት ቢኖራቸውም ሙስናን መቆጣጠር እስካልቻሉ ድረስ ህዝባቸውን ከድህነት አረንቋ ማውጣት እንደሚቸገሩ ነው። በመሆኑም ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል የጋራጠላታችን የሆነውን ሙስና ለመታገል ዝግጁ መሆን ይኖርበታል፣ መንግስትም ቢሆን የልማት ፀር የሆነውን ሙስናን ለመዋጋት ፖለቲካዊ ቁርጠኝነቱን ሊያድስ ይገባል።

ዘንድሮም 20ኛው ዓለም አቀፍ የፀረሙስና ቀን በዓለም ደረጃ ‘’Uniting the World against Corruption’’ በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን በኢትዮጵያም በዓሉ ሙስና የጋራ ጠላታችን
ዘንድሮም 20ኛው ዓለም አቀፍ የፀረሙስና ቀን በዓለም ደረጃ ‘’Uniting the World against Corruption’’ በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን በኢትዮጵያም በዓሉ ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤ በሕብረት እንታገል! በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ይህ መሪ ቃል ለበዓሉ የተመረጠበት ምክንያት ሙስና ያለልዩነት ሁሉንም ኢትዮጵያውያንን የሚጎዳ፣ ውስብስብ፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ዓለም ቀፍ ችግር መሆኑን በመገንዘብ የጋራ ጠላት የሆነውን ሙስና በጋራ መታገል በማስፈለጉ ነው፡፡ በተለይ ሚዲያ የሙስናን ምንነት፣ መንስኤውን፣ ጉዳቱንና የመከላከያ ሥልቶቹን በማስተማር ማህበረሰባችን የፀረሙስና ትግሉ አጋር እንዲሆን የማድረግ ሀላፊነት አለበት። "ሙስና ጣፋጭ መርዝ" ነው። አመራሮች እና ስራተኞች በኃላፊነትና በተጠያቂነት መንፈስ ህግን ተከትሎ በመስራት የሀገራዊ ጸረ-ሙስና ትግል አካል መሆን ይገባናል! ሙስናን መታገል ድህነትን ድል ለማድረግ የሚካሄድ ትግል አካል ተደርጎ መወሰድ አለበት፣ በምጣኔ ሀብት ልማት የቱንም ያክል ውጤታማ ስራ ቢሰራ ሙስናን/ሌብነትን መቆጣጣር እስካልተቻለ ድረስ ፍትሃዊ የሁብት ክፍፍልን እውን ማድረግም ሆነ የዜጎችን ቁሳዊ መብት ማረጋገጥ አይቻልም። መንግስት በድህነት ቅነሳ ላይ የከፈተውን ጦርነት የሚመጥን ትግል በፀረ-ሙስናም ትግል ላይ ሊደግም ይገባል ።በመሆኑም አስተማሪ ቅጣት የሌላት አገር በምንም አይነት የፀረ-ሙስና ትግሏ ስኬታማ ሊሆን አይችልም።

ለኮርፖሬሽኑ አመራሮች በሙሉ ========== ========== ሀብትን ለማሳወቅ እና ለማስመዝገብ በወጣው አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት ሀብት የማሳወቅና የማስመዝገብ ግዴታ ለተጣለባቸው የመንግስት ተሿማች ፤የሕዝብ ተመራጮች እና የኮርፖሬሽኑ አመራሮች ከሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ጋር በተያያዘ ግዴታቸውን እንዲወጡ ከኮርፖሬሽኑ የማስተባበሪያ ኃላፊ ባላይ ያላችሁ አመራሮች እና የመንግስት ተሿማች እስከ ጥቅምት 20/2016 ዓ.ም ድረስ ሀብትና የገቢ ምንጫችሁን በኮርፖሬሽኑ ስነምግባር ክፍል እንዲታሳዉቁ አሳስባለሁ፡፡ ከሠላምታ ጋር የስነምግባር ዲፓርትመንት ማሳሰቢያ ፡-  በEBC-Family እና EBC-Ethics Department በሚለው የቴሌግራም ቻናል ላይ በፒዲፍ የተለጠፈው የሀብት ምዝገባ ቅፅ Print በማድረግ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ የአስመዝጋቢ ፊርማ ይቀመጣል ፡፡  ሀብታቸውን የማያስመዘግቡ ሀብት አስመዝጋቢ አመራሮች አግባብነት ባለው የወንጀል ህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ እና ኮርፖሬሽኑም ሆነ የስነምግባር ክፍሉ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑ ያሳስባል፡፡

ህዳር 11ቀን 2016 ዓ.ም ማስታወቂያ በዲጋሚ ************************ ከዘህ በፈት ጥቅምት 02/02/2016 ዓ.ም በቴሌግራም ቻናል ላይ ለሁሉም አመራሮች ሀብትና የገቢ ምንጫችሁን እ
ህዳር 11ቀን 2016 ዓ.ም ማስታወቂያ በዲጋሚ ************************ ከዘህ በፈት ጥቅምት 02/02/2016 ዓ.ም በቴሌግራም ቻናል ላይ ለሁሉም አመራሮች ሀብትና የገቢ ምንጫችሁን እንዲታሳዉቁ ያሳወቅን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ማንኛውም የኮርፖሬሽኑ አመራር እስከ አሁን ሀብቱን እያስመዘገበ አይደለም ፡፡ ስለሆነም የጋራ ጠላታችን የሆነውን ሙስናን በህብረት በመከላከል የሀገራችን የኢኮኖሚ ልማት ዕድገትና ብልጽግና እውን እንዲሆን በተቋም ውስጥ የምንገኝ ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ አመራሮች የ20ኛውን የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን ሲናከብር እስከ ህዳር 21 ቀን 2016 ዓ/ም በአዋጅ 668/2002 መሠረት ሀብታችንን በማሳወቅና በማስመዝገብ የሙስና መከላከል ግዴታችንን በትኩረት እንወጣ

photo content

ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የወንጀል አይነቶች በሙስና ወንጀል ስር የሚወድቁ እና ክስ የሚመሰረትባቸው የሙስና ወንጀል አይነቶች ናቸው፡፡  በስልጣን አለአግባብ መገልገል፣  የመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅቶች ስራን በማይመች አኳሃን መምራት፣  አደራ የተሰጠው እቃ ያለ አግባብ ማዘዝ፣  በስራ ተግባር የሚፈፀሙ የመውሰድና የመሰወር ወንጀል፣  በስልጣን ወይም በሃላፊነት መነገድ፣  ያለ አግባብ ጉዳይን ማጓተት፣  ያለ አግባብ ፈቃድ መስጠት ወይም ማፅደቅ፣  የስራ ሚስጥርን መግለፅ፣  በሌለው ስልጣን መጠቀም፣  በግል ተሰሚነት መነገድ፣  ጉቦ መቀበል ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም መስጠት ወይም መቀበል፣  አስታራቂ ሽማግሌዎች የሚፈፅሙት ጉቦ መቀበል ወንጀል፣  በሙስና ወንጀሎች የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ስለመርዳት፣  በህገ ወጥ መንገድ ዋጋ ያለውን ነገር ያለ ክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማግኘት፣ ዋጋ ያለው ነገር ያለ በቂ ክፍያ መስጠት፣  ምንጩ ያልታወቀ ገንዘብና ንብረት ይዞ መገኘት፣  ገንዘብ ማቀባበል፣  በምርጫ ላይ የሚስጥ መደለያ፣  በከባድ አታላይነት የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች፣  በከባድ እምነት ማጉደል የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች፣  የመንግስታዊ ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት ወደ ሀሰት መለወጥ፣ ማጥፋት ወይም ጉዳት ማድረስ፣ ወይም በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ሙስና ወንጀሎች፣  ከሙስና ወንጀሎች ጋር በተያያዘ ጠቋሚ፣ ምስክር የሆኑ ሰዎች ላይ የሚደርስ ጥቃትን አስመልክቶ የሚፈጸም ወንጀል  የሙስና ወንጀሎችን ምርመራ እና ክስ ከማደናቀፍ ጋር ተያይዞ በአዋጁ ቁጥር 433/97 (አዋጅ ቁጥር 883/07 እንደተሻሻለ) የተደነገጉ ወንጀሎች፤ እና በልዩ ህጎች የሙስና ወንጀል ተብለው የተደነገጉ ጉዳዮች