1 064
Subscribers
No data24 hours
-77 days
+230 days
Posts Archive
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎፈቃድ ስራዎች ማስጀመሪያ እና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በኮሌጁ ተካሄደ።
በዘንድሮ ክረምት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን ይህን ምክንያት በማድረግም በተቋም ደረጃ በኮሌጁ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩን በዛሬው ዕለት ማከናወን ተችሏል::
በዛሬው ዕለት በኮሌጁ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በተቋሙ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ስፍራ ላይም አሻራቸውን እኑረዋል::
በቀጣይም በኮሌጁ የክረምት የበጎፍቃድ ስራዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የሚያከናውኑ ሲሆን በዚህም የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ መሰል ማህበረሰብ ተኮር ንቅናቄዎች ላይ እንደሚሰራ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ሃቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያ (Habitat For Humanity Ethiopia) የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከድሬዳዋ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ድርጅቱ ለገሃሬ አካባቢ ባስክፊ ሁኔታ (informal settlement) እየኖሩ ለነበሩ 28 አባውራዎች በመልካ ደረጃውን የጠበቀ መኖሪያ ቤት የገነባላቸው ሲሆን በእነዚህ ወላጆች ስር ለሚገኙ ሀምሳ አንድ የቤተሰብ አባላት (ወጣቶችና ሴቶች) ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር አቅማቸውን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማጎልበት ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጣሪ ሆነው የኑሮ መሰረታቸውን እንዲያሻሽሉ (sustainable livelihood) በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአጫጭር ስልጠና ዕድል ተመቻቸላቸው።
ድርጅቱ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሰው ተኮር የሆኑ የመኖሪያ ቤት ግንባታ እና እድሳት እንዲሁም የመጠጥ ውሃ የመሳሰሉ ስራዎችን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ (highly vulnerable and low-income group) ላይ ለሚገኙ እና ለተለያዩ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ሃቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያ (Habitat For Humanity Ethiopia) የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ስናይ ድርጅት ከድሬደዋ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ድርጅቱ ለገሃሬ አካባቢ ባስክፊ ሁኔታ (informal settlement) እኖሩ ለነበሩ 28 ኣባውራዎች በመልካ ደረጃውን የጠበቀ መኖሪ ቤት የገነባላቸው ሲሆን በነዚህ ወላጆች ስር ለሚገኙ ሀምሳ አንድ የቤተሰብ ኣባላት (ወጣቶችና ሴቶች) ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር አቅማቸውን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማጎልበት ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጣሪ ሆነው የኑሮ መሰረታቸውን እንዲያሻሽሉ (sustainable livelihood) በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአጫጭር ስልጠና ዕድል ተመቻቸላቸው።
ድርጅቱ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሰው ተኮር የሆኑ የመኖሪያ ቤት ግንባታ እና እድሳት እነዲሁም የመጠጥ ውሃ የመሳስሉ ስራዎችን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ (highly vulnerable and low-income group) ላይ ለሚገኙ እና በተለያዩ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ኣደጋዎች ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ማስተባበሪያ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር የ2018 በጀት ዓመት ለወረዳዎቹ የተሸነሸነ ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ሥራዎችን በመቁረስ በከተማና በገጠር ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ማውረድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት እንደሚደረግና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡
ዕቅዱን ወደ ታች ሸንሽኖ ከማውረድ ስራው ጎንለጎን በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ በ2018 ዓ.ም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች በተለይም በቀጣይ በአገራዊና በዘርፉ አዲስ ዕሳቤዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ ይዞ የተናበበና የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ የተመላከተ ሲሆን በዋናነት የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ንግድ፤አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ማደራጀት፤ ከኢ-መደበኛ ወደ መደበኛ የሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞችን ማስፋፋት አንዲሁም የማደግ አቅም ያላቸው ኢንተርፕራይዞች መለየት እና መደገፍ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ለሥራ ፈላጊዎች
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተለያየ የሥራ ዘርፍ በቋሚነት፣ ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በዝውውር እና በኮንትራት የቅጥር አይነት፤ ከዜሮ ዓመት እስከ አስር ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸውን 237 ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በለማው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) በመጠቀም ምዝገባው ይካሄዳል፡፡
ስለሆነም የዚህ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን lmis.gov.et ላይ በመመዝገብና አቅራቢያችሁ ባለ ወረዳ/ቀበሌ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሠራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ ማግኘት ይኖርባችኋል፡፡
የተሰጣችሁን የሠራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ በመጠቀም በዚህ ማስፈንጠሪያ (https://forms.gle/AMm2LCHBvdqMwW5AA ) ላይ በመገባት ትክክለኛ የትምህርት፣ የሥራ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በማሰገባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ምዝገባው ይህ ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ይካሄዳል፡፡
ነሐሴ 8/2017 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 ዓ.ም መሪ እቅድ ለኮሌጁ የቦርድ አባላት አቀረበ፡፡
በበጀት አመቱ የተቋሙን አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ በበጀት አመቱ የነበረውን የእቅድ አፈፃፀምና አጠቃላይ በኮሌጁ የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን እንዲሁም የተገኙ ውጤቶችን ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበው ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊሰሩ በእቅድ የተያዙ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን የሚያመላክት የ2018 ዓ.ም መሪ እቅድ ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር አመላክተዋል፡:
በመድረኩ የቀረበውን ሪፖርትና መሪ እቅድን መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ግብረ- መልሳቸውን የሰጡበት ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው የስራ እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል::
በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በቀረበው የኮሌጁ አጠቃላይ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያን በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በአስተዳደሩ ለሚገኙ ወጣቶች የክረምት ወቅት የሙያ ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ተጀመረ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክረምት ወቅት አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃ-ግብር በአስተዳደሩ እረፍት ላይ ለሚገኙ የአጠቃላይ የ1ኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ስልጠናዎችን መስጠት ጀምሯል::
ለወጣቶቹ በተዘጋጀ ኦረንቴሽን ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልዕክትም የዚህ የክረምት ወቅት ስልጠና የተዘጋጀበት ዋና አላማ ወጣቶች እረፍታችሁን ቁምነገር ላይ በማዋል ቢያንስ በክረምቱ የአንድ ሙያ ባለቤት እንድትሆኑ ለማስቻል ነው ያሉ ሲሆን አክለውም የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ክረምቱን በኮሌጃችን በሚኖራችሁ ቆይታ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት የምትገነዘቡ በመሆኑ በቀጣይ ምዕራፋችሁ ለሙያ ተኮር ስልጠናዎች ቅድሚያ እንድሰጡ ያግዛችኃልም ብለዋል::
የአንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ የክረምት ስልጠና ላይ ለመሳተፍ ወደ ኮሌጁ የመጡ ወጣቶች በቅድሚያ የህይወት ክህሎት ስልጠና ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚወስዱ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናው ወጣቶች የቀጣይ ህይወታቸውን የመምራት ክህሎት፣ችግሮችን የመፍታት ክህሎት እንዲሁም የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎቶችን እንደሚያገኙበት የተገለፀ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ በቀጣይ በመረጡት የሙያ ዘርፍ ላይ ስልጠናቸውን የሚጀምሩም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የውጭ ተጓዦች ተጠቃሚነት
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ለሥራ ዕድል ፈጠራ የፋይናንስ አቅርቦት
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በዛሬው ዕለት የብልጽግና ፓርቲ ድሬደዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደረጀ ጸጋዬ፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም የኮሌጅ ዲኖች፣ አሰልጣኝ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት የ2017 የክረምት በጎፈቃድ ስራዎች ማስጀመሪያ እና የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።
የዛሬው ችግኝ የመትከል መርሐ-ግብር በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጊቢ ውስጥ በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን የተከናወነ ሲሆን ለትውልድ ተሻጋሪ በሆነው በዚህ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ተሳታፊዎች የተሰማቸውን ደስታ የገለጹ ሲሆን ይህ ተግባርም በቢሮው የሚተገበረው የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች መጀመሪያ መሆኑና በቀጣይም ለአቅመ ደካሞች ቤቶችን በመስራት፣ በደም ልገሳ እንዲሁም ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን በማገዝ የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል፡፡
በመትከል ማንሰራራት!
ፎቶ፦ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት
ዘገባ፦ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉን ለማጠናከር በአስተዳደሩ ገጠር ቀበሌዎች ተደራጅተው የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት(LLRP) አጠቃላይ አፈጻጸም እና ቀጣይ ዕቅድ ላይ ከቴክኒካል ኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በዚህም በ2017 ዓ.ም ትግበራ አስራ አምስት በግብርና ዘርፍ እያንዳንዳቸው አምስት መቶ ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ የተደረገላቸው የተለዩ ስራ ፈጣሪ በሴቶችና በወጣቶች የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን ተደራሽ ማድረጉ በአፈጻጸሙ ተመላክቷል፡፡
በውይይቱ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ከዚህ ቀደም በአጠቃላይ የሥራና ክህሎት ስራዎች ተደራሽነት ጋር በተያያዘ ተቀናጅቶ እና ተናብቦ የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች በሚሰሩበት አግባብ ላይ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በተለይም በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ትኩረት በመስጠት የገጠር ስራ ዕድልን ስርዓትን ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ማረምና መለወጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በቀጣይ ፕሮጀክቱ በተለያዩ ዘርፎች የተደራጁ አርባ ለሚሆኑ ኢንተርፕራይዞች ለእያንዳዳቸው ከአንድ ሚልዮን ብር በላይ ድጋፍ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ ማወቅ ተችሏል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
