1 085
Subscribers
+924 hours
+207 days
+1530 days
Posts Archive
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጣ ከፍተኛ ባለሙያ በ E-LMIS (Ethiopian Labor market information system) አተገባበር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለኮሌጁ ማህበረሰብ በዛሬው እለት ተሰጠ::
የE-LMIS በስራና ክህሎት ሚንስቴር መስሪያ ቤት የበለጸገና የስራና ሰራተኛ ፍላጎትን ለማቀራረብ ታስቦ የተሰራ ሲስተም ሲሆን በተለይ በቴክኒክና ሙያ በኩል ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁና ለምናሠለጥናቸው ሠልጣኞች የሥራ ትስስር ለመፈጸም የሚያግዝ ሲስተም ሲሆን የሀገራችንን የስራ አጥ ቅነሳው ስራ ላይ የራሱን ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችል ተደርጎ የበለጸገ ሲስተም እንደሆነ በግንዛቤ ማስጨበጫ ወቅት ተብራርቷል፡፡
በተጨማሪም ይህ ሲስተም ሲበለጽግ ተጨማሪ ከሌሎች ሲስተሞች የሚለይበትን ጉዳይ በባለሞያው ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ የውጪ ሃገር ስራ ስምሪት እንዲሁም ከቅጥር ጋር የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ ታስቦ እንደተሰራም በእለቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኮሌጁ ኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ዲን ወይዘሮ ትግስት በዙ እንዲሁም የዲፖርትመንት ተጠሪዎችና የማኔጅመንት አባላቶች መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡
የኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ግንቦት 07/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
አስተዳደሩን ፀጋ መሰረት ያደረገ ክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል፥ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ
ግንቦት 6/2016 ዓ/ም
የክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር ተያይዞ ገበያ ተኮር አጫጫር ስልጠናዎች አፈጻጸም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚመክር መድረክ ተካሄደ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት በተዘጋጀው መድረክ ላይ የአስተዳደሩ የከተማ ወረዳዎችና የገጠር ክላስተር አመራሮች፤ የአንድ ማዕከላት አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ከስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር በሁሉም ወረዳዎች ፀጋን መሰረት ያደረገና ክህሎት መር በሆነ መንገድ ማህበራትን በማደራጀት በተለይ ኮሌጆች በሚሰጧቸው ስልጠናዎች ተጠቃሚ ለመሆን በቅንጅት ሁሉም አካላት በመናበብ የሚሰሩበት ሁኔታ መፈጠር አለበት ብለዋል።
በመጨረሻም ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ እስከ አሁን ስልጠና እየተሰጠ ካለባቸው የተወሰኑ ዘርፎች በተጨማሪ በሌሎች ዘርፎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በየአካባቢው ወደ ስራ ያልገቡ ወጣቶችን በመለየት ወደ ስራ እንዲገቡ በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባው በመግለጽ ቀጣይ ሥራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ማጠቀለያ ሰጥተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተገነባ የሚገኘው የEASTRIP ፕጀክት የ Railway ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ህንጻ ግንባታ ያለበትን ደረጃ የድሬዳዋ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የኮሌጁ የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በተገኙበት የአንድ ወር የግንባታ አፈጻጸም ግምገማ በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በግምገማው ላይ የልህቀት ማእከሉ አሁን ያለበትን ደረጃ በአማካሪ ድርጅቱ ተወካይ እንዲሁም ግንባታውን ለመገንባት ውል የገባው የአተም ኮንስትራክሽ ድርጅት ተወካይ በኩል ቀርቧል፡፡
በሪፖርቱ መሰረትም የተለያዩ ውይይቶች የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንዳሉት ይህ ህንጻ እንደ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ ከሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ስለዚህ የህንጻው ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለታለመለት አላማ እንዲውል ሁሉም አካላት በጋራ እና በርብርብ መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ግንቦት 2/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ለመስራትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የወረዳ እንዲሁም የክላስተር ማእከላት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል››
አቶ ሳሊም ኡስማን
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
*******************************
በድሬዳዋ ከተማ ያሉ ስራ ፈላጊ ወጣቶች የስልጠና ፍላጎትን በመለየት በፍላጎታቸው መሰረት ስልጠናዎችን መስጠት እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ከወረዳ እና ከክላስተር ከተውጣጡ አመራሮች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተዘጋጀ፡፡
ውይይቱን የመሩትና የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጃችን በላባቸው አምርተው በእጃቸው ሰርተው እራሳቸውን መጥቀም የሚችሉ ከዛም አልፎ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች የሚፈሩበት ትልቅ ተቋም ነው፡፡ ስልዚህም በዚህ ተቋም እና በወረዳዎች እንዲሁም በክላስተር ማእከላት ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ለመስራትና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የወረዳ እንዲሁም የክላስተር ማእከላት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም በከተማም እንዲሁም በገጠር ያሉ ወጣቶችን የክህሎት ፍላጎት ለማሟላት ይቻል ዘንድ Mobile TVET ለማቋቋም እቅድ ይዘን እየተንቀሳቀስ እንገኛለን ይህም የወጣቶቻችንን የስራ በሃል እንዲሻሻል እንዲሁም በኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚፈጠረው የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በኢንተርፕራይዝ ልማት እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት አንጻር በከተማም እንዲሁም በገጠር የሚገኙ ወጣቶች በኮሌጃችን ያለውን እምቅ አቅም እንዲጠቀሙ በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ግንቦት 2/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
የግብርናውን ዘርፍ ሊያዘምኑ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን ለማሻሻልና ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማዘመን የአስተዳደሩን የገጠር ነዋሪ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን መስራት እንዲያስችለው ከአስተዳደሩ የግብርና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ጋር ከዚህ በፊት የተደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር መቀየር ባለባቸው ጉዳዮች ላይ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እንዲሁም የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አመራርና ቴክኖሎጂ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራን በተገኙበት ውይይት በማድረግ በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መግባባት ተፈጥሯል፡፡
በዚህ የሁለትዮሽ የውይይት መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተሰሩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተግባር ለማስገባት በቅንጅት መስራትና በተለይ የተጠቃሚውን ማህበረሰብ ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡
አቶ መሀመድ አሚን የአስተዳደሩ የግብርና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ም/ኃላፊ በበኩላቸው ፍላጎትን የመለየት ስራ በጋራ የሚሰራበትን ሁኔታ በማመቻቸትና የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት ኃላቀር የአስተራረስ አካሄድን ለመቀየር በቁጭት መነሳት ይገባናል ያሉ ሲሆን በቀጣይ አመራሩ በበላይነት የሚመራው ከሁለቱም ቢሮዎችና ኮሌጆች የተወጣጡ ቴክኒካል ኮሚቴዎችን በማዋቀር ወደ ስራ ለመግባት ከስምምነት ተደርሷል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 1/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የግብርናውን ዘርፍ ሊያዘምኑ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን ለማሻሻልና ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማዘመን የአስተዳደሩን የገጠር ነዋሪ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን መስራት እንዲያስችለው ከአስተዳደሩ የግብርና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ጋር ከዚህ በፊት የተደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር መቀየር ባለባቸው ጉዳዮች ላይ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እንዲሁም የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አመራርና ቴክኖሎጂ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራን በተገኙበት ውይይት በማድረግ በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መግባባት ተፈጥሯል፡፡
በዚህ የሁለትዮሽ የውይይት መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተሰሩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተግባር ለማስገባት በቅንጅት መስራትና በተለይ የተጠቃሚውን ማህበረሰብ ግንዛቤ ማሳደግ ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡
አቶ መሀመድ አሚን የአስተዳደሩ የግብርና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ም/ኃላፊ በበኩላቸው ፍላጎትን የመለየት ስራ በጋራ የሚሰራበትን ሁኔታ በማመቻቸትና የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት ኃላቀር የአስተራረስ አካሄድን ለመቀየር በቁጭት መነሳት ይገባናል ያሉ ሲሆን በቀጣይ አመራሩ በበላይነት የሚመራው ከሁለቱም ቢሮዎችና ኮሌጆች የተወጣጡ ቴክኒካል ኮሚቴዎችን በማዋቀር ወደ ስራ ለመግባት ከስምምነት ተደርሷል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 1/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ ባለሙያዎች በ E-LMIS ሲስተም አተገባበር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ምክትል ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ እንዲሁም የዲፖርትመንት ተጠሪዎችና በሂደቱ ስር የሚገኙ ባለሙያዎች በተገኙበት ስለ ሲስተሙ አሠራር፣ ፋይዳ እና ዉጤት ከዉጭ ሃገር ሥራ ስምሪትና የውስጥ ሥራ እድሎችን በማመቻቸት ላይ እንዲሁም የተለያዩ ብልሹ አሠራሮችን ለማስቀረት የስርዓቱ ሚና የጎላ መሆኑንና ለዜጎች በE-LMIS ሲስተም ምን ጥቅሞች እና እንዴት በቀረበላቸው ሲስተም መጠቀም እንደሚችሉ ጥልቅ የሆነ ግንዛቤ ተሰጥቷል።
እንዲሁም የE-LMIS ሲስተም ተጠቃሚ ለመሆን እንዴት በራስ መመዝገብ እንደሚቻል እና በቀረቡት ብዙ አማራጮች ተጠቃሚ መሆን ኢንደሚችሉም በቂ የሆኔ ግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፡፡ በዓሉ የደስታ፣ የሰላም፣ የጤና እንዲሁም የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን፡፡
መልካም በዓል!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና
ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
ለመላ የክርስትና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም በዓል!
****
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የ2016 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
መድረኩም በአዲሱ አገራዊ እሳቤ መሰረት አድርጎ ለዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የሥራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደው ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከስራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ረገድ እንደ አስተዳደር በከተማና በገጠር የተሰሩ ስራዎች ተገምግመዋል፡፡
በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች፣ የወረዳ ሥራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች እንዲሁም የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ አስተባባሪዎች በተገኙበት በ2016 በጀት አመት በዘጠኝ ወራት የተሰሩ አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ በተለይም በብቃት ፕሮግራም የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ በአጭር እና በረጅም መሰራት በሚገባቸው ስራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
በመድረኩም ላይ የቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በቢሮ እና በአንድ ማዕከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ስራዎችን አበረታተው በቀጣይ በተለይ በአዲሱ ዕሳቤ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ዘለቄታቸውን እና አስተማማኝነታቸውን ከማረጋገጥ አኳያ ድጋፍ እና ክትትሎችን አጠናክሮ መቀጠል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 23/2016 ዓ.ም
ሐረር
በኢትዮጵያ ለ49ኛ በአለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ135ኛ ጊዜ እየተከበረ ላለው የአለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን እንኳን አደረሳችሁ!
ቀኑን ስናከብር የሠራተኞችን ጥቅምና መብቶች የማስከበር እንዲሁም ደህንነታቸውን የማስጠበቅ ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል ቁርጠኝነታችንን የምናሳይበት ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
ድሬዳዋ
የ2016 ዓ.ም የላብአደሮች ቀን በድሬዳዋ ናሺናል ሲሚንቶ አ.ማ ቅጥር ግቢ ቡስጥ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ
ቀኑን በማስመልከት የቻይና ቲም ሰራተኞችና ኢትዮጵያዉያን ሠራተኞች የተሳተፉበት የተለያዩ አዝናኝ ስፖርታዊ ጫወታዎች ተካሄደዋል::
ሚስተር ዣንግ ለሰራተኞች ኢለቱን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላልፈዋል
ዕለቱን በማስመልከት በመረሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዉ መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ተወካይ የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም የዘንድሮ በዓል በአዲሱ እሳቤ ምርትና ምርታማነትን ማዕከል ያደረገ መርህ የሚከበር መሆኑን ገልፀዉ አሰሪና ሰራተኛዉ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ግንኙት ማደበር እንደሚጠበቅባቸዉ መልዕክታቸዉን አሰተላልፈዋል
በዕለቱ በተካሄዱ ስፖርታዊ ዉድድሮች በግልና በቡድን አሸናፊ ለሆኑ በድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ Mr.ዣንግ ሚንሂንጉኣ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል::
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
