362
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
ጳጉሜን 5፤ 2016 - የነገ ቀን
“የዛሬ ትጋት፤ ለነገ ትሩፋት”
የትላንት የአባቶቻችን አሻራዎች ለዛሬ ማንነት አብሮነታችን መሰረት ጥለው በማለፋቸው ትውልድ በአርያነት ይዘክራቸዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን አብሮ የመኖር፣ የመቻቻልና የመተባበር አኩሪ ባህልና ታሪክ ያላቸው ህዝቦች ናቸው። በእነዚህ ዘመን ተሻጋሪ በሆኑ የጋራ እሴቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ሀገራዊ አንድነት የበለጠ እንዲጠናከር የነገ መዳረሻችን የተደላደለና ሁለንተናዊ ብልጽግናን በአጭር ግዜ እውን እንዲሆን በማስቻል ከፍሬው ተቋዳሽ የሚያደርግ ነው፡፡
የዛሬ ጥንካሬዎቻችን፣ አቅሞቻችን ለጋራ ስኬት ለጋራ ብልጽግና በአንድነትና በሕብረት ማሰለፍ መቻል የውጭ ወራሪ ድል አድራጊነት እንዲሁም የሕዳሴ ግድብ ወደ ማጠቃለያ ምዕራፍ መድረስ ነገ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ኢትዮጰያን ከፍ ያደረጉ ህያው የስኬት ምስክሮች ናቸው፡፡
ጳጉሜን 5 የነገ ቀን
“የዛሬ ትጋት፣ ለነገ ትሩፋት"
#Prosperity
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+4
“የምትተክል ሀገር፣ የሚያፀና ትውልድ”
የዘንድሮ የ#አረንጓዴዓሻራ ተካፋይ እንድትሆኑ ጥርዬን አቀርባለው::
“A nation that plants; a generation that sustains”
I call upon all to continue being a part of this year’s #GreenLegacy.
Repost from Prosperity Party A.A - ብልፅግና
+2
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይጀምራል።
በምክር ቤቱ በ4ኛ መደበኛ ጉባኤው ሊመክር ከያዛቸው ጉዳዮች ውስጥ:-
1. የም/ቤቱ 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ-ጉባዔ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
2. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
3. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዋና ኦዲተር የ2016 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
4. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት የ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
5. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
6. የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አደረጃጀት፣ አሰራር እና የአባላት ስነ ምግባር ማሻሻያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ እንዲሁም በሌሎች ልዩልዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ በማጽድ 3ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ያጠናቅቃል ተብሎ ይጠበቃል።
#aa_prosperity
የጤናውን ዘርፍ በተመለከተ :-
👉የምንከተለው ጤናማ የሆነ የአኗኗር ዘይቤን መፍጠርን ነው።
👉 ኮሌራን፣ ኩፍኝን ፣ ወባን እና ሌሎችንም በሽታዎች ለመከላከል ክትባትን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎች ተከናውነዋል።
👉 መድሀኒቶን ከውጭ በማስገባት ፍላጎቶቻችንን ሟሟላት ስለማንችል በራስ አቅም መዳኒቶችን ከማሟላት አኳያ ከ 8% ወደ 36 % ከፍ ማድረግ ተችሏል።
👉 የተወሰኑ መዳኒቶን ለተወሰኑ አገራት ማቅረብም ተጀምሯል።
👉 ሆስፒታሎች በግሉ ዘርፍም በመንግስትም እየተስፋፉ ነው ::
#aa_prosperity
ህግ ማስከበርን በተመለከተ፦
"ሶስት ክላሽ ሲይዙ አራት ኪሎ ይታያቸውና ውርውር የሚሉ አካላት፤ ትንሽ ሲቆነጠጡ ደግሞ ጀኖሳይድ ይላሉ፡፡ ይህ ተገቢነት የለውም፡፡ መንግስት በሰለጠነ መንገድ ችግሮች በውይይትና ድርድር እንዲፈቱ ቅድሚያ መስጠቱን እንደ ድክመት የሚቆጥሩ ካሉ፤ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላይ ጠንካራ ነው፡፡"
#aa_prosperity
ሲንከባለሉ የመጡ ፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊ እና ሌሎች እንዲሁም ወቅታዊ ችግሮች አሉ።
ለነባር ችግሮቻችን መፍትሄ ብሎ ለውጡ ያቀረበው ሀገራዊ ምክክርን ነው። ሁሉም ተመካክሮ የጋራ ሀሳብ መያዝ ስለሚገባው ነው።
የምክክሩ ውጤት ለነገ ነው። ያደሩ ችግሮቻችንን ለመፍታት ደግሞ የሽግግር ፍትህን እንተገብራለን።
👉 ጥያቄዎች ይነሳሉ ፤ ለጥያቄያች ምላሽ ሲሰጥም ጥያቄዎች ይነሳሉ። ታግለን ላመጣነው ፣ በልፋታችን ላስመዘገብነው ውጤት ክብር ሊኖረን ይገባል።
#aa_prosperity
ኢትዮጵያ ለምለም ትሆናለች ፤ከርሰ ምድሯና ገጸ አፈሯ ለም ነውና ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ምድሯን ያረሰርሳል ፤ተፈጥሮ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ትታደሳለች !!
ኢትዮጵያ ለምለም ትሆናለች ፤ከርሰ ምድሯና ገጸ አፈሯ ለም ነውና ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ምድሯን ያረሰርሳል ፤ተፈጥሮ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ትታደሳለች። በዛፍ መጨፍጨፍ የተራቆተው ምልክአ ምድራ ደን ይለብሳል ፤በአፈር መሸርሸር የደረቀው ሰውነቷ ሕይወት ይዘራል።
በነገዋ ኢትዮጵያ የድርቅ ንፋስ እንደፈለገ አያፏጭም ቢያፏጭም ድምጹ አያስተጋባም።የነገዋ ኢትዮጵያ ርጥብ ፣ለምእና በዛፎቿ ጥላ ሥር የሚታረፍባት ትሆናለች ።
መትከል እንጂ መንቀል ባህል መሆኑ ይቀራል ።ማሳደግ እንጂ መቁረጥ ልማድነቱ ያበቃል ።ሀገርም እንደሰው ካልተንከባከቧት እንደምትገረጣ ልጆቿን የምታጠባበት ጡት እንደሚነጥፍ የተገነዘበ ትውልድ ይመጣል።
ከመደመር ትውልድ ገጽ 96 የተወሰደ
መልካም ቀን
የቀደሙትን የኮሪደር ልማት ስራዎች ግምገማ ስናጠናቅቅ ቀጣዩን ግምገማችንን በስራው ስፍራ ተገኝተን እንደምናካሂድ ቃል ገብተን ነበር። የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር ስራ በተያዘው የሶስት ወር መርሃግብር ማጠናቀቃችንን ስገልፅ ደስታ ይሰማኛል።
በቀጣይ ስራ ሀብት ቁጠባ ቀዳሚ ትኩረት ሆኖ በቀሪ ኮሪደሮች ስራዎቻችን ፈጣን እና ፈጠራ መር ልንሆን ይገባል። ጥራትን ማስጠበቅ እና ለዜጎቻችን ሁሉ የተመቸ ከባቢን መፍጠር ቅድሚያ የምንሰጣቸው ተግባራት ናቸው።
ይህ ፕሮጀክት የሚራመደው በብዙሃን ትብብር ነው። ከጅማሮው በስራችን ባገኘነው በጎፈቃድ ምስጋና አቀርባለሁ። ይህም በእቅድ እና አፈፃፀም ላይ የታየውን ጥረታችንን እና መልካም ፈቃዳችንን የመጠነ ሆኖ ታይቷል።
በዚህ ከተማችንን ለተሻለ ለውጥ ለማብቃት በተደከመበት ታላቅ ስራ ሂደት ውስጥ በዜጎቻችን ላይ ፈጥረነው ሊሆን ለሚችል አለመመቸት ይቅርታ እንጠይቃለን። ኢትዮጵያችን እንድትለወጥ በፅናት እንደምንሰራ በዚህ የኮሪደር ልማት ስራ ሂደትም ያሉ የዲዛይን እና የጥራት ክፍተቶችም ካሉ ማስተካከል እንደምንቀጥል እንድትተማመኑ ለመግለፅ እፈልጋለሁ።
በግሉ ዘርፍ ያሉ አጋሮቻችንን ጨምሮ ትናንት ምሽት በጎዳናዎች ፍቅራችሁን ለገለፃችሁልን፤ በአጠቃላይም በዚህ ስራ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
#prosperity #aa_prosperity
#የሁለተኛው_አርበኝነት_ምዕራፍ_ጀግኖች
#heroes_of_the_second_patriotic_chapter
#ማን_ሰራው
#who_made_it
Repost from N/a
ህብረብሔራዊ አንድነታችን ለሁለንተናዊ ብልፅግናችን መሰረት ነው!
በሀገራችን የነፃነት፣ የእኩልነት፣ የዴሞክራሲና የልማት ጥያቄዎችና ፍላጎቶች እርስ በእርስ የተሳሰሩ ናቸው፡፡
ዴሞክራሲ ሳይረጋገጥ የብሔሮችን ጥያቄ ከመሰረቱ መፍታት እንደማንችለው ሁሉ፤ ኢኮኖሚያችን ሳያድግ ለዴሞክራሲ የተመቸ ህብረተሰብና ባህል መገንባት አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ በውይይት፣ በክርክር፣ በምክንያታዊነትና በሀሳብ የበላይነት የሚያምን፣ አብሮ በመስራትና በአብሮነት መልማትንና መከባበር የሚለማመድና ለተፈፃሚነቱ የሚተጋ እውነተኛ ሀገር ወዳድ ትውልድ መፍጠር የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን ግዴታ ነው፡፡
የብልጽግና ፓርቲና የለውጡ አቅጣጫዎች እውነተኛ ህብረ-ብሔራዊ ፌደራሊዝም ሥርዓት እየገነባን መሄድ፣ የዜጎች ነፃነትና ክብር፣ የኢትዮጵያውያንን ወንድማማችነት ማጎልበት፣ ዴሞክራስያዊነት እና ብልፅግናን ዕውን ማድረግ ነው። የብልጽግና ፓርቲን ዕሳቤዎችንና ራዕይ ሰንቀን የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ እናሳካለን!!
Repost from Prosperity Party A.A - ብልፅግና
+7
ባለፉት ጥቂት አመታት ዋናውን የዝናብ ወቅት ምርት ሳናስተጓጉል የበጋ ስንዴ ልማት ጥረታችንን ለማስፋፋት ችለናል። የዛሬው ምልከታ የስራዎችን ቀጣይነት የተመለከትንበት ነበር። ግብርና ጠንካራ ኢንቨስትመንት ይፈልጋል። በሰብል የምንሸፍነው የመሬታችን ይዞታም ቀስ በቀስ በመጨመር ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ( ዶ/ር)
#prosperity
#aa_prosperity
#aappaddis
ቅቡልነት ጠንካራ ትርክት ይፈልጋል::
ትርክት ማለት ዜጎች እንደ አንድ ማኅበሰሰብ ስላለፈው የጋራ ታሪካቸው፣ ዛሬ ላይ ስላላቸው ሁኔታና በቀጣይ ለመድረስ ስለሚያልሙት መዳረሻ የሚኖራቸው የጋራ ተቀባይነት ያለው ሀሳብ ነው::
ትርክቶች በፓራዳይም ውስጥ ይወለዳሉ:: ፓራዳይም ያለፉ ድሎቹቻችንንና ችግርቻችንን የምንመለከትበት ዛሬ ላይ ያሉ ክፍተቶቻችን የምንደፍንበት ዕድሎችን የምንጠቀምበት ወደ ነገም የምንዘረጋበትና የምንደርስበት የእሳቤ ማዕቀፍ እናየመርዳት ምልክታችን ነው::
ይህ እሳቤ ማህቀፋችን እና ምልከታችን ካለፈው የታሪክ ሂደታችን ተነስቶ፣ በዛሬና በነገ ዙሪያ ትውልዶች የሚኖራቸውን የጋራ ሕልምና አመለካከት በመቅረጵ፣ቅቡልነትን ያጠናክራል ::
ይህ ቅቡልነት ተረክና የተረኩ አጠቃላይ ፓራዳይም ፣ ትውልድን ከመፍጠርና ከመቅረጽ አንጻር የሚኖራቸው ተፅዕኖና ሚና ከፍ ያለ ነው።
#ቃልን_ወደ_ተግባር መቀየር የፓርቲያችን ብልፅግና አብይ መገለጫ ነው‼️
አዲስ አበባችን እንደስሟ ፅድት፣እምር፣ፍክት፣ውብ ሆና እንድትታይ የሁለንተናዊ ብልጽግና ተምሳሌትነቷ እንዲረጋገጥ ፓርቲያችን ብልፅግና ያለዕረፍት በትጋት 7/24 እየሰራ ይገኛል፡፡
ፓርቲያችን ብልፅግና አዲስ አበባን ማዕከል ያደረጉ ዘርፈ ብዙ የልማትን አጀንዳዎች በመንደፍ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባ የሀገራችን ርዕሰ መዲና የአፍሪካ ብሎም የአለም አቀፍ ዲፕሎማቶች መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን ስሟንና ክብሯን በሚመጥን መልኩ ተመራጭ ተወዳጅና በአለም አቀፍ ደረጃም ተወዳዳሪ ከተማ የሚያደርጋትን ስራዎችን በጥራትና ፍጥነት በተባበሩ ክንዶች ከዳር ለማድረስ ፓርቲያችን ብልፅግና በትጋት ያለ ዕረፍት እየሰራ ይገኛል፡፡
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+8
በግብርና ዘርፍ ያገኘነውን ስኬት በኢንደስትሪው ዘርፍ ለመድገም ትልቅ ትልም አለን። ለዚህም የገዳ ኢንደስትሪ ዞን የሀገራችንን እና የቀጠናችንን አቅም በመግለጥ ይህን ርዕያችንን ለማሳካት የሚረዳ ቁልፍ ተቋም ሆኖ ያገለግላል። የሉሜ ነፃ የንግድ ቀጠና በኢንደስትሪ ዞን ውስጥ ሆኖ በምስረታው ብሎም ተግባራዊ ስራ በሚጀምርበት ወቅት ከድሬዳዋ በመቀጠል ሁለተኛው ነፃ የንግድ ቀጠና የሚሆን ሲሆን ይህም ለኢኮኖሚ እድገት እና ልማት ያሉ እድሎችን ያሰፋል።
We aim to replicate the successes of our agricultural sector in the industrial domain, and the Gada Special Economic Zone serves as a pivotal platform to realize this vision, unlocking the vast potential of our region and nation. With the establishment and operation of the Lume Free Trade Zone within the SEZ, it will become the second free trade area after Dire Dawa, amplifying opportunities for economic growth and development.
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+7
ሩዋንዳውያን የ’ኪዊቡካ 30’ አመት በምታስብቡት ወቅት ኢትዮጵያ አብራችሁ ቆማለች።
#Ethiopia stands with the people of Rwanda as you commemorate ‘Kwibuka30’.
