1 369
Subscribers
No data24 hours
-107 days
-9030 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Belay Bekele Weya 👌 👌 እንደፃፈው
#ሙክታሮ|ቪች:—
እኔን ብትመርጡኝ ፣ ለሚመጣው ምርጫ
መብራትና ውሃ ፣ እንደ አለም ዋንጫ
በአራት አመት አንዴ ፣ መምጣቱ ይቀራል
ማይደፈርስ ውሃ
የማይጠፋ ብርሃን ፣ ቀን በቀን ይኖራል
።።።
ለሚመጣው ምርጫ
እኔን ብትመርጡኝ ፣ በውድም በግድም
ሰው እየረከሰ ፣ ኑሮ አይወደድም
ቀን በቀን ሰንጋ እንጂ ፣ ሰው አይታረድም
።፣፣፣
ለሚመጣው ምርጫ
እኔን ብትመርጡኝ ፣ ያላንዳች ውይይት
በዳቦ ቀይሬ ፣ እያንዳንዷን ጥይት
ህዝቤን አጠግባለሁ
ለእያንዳንዱ ቤት ፣ በነፃ አድላለሁ ፣ በርሜል ሙሉ ዘይት
።።።።።
ለሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡኝ
እንድደግፋችሁ ፣ ድጋፍ ብትሰጡኝ
ቤት እየገነባሁ ፣ ከወዳደቀ ፖል
ያለ ሞት መበልፀግ ፣ ብርሃን ያለ አምፖል
ለእያንዳንዱ ሰው ፣ ሰጣለሁ በነፃ
እንኳንስ የሰው ነፍስ ፣ አይጠፋም አንድ ህንፃ
።።፣፣
እኔን ብትመርጡኝ ፣ ለሚመጣው ምርጫ
ለጠጪዎች ውስኪ ፣ ለቃሚዎች በርጫ
ለእግር ኳስ ክለቦች ፣ ለእያንዳንዱ ዋንጫ
ለፈረሶች ፍጥነት ፣ ለአህዮች እርግጫ
በነፃ አድላለሁ።
።።።
በሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡኝ
ድምፃዊ ሳትሆኑ ፣ ድምፅ ብትሰጡኝ
አንድ ዜማ ሰሪ ፣ አንድ ጊልዶ ካሳ😂
አንዲት ውብ ኮረዳ ፣ አንድ ውብ ጎረምሳ
አንድ ካሜራ ማን ፣
አንድ የባህል ቡድን ፣ ክሊፕ የሚሰሩ
ወይም ዘመናዊ ፣ ዳንስ የሚጨፍሩ
አስቀምጣለሁኝ ፣ በየ አንድ ሜትሩ
(ግጥሙን ለኔ ተውት 😂)
።።።
ለሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡ
በዘር በሀይማኖት ፣ ምትቦጣቦጡ
ሰላም ያልገባችሁ ፣ ለፀብ የምትሮጡ
ከኪሴ መድቤ ፣ ከፍተኛ ባጀት
ጠብመንጃ ገጀራ ፣ ታንክና የጦር ጀት
ከሆነ ቦታ ጋር ፣ ለጦር ሜዳ ምቹ
በነፃ አድላለሁ ፣ እንዲዋጣላቹ !
።።።
ለሚመጣው ምርጫ ፣ ብትመርጡኝ እኔን
በምስራቅ ፣ በደቡብ ፣ በምእራብ ፣ በሰሜን
ላሉ ህዝቦች ሁሉ ፣ አንዳች ሳላዳላ
ቀስት የፈላ ውሃ ፣ ክላሽና ዱላ
ለተጠቃሚዎች ፣ በነፃ አድላለሁ
ለእያንዳንዱ ቤት ፣
ቤት ቁጥር አንስቼ ፣ ክልል እሰጣለሁ😂
።።።።
ለሚመጣው ምርጫ
እኔን ብትመርጡኝ ፣ ሔዋኔና አዳሜ
አልጋ ቤት በነፃ
አድላችኃለሁ ፣ ቅዳሜ ቅዳሜ😂
።።።
ለሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡ
ላመት ባል ላመትባል
ነጭ የጤፍ እንጀራ ፣ ጥብሱ ዶሮ ወጡ
ጥሬ ስጋ ቁርጡ
ጠላው እና ጠጁም
በቴሌቭዥን መስኮት ፣ አይታችሁ አትጎመጁም
ሁሉንም በቤታችሁ ታገኙታላቹ
ምርጫ በሌለበት
ምርጫችሁ እኔ ነኝ ፣ ምረጡኝ ባካቹ
።።።
ሁሉ እንደ ፈቀደው
ሁሉ እንደወደደው
ሚኖርባት ሀገር
መኖር ብትፈልጉ ፣ ምረጡኝ በሞቴ
ፍላጎታቹ ነው ፣ ምርጫ ምልክቴ "
Repost from Muktarovich Ousmanova
የዕለቱ የሁለት ፎቶዎች ወግ፦
ፎቶ 1፡-ጠ/ሚኒስትሩና ቀዳማዊት እመቤት ለአቅመ ደካሞች ቤት አደሱ።
ፎቶ 2፦ቤት የፈረሰባቸው ሰዎች በጥይት ተገደሉ
ለታሪክ ይቀመጥ እዚሁ 👇
ሌብነት ባልጠበቅነው መልኩ ባህሪውን እየቀያየረ ብዙዎችን እያከሰረ ነው❗
የዛሬውን የአንድ ነጋዴ ገጠመኝ አንብቡት👇👇👇
."ዛሬ ሱቄ ኣንድ ሰው ሞባይል ሊገዛ ይመጣል እናም ሲመጣ የቤት መኪና ፣ ህፃን ልጁንና ለመውለድ የተቃረበች ሚስቱን ይዞ ነበር ....... እናም ሚስቱን መኪናው ውስጥ ኣስቀምጧት ህፃን ልጁን ይዞ ወደ ሱቄ ይገባና #iphone14 ስልክ ኣሳየኝ ብሎኝ ካሳየሁት በኃላ ዋጋውን ሲጠይቀኝ 165ሺ ኣልኩት እሱም እባክህ ሚስቴ ስላማራት ነው ቀንስልኝ ሲለኝ እሺ ብዬ 2ሺ ብር ስቀንስለት ተስማማን.............. ከዛም ባለቤቴን ከለር ላስመርጣት ብሎ ሶስት የተለያዩ ከለር ያላቸውን iphone 14 ስልኮች ልጁን ሱቄ ጥሎ ይዞ ወጣ............. ያው እኔም ልጁን እዛው ስለተውና እርጉዝ ሴት ስላየው ይመለሳል በሚል እሳቤ ሰጥቼው ትኩረቴን ሌሎች ደንበኞች ላይ ኣደረኩኝ............. ከዛም ብጠብቅ ምንም የለም ወጣ ብዬ ስመለከትም መኪናዋም እነሱም የሉም ..............ከዛ ወደሱቅ ተመልሼ ፈላውን ስጠይቀው ከጎዳና ላይ ጠዋት ኣንስተውት ልብስ ገዝተውለት ፤ ፀጉሩን ኣሰሰተካክለው ፤ ገላውን ምናምን ኣጠበው እንዳመጡት ነገረኝ ማለት ነው" 165K * 3 = 495 ሺ ኣነደዱት ማለት ነው ❗
ምንጭ:-👉Andinet Nafkot
ከአፈሙዝ ይልቅ ውይይት ከሁሉ የተሻለ ነው‼️
ትናንት ጀምሮ በጎንደር ተዘግቶ የነበረው መንገድ ትናንት እና ዛሬ ወጣቶቹ ከአመራሮቹ ጋር ባደረጉት ውይይት በአሁኑ ሰዓት መንገድ የመክፈት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
Repost from Wasu Mohammed(ዋሱ መሀመድ)
ከሰሞኑ አዲስ አበባ እየተደረገው ያለው ነገር…
የአማራ እና የደቡብ ተወላጅ የሆኑ የፀጥታ አባላት ከሚሰሩበት ፖሊስ ጣቢያ ከስራ እየታገዱ መሆኑን የደረሱኝ መረጃዎች ያመለክታሉ።ልክ ከዚህ በፊት ከህውሃት ጋር ጦርነት ውስጥ በተገባበት ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ ሲደረግ የነበረው ማዋከብና ማግለል አሁን ደግሞ በአማራ ደቡብ ተወላጆች ላይ እየተፈፀመ ነው ተብሏል።ዛሬ በፖሊስ ጣቢያ ማስታወቂያ ቦርድ ላይ የተገለፀላቸውም እንዳሉ ታውቋል።ከሰሞኑ ቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የእነዚሁ ፖሊስ አባላት ስልክ ተወስዶ ሲበረበር እንደነበር ተሰምቷል።ነገሮች በልክ ቢሆኑ መልካም ነው።
በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ‼️
ከካርቱም ዜጎቻቸውን በአየር ትራንስፖርት ለማውጣት ያልተሳካላቸው ሀገራት በየብስ ትራንስፖርት በኢትዮጵያ ድንበር በኩል እያስወጡ መሆኑን አል ዐይን ከምንጮቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል። ሀገራት ዜጎቻቸውን እያስወጡ ያሉት በጋላባት-መተማ በኩል ነው ተብሏል።
መተማ‼️
የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች በሱዳን ተይዞ የነበረው የእርሻ መሬታችን ተለቋል፣ማረስ እንፈልጋለን የመንግስት እሳቤ ምንድን ነው? በማለት የአካባቢው አመራሮችን እየጠየቁ ይገኛሉ። የሰሜን ዕዝን ጥቃት ተከትሎ ሱዳን ይሄን ክፍተት በመጠቀም በርካታ የኢትዮጵያ መሬቶችን መውሰዷ ይታወቃል። በዚህ የተነሳ በርካታ አርሶአደሮች ማሳቸውን ማረስ ካቆሙ አመታት ተቆጥረዋል። ሰሞኑን በሱዳን ፈጥኖ ደረሽ ሀይል እና በሱዳን መከላከያ ጦር መካከል ጦርነት መጀመሩን ተከትሎ የሱዳን ጦር እነዚህ መሬቶች ለቆ ወደ ኋላ ሄዷል። ለምሳሌ ደለሎ ቁጥር ሶስት እና አራት ሙሉ በሙሉ ተለቀዋል። መንግሥት በበኩሉ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ መሬቶች ከሱዳን ጋር ተወያይቶ በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚሞክር በተደጋጋሚ ገልጿል(አዩዘሀበሻ)።
ሚያዝያ 14/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ👇👇
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.