ትብል ተዋሕዶ
Open in Telegram
🔊 "ለእመ ረሳእኩኪ ቤተክርስቲያን ለትርስአኒ የማንየ" ❖ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ✞ ትምህርቶችን፥ ✞ እለታዊ ዜናዎችን፥ ✞ የየዕለቱን ስንክሳር፥ ✞ ቅዱሳን ስዕላት፥ ✞ ዝክረ ቅዱሳን እና ✞ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን የሚያገኙበት ቻናል ነው። በዚህ ቦት ያገኙናል ፤ @demesetewahedo_bot
Show more521
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+2230 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '24
September '24
+9
in 0 channels
August '24
+23
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '24
+6
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 1 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '24
+7
in 0 channels
Get PRO
January '24
+19
in 0 channels
Get PRO
December '23
+6
in 0 channels
Get PRO
November '23
+46
in 0 channels
Get PRO
October '23
+61
in 0 channels
Get PRO
September '23
+9
in 0 channels
Get PRO
August '23
+5
in 0 channels
Get PRO
July '23
+13
in 0 channels
Get PRO
June '23
+3
in 0 channels
Get PRO
May '23
+7
in 0 channels
Get PRO
April '23
+25
in 0 channels
Get PRO
March '23
+12
in 0 channels
Get PRO
February '23
+49
in 0 channels
Get PRO
January '23
+93
in 0 channels
Get PRO
December '22
+47
in 0 channels
Get PRO
November '22
+91
in 0 channels
Get PRO
October '22
+50
in 0 channels
Get PRO
September '22
+12
in 0 channels
Get PRO
August '22
+40
in 0 channels
Get PRO
July '22
+12
in 0 channels
Get PRO
June '22
+10
in 0 channels
Get PRO
May '22
+21
in 0 channels
Get PRO
April '22
+40
in 0 channels
Get PRO
March '22
+244
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 20 September | 0 | |||
| 19 September | 0 | |||
| 18 September | +2 | |||
| 17 September | 0 | |||
| 16 September | 0 | |||
| 15 September | 0 | |||
| 14 September | 0 | |||
| 13 September | 0 | |||
| 12 September | 0 | |||
| 11 September | +1 | |||
| 10 September | +1 | |||
| 09 September | +1 | |||
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | +1 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | +1 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | +1 |
Channel Posts
🌹እንኳን ለጌታችንና ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🌹
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ አንድ በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ዮሐንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።
ሰላም ለጥምቀትከ በኍልቈ ክራማት ሠላሳ፥
እምዘወለደተከ ድንግል ዘኢተአምር አበሳ፥
አመ ቆምከ ዮም እግዚኦ ለዮርዳኖስ ማዕከለ ከርሣ፥
ለወድሶትከ ማዕበላቲሃ ተከውሳ፥
ወባረኩከ አናብርት ወዓሣ።
ለእርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት፣ ክብር፣ ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄| 2 | #መጽሐፍ_ቅዱስ_ንባብ
ማቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
¹⁴ ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
¹⁵ ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት።
¹⁶ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤
¹⁷ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 176 |
| 3 | ከተራ
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው 'ውኃ መከተር፣ መገደብ' ማለት ነው፡፡
የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ወደ አለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡
ድንኳን ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ጉድጓድ እየተቆፈረ ኃው እንዳይሔድ ይገደባል፡፡
'ከተረ' የሚለውን ቃል በቁሙ ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ ማለት ነው ብለው ይፈቱታል፡፡ ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው፡፡
በየሰበካው ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ ወይም በድንኳን የሚያድሩበት ወይም ሰው ሠራሽ የግድብ ውኃ የሚበጅበት ስፍራ “ባሕረ ጥምቀት”፣ “የታቦት ማደርያ” እየተባለ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል፡፡
በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260 – 1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203 – 1304 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዓተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡
ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ፡፡
ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15 ኛው ክፍለ ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1426 – 1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ ሀገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡
ይህን ታሪክ በመከተል በዐፄ ናዖድ (1486 – 1500 ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅበቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት በዐዋጅ አስነግረው ነበር፡፡
ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ከአወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ፡፡
ታቦታት ከአንድ በላይ ሆነው ወደ ከተራው ስለሚሔዱ እግዚአብሔር አምላክ ለነቢዩ ሙሴ “የታቦት መኖር ከእናንተ ጋር የመኖሬ ምልክት ነው” ዘፀ 25 – 1 እንዳለው ታቦተ ሕጉን ተሸክመው ዮርዳኖስን እንደተሸገሩ ካህናተ ኦሪት፣ ካህናቱ የማይለወጠውን ታቦተ ሕጉን በራሳቸው ተሸክመው የብሉዩን ሥርዓት ከሐዲስ ኪዳን ጋር አንድ አድርገው የሐዲስ ኪዳን መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰቡ፤ ካህናተ ሐዲስም ወደ ከተራ (ዮርዳኖስ) ይጓዛሉ፡፡ ሊቃውንቱም እንዲሁ ለበዓሉ የሚስማማውን ቃለ እግዚአብሔር እያደረሱ እንደሚያድሩ ሊቀጠበብት ሐረገ ወይን አገዘ ያስረዳሉ፡፡
ሊቀጠበብት አያይዘውም የከተራ ዕለት ጥር 10 ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ የሔደበትን ለማዘከር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ኃዳፌ ነፍስ ለጻድቃን የሚለውን ዋዜማ ይቆማሉ፡፡
የከተራ በዓል ምሳሌያት
በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድና የባሕረ ጥምቀቱ መዘጋጀት ሃይማኖታዊ ታክና ምሳሌ አለው፡፡የቃል ኪዳኑን ታቦት አክብሮ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡
ኢያሱ በሙሴ እግር ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ከዮርዳኖስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ከሁለት ይከፈልና ወራጁም ይቆም /ይከተር/ ነበር፡፡ እስራኤል ዘሥጋ ወደ ምድረ ርስት ለመግባት የዮርዳኖስን ወንዝ ሲሻገሩ፡- ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳኑን ታቦት በድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ በዙሪያው፣ ካህናቱ ደግሞ በውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አድረው በማለዳ ተሻግረዋል /ኢያሱ 3-8/፡፡
ካህናቱ የቃል ኪዳኑን ታቦተት አክብረው የወንዙን ዳርቻ በረገጡት ጊዜ እንደ ክረምት ማዕበል ይወርድ የነበረው ውኃ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ወደ ላይ ቆሟል፡፡ ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ታቦተ ጽዮንን ያከበሩት ካህናት ከወንዙ ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
ታቦታቱ በጥምቀት ዋዜማ ከመንበራቸው ወደ ጥምቀተ ባሕር መውረዳቸውና በዚያ ማደራቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በፈለገ ዮሐርዳኖስ ከማታው ጀምሮ መውረዱንና ተሰልፎ ተራውን ሲጠብቅ ማደሩን ያጠይቃል፡፡
ጌታችን የተጠመቀበት ወርኃ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናብ፣ የበረዶ ወራት ነው፡፡ ከወንዝ ዳር ያለ መጠለያ መዋልና ማደር አይቻልም፡፡ በመሆኑም ከዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ድንኳናቸውን ተክለው ያርፉ ነበር፡፡ በዚህ አንጻር ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙሪያ ድንኳኖች ዳሶች ይጣላሉ፡፡
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በተሌ በአክሱም የንግሥት ሳባ መዋኛን “ማይ ሹም” በጎንደር የዐፄ ፋሲል መዋኛን፣ በሸዋ የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ፍርድ መስጫ አደባባይን፣ አርባ አራት ታቦታት የሚያድሩበትን የሸንኮራ ሜዳን “ራቡቴ ወንዝ” በአዲስ አበባ ደግሞ ጃንሆይ ሜዳን /ጃንሜዳን/ ወዘተ ለአብሕርተ ምጥማቃት እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል፡፡ እኒህ ቦታዎች ዛሬም ድረስ ተከብረው ይገኛሉ፡፡ እኛ በዚህ ወቅት ታቦት ይዘን፣ ከወንዝ ወርደን፣ ድንኳን ተክለን በማክበራችን ይፈጸማል፡፡
ሐመር 19ኛ ዓመት ቁጥር 9 ጥር 2004 ዓ.ም
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 205 |
| 4 | 🌹እንኳን ለጌታችንና ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን! አደረሳችሁ!🌹
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዚች ቀን የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ፤ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት።
ሰላም ለልደትከ እሳተ መለኮት በላዒ፥
እምልምልምት ዕፅ እንተ ኢትውዒ፥
ስብሐተ ልደትከ ዝንቱ ኀበ ያስተርኢ፥
በወይነ ማኅሌት እንተ ይቀድሖ ገዛዒ፥
ትኩዝ ይትፌሣሕ ወሕሙም ይጥዒ።
ለእርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት፣ ክብር፣ ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ለዘላለሙ አሜን።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 270 |
| 5 | #ዝማሬ_ተዋሕዶ
እሰይ ተወለደ
እሰይ ተወለደ የአለም መድሀኒት /3/
ይኸው ተወለደ የአለም መድኃኒት/3/
ትንቢት ተናገሩ ነቢያቱ ሁሉ/3/
አምላክ ቀዳማዊ ይመጣል እያሉ/3/
- - - - -አዝ - - - - - -
ሰብአ ሰገል መጡ ሊሰግዱ በሙሉ/3/
እስራኤል ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ
- - - - - አዝ - - - - - -
ሰብአ ሰገል መጡ ይዘው እጅ መንሻ /3/
ወርቅ እጣን ከርቤውን ለማርያም እጅ መንሻ/3/
- - - - - አዝ - - - - -
ሕፃናት እንሂድ ከልደቱ ቤት/3/
ውኃው ሆኗልና ማርና ወተት/3/
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 212 |
| 6 | 🌸እንኳን ለአምላኮች አምላክ፡ ለጌቶች ጌታ ፡ ለንጉሦች ንጉሥ ለሆነው አምላካችን ለቅዱስ አማኑኤል የልደት በዓል በሰላም አደረሰን።🌸
🤲 የዚህ ታላቅ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት እነሆ 🤲
✨✨✨መልካም በዓል✨✨✨
🌸🌺🌹🌷💐🌸🌺🌹🌷💐🌸🌺
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 208 |
| 7 | 🌹እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🌹
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ አራት በዚች ዕለት ምድራዊ መልአክ የተባሉ የተመሰገነና የከበረ አዲስ ሐዋርያ አባታችን ተክለ ሃይማኖት የልደታቸው መታሰቢያ ነው።
ሰላም ለልደትከ ድኅረ ነበረት መካነ፥
ለእምከ ልባ ከመ ቃለ መልአክ አምነ፥
ተክለ ሃይማኖት በርትዕ እንተ ቀነይከ አዝማነ፥
መልአ ምድረ ትምህርትከ እምወሰን ወሰነ፥
ወሰማያተ ጽድቅከ ከደነ።
የአባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ረድኤታቸው በረከታቸው ይደርብን እንዲሁ ምላጃ ጸሎታቸው ይጠብቀን፤ ሀገራችን ሰላም ፍቅር ያድርግልን።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 283 |
| 8 | #ቅዱሳት_መካናት
እቲሣ ገዳም (የአቡነ ተክለሃይማኖት የልደት ሥፍራ)
❖ እቲሳ ገዳም (ዞረሬ /ጽላልሽ/ /ምስካየ ኅዙናን/) ክርስትናን በመላዋ ኢትዮጵያና እስከ ጎረቤት ሀገሮች መዳረሻ ድረስ በስፋት የሰበኩ ፥ ገዳማትና አድባራት የተከሉ ፤ ከዋክብት ሰማይን በብርሃናቸው እንደሚያደምቁት ፥ እንዳስጌጡት ሁሉ፤ በጽድቃቸው፥ በትሩፋታቸው ለቤተ ክርስቲያን ፋና የሆኑ፤ የ99 ቅዱሳን፥ የ566 መናንያን ቅዱሳን መፍለቂያ፤ 17 የጥንት ዋሻዎች፣ 31 አዳዲስ ዋሻዎች የሚገኙበት ነው።
❖ ይህ ታላቅ ገዳም በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው።
❖ ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት።
❖ ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)
❖ አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት ኋላም ክብር አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡
✞ ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፥
✞ ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፥
✞ ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፥
✞ ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል።
✞ ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖረውበታል።
✞ በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው።
✞ እንዲሁም ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ቦታ ነው።
ጸሎትና በረከታቸው፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 193 |
| 9 | ❖ ቅዱስ ደቅስዮስ - የእመቤታችን ተአምር የሰበሰበ፥
❖ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - እሰግድ ለኪን የደረሰው፥
❖ ቅዱስ ያሬድ -የተአምሯን ሃሌታ፥
❖ ቅዱሳን ሊቃውንት - የዘወትሩን መቅድም፥
❖ ቅዱሳን አበው ማቴዎስ ማርቆስና አብርሃም ሶርያዊ - የተአምሯን ሥርዓት ያዘጋጁ፥
የቅዱሳኑ በረከት ረድኤት ይደርብን፤ አሜን!
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 176 |
| 10 | 📜ተአምረ ማርያም
❖ "ተአምር" የሚለውን ቃል በቁሙ "ምልክት" ብሎ መተርጐም ይቻላል፤ መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው፤ ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ (በላይ) ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ (ሲፈጸም) ተአምር ይባላል።
❖ ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው፤ እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው፤ ስለዚህም ነው "ኤልሻዳይ - ከሐሌ ኩሉ ሁሉን ቻይ" እያልን የምንጠራው እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል።
❖ በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ መና ሲያዘንሙ ውሃ ሲያፈልቁ (ኦሪትን ተመልከት) እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ እሳትን ሲያዘንሙ ሙታንን ሲያስነሱ እንደ ነበር ይታወቃል።
❖ እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል፤ በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል።
❖ በተአምራት ብዛት ደግሞ ከጌታ ቀጥላ ድንግል እመ ብርሃን ትጠቀሳለች፤ ዛሬም የምናስበው የእርሷን ተአምራት ነው፤ የእግዝእትነ ማርያም ሙሉ ሕይወቷ ተአምር ነው።
❖ ድንግል እመቤታችን በሕይወተ ሥጋ ከሠራችው ተአምራት በበዛ መንገድ ላለፉት 2ሺ ዓመታት ስትሠራ ኑራለች፤ እየሠራች ነው፤ ገናም ትቀጥላለች፤ ለሚያምናት ተአምራትን መሥራት ብቻ አይደለም ነፍሱንም ከሲዖል ታድነዋለች፤ ሁሉን ቻይ ልጅ አላትና እርሷም ሁሉን ትችላለች፤ እንኳን የፈጣሪ እናት ድንግል ማርያም የክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያቱም "የሚሳናችሁ የለም" ተብለዋል። 📖ማቴ 17፥20
ልመናዋ ክብሯ የልጇ ቸርነት በእኛ በሕዝበ ክርስቲያን ላይ ይደርብን!
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 211 |
| 11 | ታኅሣሥ 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ተአምረ ማርያም
2.ቅዱስ ደቅስዮስ ጻድቅ
3.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
4.ቅዱስ አንስጣስዮስ ሊቅ
5.አባ አርኬላዎስ
ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2.አባ እንጦንስ
3.አባ ዻውሊ የዋህ
4.ቅዱስ ዮልዮስ
5.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
"የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው፤ ጌታም አንድ ነው. . . ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ለጥቅም ይሰጠዋል፤ ለአንዱ ጥበብን መናገር . . . ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ ለአንዱም ተአምራትን ማድረግ . . . ይሰጠዋል"
📖1ኛ ቆሮ 12፥4
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 164 |
| 12 | #ታሪክን_የኋሊት
ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል 1960/1961 ዓ.ም
ምንጭ ፦ Mr Mike O'Brien የቀድሞ የአሜሪካ ፈቃደኛ ሰላም አስከባሪ አባል
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 187 |
| 13 | ሰላም ለአእዛኒከ ኖኅያተ ቃለ አብ ሕያው፥
ወለመላትሒከ ልሑያት አምሳላተ ጽጌ ዘበድው፥
ኦ #ገብርኤል መልአከ አድኅኖ ፍንው፥
አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው፥
አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ ዕደው።
ትርጓሜ
ገብርኤል ሆይ የአብ አካላዊ ቃል መሳክወ ብርሃን ለሚሆኑ ጆሮችህ ሰላም እላለሁ። የውበታቸው ጸዳል የበረኃ አበባ ለሚመስለውም ጉንጮችህ ሰላም እላለሁ።
ገብርኤል ሆይ ከጭንቅና ከመከራ ለማውጣት የተላክህ መልአክ ነህና። ሠለስቱ ደቂቅ በእሳት ጉድጓድ በተጣሉ ጊዜ ሁለቱ ክንፎችህን ጋርደህ ከመቃጠል እንዳዳንሃቸው እኔንም አገልጋይህን በረድኤትህ ኃይል አድነኝ።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 189 |
| 14 | 🌹እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🌹
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው። እርሱም በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሩአቸው ጊዜ አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳናቸው ነው።
ሰላም እብል ኪያከ ክቡረ፥
ለስመ ዚአከ ገብርኤል እንዘ አነሥእ መዝሙረ፥
እግዚአብሔር መንበሮ ሰማየ ሰማያት ዘገብረ፥
ይትመሰል በአርአያከ አመ ጊዜ ሐወጸ ምድረ፥
እምነ መላእክት ኲሉ ስነከ አፍቀረ።
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ አማላጂነት፣ የሊቃነ መላእክቱ ጥበቃና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃ አይለየን፤ ሀገራችን ሰላም ፍቅር ያድርግልን። አሜን!
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 158 |
| 15 | 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
እንኳን ለበዓታ ለማርያም በዓለ ንግስ በሰላም እና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ።
ይህ ታላቅ በዓለ ንግስ በአሁኑ ሰዓት በዳግማዊ ምኒልክ ታዕካ ነገስት በዓታ ለማርያም ገዳም በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 324 |
| 16 | ንጽሕተ ንጹሐን ከዊና ፤ ከመ ታቦር ዘዶር ዘሲና፤ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በቅድስና ፤ ሲሳያ ኅብስተ መና ፤ ወስቴሃኒ ስቴ ጽሙና፡፡
ትርጓሜ
በሲና እዳለች እንደ ታቦት ዘዶር ከንጹሐን በላይ ንጽሕት ሆና በቤተ መቅደስ ኖረች፤ መግቧ ኅብስተ መና መጠጧ የጽሙና መጠጥ ነው፡፡
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 243 |
| 17 | 🌹እንኳን ለበዓታ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሦስት በዚች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው ። እርሷ ለእግዚአብሔር የስእለት ልጅ ነበረችና ።
ሰላም ለበአትኪ ውስተ ኦሪታዊት ጠረጴዛ፥
ዘብፅዓት ለኪ እንበለ የሀቡ ቤዛ ፥
ማርያም አንቲ ሰዋስው ዘምድረ ሎዛ ፥
ዲቤኪ ትዕርግ ጸሎትየ ከመ ጹና ሠናይ መዓዛ፥
ኀበ ለነፍስየ ታሰስል ትካዛ ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአማላጅነቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 223 |
| 18 | አንድ ሰው መጥቶ እናንተ የምትለብሱትን አንዲት ቁራጭ ልብስ እንኳ ሳይሰጣችሁና ሰውነታችሁ በብርድና በዋዕየ ፀሐይ እየተቆራመደ ሳለ ቤታችሁን በወርቅና በተንቆጠቆጠ የመጋረጃ ዓይነት ቢያስጌጥላችሁ ምን ጥቅም አለው? እኛስ ነፍሳችን ዕራቁቷን ሳለች ሥጋችንን ወርቅ ብናለብሰው በወርቅ ብናስተኛው ምን ትርጉም አለው? ነፍሳችን በመሬት ላይ እየተንፏቀቀች ሳለ ሥጋችን በከበሩ ሠረገላዎችና የተለያዩ ማጓጓዣዎች ብትንፈላሰስ ምን ጥቅም አለው?
ልጆቼ ! እውነተኛውን ልብስ ልበሱ ብዬ እመክራችኋለሁ። እዚህ የሚቀረውን ሳይኾን ዘለዓማዊውን ልብስ ልበሱ። የሰርጉን ልብስ ልበሱ።
እስኪ በየገዳማቱ ሒዱና ይህን ከቅዱሳን አበው ወእማት ተማሩ። እነዚህ ቅዱሳን በእልፍ ወትእልፊት ዕንቁ የተሽቆጠቆጠ ልብስ ብትሰጥዋቸው አይቀበሏችሁም። ለምን? እነርሱ ጋር ያለው ልብስ እናንተ ይዛችሁት ከሔዳችሁት ይልቅ በእጅጉ እንደሚበልጥ ስለሚያውቁ! ይኸውም የነፍሳቸው ልብስ ማለቴ ነው።
ለእነርሱ ይዛችሁት የሔዳችሁት ልብስ ለአንድ ምድራዊ ንጉሥ ብትሰጡት እጅግ ያመሰግናችኋል። እነርሱ ግን ከዚህ ንጉሥ በላይ በከበረ ልብሱ ያጌጡ ናቸውና አይቀበሏችሁም። ወርቃቸውን ወደሚያስቀምጡበት መዝገብ (ልቡናቸው) ገብታችሁ ስታዩ'ማ ራሳችሁን ስታችሁ ትወድቃላችሁ ። የሀብታቸውን (ምግባር ትሩፋታቸውን) ብዛት የወርቃቸውን ንጻት እንዲህ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም ። እናንተም ከእነርሱ ተማሩና እውነተኛውን ልብስ ለመልበስ ተሽቀዳደሙ ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
📖 ሰማዕትነት አያምልጣችሁ መጽሐፍ
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 282 |
| 19 | #ዜና
ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳወቀ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫው በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ባይገለፅም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ተነግሯል።
ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ለሚሰጠው መግለጫ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ላልሆኑና በቤተክርስቲያኗ ህዝብ ግንኙነት ለተመዘገቡ መገናኛ ብዙሃን በስፍራው እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄
📖 @demesetewahedo
┄┉✽»༺ ═ ✞ ═ ༻»✽┉┄ | 253 |
