cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ቃለ ጽድቅ ዘመካነ ሕይወት | የመ/ሕ/ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ንዑስ ክፍል

ይኽ የፈረንሳይ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን መካነ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ቻናል ነው። በዚኽ ቻናል በመንፈሳዊ ሕይወትዎ የሚበረቱባቸውን መንፈሳዊ ጽሑፎችና መልእክቶች ባሉበት ሆነው መከታተል ይችላሉ።

Show more
Advertising posts
1 010
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+2130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

🔔 ✥✥✥ ፱ ሰዓት ✥ተንስኡ ለጸሎት✥ #መዝሙረ ዳዊት 118_25 አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና። #በዚህ ሰዓት ይህንን የምታዩ የምታደርጉትን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔርን እያሰብን አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን የእግዚሐብሔር ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረን
Show all...
#እንደ_ወሮቻችን_ኑ_በእርሷ_እንጀምር (ዲ/ን ሕሊና በለጠ) የወር መጀመሪያ የእርሷ ልደት ነው። ወሮቻችን ኹሉ በእርሷ ልደት ጀምረው በመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ነቢይና የሐዲስ ኪዳን መንገድ ጠራጊ በመጥምቁ ዮሐንስ ያበቃሉ። እርሱ የብሉይን ማለፍና የሐዲስን መምጣት በማብሰር መንገድ እንደ ጠረገ ፣ የብሉይ ምሳሌ የኾነውን የአሮጌውን ዓመት ማለፍና የሐዲስ ምሳሌ የሚሆነውን የአዲሱን ዓመት መምጣት ያበሥር ዘንድ መስከረም አንድ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲባል ኾነ። ልክ እንዲሁ ደግሞ የአሮጌው ወር መጨረሻ ላይ ወርኀዊው መታሰቢያው በመሆኑ በእርሱ ትምህርት ላይ ቆመው፣ እርሱ መንገድ ጠርጎላቸው ሐዲስን እንዳዩት የብሉይ ኪዳን ሰዎች፣ እኛም በእርሱ መታሰቢያ በዓል ላይ (በ30) ላይ ቆመን ሐዲስ ወርን እናያለን። እነርሱ በእርሱ ትምህርት ጸንተው የአሮጌውን ኪዳን መጨረሻነት ተረድተው የሐዲስ ኪዳንን ሐዲስ ሕይወት "1" ብለው እንደ ጀመሩ፣ እኛም 30 ላይ ቆመን የአሮጌው ወር ብልየታችንን መጨረሻነት ተረድተን የአዲሱን ወር ሐዲስ ሕይወት "1" ብለን እንጀምራለን። "1" ደግሞ ልደታ ለእግዝእትነ ነው - የኹሉ ነገር ጅማሬ የኾነችው የእመቤታችን ልደት። ወሮቻችን ኹሉ በእርሷ ልደት ስለሚጀምሩ ቀና ናቸው። ወሩን እርሷን አክብሮ፣ ዘክሮ ስሟን ጠርቶ የሚጀምር ሰው መንገዱ የቀና ነው። በእርሷ ጀምሮ ያፈረ የለም። የአዳም የመዳን ተስፋ "እምወለተ ወለትከ" በሚለው እርሷን በሚያነሣው ቃል ኪዳን ተጀምሮ ፍጻሜው ያማረ ሆነ። ኖሕ ከጥፋት ውኃ መዳኑን ለእርሷ ምሳሌ በሚሆን መርከቡ ጀምሮ አላፈረም። ሙሴ እስራኤልን ከፈርዖን የማዳን ሥራውን የጀመረው ሐመልማሉ እሳቱን ሳያጠፋው እሳቱም ሐመልማሉን ሳያቃጥለው ባየው ድንቅ ምሥጢር ነው፤ ይህ ደግሞ እሳተ መለኮት ሐመልማል የሆነች እርሷን ላለማቃጠሉና ላለመዋጡ፣ በእርሷ የተፈጸመውን ተዋሕዶ የሚያሳይ ነው። ሠለስቱ ዮሐንሶችም እንዲሁ ናቸው። ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ የፍቅር እናትን ተቀብሎ የጀመረው ሕይወት "ነባቤ መለኮት" አስብሎታል። ዮሐንስ መጥምቅ በእናቱ ማህጸን ሳለ ለእርሷ ሰግዶ የጀመረው ሕይወት "ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከእርሱ የሚበልጥ አልተነሣም" አስብሎታል። (ማቴ.11:11)። አፈ በረከት ዮሐንስ ስለ እርሷ አመሥጥሮ የጀመረው ሕይወቱ "አፈ ወርቅ" አስብሎታል። (ግንቦት 1 ዓመታዊ በዓሏ እንደ ሆነው ግንቦት 12 የሊቁ ፣ ግንቦት 16ም የሐዋርያው በዓል መሆኑን ልብ ይሏል) እርሷ የወራችን ብቻ ሳይሆን የሰማይና የምድርም መጀመሪያ ናት። (ሰማይና ምድር በውስጣቸውም ያሉት ስላንቺ ተፈጠሩ እንዲል ድርሳነ ማርያም)። ሰማይና ምድር ሳይጋፉ ፣ ሳይራበሹ "ይህ የኔ ክልል ነው፣ ይህ የኔ ወሰን ነው" ሳይባባሉ ሺህ ዘመናትን በፍቅር የጸኑት እርሷን መጀመሪያቸው ስላደረጉ ይሆን? እርሷ የአዳምና ሔዋን መጀመሪያ ናት። ስለ እርሷ አዳምና ሔዋን ተፈጥረዋል። (መላእክትን ከፈጠረ በኋላ በጸፍጸፈ ሰማይ ቀጥሎ ማንን እንደሚፈጥር ያሳያቸው ነበር። ቀጥሎ የሚፈጠረው ሰው: አምላኩን እንደሚክድ ሲያዩ መላእክቱ "አትፍጠረው" አሉ። ድንግልን አሳያቸው፤ ሊያዩት የሚጓጉለትን አምላክን መውለዷን ሲያዩ "ይህችን ፍጠርልን" ብለው ተማጸኑ። "ካለ እርሱ (አዳም) እርሷ አትገኝም" ቢላቸው "እንግዲያውስ ስለ እርሷ እርሱን ፍጠርልን" አሉ። \ትርጓሜ. ኢዮብ? ኩፋሌ?)። ነገረ ልደቱ በእርሷ የጀመረለት አዳም ነገረ ልደቱ በእርሷ እንዳልጀመረለት ሳጥናኤል ወድቆ አልቀረም - ተነሣ እንጂ። በእርሷ የሚጀምር ቢወድቅ እንኳን ይነሣል። መጽሐፍ ቅዱስ ካምና ያፌትን ትቶ የሴም የትውልድ ሐረግን ለምን ተረከ? እመቤታችን ከሴም ዘር ስለምትወለድ ነው። ከሌሎች ሕዝቦች መኻል እስራኤልን መርጦ ለምን ቀጠለ? እመቤታችን ከእስራኤል ስለምትወለድ ነው። የካም ዘር የሆነውን መልከጼዴቅን ትቶ የሴም ዘር ስለ ሆነው ስለ አብርሃም እየተረከ ለምን ቀጠለ? አብርሃም ስለሚበልጥ ነውን? አይደለም። መልከጼዴቅ ታላቅ አብርሃም ታናሽ እንደ ሆነ ቅዱስ ጳውሎስ ነግሮናል። (ዕብ.7)። ታዲያ ምክንያቱ ምንድን ነው? እርሷ ከአብርሃም ዘር ስለምትወለድና ጌታችንና አምላካችንም ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ስለሚሆን ነው። መጽሐፍ ቅዱሳችን እንኳን እርሷን በሩቅ ዐይቶና በእርሷ ላይ ተመሥርቶ የተጻፈ ነው። ድኅነታችን በእርሷ ምክንያትነት የተገኘ ነው። "አንዲት ዘር" የሆነች እርሷን ባያስቀርልን ኖሮ ከምድር በታች መውደቃችን ለመቀበር እንጂ ተዘርቶ ለማበብ አይሆንም ነበር። ኢትዮጵያውያን በእርሷ በመጀመር አንታማም። በእርሷ እየጀመርን ከብዙ ውድቀትም ተርፈናል፣ ተነሥተናል። እርስ በእርስ የመባላታችንም ሆነ የመጠላላታችን ነገር ምናልባት የፍቅር እናት የሆነች እርሷን ዘንግተን የመጡብን ይሆኑ ይሆን? ምናልባትም እርሷን የማይጠሩ ዜጎች በርክተው እኛም በዚህ ደክመን ይሆን? ኑ ልክ እንደ ወሮቻችን በእርሷ እንጀምር። ያለፈውን ብልየት ኹሉ በመጥምቁ ትምህርት ላይ ቆመን እንሻገርና እርሷን ይዘን እንጀምር። ባለፈው ወር ያለቀስን፣ ያዘንን፣ የወደቅን፣ የከፋን፣ ያቄምን፣ የሞትን፣ የዘረፍን፣ የገደልን፣ የዘሞትን በክፋትና በሥጋ ሥራ ያረጀን ኹሉ በመጥምቁ ትምህርት ላይ እንቁምና ብሉዩን እንሰናበተው፤ ሐዲሱን ሕይወት ልክ እንደ ወሮቻችን "1" ብለን በእርሷ እንጀምር።
Show all...
✝✝✝ እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✝✝ +*" 🌷ልደታ ለማርያም ድንግል🌷 "*+ ✝ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ: ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ:: ✝ " ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን: ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) " =>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን:: +ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል:: +እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9) +ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች:: "ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8) =>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር:: +ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም:: +የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች:: +ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ:: +እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ:: +በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ:: +እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች:: "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . . ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም) +"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ." "ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9) +እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች:: =>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:- *አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ= *በእናቷ:- -ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና:: *በአባቷ በኩል:- -ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል:: +ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች:: =>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን:: =>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ) 2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና 3.ቴክታና በጥሪቃ 4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት) =>ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት 2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ 3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር =>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው:: ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል:: የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . . ሰው እናታችን ጽዮን ይላል:: በውስጧም ሰው ተወለደ:: እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>> https://t.me/zikirekdusn
Show all...
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)

በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

#እንኳን _ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_የልደት_በዓል_በሰላም_አደረሳችኹ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ''ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ: ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ:: '' " ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን: ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "
Show all...
Show all...
ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት   

✝🔔✝🔔✝🔔✝🔔✝🔔✝🔔✝🔔✝🔔✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ         አሜን ክፍል አንድ በቃል ያለ ይረሳል፤ በጽሁፍ ያለ ይወረሳል     ✥•• ┈•• ●◉ ✞ ◉●•• ┈••✥      ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት        ✥•• ┈•• ●◉ ✞ ◉●•• ┈••✥   ✍መግቢያ 📌 የጾታ አጠቃላይ ትርጉም ❖ ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ሲባል፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስለ ጾታ የሚሰጠውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት፣ ስለ ጾታ ያላትን አመለካከት፣ ቀኖናዊ ሥርዓትና ባህላዊ ትውፊት የሚያመለክት ትምህርት ማለት ነው ።  ❖ ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንረዳው ጾታ የሚለው ቃል በአርአያ እግዚአብሔር ከተፈጠረው የሰው ዘር ጀምሮ፣ በመውለድ መዋለድ፣ የመብዛትንና የመባዛትን ተፈጥሮአዊ ጸጋ ከእግዚአብሔር አምላክ ያገኘ ፍጡር ሁሉ "ተባዕታይ አንስታይ " ወይም "ወንዴና ሴቴ "…

#ክፉ_አሳብ ልጆቼ! ከመጀመሪያውኑ ክፉ አሳብ ባታስቡ መልካም ነው፡፡ ካሰባችሁ ግን ቢያንስ አትናገሩት፡፡ በዚያው በሕሊናችሁ ውስጥ እያለ ዝም አሰኙት፤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም ወዳለመኖር ይኼዳል፡፡ እኛ ሰዎች ነን፡፡ በመኾኑም ብዙውን ጊዜ ክፉ፣ ያልተገቡና ጸያፍ ነገሮችን እናስባለን፡፡ ነገር ግን ቢያንስ እነዚህን አሳቦች አንናገራቸው፤ ቢያንስ ወደ ቃል አንለውጣቸው፡፡ ወደ ውጭ እንዳይወጡ አምቀን እንያዛቸው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየከሰሙና እየደከሙ እየጠፉም ይኼዳሉ፡፡ አንድን እንስሳ ወደ ጉድጓድ ብትጥሉትና ጉድጓዱንም በመክደኛ ብትከድኑት ያ ወደ ጕድጓድ የጣላችሁት እንስሳ የሚተነፍሰውን አየር አጥቶ ይሞታል፡፡ ምናልባት ጥቂት ቀዳዳ ካገኘ ግን በዚያች ቀዳዳ በምትገባው አየር በሕይወት መቆየት ይችላል፡፡ ሲጨንቀውም እናንተን ክፉኛ ለመጉዳት ይዝታል፤ ከወጣም በኋላ ይጎዳችኋል፡፡ ልክ እንደዚሁ እናንተም በልቡናችሁ የተመላለሰውን ኩላሊታችሁ ያጤሰውን ክፉ አሳብ መውጫ ቀዳዳ እንዳይኖረው አድርጋችሁ ብትከድኑት (ብታፍኑት) ይሞታል፤ ከመኖር ወዳለመኖር ይለወጣል፡፡ በአንደበታችሁ በመናገር ጥቂት ቀዳዳ ከከፈታችሁለትና እንደ እንስሳው እንዲተነፍስ ከፈቀዳችሁለት ግን ክፉው አሳብ ክፉ ግብርን ይወልዳል፡፡ ያቆጠቁጣል፡፡ በአሳብ ሳለ ከጎዳችሁ በላይም በገቢር ተወልዶና ተለውጦ ክፉኛ ይጎዳችኋል፡፡ (#የክርስቲያኖች_መከራ #በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ገጽ 7➛በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
Show all...
ማክሰኞ ቶማስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ትንሣኤው ሐዋርያት ተሰብስበው በነበረበት በዝግ ቤት ገብቶ ሲገለጽላቸው ሐዋርያው ቶማስ ከእነርሱ ጋር አልነበረም፡፡ ሐዋርያትም የጌታችንን ከሙታን ተለይቶ መነሣት ቢነግሩት ‹‹እኔ ሳላይ አላምንም›› አላቸው፡፡ በሚቀጥለው ሳምንትም ጌታችን ቶማስ በተገኘበት በድጋሜ  ተገለጠላቸው፡፡ ጌታችንም ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ‹‹ጣትህን ወደዚህ አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን›› ብሎ በጦር የተወጋ ጎኑን ፥ በችንካር  የተቸነከረ እጁንና እግሩን እንዲዳስሰው በማድረግ ትንሣኤውን  አረጋገጠለት፡፡ ቶማስም ሲዳስሰው እጅ ከእሳት እንደገባ ጅማት ስለተኮማተረ ‹‹ጌታዬ አምላኬም›› ብሎ መሰከረ፡፡  በኋላ ግን ፈውሶታል፤ ኢየሱስም ‹‹ስለ አየኸኝ አምነሀል ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዐን ናቸው›› አለው፡፡  ምንም አንኳን ድርጊቱ የተፈጸመው በዳግም ትንሣኤ ቢሆንም የሐዋርያው መታሰቢያ ሆኖ ዕለተ ማክሰኞ ‹ቶማስ› ተብሎ ተሰይሟል፡፡ (ዮሐ. ፳ ፥ ፳፬ -፴) ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Show all...