ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 097
المشتركون
+424 ساعات
+267 أيام
+2530 أيام
أرشيف المشاركات
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ክህሎት ለሽግግርና ቀጠናዊ ትስስር ፕሮጀክት(EASTRIP) በራስ አቅም ያስጠናው የምሩቃን እና የስራ ገበያና ፍላጎት የጥናት ውጤት ሪፖርት የቀረበበት መድረክ ተካሄደ፡፡ ይህ የዳሰሳ ጥናት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር ያለብንን ክፍተት የለየና በቀጣይ በምን የስልጠና መስኮች ስልጠናዎችን መስጠት እንደሚኖርብን ያመላከተ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ ኃላፊዋ በንግግራቸው ወቅት ወጣቶችን አሰልጥኖ ማስመረቅ ብቻ ሳይሆን በሰለጠኑበት ሙያ ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉ ሰልጣኞችን ወደ ገበያው ማስገባትና ክትትል ማድረግ እንዲሁም የድሬዳዋና የአካባቢውን ጸጋ ተጠቅመው ራሳቸውንና አካባቢያቸውን መለወጥ የሚችሉ ሰልጣኞችን ማፍራት ላይ ትኩረት አድርገው ኮሌጆች መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስራዎችን እየሰራበት ያለው መንገድ የሚበረታታና ለሌሎች አቻ ኮሌጆች እንደ ተሞክሮ የሚቀርብ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ዲን የሆኑት አቶ ሳሊም ኡስማን እንዳሉት ይህ የዳሰሳ ጥናት በተከታታይ ሁለት አመታት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገበያው ከሚፈልገው የሰው ሀይል ፍላጎት አንጻር ያሉበትን ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበረና የጥናቱ ውጤትም ኮሌጁ ከተቋቋመበት አላማ አንጻር ሲታይ አላማውን ለማሳካት ምን አይነት ስራዎችን በቀጣይ መስራት እንዳለበት የጠቆመ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉ ሲሆን በቀጣይ በዳሳ ጥናቱ የተገኙ ግብአቶችን እቅድ ውስጥ በማካተት የሚሰራ ይሆናል በማለት በመጨረሻም ለዚህ ጥናት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ጥናቱን አስመልክቶ የEASTRIP ፕሮጀክት የM & E Specialist የሆኑት አቶ መሳይ ጥላሁን እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በICOS Consulting PLC ተመሳሳይ ጥናት መደረጉን አስታውሰው አሁን የተጠናው ጥናት በራስ አቅም ማስጠናት መቻላችን በወጪ ረገድ ዋጋ ቆጣቢ የሆነና ከመረጃ ጥራት ጋር በትኩረት መስራት እንድንችል ያደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጃችን ከኢንዱስትሪው ጋር የማስተሳሰር ስራ እንዲሁም ቀሪ ጥናቶችን ደግሞ ሁሉን አሳታፊ አድርገን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክትር ፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ም/ኃላፊ፤የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊዎችና ተወካዮች፤የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት፤የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላቶች እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መስከረም 12/2016 ዓ.ም ሀረር

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቢሮው ለሚገኙ ሠራተኞች ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለልጆቻቸው መማሪያ የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ:: ቢሮው ከዚህ
+5
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቢሮው ለሚገኙ ሠራተኞች ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለልጆቻቸው መማሪያ የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ:: ቢሮው ከዚህ ቀደም ሠራተኛውን ሊደጉሙ የሚችሉ የፍጆታ ግብዓቶችን በቅናሽ በማቅረብ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው።

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) ጋር በመተባበር እድሜያቸው ከ 18 እሰክ 35 የሆኑ ለተደራጁ ዘጠኝ ኢንተርፕራይዞች የኢንተርፕሩነርሺፕና የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው ግምቱ ሃምሳ ሺህ ብር የሚገመት ለእርባታ የሚሆኑ የዶሮዎች ድጋፍ ተደረገ፤ የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ የቢሮው ተወካይ እና የቀበሌ የአንድ ማዕከላት እንዲሁም የእንስሳት ጤና እና ሀብት ልማት ተወካይ በተገኙበት የተደረገ ሲሆን ድጋፉን በተመለከተ ንግግር የደረጉት የSNV ድርጅት ተወካይ አቶ ኃይለየሱስ ለምለም የተደራጁት ወጣቶች የሥራ እድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንደሚፈጥሩ እንዲሁም ለሌሎች ምሳሌ በመሆን ዶሮ እርባታ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት አሁን በመጀመር በቀጣይ አስፍተውና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ከባለሙያዎች ጋር ገለጻ አድርገዋል፤ አክለውም ድርጅታቸው ከቢሮው ጋር በመተባበር ሥራ የሌላቸው ሴቶችና ወጣቶችን በገጠርና በከተማ በማደራጀት በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮዎች በተለይ በኢንተርፕሩነርሺፕና በህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት እና ተደራጅተው በሚሰማሩበት ሥራ ዘረፍ ላይ አሰፈላጊው ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰው የዛሬውን ድጋፍ ጨምሮ በአጠቃላይ ለሃያ ስድስት በከተማና በገጠር ለተደራጁ ወጣቶች ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ መደረጉንና በቀጣይም በተመሳሳይ ኢንተርፕራይዞቹን በቅርበት በመከታተል ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ በመቀጠል ድጋፍ የተደረገላቸው ተጠቃሚዎች እንደተናሩት በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮና በSNV የጋራ ትብብር ለተሰጣቸው  ስልጠና እና የአይነት ድጋፍ በማመስገን ለበለጠ ሥራ ለመሥራት እንደሚያነሳሳቸው ተናግረው ከዚህ በፊት በዚሁ የዶሮ እርባታ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት የጀመሩትን  አስፍተውና አጠናክረው ለመስራትም መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡  የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት 105 ደርዘን ደብተር ባለ50 ፍሬ የሚይዝ 6 ፓኬት ብዕር እንዲሁም ባለ12 ፍሬ የሚይዝ 12 ፓኬት ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት 105 ደርዘን ደብተር ባለ50 ፍሬ የሚይዝ 6 ፓኬት ብዕር እንዲሁም ባለ12 ፍሬ የሚይዝ 12 ፓኬት ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች ልጆች የሚሆን የመማሪያ መርጃ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ፡፡ ይህንንም ድጋፍ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ፈጡም ሙስጠፋ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ ያስረከቡ ሲሆን በቀጣይም መሰል ድጋፍ ማድረግ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዘጠኙም የከተማ ወረዳ አስተዳደር ስር ከሚገኙ አስራ አንድ የወረዳ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ጋር  የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ስራዎችን በመቁረስ ለአስራ አንዱም የቀበሌ አንድ ማዕከላት ማውረድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት እንደሚደረግና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ ከታቀደው በዋናነት ከተመላከተው፡-   14,300 ስራ ፈላጊዎች ይመዘገባሉ፡፡   14,456 ቋሚ የስራ ዕድል ይፈጠራል፡፡   3,554 ጊዜያዊ የስራ ዕድል ይፈጠራል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

photo content

የድሬዳዋ አሰተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት በቀበሌ 05 እና በ08 አስተዳደር ስር የሚገኙ የሁለት አቅመ ደካማ እናቶችን የፈራረሰ ቤት በአዲስ ገንብቶ አስረከበ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ከሚገኘው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ውስጥ አንዱ አቅመ ደካማ የሆኑ ዜጎችን መደገፍ ነው። በዛሬው ዕለትም በሁለቱ ቀበሌ የሚገኙት እኚህ ቋሚ የገቢ ምንጭም ሆነ በአጠገባቸው የሚረዳቸው የሌለ፤ በፈረሰና ለመኖር እጅግ የሚከብድ ቤት ውስጥ በሚያሳዝን ሁኔታ እየኖሩ የሚገኙ እናቶች ናቸው። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሠራተኞችና አመራሩ ይህን ችግር በመረዳት የሁለቱን እናቶች መኖሪያ  ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርቶ በማጠናቀቅ ከአስፈላጊ የቤት ዕቃዎች ጋር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም ሌሎች የአስተዳደሩ አመራሮች በተገኙበት ርክክብ ተደርጓል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጳጉሜ 3/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ስራ አስኪያጅ አቶ አየለ ወ/ዮሀንስ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ተቋም ጋር በርከት ያሉ ስራዎችን በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልሓዲን አብዱልሓሚድ ሲሆኑ አጠቃላይ ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ከስራ ፈጣሪነትና ለኮሌጁ ተጨማሪ ገቢን ከማፈላለግ አንጻር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሌሎች አቻ ኮሌጆች አንጻር የተሸለ አፈጻጸም እንዳለው ያብራሩ ሲሆን በቀጣይም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ጋር መምህራንን ከማብቃት እንዲሁም ኮሌጁ ላይ ያለውን እምቅ አቅም ከመጠቀም አንጻር ሁለቱም ተቋማት አብረው በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ለዚህም ደግሞ ኮሌጁ ቁርጠኛ ነው ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑን የመሩት አቶ ተስፋዬ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ተቋም የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ከተማችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት በአቶ መሳይ ጥላሁን የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በኮሌጁ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጳጉሜ 2/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱ በአስተዳደሩ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ። በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በልጽጎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት የሰራተኛና የሥራ መረጃዎችን በዘመናዊ መንገድ በማስተዳደር ዜጎች በሃገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ስርዓት ነው። በመሆኑም በዛሬው ዕለት የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የቢሮው አመራሮች በተገኙበት ለተግባራዊነቱ የሚያስፈልጉ የባዮሜትሪክስ፣ የላፕቶፕ፣ የዋይፋይ ራውተር እና ሌሎች ቁሳቁሶች ለአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ርክክብ የተደረገ ሲሆን የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓቱ በድሬዳዋ የማገኙ በተመረጡ የወረዳ አንድ ማዕከላት አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸው ይሆናል። በዚህም ከዚህ ቀደም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ባስተላለፈው የምዝገባ ጥሪ መሰረት ከ180,000 በላይ ዜጎች በድረ-ገጽ (በኦን ላይን) ተመዝግበው የባዮሜትሪክስ ምዝገባ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ  ስራ ፈላጊዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ማለትም በአስተዳደሩ 02፣ 03፣ 05፣ 06፣ 07፣ 09 የወረዳ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች በአካል በመቅረብ አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጳጉሜ 1/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+5

#ጳጉሜን_1 #የአገልጋይነት_ቀን የአገልግሎት ቀንን ለተገልጋይ ብቻ!! በቀኑ ከተሰሙ ድምጾች "ሁሉም በተመደበበት ዘርፍ በአግባቡ ህብረተሰቡን በቅንነት በታማኝነትና በፍጥነት ማገልገል አለበት።" "ህ
+5
#ጳጉሜን_1 #የአገልጋይነት_ቀን የአገልግሎት ቀንን ለተገልጋይ ብቻ!! በቀኑ ከተሰሙ ድምጾች "ሁሉም በተመደበበት ዘርፍ በአግባቡ ህብረተሰቡን በቅንነት በታማኝነትና በፍጥነት ማገልገል አለበት።" "ህብረተሰቡን በአግባቡና በሚፈለገው ልክ ለማገልገል ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተገልጋዩን እርካታ ከፍ ለማድረግ መሠራት ይኖርበታል።" "ልናገለግልዎ ዝግጁ መሆናችንን ቃል በገባነው የአገልግሎት ስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት እናረጋግጣለን።" የአገልጋይነት ቀን በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፤ እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት በመከበር ላይ ይገኛል ። ዛሬ ያገለገልከዉ ነገ ያከብርሃል!

የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት እቅድ ገመገመ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት
+2
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት እቅድ ገመገመ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትላንትናው እለት የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት እቅድ የገመገመ ሲሆን በመድረኩም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢና አባላት እንዲሁም የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የማኔጅመንት አባላት ተገኝተውበታል። የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2016 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ የእቅዱ አዘገጃጀት በጥሩ ጎን የታየ ሲሆን የተሰጠው አስተያየትና ሀሳብ ተካቶበት ለምክር ቤት መላክ እንዳለበት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ©️ መረጃው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት

በአስተዳደሩ ከ6ሺ በላይ ወጣቶችን ወደስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ከስራ እድል ፈጠራ ጋር በተያያዙ ሊ
+8
በአስተዳደሩ ከ6ሺ በላይ ወጣቶችን ወደስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ከስራ እድል ፈጠራ ጋር በተያያዙ ሊቀርብ ስለሚገባው የፋይናንስ አቅርቦት ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ የምክክር መድረኩ በዋናነት የፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነትን በማሻሻል ረገድ ስራ ፈጣሪ ዜጎችን መደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ በስልጠና፣ ስራ ዕድል ፈጠራና በኢንቨስትመንት ስፍራዎች ላይ ምቹ የስራ ሁኔታን መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲገልጹ ተቋሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚንቀስቀስባቸው ጉዳዮች መካከል በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የማደራጀት፣ የማሰልጠን እንዲሁም የመስሪያ ቦታ ምችችት በማድረግ ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታዎችን መፍጠር ላይ በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተያዘው በጀት አመት አጋማሽም 524 ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት ለ6,029 ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የፋይናንስ ስልጠና እና ድጋፍ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ የተደራጁ ኢንተርፕራዦችን ወደ ስራ ለማስገባት በቂ የፋይናንስ አቅርቦት በማመቻቸትም በኩል በአስተዳደሩ የሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ከባንክ አመራሮች ጋር ከፋይናንስ አቅርቦት ድጋፍ ጋር በተያያዙ ሰፊ ውይይቶችን አካሂደዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊ የፋይናንስ ተቋማት አመራሮችም የአስተዳደሩ ነዋሪ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመቅረፍ ከልማቱ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸው የስራ ፈጠራ ሃሳብ ይዘው የፋይናንስ አቅም የሌላቸውን ዜጎች በማገዝ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡ ©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን

ቢሮው የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ-ግብርን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ-ግብር የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ መጀመሩ ይታወቃል፤ በዛሬው እለት በወረዳ 05 ለሚገኙ አጋዥ ለሌላቸው አባት ቤት ሰርቶ ለማስረከብ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ   የግንባታ ስራውን ለመጀመር ተረክበዋል። በተያያዘ በዚህ ክረምት በቢሮውና በሁለቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች በድምሩ 4 የአቅመ ደካሞች ቤትን በአዲስ ገንብተን የምናስረክብ አቅዶ ወደተግባር የገባ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ቀደም ሲል በይፋ እድሳታቸው የተጀመሩ ቤቶችን የግንባታ ሂደት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፤ በዚህም የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነው የመተጋገዝ እና የመደጋገፍ ባህልን መሰረት በማድረግ የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ በመቻላቸው ደስታ  እንደተሰማቸው ገልጸው ከዚህ በተጨማሪ ቢሮው በክረምቱ መርሃ-ግብር በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች በመሳተፍ ወገንና ሀገርን የማገዝ ሃላፊነቱን በንቃት የሚወጣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ነሐሴ 8/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ