69
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-430 days
Posts Archive
69
+1
#ቲክቶክ #ስናፕቻት
አልባኒያ ውስጥ አንድ የ14 ዓመታ ታዳጊ ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደለ በኃላ የሀገሪቱ መንግሥት ቲክቶክ እና ስናፕቻትን እስከወዲያኛው ለማገድ ሊያቅድ እንደሚችል ተነገረ።
ባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት በዋና ከተማዋ ቲራና በሚገኝ ፋንኖሊ በተባለ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ በሌላ ተማሪ በስለት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሏል።
ተማሪዎቹ ክርክራቸው እና አለመግባባታቸው የጀመረው በማህበራዊ ሚዲያ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የሀገሪቱ ጠ/ሚ ኢዲ ራማ ባለፈው ሳምንት ከሀገሪቱ የካቢኔ ስብሰባ በኃላ በሰጡት ቃል ፤ " አሰቃቂው የታዳጊው ሞት ከመንግሥት እንዲሁም ከህብረተሰቡ ጠንካራና ውጤታማ ምላሽ የጠየቀ አሳዛኝ ክስተት ነው " ብለዋል።
ይህን ተከትሎ ቲክቶክና ስናፕቻት እስከመጨረሻው ድረስ ሀገሪቱ ላይ ለማገድ እናስብበት ይሆናል ሲሉ ገልጸዋል።
አንዳንድ ሀገራት ከ16 አመት በታች ለሆኑ ልጆች የማህበራዊ ሚዲያ ተደራሽነትን እንደሚገድቡ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስካሁን ሀገሪቱ የማጣሪያ መንገዶች (ለልጆች የማይሆኑትን ማጣሪያ ሲስተም) ውጤታማ ከሆኑ በሚል ሲታዩ ቢቆዩም ውጤት አልባ እንደሆኑ ገልጸዋል።
" ይልቅም የኦንላይን ጥቃት ፣ ሰዎችን ማዋረድና ማጥቃት እየጨመረ መጥቷል " ብለዋል።
ራማ ቲክቶክ እና ስናፕቻትን እስከመጨረሻ የማገድ ሃሳቡ ከወላጆች እና ትምህርት ቤቶች ጋር ውይይት እንደሚደረግበት ጠቁመዋል።
ይህም የውሳኔ አሰጣጡ ሂደት በተቻለ መጠን ዲሞክራሲያዊ መሆኑን ለማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል።
#TikTok #Snapchat #Albania
@tikvahethiopia
69
#ጥቆማ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ጥሪ ማስታወቂያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ በቀጣይ የካቲት ወር በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገች ነው።
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአቀባበል እስከ አሸኛኘት ባለው የመስተንግዶ መርሃግብር በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል ካዴቶችን በመቀበል አሰልጥኖ በተለያዩ የፕሮቶኮል ሥራዎች ላይ ማሰማራት እንደሚፈልግ ገልጿል።
በመሆኑም ፦
- የእንግሊዘኛ፣
- የፈረንሳይኛ
- የዓረብኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ የሚችሉ እና ዕድሚያቸው ከ18-30 የሆነ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ከህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።
ምዝገባው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋናው መ/ቤት በአካል በመገኘት ነው የሚከናወነው።
ተመዝጋቢዎች ለምዝገባ ሲመጡ የትምህርት ማስረጃቸውን እና ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው እንዲቀርቡ ተብሏል።
ሚኒስቴሩ " የአገራት መሪዎች፣ የዓለምአቀፍና ቀጠናዊ ተቋማት ኃላፊዎች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በሚሳተፉበት የአህጉራችን ትልቁ ጉባዔ ላይ በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል በመሆን የዚህ ታሪክ አካል ሆናችሁ አገራችሁን ያለ ክፍያ በኩራት እንድታገለግሉ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
https://t.me/w_inf0
69
የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።
ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።
የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።
ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።
የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 08/2017 ዓ/ም እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ነው።
ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።
ተጨማሪ መረጃዎች፣ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፣ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም የወጡ ማስታወቂያዎች በዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረገጽ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ይመልከቱ 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
Via tikvahethiopia
69
Repost from Tikvah-University
#WolaitaSodoUniversity
በ2017 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።
በ2017 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ ጊዜ ወደፊት በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ ይደረግላችኋል ተብሏል።
@tikvahuniversity
69
+1
#DV2026 ዛሬ እኩለ ሌሊት ይጠናቀቃል‼️
ዲቪ ለመሙላት የመጨረሻ ቀናት ስትጠብቁ ለነበራቹህ ሰዎች ለዘንድሮ ዲቪ ለማመልከት ጥቂት ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል።
⚠️ዲቪ ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም።
ለማመልከት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ 👇
https://dvprogram.state.gov/
69
እንዳትቅጩ፣ትራምፕ መመረጡን ተከትሎ መጪው ጊዜ የክሪፕቶ ነው❗
Major ሁለት ቀናት ብቻ ቀረው‼️
ዋጋው እየጨመረ የመጣው ፕሮጀክት‼️
በራሱ በቴሌግራም መስራቾች እና በሌሎች የቴሌግራም entrepreneur የተመሰረተው Major ፕሮጀት ወደ ገንዘብ ሊቀየር ሶስት ቀናት ብቻ ቀርተውታል።
አሁንም ላልጀመራችሁ ሊንኩ ከስር ተቀምጧል👇👇👇https://t.me/major/start?startapp=5785896687
69
የአሜሪካ ዶላር እና ቢትኮይን ዋጋ ጭማሪ አሳየ...
47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ተደርገው የተመረጡት ዶናልድ ትራምፕ ለክሪፕቶከረንሲ ግብይት የግብር ቅናሽ እንደሚያደርጉ መናገራቸው ይታወሳል
የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ማሸነፋቸው ተረጋግጧል፡፡
ትራምፕ እስካሁን በተረጋገጡ የወኪል መራጮች ምርጫ አማካኝነት 278 በ224 ድምጽ እየመሩ የሚገኙ ሲሆን በቀጣዮቹ ሰዓታት ውስጥ የምርጫው አጠቃላይ ውጤት ይታወቃል፡፡
የዶናልድ ትራምፕን ማሸነፍ ተከትሎ ዶላር ከሌሎች ሀገራት መገበያያ ገንዘቦች ጋር ሲነጻጸር እስከ 2 በመቶ ብልጫ አሳይቷል፡፡
69
#በአዳማ ከተማ የተፈፀመ አሰቃቂ ወንጀል‼️
በአንድ ምግብ ቤት ውስጥ ማናጀርነት ተቀጥራ ምትኖር ሴት ተናግራኛለች በሚል ምክንያት በምግብ ቤቱ ፍየል የሚያርደው ልጅ የልጅቱ ቢሮ ገብቶ 4ጊዜ ልቧን ወግቶ አንገቷን አርዶ ቢሮዋን እራሷ ላይ ቆልፎ ተሰወረ።
በአዳማ ከተማ ወንጂ ማዞሪያ እቴቴ ሬስቶራንት በተባለ ጊቢ ውስጥ ነው ወንጀሉ የተፈፀመው ከቀኑ 7:33 በጠራራ ፀሐይ ሲሆን እድሜዋ 20 መጨረሻዎች የምትገኝ ወጣት ናት።
በሆቴሉም ገንዘብ ያዢነትና የሂሳብ ሰራተኞችን የመቆጣጠር ሃላፊነት ነበራት። ጥቃት የፈፀመባት ከትላንት በስቲያ አብሯት በሚሰራ ሰራተኛ ነው። ግለሰቡ ለሬስቶራንቱ ፍየል አራጅ ሲሆን "ቀን አብረው ገበያ ውለው መተዋል ሲሉ የአይን እማኞች ተናግረዋል።
ታዲያ በሩን ሰብሮ እርዳታ ለመስጠት የፖሊስ የአንቡላንስ አገልግሎት ማግኘት የተቻለው ከአንድ ሰዓት በኃላ ህይወቷ ካለፈ በኃላ ነበር።
69
Repost from Tikvah-University
+1
#DireDawaUniversity
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ህዳር 16 እና 17/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ማስረጃ፣
- የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
- ስድስት 3X4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የመኝታ አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ።
Note:
በ2016 ዓ.ም አንደኛ ሴሚስቴር ጀምራችሁ በተለያዩ ምክንያቶች ዊዝድሮዋል በመሙለት ያቋረጣችሁ ተማሪዎች፥ የሞላችሁትን ቀሪ ፎርም ይዛችሁ መሔድ ይጠበቅባችኋል፡፡
የ2017 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ የሪሚዲያል ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ወደፊት እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
@tikvahuniversity
69
JIjiga university
ለ ሁሉም የመጀመሪያ አመት አዲስ የተመደባቹ እና በ2016 በ ሬመዲዓል ስትከታተሉ ቆይታቹ የማለፊያ ነጥብ ያወጣቹ የመግቢያ ቀን ከ ህዳር 4-6 መሆኑን አሳውቋል ለበለጠ መረጃ ከላይ የተያያዘ ምስል ይጠቀሙ
የተረጋገጠ
69
#HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ኀዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡
የምዝገባ ቦታ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
- የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ግቢ
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➭ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➭ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➭ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
➭ የስፖርት ትጥቅ
69
#RayaUniversity
በ2017 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች እና በ2016 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የማጠናከሪያ ትምህርት (Remedial Program) ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 2 እና 3/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ትምህርት ህዳር 9/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡
69
#HaramyaUniversity
በ2017 ትምህርት ዘመን ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የፍሬሽማን ቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ከህዳር 9 እስከ 11/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ፦
- የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
- ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- የ12ኛ ከፍል ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- 6 ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
- ብርድልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
ከላይ የተዘረዘሩትን የትምህርት ማስረጃዎች እና ፎቶግራፍ ስካን አድርጋችሁ በሶፍት ኮፒ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
69
#OdaBultumUniversity
በ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ስትከታተሉ ቆይታችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያስመዘገባችሁ እና በ2017 ዓ.ም ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 4 እና 5/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ፦
- የ8ኛ ክፍል ስርትፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
69
የአሜሪካ ምርጫ በትራምፕ እና በሃሪስ እኩል ነጥብ ቢጠናቀቅ ምን ይፈጠራል?
******
የዴሞክራት ፓርቲ ፕሬዚደንታዊ እጩ ካማላ ሃሪስ እና የሪፐብሊካን ብርቱ ተፎካካሪያቸው ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ምርጫ ባላቸው ፉክክር የተነሳ እኩል ነጥብ ቢያመጡ ምን ይሆን መጨረሻው የሚሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎች የመከሰት እድላቸው ሰፊ ባይሆንም አይከሰቱም ማለት ግን አይቻልም።
አሜሪካውያን በእነሱ አቆጣጠር ከህዳር 5 ምርጫ በፊት ቀደም ሲል የእኔ ሚሉትን ወስነው እየጠበቁ የነበረ ቢሆንም፤በአሜሪካ ምርጫ ታሪክ ውስጥ እስከመጨረሻው ሰዓት የማይወስኑ እና በመጨረሻ ሀሳብ የሚቀይሩ “ስዊንግ ስቴትስ” በመኖራቸው ውጤቶችን ለመገመት አዳጋች ነው።
በአሜሪካ ሥርዓት ማን ፕሬዚደንት እንደሚሆን የሚወስነው የብሔራዊ የህዝብ ድምጽ ሳይሆን 538 አባላት ያሉት "የምርጫ ኮንግረስ" ነው።
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
