en
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Open in Telegram
1 085
Subscribers
+924 hours
+207 days
+1530 days
Posts Archive
የድሬዳዋ ቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ለክዋኔ ኦዲት ግኝት የሰጠው ምላሽ በአርአያነት ሊወሰድ የሚገባው መሆኑ ተገለጸ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2014 ዓ.ም የ ኤስ ዲ ጂ በጀት ኦዲት ሪፖርት ፣ የ2015 ዓ.ም መደበኛ በጀት ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የተቋሙ ተጠሪ ተቋም የሆነው የቴክኒክና ሞያ ትምህርት እና ስልጠና ኤጀንሲ የ2013 – 2015 የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ የሂሪንግ መድረክ አካሂዷል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ አመራሮች በግኝቶቹ ዙሪያ ምላሽ ይዘው የቀረቡ ሲሆን የተቋሙ አመራሮች በተሟላ ሁኔታ በኦዲት ሂሪንግ መድረኩ መገኘታቸው ጥሩ መሆኑን የገለጹት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አንድነት ሀይሉ የኤስዲጂ እና የመደበኛ በጀትን አስመልክቶ የግኝት አቀባበላቸው ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው የቀረቡ ግኝቶች ምላሽ ማግኘታቸውን እና በኤጀንሲው የክዋኔ ኦዲትን በተመለከተ የ ኦዲት ግኝቶቹን ወስዶ የመፉቻ እቅድ አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱ በአርአያነት እንዲታይ የሚያደርገው መሆኑን የተከበሩ ወ/ሮ አንድነት ሀይሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም በሰነድ ሊደገፉ የሚገባቸው ምላሾች በተሰጡት ቀናት ለምክር ቤት እና ለዋና ኦዲተር እንዲላክ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል :: ©️ Dire Dawa Administration Council

photo content
+8

photo content
+3

photo content
+9

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተተገበረ የሚገኘው የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት በ 2016 ዓ.ም የተሰሩ ስራዎችና የተገኙ ልምዶችን የሚያሳይ ሪፖርት ለባለ ድርሻ አካላት አቀረበ:: የፕሮጀቱ አመታዊ ሪፖርት በፕሮጀክቱ ማናጀር አማካኝነት ለመድረኩ የቀረበ ሲሆን በዚህም የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት በዓመቱ ያከናወናቸው ተግባራቶች በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን ፕሮጀክቱ ያስገኛቸው ጥሩ ልምዶችን ጨምሮ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም ጠቅለል ተደርገው ቀርበውበታል:: በተጨማሪም በመድረኩ የቀረበው አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በSolar Pv installation and maintenance እያሰለጠናቸው የሚገኙ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ሰልጥኞቹ የስራ ላይ ልምድ የሚያገኙበትን እድል በማመቻቸቱ ረግድ የተሰሩ ስራዎች በመድረኩ ቀርበዋል:: በዚህም ሰልጣኞች ስራ እየሰሩ ልምድ የሚያዳብሩበትን መንገድ ከጤና ቢሮ፣ከትምህርት ቢሮ እና ከኢነርጂ ቢሮ ጋር በመነጋገር የገጠር ሶላር ስራ ላይ የጥገና ስራ እንዲሰሩ መንገድ የተመቻችላቸው ሲሆን ከፊልድ ስራ ሲመለሱ የብቃት ምዘና(COC) በመውሰድ ወደ ስራው ዓለም እንደሚሰማሩ ይጠበቃል:: በፕሮጀክቱ እቅድ መሰረት 40% በቅጥር 60% ደግሞ የራስ ስራ በመፍጠር ወደ ስራ ይሰማራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለዚህም ይሆን ዘንድ ከፐብሊክ ሰርቪስ በተላከ ባለሞያ አማክኝነት በተደረገው ገለፃ መሰረት እንደ ሀገርም አዲስ የሆነውን የሶላር ባለሙያ JOB BOX በማዘጋጀት የመጀመሪያ ድራፍት ዶክመንት በዛሬው እለት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ የተተቸ ሲሆን በቀጣይም በተሰጠው ግብረ መልስ መሰረት ማስተካከያ ተደርጎበት እንደሚፀድቅ ተገልፇል:: በመጨረሻም በቀጣይ ለሚገቡት ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የምልመላ መስፈርት ላይ በመድረኩ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግና መስፈርቱንም በማሻሻል መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሰኔ 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተተገበረ የሚገኘው የEASTRIP ፕሮጀክት የRailway የልህቀት ማእከል አጠቃላይ የህንጻ ግንባታ የስራ አፈጻጸም በሥራና ክህሎት ሚንስቴር መስሪያ ቤት ግምገማ ተ
+6
በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተተገበረ የሚገኘው የEASTRIP ፕሮጀክት የRailway የልህቀት ማእከል አጠቃላይ የህንጻ ግንባታ የስራ አፈጻጸም በሥራና ክህሎት ሚንስቴር መስሪያ ቤት ግምገማ ተከናወነ፡፡ በኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው ይህ የEASTRIP ፕሮጀክት የRailway የልህቀት ማእከል የህንጻ ግንባታ አሁን ያለበትን እንዲሁም በቀጣይ ሊደርስበት የሚገባውን ደረጃ በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ፣ ክብር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቦርድ ሰብሳቢ እና የድሬዳዋ ብልጽግና ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም ኮሌጅ ም/ቦርድ ሰብሳቢና የድሬዳዋ ስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው በተገኙበት የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም በጥልቀት የገመገሙ ሲሆን በቀረበው የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን በእለቱ የተገኙ ክቡራን እንግዶች የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ እና ክብር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ መሰረት ተጠናቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት እንዲችል አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ አጠቃላይ የህንጻ ግንባታ አፈጻጸሙን በአማካሪ ድርጅቱ በቢይቦኔ አማካሪ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ በግምገማው ሂደት ላይ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ፣ ክብር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ፣ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው፣የስራ ና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ የአለም ባንክ ተወካዮች፣የኮሌጁ አመራሮች ፣ የኮሌጁ የEASTRIP ፕሮጀክት ኃላፊዎች እንዲሁም የአተም ኮንስትራክሽ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ አያሌው መሸሻ ተገኝተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሰኔ 7/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዘጠኙም የከተማ ወረዳ አስተዳደር ስር የሚገኙ አስራ አንድ የወረዳ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ አመራሮች በአዲስ አበባ አስተዳደር የሥራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በዚህም የሥራ ጉብኝት በአዲስ አበባ የሚገኙ አንድ ማዕከላትን እንቅስቃሴ ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን እንደ አገር የተያዘውን የለውጥና የብልጽግና ጉዞ ለማሳለጥ በዘርፉ የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን አቻ ተቋማትን መመልከትና ተሞክሮን እንደ አስተዳደራችን ተጨባጭ ሁኔታ በመቀመር ማስፋት አስፈላጊ በመሆኑ ድጋፍ መደረጉንና የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት ማድረግ እንደሚቀጥልና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ተቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፤ እንደሚታወቀው በድሬዳዋ የሚገኙ አንድ ማዕከላት የጋራ ፎረም መስርተው አገልግሎት አሰጣጡን ከማሳደግ አንጻር ከአስተዳደሩ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በቅንጅትና በመናበብ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ስራዎችን በመቁረስ ለአስራ አንዱም የወረዳ አንድ ማዕከላት ማውረድ ሥራዎች እየተሰሩ እንዳለና በቀጣይም ከሥራ ጉብኝቱ በመነሳት በተሻለ ለመፈጸም የሚስችል ውጤት ያስገኙ የአደረጃጀት እና የአሰራር ተሞክሮዎችን በመቀመር ወደ ተግባር ለመግባት ከፍተኛ መነቃቃትና መነሳሳት መፈጠሩን የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያዎቹ ፎረም ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ቢፍቱ መሐመድ ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛ ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ እያ
+1
እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን  እንኳን ለ1445ኛ  ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። በዓሉን ስናከብር የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነዉን አብሮነት በማጠናከር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመደገፉ ሊሆን ይገባል።       ኢድ ሙባረክ               አቶ ሮቤል ጌታቸው              የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ

እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛ ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ እያ
+1
እንኳን ለ1445ኛው ዓ.ሂ ኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛ ዓመት ሂጂራ የኢድ አል አድሃ/አረፋ በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። በዓሉን ስናከብር የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነዉን አብሮነት በማጠናከር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመደገፉ ሊሆን ይገባል። ኢድ ሙባረክ አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ

በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ የሚገኘው የሉሲ ኮሌጅ አመራሮች ከአስተዳደሩ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጋር ውይይት ተደረገ። ይህም ውይይት በዋናነት ከዚህ በፊት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ከማስጠበቅ አንጻር በተደረጉ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ላይ ተመስርቶ ኮሌጁ ማስተካከያ እንዲያደርግ በተሰጠው ግብረ-መልስ መሠረት የተወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎች በሪፖርት ቀርበዋል። በዚህም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ኮሌጁን ወክለው በቢሮው ከተገኙ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከዚህ በፊት በተሰጠው ግብረ-መልስና አስተያየት መሠረት የተወሰዱ እርምቶችና ማስተካከያዎችን በማበረታታት በቀጣይ ቀሪ የሚባሉ መስተካከል የሚገባቸውን ጉዳዮች በአጭር ጊዜ ተስተካክለው ሪፖርት እንዲደረጉ አቅጣጫ ሰጥተዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 4/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ የሚገኘው የሉሲ ኮሌጅ አመራሮች ከአስተዳደሩ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ጋር ውይይት ተደረገ። ይህም ውይይት በዋናነት ከዚህ በፊት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ከማስጠበቅ አንጻር በተደረጉ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ላይ ተመስርቶ ኮሌጁ ማስተካከያ እንዲያደርግ በተሰጠው ግብረ-መልስ መሠረት የተወሰዱ የማስተካከያ እርምጃዎች በሪፖርት ቀርበዋል። በዚህም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ኮሌጁን ወክለው በቢሮው ከተገኙ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከዚህ በፊት በተሰጠው ግብረ-መልስና አስተያየት መሠረት የተወሰዱ እርምቶችና ማስተካከያዎችን በማበረታታት በቀጣይ ቀሪ የሚባሉ መስተካከል የሚገባቸውን ጉዳዮች በአጭር ጊዜ ተስተካክለው ሪፖርት እንዲደረጉ አቅጣጫ ሰጥተዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 4/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ሂደት አዘጋጅነት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ሂደት ኬዝ ቲም እና የቀበሌ አንድ ማዕከል አስተባባሪ
+5
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ሂደት አዘጋጅነት  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ሂደት ኬዝ ቲም እና  የቀበሌ አንድ ማዕከል አስተባባሪዎች በሐረር ከተማ በሚገኙ  የባህላዊ ዕደ-ጥበብ ማሰልጠኛ ተቋማት ጋር  የልምድ ልውውጥ በዛሬው እለት አደረጉ።  የልምድ ልውውጡ ዋና አላማም በአገር በቀል እውቀቶች (Indigenous knowledge) ላይ በቂ የሆነ ልምድ ለመውሰድ፣ ተሞክሮዎችን በመቀመርና በመሰነድ ለሰልጣኞችና ለኢንተርፕራይዞች ስልጠና በመስጠት አገር በቀል የሆኑ ግብአቶችን በመጠቀምና በማምረት ወደ ስራ እንዲገቡ ለማስቻል  አንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምንኬሽን ሰኔ 03 / 2016 ሀረር

በ EASTRIP ፕሮጀክት አማካኝነት የሚተገበረው Teacher Industrial Attachemet በ 2016 የተሰሩ ስራዎችን ልምዶችን ለባለ ድርሻ አካላትና ለት/ት ክፍል ተጠሪዎች በዛሬው እለት አካ
+6
በ EASTRIP ፕሮጀክት አማካኝነት የሚተገበረው Teacher Industrial Attachemet በ 2016 የተሰሩ ስራዎችን ልምዶችን ለባለ ድርሻ አካላትና ለት/ት ክፍል ተጠሪዎች በዛሬው እለት አካፈላ ። በexperience sharing ወቅት በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሣሊም ኡስማን እንዳሉት ትምህርትና ስልጠና በተቋም ውስጥ ከሚሰራው ስራ ውጪ ከኢንዱስተሪዎች ጋር በIndustrial Attachemet በጋራ በመስራት በትምህርትና ስልጠናው ውጤታማ አንድንሆን ያደርገናል ። ለዚህም ማሣያው ኮሌጃችን ለተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ተተኪ ምርት በማምረት በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚኖረውን የ ተተኪ ምርት እጥረት ማስቀረት ችለናል ብለዋል። በመጨረሻም በዚህ ስራ ላይ ለተሣተፉችሁ አካላት ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል። በ 2016 በትምህርት ክፍሎች  በኩል የተለያዩ ችግር ፈቺ ተለዋጭ ምርት ስራዎች ተሠርተዋል። የኮሌጁ ኮምንኬሽን ሰኔ 1/2016 ድሬዳዋ

#ዜና | ስራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና የንግድ ሃሳብ ያላቸው አካላትን መደገፍ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር ስራ፥ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ፥ የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ከሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የፈጠራ እና የንግድ ሀሳብ ውድድር ሽልማት ተካሄደ፡፡ በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በሀገራችን የሚታየውን ስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት የቴክኖሎጂ ፈጠራና የንግድ ሃሳብ ያላቸውን አካላት መደገፍ ይገባል ብለዋል፡፡ ውድድሩ የፈጠራ ስራ ያላቸውን አካላት ሃሳባቸው ተግባራዊ የሚደረግበትን መድረክ ለመፍጠር ከማስቻሉም በላይ ለበርካቶቹ የሥራ እድል የመፍጠር ዓላማ እና ግብ አለው። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው በፈጠራ ስራው የተወዳደሩት አካላት በከተማችን የሚታየውን ችግር በመቅረፍ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልፀው፥ ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ ሲካሄድ የነበረውን ውድድር ወደ አንድ ማዕከል ማምጣት መቻሉን ገልፀዋል፡፡ አሸናፊዎች በበኩላቸው ይህን ውድድር በመዘጋጀት የፈጠራ ስራቸውን ለታለመለት አላማ ለማዋል ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ #DireTvአማርኛ | ግንቦት 2016 ዓ.ም

የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን መደበኛ ፣የEASTRIP እና የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸ
+5
የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን መደበኛ ፣የEASTRIP እና የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ፡፡ የቋሚ ኮሚቴውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግራቸውም የኮሌጁን መደበኛ ፣የEASTRIP እና የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ እስከ በጀት አመቱ ማጠቃለያ ድረስ በከፍተኛ ትጋትና የሁሉም ተሳትፎ በጋራ እየሰራን እንገኛለን ፡፡ ከባለፈው አመት ጋርም ሲነጻጸር የእቅዱን አብዛኛውን ፐርሰንት ያሳካንበት አመት ነው ብለዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴውን ልኡክ ቡድን የመሩት ወ/ሮ አይናለም ጌታቸው እንዳሉት ኮሌጁ በመደበኛ እንዲሁም በኮሌጁ ባሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር አመርቂ ውጤት የታየበት ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ተቋሙን ሞዴል እንዲሆን የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡በመጨረሻም ልኡክ ቡድኑ ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 30/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ