EBC Ethics Department
Open in Telegram
351
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+6630 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+9
in 0 channels
November '24
+31
in 0 channels
Get PRO
October '24
+60
in 0 channels
Get PRO
September '24
+296
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 21 December | 0 | |||
| 20 December | 0 | |||
| 19 December | 0 | |||
| 18 December | +1 | |||
| 17 December | 0 | |||
| 16 December | +1 | |||
| 15 December | 0 | |||
| 14 December | 0 | |||
| 13 December | 0 | |||
| 12 December | 0 | |||
| 11 December | 0 | |||
| 10 December | 0 | |||
| 09 December | +1 | |||
| 08 December | +3 | |||
| 07 December | 0 | |||
| 06 December | 0 | |||
| 05 December | 0 | |||
| 04 December | +1 | |||
| 03 December | +1 | |||
| 02 December | 0 | |||
| 01 December | +1 |
Channel Posts
ይህ ግለሰብ በተቋም ውስጥ ሌላ አላማ እና ተልዕኮ ይዞ ለመስፈፀም እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በመረዳት ከአስተዳደራዊ የእረምት እረምጃ በተጨማሪ በወንጀል የምንጠይቅ መሆኑ ተቋሙን ማሳወቅ እንፈልጋለን
| 2 | ነብስ ይማር | 1 |
| 3 | ብሔራዊ የሙስና ወንጀል መረጃ ጥቆማ መስጫ መተግበሪያ አጠቃቀም እና በውስጡ የያዛቸው አገልግሎቶች
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የበለፀገው ብሔራዊ የሙስና ወንጀል መረጃ ጥቆማ መስጫ መተግበሪያ ባሳለፍነው ሳምንት በይፋ ወደሥራ ገብቷል።
ለመሆኑ ይህን የሙስና መረጃ ጥቆማ ሥርዓት እንዴት መጠቀም እንችላለን? ምን አይነት አገልግሎቶችንስ አካቷል?
➡️ሥርዓቱ በኮምፒዩተር ብራውዘር አማካኝነት ወይም በስልኮቻችን በመጫን በኢንተርኔት አማካኝነት መጠቀም እንድንችል ተደርጎ የበለፀገ ነው፡፡
➡️መተግበሪያውን በስልክ ለመጠቀም አፕስቶር እና ፕሌይስቶር ላይ “NCRS” ብለን በመፈለግ ማውረድ እንችላለን፡፡
➡️መተግበሪያውን ለመጠቀም በስልክ ቁጥራችን መመዝገብና የይለፍ ቃል መጠቀም ይኖርብናል፡፡
➡️ማንኛውንም አይነት የሙስና ወንጀል ጥቆማ ለመስጠትም ሚስጥራዊነቱ በተጠበቀ መልኩ በተቀመጡልን አማራጮች መሠረት ለፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መላክ ያስችለናል፡፡
➡️የሙስና ወንጀል ጥቆማዎችን በምስል፣ በጽሁፍ፣ በድምጽ፣ በቪዲዮ ወይም በሰነድ አስደግፈን መላክ ከፈለግን መተግበሪያው አማራጮች አሉት፡፡
➡️ ጥቆማ ከላክን በኋላም፥ የላክነው ጥቆማ የደረሰበትን ሂደት ለመከታተል ያስችላል፡፡
➡️ሥርዓቱ በአምስት የቋንቋ አማራጮች ጥቆማዎችን እንድንሰጥ ያስችለናል፡፡
ቋንቋዎቹም ከአገር ውስጥ አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ እና ሶማልኛ ሲሆኑ ከውጭ ደግሞ እንግሊዘኛ ቋንቋን ማካተቱን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማህበራዊ ትስስር ገፅ አስፍሯል።
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ | 1 126 |
| 4 | ቀን 20/2017 ዓ.ም
ኢቢሲ አመራሮችና ሠራተኞች
*************************
መመሪያና ህግ ማክበር የስነ-ምግባር አንዱ መለኪያ ነው!!!
ሀብታችሁን እንድታስመዘግቡ ባስተላለፍነው ጥሪ መሰረት በአግባቡ በማስመዝገብ ለላኩልን ከ60 በመቶ ያላነሰ አመራርና ሰራተኞች ናቸው፡ ሆኖም ጊዜው እየፈጠነ በመሆኑ ቀሪ አመራርና ሰራተኞች ፎርሙን በአግባቡ በመሙላት እንድትልኩልን በድጋሚ እናሳስባለን፡፡ የሀብት ምዝገባው የክልል ማሰራጫ ጣቢያ ያሉትን ሠራተኞችንም ይመለከታል | 1 735 |
| 5 | ክቡራን የሀብት ምዝገባው የተቀመጠለት ጊዜ መስከረም 30/2017 ዓ.ም almost ከ10 ቀን እያነሰ ነው ቅፁን ለመሙላት 10 ደቂቃ አይፈጅም እና ከ30 ቦኃላ whatsAAp አችን ይዘጋል ለማለት ነው ፡፡
ያልሞላችሁ ሙሉ | 1 652 |
| 6 | NB
ቅፁ የማያሻማ እና ግልፅ ነው ምክንያቱም በ word Form የተዘጋጀ ነው አሁንም አንዳንዶቻችሁ እየዘለላችሁ ነው እና በትክክል ካልተሞላ አንቀበልም ፡፡ | 638 |
| 7 | የሀብት_ምዝገባ_ቅፅ_በ2016_ዓ_ም.docx | 1 877 |
| 8 | የሀብት ምዝገባና ሌሎች መረጃ ለመግኝት https://t.me/ebcethics የቴሌግራም ሊንኩን ይቀላቀሉ!!
Telegram
EBC Ethics Department
Integrity is our currency to fight corruption | 1 631 |
| 9 | #ለኢቢሲ አመራርና ሰራተኞች በሙሉ!!
************************
ሀብትና ንብረት እንድታስመዘግቡ ባስተላለፍነው መልእክት መሰረት መረጃዎች በመላክ ለምታደርጉት ትብብር በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡ ይሁን እንጂ መሰረታዊ የሆኑ መረጃዎች ሳይሞሉ ወይም በተሳሳተ ሁኔታ ተፅፎ የምትልኩ አላችሁ፡፡ የስህተቶቹ ዋና ዋናዎቹ ለምሳሌ የባንክ አካውንት ቁጥር፣ የደሞዝ መጠን፣ የትውልድ ጊዜ፣ ፊርማ፣ የመሳሰሉትየተሞላ ባለመሆኑ ለአሰራር ተቸግረናል፡፡ በዚህ መሰረት የላካችሁትን መረጃ ጊዜ በመውሰድ በድጋሚ አይታችሁ በጥንቃቄ ተሞልቶ እንዲደርሰን በድጋሚ እናሳስባለን፡፡
ከሠላምታ ጋር | 1 558 |
| 10 | ቀን 13/01/2017 ዓ.ም
ማስታወቂያ
*************
በሀብት አስመዝጋቢው የሐብት ማሳወቂያ ቅጽ ውስጥ ተመዝግበው ያሉ መረጃዎች ሚስጥራዊነታቸው በአግባቡ ለመጠበቅ ሲባል #የኢሜል አድራሸ የላክን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የሀብት ምዝገባ መረጃ More secure ለማድረግ የሃብት ምዝገባ መረጃን በሚመለከት #Tegenu Goshime በማለት በ0912842753 በዋትስአፕ ብቻ የሚላክ ይሆናል ::
በሀብት ምዝገባ ወቅት ሊንከተላቸው የሚገቡ አንዳንድ ማሳሰቢያዎች በከፊል
1. እረሶዎን የሚገልፅ የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም የተቋምዎ የተሰጠዎትን መታወቂያ ያስገቡ፤
2. 3x4 የሆነ ፎቶ ግራፈዎን ያስገቡ፤
3. ለፈርማ የጠቀመጡ ክፍት ቦታዎች ላይ ስካን (digital signature )ወይም 2በ2 የሆነ በፎቶ መልክ ፈርማዎን ያስገቡ፤
4. ሁሉንም መረጃ ከሞሉ ቦኃላ ይህንን word ፎርማት ወደ PDF ቀይረው ካሉበት ቦታ ሆነው ከላይ በተቀመጠው #ዋትስአፕ ለስነምግባር ዲፓርትመንት ያስተላልፉ፡፡
5. #ሁሉም ሠራተኛ እና #አመራር ሀብት የማስመዝገብ ግዴታ አለባቸው ፡፡
6. ለበለጠ መረጃ በቅፁ ላይ ገፅ ገፅ 2 ላይ ያለውን ማሳሰቢያ ያንብቡ፡፡ | 1 714 |
| 11 | ቀን 9/01/2017 ዓ.ም
ክቡራን የሀብት ምዝገባ የሚመለከታችሁ ሀብት አስመዝጋቢዎች !
**********************************
የሀብት ምዝገባ የሚመለከታችሁ ሀብት አስመዝጋቢዎች ባለፈው መስከረም 7ቀን 2017 ዓ.ም ኮርፖሬሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን እንዲያስመዘግቡ ያሰወቅን መሆኑ ይታወቃል ፡፡
በመሆኑም ቅፁ ከተሞላ ቦኃላ የሚላክበት ebcdars2017@gmail.com ኢሜል የቴክኒክ ችግር ስለአጋጠመን አመራጭ መላኪያ እስከሚናሳውቅ ድረስ ከላይ በተገለፀው ኢሜል እንዳትጠቀሙ በአክብሮት እያሳወቅን ለተፈጠረው የቴክኒክ ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን ፡፡
ከሠላምታ ጋር
ሥነምግባር ዲፓርትመንት | 1 602 |
| 12 | የሀብት_ምዝገባ_ቅፅ_በ2016_ዓ_ም_የታተመ.docx | 276 |
| 13 | ከስነምግባር ዲፓርትመንት ክፍል! | 469 |
| 14 | የሀብት_ምዝገባ_ቅፅ_በ2016_ዓ_ም_የታተመ.docx | 1 579 |
| 15 | ጉዳዩ፡- የሀብት ምዝገባን ይመለከታል፡፡
የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት በመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ አመራሮች የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ሀብትና የገቢ ምንጫቸውን የሚያሳውቁና የሚያስመዘግቡ መሆኑ በግልፅ ተደንግጓል፡፡ ለ2017 በጀት አመት የሀብት ምዝገባ ሥራ በሥነምግባር ዲፓርትመንት በበጀት አመቱ ከተያዙት ዕቅድ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡
ስለሆነም ሀብት ምዝገባ የሚመለከታችሁ ሀብት አስመዝጋቢዎች (ተሹመው ወይም ተመድበው እና ተቀጥረው የሚሰሩ በኮርፖሬሽኑ ከከፍተኛ አመራሮች እስከ ማስተባበሪያ ኃላፊዎች ድረስ ሀብትና የገቢ ምንጫችሁን እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ተጠናቅቆ እንዲላክ በጥብቅ እያሳሰብን አዲሱን WORD FORM የሀብት ምዝገባ ቅፅ 18 ገፅ አባሪ አያይዘን የላክን መሆኑን እንገልፀለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ማሳሰቢያ:-
የተሞላው የሀብት ምዝገባ ቅፅ ebcdars2017@gmail.com በሚለው ኢሜል አድራሻ በኩል ለስነምግባር ዲፓርትመንት ብቻ ይላኩ፡፡
ሀብት ለመስመዘገብ ፈቃደኛ የማይሆኑ አመራሮች ላይ በሕጉና በአሠራሩ መሠረት ለሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ዲፓርትመንቱ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡ | 1 344 |
| 16 | No text... | 1 100 |
| 17 | የትኛው ደስታ ይቅደም ?
.........✍️ ካለፈው የቀጠለ
በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ የዚህን ፍልስፍና እሳቤ በጣም እንዳጎሉት የሚነገርላቸው ጄርሚ ቤንትሀም (Jeremy Bentham) እና ጆን ስቱዋርት ሚል (John Stuar Mill) ሲሆኑ ቤንትሀም ደስታን በተመለከተ በጥራት ሳይሆን በብዛት ላይ እንድናተኩር ሲመክረን በአንፃሩ ሚል "ከብዛት ይልቅ ጥራት ይቀድማል" ይለናል፡፡ እስቲ ሁለቱንም በዝርዝር እንመልከት . . .
የዩቲሊቴሪያኒዝምን ሀሳብ መጀመሪያ እንዳገኘ የሚነገርለት ጄርሚ ቤንታም "መልካም ስነምግባርን ለማሳየት ስትፈልግ በቅድሚያ ለአንተ የቀረቡልህንና ልትፈፅማቸው የምትፈልጋቸውን ተግባራት አጢን፡፡ ከዚያም ድርጊቴ እኔን ጨምሮ ምን ያህል ሰዎችን ሊያካትት ይችላል ብለህ አስብ ። ቀጥሎም በዚህ ድርጊቴ ምን ያህል ደስታን አልያም ምን ያህል ሀዘንን አተርፋለሁ የሚለውን ከግምት ውስጥ አስገባ፡፡ በስተመጨረሻም ደስታህ ከህመም በልጦ ካገኘኸው ያኔ መልካም ነገርን ሰርተሀል" ሲል ንፅፅራዊ እሳቤውን ይገልፃል፡፡ ቤንታም ይህንን ሲል ደሰታን በቁጥርና በሂሳብ ስሌት ቀመር ወስኖ እንዲያልፍ እያደረገው ነው፡፡ " አብላጫው ደስታ ለአብላጫው ቁጥር" ማለቱም ይህንኑ አያረጋገጠለት ነበር፡፡ "ለምሳሌ ማንኛውም አንተን ሊያዝናናህ የሚችል ጨዋታ (game) በመጀመሪያ ከሙዚቃ ፣ ከስዕልና ከግጥም ጋር እኩል ዋጋ አለው ነገር ግን ጥቅም ላይ ስናውለው ጨዋታው የበለጠ ደስታን ከሰጠን ዋጋውም ያንኑ ያህል ይጨምራል" ይለናል፡፡ ታዲያ እዚህ ጋር አብላጫ ደስታ የሚሰጠንን ነገር እንዴት ልናውቅ እንችላለን? ብለን መጠየቃችን አይቀሬ ነው፡፡ ቤንትሀም ለዚህ ምላሽ ሲሰጥ "አንድ ነገር አብላጫ ደስታን ልናገኝበት እንችላለን የምንለው በቅድሚያ ጥንካሬውን፣ የቱን ያህል ጊዜ መቆየቱን፣ እርግጠኛነቱን፣ ቅርበቱን፤ ሌላ ደስታን መጨመር መቻሉን፣ ከህመም ነፃ ማውጣቱን፣ አና ለምን ያህል ሰዎች ሊዳረስ መቻሉን ጠይቀን ካመዛዘንን በኋላ ነው" በማለት መስፈርቱን ይናገራል፡፡ ቤንትሀም በተጨማሪም "ምን ማድረግ እንዳለብን በማወቅና ተግባራዊ በማድረግ መካከል ከፍተኛ ልዩነት መኖሩን ልብ በሉ ምክንያቱም ይህንን ማወቅህ የሌላ ደስታ ምናልባትም ለአንተ መስዋዕትነት ሊያስከፍል አልያም ህመምን ሊያስከትል ስለሚያስችል ነው፡፡ በእርግጥም አንድ ነገር በምናደርግበት ጊዜ አራት ማዕቀቦች ሊያጋጥሙን ይችላሉ፡፡ እነዚህም ማዕቀቦች የተፈጥሮ ህግ ፣ የሰው ሰራሽ ህግ፣ ከሌሎች ሰዎች የሚመጡ አስተያየቶችና እግዚአብሄር ናቸው፡፡ እናም ድርጊታችንን ስንፈፅም ከእነዚህ አራት ነገሮች ጋር እያነፃፀርን ሊሆን ይገባል።"በማለት ሀሳቡን በዝርዝር ያስቀምጣል፡፡
ከዚህ ፈላስፋ ቀጥሎ በስራው በጣም እውቅናን ያተረፈው ጆን ስቱዋርት ሚል ሲሆን እንደሱም አገላለፅ "የጄርሚ ቤንታም ሀሳብ ደስታን ከማስተዋወቅ ጋር ሲነፃጸር ምናልባትም ትክክል ሊሆን ይችላል ግን ተግባራዊ ስናደርገው የደስታን ተቃራኒ ልናገኝበት እንችላለን" በማለት ለምሳሌ "የወሲብ ደስታ ከነፍስ ደስታ ጋር ሊነፃፀር ይችላል?" ሲል ጥያቄን ይሰነዝራል፡፡
ልክ እንደ ቤንታም ሁሉ ሚልም አብላጫ ደስታ ለአብላጫ ቁጥር በሚለው ቢያምንም ለቤንታም አብላጫ የሚለው ቃል ብዛትን ሲያመለክት ለሚል ግን ጥራት የሚለውን ይተካል፡፡ ታዲያ የደስታ ጥራት(quality) እንዴት ያለው ነው? የደስታን ጥራት መለየት የሚችለውስ ማን ነው? ብለን ብንጠይቅ "ሁለት ደስታዎች በብቃት ሊለያዩ ይችላሉ ፤ ያንን ሊናገር የሚችለው ሰው ደግሞ ሁለቱንም አይቶ ወይም በድርጊቱ ተፈትኖ ያለፈው ብቻ ነው፡፡ ስለዚህም ዓይተውት ያለፉት እነሱ ከፍተኛውንና በጣም ጥራት ያለውን ደስታ መመዘን ወይም መምረጥ ይችላሉ" ብሎ ይናገራል፡፡ እናም እንደ ሚል አባባል ከሆነ 'የጠገበ አሳማ ከመሆን ይልቅ የራበው ሶቅራጠስ መሆን ይሻላል። (better be a starved Socrates than a satisfied pig)::'
ስለዚህም "ደስታን መሻት ከግላዊ ጥቅም አንፃር ብቻ ከታየ ሀድሰን ባዶውን ይጮሀል፡፡ በመከራ ጊዜም አብዝቶ ይጣራል . . . " እንደ ዩቲሊቴሪያኒስቶች አባባል፡፡
ምንጭ ፦ ፍልስፍና | 396 |
| 18 | የትኛው ደስታ ይቅደም? የግለሠብ ወይስ የማህበረሠብ?
********************************************
አንድ ሰው መልካም ነገርን የሚያደርገው ገሀነምን በመፍራት እና ገነት ለመግባት ካለው ጉጉት ? ወይስ ግዴታ ስለሆነ ? ውጤትን አስቀድሞ አያሰበ ወይስ ዝም ብሎ? ወይስ መልካም ነገር መስራት በራሱ ደስታን ስለሚሰጥ? የሰው ልጅ ሁሌም - በእነዚህ ሁለት የተለያዩ አመለካከቶች ተጠምዶ የሚገኘው የበጎ አመለካከት አሳቤዎች (morality) ወደ ምድር ወርደው በእያንዳንዳችን የዕለት ተዕለት ክንውኖች ውስጥ ጣልቃ መግባት ሲጀምሩ ቋሚ የሆነ መገለጫ ላይኖራቸው በመቻሉ ነው፡፡ ለዚህም ነው አንዱ መልካም ብሎ ያሰበውን ሌላው መጥፎ ብሎ የሚፈርጀው፡፡ ይህም ፅሁፍ የሚያጠነጥነው ሔዶኒዝም (Hedonism) ተብሎ በሚጠራው የፍልስፍና ዘርፍ ሲሆን የዚህ ፍልስፍና ተከታይ የሆኑት ‹‹አንድ ሰው መልካም ነገር የሚያደርገው ደስታን ለማግኘት ነው፡፡ ድርጊቱም ጥሩ ወይም መጥፎ ተብሎ የሚመዘነው በውጤቱ ሲሆን ውጤቱም የደስታው ምንጭ ሊሆን ይገባል” ብለው ያምናሉ፡፡
የዚህ ፍልስፍና አራማጆች ሲቀጥሉም ‹‹ደስታ ስራህ ትክክልና መልካም መሆኑን መመዘኛ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ሰው አንድን ድርጊት ሲፈፅም ስጋውንና ነፍሱን ማስደሰት ከቻለ የሰራው ስራ ከጅምሩም መልካም አንደነበር ማረጋገጥ ይቻላል” ይሉናል። ታዲያ የዚህ ፍልስፍና አራማጆች ራሳቸው ደስታን መፈለግ (መሻትን) በተመለከተ የራስን ደስታ መሻት (egoistic hedonism) እና የህብረተሰብን ደስታ መሻት (social hedonism) በማለት በሁለት ጎራ ተከፍለው እናገኛቸዋለን፡፡ በእርግጥም እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሆኑ ሀሳቦችን በመያዝ በተለያየ ጎራ የምናገኛቸው የተቃርኖ ሀሳብ ፈላስፎች ግባቸው ደስታን ማግኘት ቢሆንም ‹‹የማን ደስታ?›› ብለን በጠየቅን ጊዜ ግን ሁለቱም የተለያየ ምላሽ ይሰጡናል፡፡
በቅድሚያ እስቲ የራስን ደስታ ብቻ መሻት (egoistic hedonism) ወይም ቅድሚያ ለራስህ ቦታ መስጠት አለብህ የሚሉንን ፈላስፎች እንመልከት፡፡ ይህንን ሀሳብ ይዘው የሚራመዱ ፈላስፎች ‹‹ሰው በቅድሚያ የራሱን ፍላጎት ማሟላት አለበት፡፡ አንድ ነገር መልካም ነው ብለን የምንናገረው በቅድሚያ የራሳችንን ደስታ ማሟላት ስንችል ብቻ ነው›› በማለት ይከራከራሉ፡፡ ቀጥሎም ደስታው የነፍስ ወይም የስጋ? ብለን ስንጠይቅ በሲሬኒሲዝም (cyrenisism) ጎራ ተሰልፈው የምናገኛቸው “ደስታማ የስጋ ነዉ!፡፡ አናም ብሉ፣ ጠጡ፣ ጨፍሩ፣ አግቡ፤ ለነገ አታስቡ . . . ነገ ምናልባትም ልትሞቱ ትችላላችሁ፡፡ በተጨማሪም የምትሰሩት ስራ ደስታችሁን እጥፍ ድርብ የሚያደርግላችሁ ሊሆን ይገባል›› በማለት “በትንሹ ልንረካ የምንችልበትንና በተቻለ አቅም ቶሎ ልናገኘው የምንችለውን ደስታ ልንፈልግ ይገባል» ብለው አበክረው ያስተምራሉ።
በአንፃሩ የኢፒኩሪያኒዝም (epicurianism) ሀሳብ አራማጆች የዚህ ዓይነት ደስታ ‹‹የአሳማ ፍልስፍና›› (pig's philosophy) ነው ይሉናል። በእርግጥ የኢፒኩሪያኒዝም አስተሳሰብ አራማጆች ደስታ የግል ሊሆን ይገባል ብለው ቢያምኑም ደስታ ሰውነትን ለማርካት ሳይሆን ለዓዕምሮ ሰላም ልንጠቀምበት እንደሚገባ አበክረው ይገልፃሉ፡፡ ሲቀጥሉም ‹‹አንድ ሰው ደስታን መሻት የሚገባው ለአጭር ጊዜ ብቻ ሳይሆን ለብዙ ጊዜ የሚቆየውን ሊሆን ይገባል፡፡ ለምሳሌ ለአንድ ሰው ወደ ጥርስ ሃኪም መሄድ በራሱ ህመም ሊሆንበት ይችላል፡፡ ግን እንደምንም ሄዶ ጥርሱን ቢታከምና ከጥርስ ህመም ነፃ ቢወጣ ለረጅም ጊዜ ሰላምን የሚያገኝበትን ዋነኛ መንገድ ተጎናፀፈ ማለት ነው፡፡ እናም ሰው ትኩረቱን መብላትና መጠጣት ላይ ካደረገና የአካሉ ጤንነት ካላሳሰበው አንድ ቀን ህመሙ ይህን የአጭር ጊዜ ደስታውን ደብዛውን ሊያጠፋበት ይችላል፡፡ በሌላ በኩል ዓዕምሮ በጭንቀትና በፍርሀት ከተሸበረ በሽተኛ መሆኑ አይቀርም፡፡ አዕምሮ ሰላም ከሌለው ሰው በትክክል ሲያስብና የዘላለም ደስታን ሊጎናፀፍ አይችልም፡፡ ስለዚህም ደስታን መሻትት ከሰውነት ጤንነትና ከዓዕምሮ ሰላም ጋር ሊስተካከል ይገባዋል " ይሉናል፡፡ እነዚህ የኢፒኩሪያኒዝም አስተሳሰብ አራማጆች ዋነኛ ግባቸው ህመምን ከማስወገድ ጋር የተያያዘ በመሆኑ ጋብቻ ፣ ቤተሰብ ፣ ፖለቲካ አልያም ጓደኝነት ከዓዕምሮ ደስታ በኋላ ሊመጡ የሚችሉ ነገሮች ናቸው ብለው ያምናሉ ። ለምን ቢባል እነዚህ ነገሮች ለጨጓራ ህመም ለአዕምሮ ጭንቀትና ለመሳሰሉ ህመሞች ሊዳርጉ ስሰሚችሉ በተቻለ አቅም ልናርቃቸውና ልናስወግዳቸው ይገባል የሚል ምላሽ አያይዘው ይሰጣሉ ፡፡
በሌላ በኩል እነዚህ ፈላስፎች ‹‹የአጭር ጊዜ ፍላጎትን ለማሟላት ከመሮጥ የሚመጣ ህመም ሊወገድ ይገባል» ይሉናል፡፡ ይህንንም ሲያብራሩ «እርግጥ ነው ዳቦና ውሀ ሰው በጣም በተራበና በተጠማ ጊዜ ከፍተኛ የደስታ ምንጭ ሊፈጥሩለት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን እህልን አብዝተን ስንወድ ቁንጣን እንዳያመጣብን ልንጠነቀቅ ደግሞ ይገባል። እናም ደስታን ለመፍጠር ብለን ለህመም ሳንዳረግ ለመጨረሻ ግባችን ልንሮጥ ይገባል፡፡ ይህ የመጨረሻው ግባችን ታዲያ ከስሜት ህዋሶቻችን የመነጨ ብሎም የስሜት ህዋሶቻችንን ብቻ ለማርካት መሆን የለበትም:: ሳያቋርጡ መጠጣት፣ መጨፈር ፣ ማመንዘር ፣ ከምግቦች ሁሉ ለቅንጦት ስጋን መምረጥ፣ ወዘተ እነዚህ ለጊዜው ደስታ ሰጥተው ... ምክንያታችንን ግን ሊያከሽፉ፣ ምርጫችንን አስተካክለን እንዳንመርጥ ሊከለክሱ፣ አስተያየታችንን ሊያጨናገሩ ስለሚችሉና ነፍሳችንንም አቆሽሸው ዘላቂ ሰላማችንን ስለሚያደፈርሱ በተቻለን አቅም ቅንጦትን ልናስወገድ ይገባናል በማለት አበክረው ይመክራሉ::
አንደ ኤጎይስቲክ ሄዶኒዝም (egoistic hedonism) ሁሉ የዩቲሊቴሪያኒዝም (utilitarianism) አስተሳሰብ አራማጆች ‹‹አንድ ሰው ስራው ትክክል መሆኑን ለማረጋገጥ የስራውን ውጤት ሊመለከት ይገባል፡ ፡ ወይም የሰራው ስራ መልካምነቱን ማረጋገጥ የሚቻለው በፍሬው ነው በሚለው ሀሳብ ቢስማሙም ‹‹አንድ ሰው ሊጨነቅ የሚገባው ለራስ ደስታ አልያም ከራስ ወዳድነት ለመነጨ ስሜት ሳይሆን ለማህበረሰቡ ( ለብዙሀን ደስታ) ነው›› በሚለው ሀሳብ ላይ ልዩነታቸው ይጀምራል፡፡ በዚህም « አብላጫው ደስታ ለአብላጫው ቁጥር›› (the greatest happiness for the greatest number) የሚል መፈክርን አንግበው ይጓዛሉ፡፡
✍️ይቀጥላል ✍️ | 332 |
| 19 | ሙስና በአደራ የተሰጠንን ህዝብን ማገልገያ ስልጣን ለግል ጥቅም ማዋል ነው ::
ሙስና በመንግስትና በህዝብ መካከል ሊኖር የሚገባውን እምነትን ይሸረሽራል፣ ዴሞክራሲን ያዳክማል፣ የኢኮኖሚ ልማትን ያደናቅፋል፣ እኩልነትን፣ ድህነትን፣ ማህበራዊ ክፍፍልን እና የአካባቢ ቀውሱን ያባብሳል። ሙሰኛውም ቢሆን ለጊዜው የገንዘብ ፍቅሩን ሊያረካ ይችላል እንጂ በዘላቂነት ነፃነቱን ተገፎ አንገቱን ደፍቶ ዘብጥያ መውረዱ አይቀርም፡፡
ሙስናን ማጋለጥ እና ሙሰኞችን ተጠያቂ ማድረግ የሚቻለው ሙስና የሚሰራበትን መንገድ እና ለሙስና በር የሚከፍቱ ስርአቶችን በመረዳት መታገል ስንችል ነው።
ሙስናን አስመልክቶ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የምትመለከቷቸውን ሊንኮች በመጫን የEBC Ethics Departmentን ቴሌግራም፦ https://t.me/ebcethics ቻናል ተቀላቀሉ። | 292 |
| 20 | No Caption , the picture speak by itself | 348 |
