1 092
Subscribers
+324 hours
+247 days
+2030 days
Posts Archive
የድሬዳዋ አሰተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት በቀበሌ 05 እና በ08 አስተዳደር ስር የሚገኙ የሁለት አቅመ ደካማ እናቶችን የፈራረሰ ቤት በአዲስ ገንብቶ አስረከበ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ከሚገኘው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ውስጥ አንዱ አቅመ ደካማ የሆኑ ዜጎችን መደገፍ ነው።
በዛሬው ዕለትም በሁለቱ ቀበሌ የሚገኙት እኚህ ቋሚ የገቢ ምንጭም ሆነ በአጠገባቸው የሚረዳቸው የሌለ፤ በፈረሰና ለመኖር እጅግ የሚከብድ ቤት ውስጥ በሚያሳዝን ሁኔታ እየኖሩ የሚገኙ እናቶች ናቸው።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሠራተኞችና አመራሩ ይህን ችግር በመረዳት የሁለቱን እናቶች መኖሪያ ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርቶ በማጠናቀቅ ከአስፈላጊ የቤት ዕቃዎች ጋር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም ሌሎች የአስተዳደሩ አመራሮች በተገኙበት ርክክብ ተደርጓል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጳጉሜ 3/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ስራ አስኪያጅ አቶ አየለ ወ/ዮሀንስ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ተቋም ጋር በርከት ያሉ ስራዎችን በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልሓዲን አብዱልሓሚድ ሲሆኑ አጠቃላይ ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ከስራ ፈጣሪነትና ለኮሌጁ ተጨማሪ ገቢን ከማፈላለግ አንጻር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሌሎች አቻ ኮሌጆች አንጻር የተሸለ አፈጻጸም እንዳለው ያብራሩ ሲሆን በቀጣይም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ጋር መምህራንን ከማብቃት እንዲሁም ኮሌጁ ላይ ያለውን እምቅ አቅም ከመጠቀም አንጻር ሁለቱም ተቋማት አብረው በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ለዚህም ደግሞ ኮሌጁ ቁርጠኛ ነው ብለዋል፡፡
የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑን የመሩት አቶ ተስፋዬ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ተቋም የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ከተማችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት በአቶ መሳይ ጥላሁን የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በኮሌጁ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጳጉሜ 2/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ
የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱ በአስተዳደሩ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በልጽጎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት የሰራተኛና የሥራ መረጃዎችን በዘመናዊ መንገድ በማስተዳደር ዜጎች በሃገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ስርዓት ነው።
በመሆኑም በዛሬው ዕለት የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የቢሮው አመራሮች በተገኙበት ለተግባራዊነቱ የሚያስፈልጉ የባዮሜትሪክስ፣ የላፕቶፕ፣ የዋይፋይ ራውተር እና ሌሎች ቁሳቁሶች ለአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ርክክብ የተደረገ ሲሆን የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓቱ በድሬዳዋ የማገኙ በተመረጡ የወረዳ አንድ ማዕከላት አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸው ይሆናል።
በዚህም ከዚህ ቀደም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ባስተላለፈው የምዝገባ ጥሪ መሰረት ከ180,000 በላይ ዜጎች በድረ-ገጽ (በኦን ላይን) ተመዝግበው የባዮሜትሪክስ ምዝገባ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ስራ ፈላጊዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ማለትም በአስተዳደሩ 02፣ 03፣ 05፣ 06፣ 07፣ 09 የወረዳ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች በአካል በመቅረብ አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጳጉሜ 1/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ጳጉሜን_1 #የአገልጋይነት_ቀን
የአገልግሎት ቀንን ለተገልጋይ ብቻ!!
በቀኑ ከተሰሙ ድምጾች
"ሁሉም በተመደበበት ዘርፍ በአግባቡ ህብረተሰቡን በቅንነት በታማኝነትና በፍጥነት ማገልገል አለበት።"
"ህብረተሰቡን በአግባቡና በሚፈለገው ልክ ለማገልገል ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተገልጋዩን እርካታ ከፍ ለማድረግ መሠራት ይኖርበታል።"
"ልናገለግልዎ ዝግጁ መሆናችንን ቃል በገባነው የአገልግሎት ስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት እናረጋግጣለን።"
የአገልጋይነት ቀን በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፤ እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት በመከበር ላይ ይገኛል ።
ዛሬ ያገለገልከዉ ነገ ያከብርሃል!
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት እቅድ ገመገመ
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትላንትናው እለት የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት እቅድ የገመገመ ሲሆን በመድረኩም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢና አባላት እንዲሁም የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የማኔጅመንት አባላት ተገኝተውበታል።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2016 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ የእቅዱ አዘገጃጀት በጥሩ ጎን የታየ ሲሆን የተሰጠው አስተያየትና ሀሳብ ተካቶበት ለምክር ቤት መላክ እንዳለበት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
©️ መረጃው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት
በአስተዳደሩ ከ6ሺ በላይ ወጣቶችን ወደስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ከስራ እድል ፈጠራ ጋር በተያያዙ ሊቀርብ ስለሚገባው የፋይናንስ አቅርቦት ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የምክክር መድረኩ በዋናነት የፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነትን በማሻሻል ረገድ ስራ ፈጣሪ ዜጎችን መደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ በስልጠና፣ ስራ ዕድል ፈጠራና በኢንቨስትመንት ስፍራዎች ላይ ምቹ የስራ ሁኔታን መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲገልጹ ተቋሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚንቀስቀስባቸው ጉዳዮች መካከል በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የማደራጀት፣ የማሰልጠን እንዲሁም የመስሪያ ቦታ ምችችት በማድረግ ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታዎችን መፍጠር ላይ በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተያዘው በጀት አመት አጋማሽም 524 ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት ለ6,029 ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የፋይናንስ ስልጠና እና ድጋፍ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
የተደራጁ ኢንተርፕራዦችን ወደ ስራ ለማስገባት በቂ የፋይናንስ አቅርቦት በማመቻቸትም በኩል በአስተዳደሩ የሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ከባንክ አመራሮች ጋር ከፋይናንስ አቅርቦት ድጋፍ ጋር በተያያዙ ሰፊ ውይይቶችን አካሂደዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊ የፋይናንስ ተቋማት አመራሮችም የአስተዳደሩ ነዋሪ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመቅረፍ ከልማቱ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸው የስራ ፈጠራ ሃሳብ ይዘው የፋይናንስ አቅም የሌላቸውን ዜጎች በማገዝ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን
ቢሮው የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ-ግብርን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ-ግብር የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ መጀመሩ ይታወቃል፤ በዛሬው እለት በወረዳ 05 ለሚገኙ አጋዥ ለሌላቸው አባት ቤት ሰርቶ ለማስረከብ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የግንባታ ስራውን ለመጀመር ተረክበዋል።
በተያያዘ በዚህ ክረምት በቢሮውና በሁለቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች በድምሩ 4 የአቅመ ደካሞች ቤትን በአዲስ ገንብተን የምናስረክብ አቅዶ ወደተግባር የገባ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ቀደም ሲል በይፋ እድሳታቸው የተጀመሩ ቤቶችን የግንባታ ሂደት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፤
በዚህም የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነው የመተጋገዝ እና የመደጋገፍ ባህልን መሰረት በማድረግ የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ በመቻላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው ከዚህ በተጨማሪ ቢሮው በክረምቱ መርሃ-ግብር በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች በመሳተፍ ወገንና ሀገርን የማገዝ ሃላፊነቱን በንቃት የሚወጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 8/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ከክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎቻችን አንዱ ለአቅመ ደካሞች የቤት እድሳትና ግንባታ ማከናወን ሲሆን በዛሬው እለት በወረዳ 05 እና 08 የሚገኙ ሁለት ቤቶችን በማፍረስ የግንባታ ስራውን አስጀምረናል።
በዚህ ክረምት በቢሮውና በሁለቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች በድምሩ 4 የአቅመ ደካሞች ቤትን በአዲስ ገንብተን የምናስረክብ ይሆናል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
አቶ ሮቤል ጌታቸው
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድራዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ትምህርትና ኮሌጆችን ለሚቀላቀሉ ተማሪዎች የገጽ ለገጽ ቅስቀሳና ኮሌጁን የማስተዋወቅ ስራ ተከናወነ፡፡
ኮሌጁ በዘንድሮ አመት የ12ኛ ክፍልን ጨርሰው ከፍተኛ ትምህርትና ኮሌጆችን ለሚቀላቀሉ ተማሪዎች በተዘጋጀው የገጽ ለገጽ ቅስቀሳ ስራ ላይ እና የኮሌጅ ጉብኝት መርሀ ግብር የተከናወነ ሲሆን ኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም እና ኮሌጁ ቀጣይ ሊደርስበት ካሰበው ስኬት አንጻር ኮሌጁ እኛ ላይ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት የሰራው ስራ የሚበረታታ ነው ያሉ ሲሆን በጉብኝቱም ኮሌጁ ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ሲታይ የተሸለ አቅም እንዳለው ለመረዳት ችለናል ብለዋል በመቀጠልም ሰልጣኞችን በእውቀት፣በክህሎትና በአመለካከት የዳበረ ትውልድ ለማፍራት እና ስራ ፈጣሪ የሆነ ትውልድ ለማፍራት የሚያስችል እምቅ አቅም እንዳለው ተገንዝበናል ብለዋል፡፡በቀጣይም ለሚኖረን የክረምት ጊዜ እንዲሁም የመደበኛ የትምህርት ሰአት ኮሌጁን ተመራጭ በማድረግ የሞያና የክህሎት ባለቤት ለመሆን ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 11/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ
በሀገረ አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ 800 ሺህ ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
ሐምሌ 10/2015 የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች
ችግኝ በመትከል መርሐ-ግብሩ ዛሬ ማለዳ መካሄድ ጀምሮ ለዚሁ መርሃ ግብር በተዘጋጀው የአየር ሃይል ጊቢ ውስጥ በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን ለትውልድ ተሻጋሪ የሆነውን ይህን ተግባር ላይ በመሳተፋቸው የተሰማቸውን ደስታ የገለጹ ሲሆን ይህ ተግባርም እስከ ምሽት 12 ሰዓት ቀጣይነት የሚኖረው ይሆናል፡፡
ነገን ዛሬ እንተክላለን!
የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
