en
Feedback
መድ🪶

መድ🪶

Open in Telegram

ከህልው ሜዳ ስንቃርም... ከልብ መድ ስናጣቅስ...እንደዚህ!

Show more
538
Subscribers
+324 hours
+107 days
+5230 days
Posts Archive
እሾህ ነው ሕይወት፣ አሜኬላ የበዛበት። ለልስልስ ነፍስ የማይመች፣ ለወንፊት ነፍስ የሚስማማ ነገር። ❝ጌታዬ የምድርን ጣእር እያወቀ ለምን ነው የኸለቀን?❞ የምንልበት ቀን አንዳንዴ ሽው ይልብን አይደ
እሾህ ነው ሕይወት፣ አሜኬላ የበዛበት። ለልስልስ ነፍስ የማይመች፣ ለወንፊት ነፍስ የሚስማማ ነገር። ❝ጌታዬ የምድርን ጣእር እያወቀ ለምን ነው የኸለቀን?❞ የምንልበት ቀን አንዳንዴ ሽው ይልብን አይደል? ለምን ይመስልሻል እንዲያ የሆነው? መቼስ የአላህን አዲልነት አንጠራጠርም? ተንከላውሰን በዱንያ እንዳንሰምጥ የሚያግደን ፍቅር መኖሩን እንድናውቅ። ከለላ የሆነ... ከዚህኛዉ አለም አርቀን ማሰብ እንድንችል! @yeruh_weg

ሳያት አንቺን ባረገኝ እያልኩ ነው፥ አውዳሚዎችሽን በድንጋይ ካባ ተከለልለሽ የምታልፊበትን ቁዋ ቢሰጠኝ እያልኩ። ወይ ደግሞ እየተንከረፈፍኩም ቢሆን ❝ቋሚ❞ ተንቀሳቃሽ ብሆን፤ ለቅፅበት ለፍቶ ቶሎ የሚ
ሳያት አንቺን ባረገኝ እያልኩ ነው፥ አውዳሚዎችሽን በድንጋይ ካባ ተከለልለሽ የምታልፊበትን ቁዋ ቢሰጠኝ እያልኩ። ወይ ደግሞ እየተንከረፈፍኩም ቢሆን ❝ቋሚ❞ ተንቀሳቃሽ ብሆን፤ ለቅፅበት ለፍቶ ቶሎ የሚደክመውን ጎኔን ብትለውጪኝ! @Yeruh_weg

❤️❤️ @yeruh_weg
❤️❤️ @yeruh_weg

Repost from Venue
አንዳንዴ ጨለምተኛ ኹነን ምናምን ይመስላል... ግን እውነት አይመስለኝም... እንዴ ይህንን ሁሉ እሳት ችሎ መኖር የሆነ ተዓምር አይደለም? ኑሮ ውድነቱ ይልፋችኋል... በዚያ በየሐገሩ ያለ ጦርነት ያደማችኋል... በዚህ ከጎንህ ያለ ደም መንቆርቆር ያራዥሃል... እንደኔ ጀናዛ ከሚወጣበትና የሚያለቅሱ ሰዎች በተኮለኮሉበት ቦታ ማለፍ በየቀኑ የሚጠበቅብህ ሲሆን ደግሞ ወይ ሞት ለካ እንዲህ ቀሏል እያልክ መገርመም ነው... ደግሞ ውስጥህ የልብህ ስብራት ይጠዘጥዝሃል...በዚህ ኑሮ ልብ ነፍስ፡ የውስጥ ህመም ምናምን እያሉ መቀባጠር እንዴት ቅብጠት ነው የሚል መንጋ ያጠናግርሃል... ያው ትውጣታለህ.. ዝም ብለህ እያገጠጥክ መቀላቀል ነው... ኧረ ተዐምረኛ ነህ ወዳጄ... (ነጃት ሐሰን) : @Venuee13

ነፃነታችን በደም የተገዝዛ ነው። ሐገራችን፣ መላእክት የሸሒድ ድግስ የሚያሰናዱባት ቅድስት መሬት ናት። ልባችን በምላስ ያልተንጠለጠለች አኺራን ብቻ የምታይበት ቁዋ ያላት ጀግናችን ናት። ጀሰዳችን ፍር
ነፃነታችን በደም የተገዝዛ ነው። ሐገራችን፣ መላእክት የሸሒድ ድግስ የሚያሰናዱባት ቅድስት መሬት ናት። ልባችን በምላስ ያልተንጠለጠለች አኺራን ብቻ የምታይበት ቁዋ ያላት ጀግናችን ናት። ጀሰዳችን ፍርሐት የማያውቅ ወደጀነት አድራሽ-ኣችን ነው። በተበደልነው እና በተገፍፋነው ቁጥር ዱንያ ላይ መልካም እናጭዳለን። በተሰዋው ነፍሳችን ምትክ ዳግም መስሰዋትን እስክንመኝ ድረስ ተድላ ፊታችን ነው። የኖርነውም፣ የታገልነውም፣ የሞትነውም ለስኬት ነው!!🇵🇸 እናንተስ? @yeruh_Weg

አሏህን መገናኘት ሳስብ የሚል የመልእክት ካርድ አገኘሁ... እንጃ እንደዛሬ ፈርቼም አላውቅ። የጌታዬን ልእልና የሚመጥን ስራ፣ ያዘዘውን የሰራሁበት የተጣራ ኒያ፣ መንገዴን ያሳመርኩበት የረሱሉ ሰለላሁ
አሏህን መገናኘት ሳስብ የሚል የመልእክት ካርድ አገኘሁ... እንጃ እንደዛሬ ፈርቼም አላውቅ። የጌታዬን ልእልና የሚመጥን ስራ፣ ያዘዘውን የሰራሁበት የተጣራ ኒያ፣ መንገዴን ያሳመርኩበት የረሱሉ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሱና፣ ተውበት አድርጌ ያልደገምኩት ስራ... እንጃ መኖሩን! ቀኔን ስገመግም ሐጥእ የሌለበት ሰአት... ለአቅሌ ይርቃል። ግና.... ከወንጀሌ ግዝፈት የማይገዳደረው እዝነቱ፣ ምሕረቱ ትናንትም፥ ዛሬም፥ ነገም ተስፋዬ ነው!! @yeruh_weg

ምን አይነት ስሜት ውስጥ እንዳለን አያውቁም ግን በዱአ ያግዙናል....ምን እንዳስጨነቀን ወይም ስላለብን ሃጃ አያውቁም ነገርግን አብረውን ይጨነቃሉ....ምን እንዳስከፋን አያውቁም ቢሆንም አብሽርን በመሰለ ቃል ያፅናኑናል.... የምላቹ ስለአንዳንድ ቅመም ልቦች ነው። የነሱን ውለታ በምን ትክሳለህ ቢሉኝ ከልቤ ተነስቶ ወደጌታዬ በምሰደው ዱአ መሆኑን እነግራቸዋለሁ። (አብድልቃድር ኑር)

<<ከመች ጀምሮ ነው 'ልቤ መሰበር አቁሟል።' ያሉኝአንቱ ሰው?>> <<ለእያንዳንዱ ሰው ወዳጄ፣ ቅርቤ ከማለት ይልቅ 'ሰው ስለሆነ ነው' እያልኩ ኡዝር መስጠት ከጀመርኩ በ
<<ከመች ጀምሮ ነው 'ልቤ መሰበር አቁሟል።' ያሉኝአንቱ ሰው?>> <<ለእያንዳንዱ ሰው ወዳጄ፣ ቅርቤ ከማለት ይልቅ 'ሰው ስለሆነ ነው' እያልኩ ኡዝር መስጠት ከጀመርኩ በኋላ!>> @yeruh_weg

ረኡፍ ፡ ረሒም ለእርሳቸው ብቻ ከተገቡ ስሞች መሃከል የሚመደቡ ሩኅሩኅ እና አዛኝ የሚል ፍቺ ያላቸው ስማቸው ሲሆን ከዚሁ ተያያዥ የሆኑ ነብዩ-ራሕማ፣ ረሱሉ-ራሕማ፣ ረሱሉል መርሐማ፣ ራሕመተል ኡምማ፣ ራሕመተል ዓለሚን የሚጠሩበት ስም ነው። ደረጃቸው ከፍፍ ማለቱ፣ ልእቅና እና ግርማቸው መናኘቱ ነው ስማቸውን ያበዛው። የስም መብዛት የግብር መስፋት ሆኖ ነው እስከ 99 ወይም 202 ድረስ ሰዎች የሰዪዳችንን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ስሞች ቆጥረው የደረሱት። "ለዓለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም" አንቢያ 107 አላህ ለፍጥረታት ሲያዝን ሐቢቡላህን ወደ'ሱ ይጠሯቸው ዘንድ ላከ። በእሳቸው መምጣት እምነተቢስ ሆኖ መንፈሱ ሞቶ የነበረው ማሕበረሰብ አንሰራራ። የመፈጠሩ ዓላማ ጠፍቶት መንገድ ስቶ ሲተራመስ የነበረ ኸልቅ ሁላ በእሳቸው ሰከነ። የእዝነት ነብይ ናቸው፡ እንኳን ላመኑባቸው ቀርቶ ለሚዋጓቸው ከሀዲያን ሳይቀር የሚራሩ። ለዓለማት እዝነት ናቸው፡ እንስሳት ብሶታቸውን የሚዘረግፉላቸው፡ እሳቸውም ሐቃቸውን የሚያስመልሱ፡ ሕፃናት ይወዷቸዋል፡ እሳቸው ያፈቅሯቸዋል፡ እርግብ የሞተበትን ብላቴና ጎንበስ ብለው እያፅናኑ የሚዳብሱ። ለፍጥረታት ሁሉ ማዘንን ያስተማሩ ሩኅሩኅ ነብይ.. لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ "ከጎሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ (እምነት) ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን (ላይ) ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ" የእሳቸው ኡመት ምን ኃጢአት ቢያበዛ ምድር ላይ ጥፋት አይላክበትም። ከሃዲም ሆነ መናፍቅ ከእሳቸው እዝነት መጠለሉ አይቀርም። "አላህም አንተ በውስጣቸው እያለህ የሚቀጣቸው አይደለም..." አላህ የአማኞችን ልብ በኢማን ያሸበረቀው፣ አላህን በማወቅ ሀሴታቸውን ያደመቀው፣ እሳቸውን አስወድዶ የመረጠውን ያነገሰው፣ ምንዳቸውን ያለ ሒሳብ የለገሰው፣ ተቆጥሮ የማያልቅ ጸጋ ያፈሰሰው በአሽረፈል ኸልቅ ምክንያት ነው። "እኔ የእዝነት ነብይ ነኝ" የሚሉት ሐቢቡላህ ሁሌም ወደ እዝነት ይጣራሉ። አማኞች በቻሉት መጠን ለፍጥረታት እንዲያዝኑ ያስተምራሉ። "አዛኞችን አዛኙ ጌታ ያዝንላቸዋል" "አላህ ከባሮቹ መሀከል አዛኞችን ይወዳል" "የማያዝን አይታዘንለትም" ከእዝነት አስተምህሮዎቻቸው በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው። اللهم صل على سيدنا محمد عدد ما فى علم الله صلاة دائمة بدوام ملك الله.

Repost from Tofik Bahiru
የደረሰብን፣ የሚደርስብን፣ የምንፈራውን መከራ የሚያስረሳ ፀጋ ናቸው #ተወዳጁ [ﷺ]። እንደውም የፀጋ መሰረት፣ የሰው ልጅ ክብረት መነሻም ናቸው። ሰው መሆናቸው እርሳቸውን አያከብርም። እርሳቸው ሰው
የደረሰብን፣ የሚደርስብን፣ የምንፈራውን መከራ የሚያስረሳ ፀጋ ናቸው #ተወዳጁ [ﷺ]። እንደውም የፀጋ መሰረት፣ የሰው ልጅ ክብረት መነሻም ናቸው። ሰው መሆናቸው እርሳቸውን አያከብርም። እርሳቸው ሰው መሆናቸውን ግን ሰውን አክብሮታል። ወዳጅ ሁላ "ሚን አንፉሲሂም" ያለውን አስተንትን!

ተምሳሌታችን ﷺ አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ! መጪውን የረቢዕ ወር በማስመልከት ስለ ውድ መልዕክተኛችን ﷺ ተምሳሌትነት ያዘጋጀሁትን አጠር ያሉ ማሽታዎሻዎች በእህት ናዲያ አማካኝነት በቡክሌት መልክ ተዘጋጅቷል! ታነቡት ዘንድ ጋበዝናችሁ። መልካም ንባብ ይሁንልን! አሏሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሐመድ ﷺ

አንድ ትልቅ ሰው ‹የአደም ልጅ ንግግር ሁሉ ልክ ቢሆንና ስራው ጥሩ ቢሆን ለኪሳራ ቅርብ ይሆን ነበር› አሉ። ‹እንዴት ይከስራል?› ቢባሉ ⟨በራሱ ይደነቃል አሉ። ⟩

Repost from Venue
ስነ - ቃል😊[ከእናቴ ሰማሁት] ነጃት ሐሰን : @Venuee13 @Venuee13
ስነ - ቃል😊[ከእናቴ ሰማሁት] ነጃት ሐሰን : @Venuee13 @Venuee13

ልናቃናው ሐይል በሌለን ጉዳይ ላይ አንጨነቅ። : ጥቅሙ ምንድነው?

ከሩቅ ስንጠብቅ ከቅርብ የሚጠቀጥቀን ሐዘን ይከሰታል። ከሁሉም ሰው ደብቀን እንታመመው ይሆናል፥ የድብቅ ሕመማችን የገሐድ ወንጀለኛ ቢያስብለንም አሏሁ በሕይወታችን እስካለ... ከሁሉ በላይ አዋቂያችን እስካለ ምንም አንሆንም። በዝምታችሁ፣ በሰብራችሁ ፅኑ። ከችግር በኋላ በእርግጥ ምቾት አልለ!!! @yeruh_weg

Repost from Best kerim
ዕለቱ ጁምዓ ነው ♥ ከሌሎች ቀናችን በሚገባ እንለየው፤ ከምሽቱ ጀምሮ በአምልኮ፣ በሰለዋት፣ በዱዓና በዚክር ክብሩን እንስጠው፣ከቤት ጀምሮ በሰደቃ እና ስጊጠው፣ ቤተሰብ ጓደኛ ወዳጆችን እናስደስትበት፣ ንጹሕ እንሁን፣ ሲዋኩ ሽቶው ይብዛበት። የካህፍን ምዕራፍ በጥሞና እናንብበት አንዴ ብቻ ሳይሆን ደጋግመን። ዐሊሞቻችን ይህን ምዕራፍ ጁምዓ ዕለት ሁለት ሦስት ጊዜ ያነቡታል። ቁርአን እንደ መጽሐፍ አንዴ አንበብኸው የምተዘጋው አይደለም። በከፈትከው ቁጥር የሚሰጥህ በረከቶች አሉ። ቁርአን ዕውቀት፣ ኢማን፣ ምንዳ፣ መድሐኒት፣ ሲሳይ፣ እዝነት፣ ተግሳጽ ነው። ከቁርአን ገጾች ጋር በጥሞና ስንቀማመጥ ከብዙ በረከቶቹ ውስጥ የሆነውን ያክል መረዘቅን እንለገሳለን። ቁርአንን ከፍቶ በባዶ እጅ የሚመለስ ሰው የለም። እስልምናን እወዳለሁ ለእምነቱ ተቆርቋሪ ነኝ የሚል ኹሉ ከዚህ ሰፊ በረከት ቀርቦ በመማር መቋደሱ ግድ ይላል። አንዴ ተምሮና አንብቦ ጨርስሁ የሚባለው አይደለም። ደጋግሞ፣ መላልሶ ማንበብን ለረዘቀው ሰው ከማያልቅ የእርሱ ችሮታዎች ውስጥ መረዘቁ አይቀሬ ነው። ጁምዓ ነው ♥ የካህፍን ምዕራፍ አነበብን? በዚህ የቁርአን ምዕራፍ ውስጥ ስለ ሰይድና ሙሳና ሰይድና ኸድር እንድንማር ብዙ ይነግረናል። ሰይድና ሙሳ በዚህ ክቡር መጽሐፍ ውስጥ ከ 100 ጊዜ በላይ ስማቸው ሲወሳ ሰይድና ኸድርን ጨምሮ በርካታ የአላህ ወሊዮች ግን ቁርአን ላይ ስማቸውን በግልጽ ሰፍሮ ላታገኝ ትችላለህ። መታወቅ ግብ አይደለም፤ በምድር ቆይታህ አላህ ካወቀህ በቂ ነው የሚለውንም ልንማርበት እንችላለና ማንም ስላላወቀህ ምንም አይሰማህ አላህ ካላወቀህ ነው ከባዱ ነገር። አላህ ደግሞ በሰዎች እንዲታወቅ ያደረገው ሰው ሌላኛው የርሱ ገጽ ነው። በዚህ መሀል በግድ ከሰዎች የበላይ መሆንን መፈለግ ደግሞ በሐዲስ እንደመጣው ውግዝና የነፍሲያ በሽታ ነው። በዚሁ ምዕራፍ ቁጥር 28 ላይ ለመልእክተኛው (ሰዐወ) አላህ እንዲህ አላቸው፦ « ነፍስህንም፤ ከእነዚያ ጌታቸውን ፊቱን (ውዴታውን) የሚሹ ኾነው በጧትና በማታ ከሚግገዙት ጋር አስታግስ፡፡ የቅርቢቱንም ሕይወት ሽልማት የምትሻ ሆነህ ዓይኖችህ ከእነሱ (ወደ ሌላ) አይለፉ፡፡ ልቡንም እኛን ከማስታወስ ያዘነጋነውን ፍላጎቱንም የተከተለውን ነገሩም ሁሉ ወሰን ማለፍ የሆነውን ሰው አትታዘዝ፡፡» ይህ አንቀጽ የወረደበትን ምክንያቱ ሙፈሲሮቹ ሲያብራሩ እነዚህ በመስጂድ ለዒባዳ ብቻ የተቀመጡ ድኾች ላይ ነበርና አንቀጹ በወረደ ጊዜ መልእክተኛው (ሰዐወ) እንዲህ አሉ፦ « ጌታዬ የተመሰገ ይሁን ከሕዝቦቼ መካከል ነፍሴን ከእነርሱ ጋር በመሆን እንዳስታግሳት ስለታዘዝኩ» (ተፍሲር አልበገዊይ ይመልከቱ) ነፍሳችንን ለማስታገስና ለመስከን የትና መቼ ከማን ጋር መቀማመጥ እንደሚገባን ጊዜያችን በምን ማለፍ እንዳለበትም አንቀጹ ያስተምረናል። ይህ የዋሻው ምዕራፍ በጥሞና ላስተነተነው በራሱ የማያልቅ ዋሻ ነውና በየሳምንቱ ጥቂት መጓዝን አንርሳ ለማለት ነው ጥቂት የሞነጨርኩት። አላህ ያስረዳን! ♥ ጁምዓ ሙባረክ ♥

እለቱ ጁሙዓ ነበር። ምዕመኑም ለሶላት ተሰብስቧል። የረከበሩት ኢማም ከሚንበራቸው ላይ ተሰይመዋል።የዕለተ ጁመዓን የኹጥባ ዲስኩር ተለከታዮቻቸው እያስደመጡ ነው። መስጂዱን የሞላው ምዕመንም በጥሞና የው
እለቱ ጁሙዓ ነበር። ምዕመኑም ለሶላት ተሰብስቧል። የረከበሩት ኢማም ከሚንበራቸው ላይ ተሰይመዋል።የዕለተ ጁመዓን የኹጥባ ዲስኩር ተለከታዮቻቸው እያስደመጡ ነው። መስጂዱን የሞላው ምዕመንም በጥሞና የውዱን ኢማምን ንግግር እየተከታተለ ነበር። ከተሰበሰበው ታጋሚ ጀመዓ መሀል ሁለት እጅግ ማራኪ እና  ውብ የሆኑ ጨቅላ ህፃናት ብቅ አሉ። የሰልፉን እኩሌታ እያቆራረጡ ወደ ኢማሙ ሚንበር ለመዝለቅ ደክ ደክ ይሉ ይዘዋል። ሁለቱም ህቀያይ ተመሳሳይ ቀሚሶችን  የለበሱ ናጨው። ገና ጨቅላ ከመሆናቸው የተነሳ ሲራመዱ እንኳን እየተንገዳገዱ ነበር። ኹጥባቸውን በመንገር ላይ የነበሩት ኢማሙ ይህን ትዕይንት ከሩቅ ሚንበር ላይ ሁነው ሲመለከቱ አንጀታቸው ተላወሰ። ለልጆች ያላቸው የበረታ ፍቅር…የ’ነኝህን ጨቅላዎች ሁኔታ አይተው ለመቋቋም አልሰጣቸውም። ልባቸው ከፊት ለፊታቸው…እርሳቸውን እያዩ ወደሚራመዱት ወደ ልጅ ልጆቻቸው ናፈቀ። እኚህ አያት የልጅ ልጆቻቸው ፣ በህፃን እግሮቻቸው ወደ አያታቸው እየተንገዳገዱ ሲመጡ ተመልክተው መቻል ቢያቅታቸው ኹጥባውን ለማቋረጥ ተገደዱ። ታዳሚውን ትተው በናፍቆትና ስስት ተሞልተው ከሚንበሩ ወረዱ። ልጆቹንም በስስት እቅፍ አድርገው ሳሟቸው። ከዚያም ሁለቱንም በታፋቸው ላይ አኑረው ወደ ታዳሚው ዘወር አሉ……‹‹እንደው አላህ ልጆች ፈተና ናቸው ያለው'ኮ እውነቱን ነው። እኔ የእነኚህን ህፃናት ሁኔታ አይቼ አንጀቴ አልችል ቢለኝ እኮ ነው ሚንበሬንና፣ኹጥባዬን ትቼ  ወደነሱ የተራመድኩት››…በማለት የተሰማቸውን ተናገሩ። ከዚያም ወደ ኹጥባቸው ተመለሱ! እነኝህ ሁለት ተወዳጅ ህፃናት…የኸሊፋው ሰይዲና ዓሊ የተባረኩ ልጆች…ሰይዲና ሐሰን እና ሰይዲና ሑሰይን ነበሩ። ኢማሙ የከውኑ ሞገስ…ሰይዲ ራሱለሏህ ነበሩ። አሏሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይሂ!❤️

ፊተ በሻሻ፣ ያያቸው ሁሉ የሚወዳቸው ተፈቃሪ ናቸው። ከግንባራቸው የሚፈነጥቀው ብርሃን ፊታቸውን በሙሉ አይን ከማየት ይጋርዳል። አጠገባቸው የተቀመጠ የዱንያን ስንክሳር ሁሉ ረስቶ ልቡ በደስታ ተደልቃ ምቷን ትጨምራለች። ቀርበው ያጫወቱት ሰው "ዓለም ላይ ከኔ አስበልጠው የሚወዱት ሰው የለም" ሲል እርግጠኛ ይሆናል። ባልደረቦቻቸው በፍቅራቸው ለፍቅራቸው ይሞታሉ። ግን አንድ ሰው አለ፡ በአላህ አምላክነት እና በ'ርሳቸው መልእክተኝነት አምኗል፤ ነገር ግን እንደሌሎቹ ሰሃባዎች አይጠጋቸውም። ራሕመት ናቸው፡ ሰዎች እርሳቸውን አግኝተው ለዓለማት እዝነት ተደርገው ከተላኩት ነብይ የድርሻቸውን ራሕመት ዘግነው ሲመለሱ አብደላህ ኢብኑ ሙገፍፈል ግን ሲያያቸው ይጨነቃል፣ ይተክዛል፣ አጠገባቸው ሲቀመጥ ይቁነጠነጣል፣ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ተነስቶ ይወጣል። የፍጥረታት አይነታ ሁነቱን ተመልክተው ጠየቁት፤ የባልደረቦቻቸውን ሁኔታ አበክረው ይከታተላሉና "አንተዬ ምነው? ሰው እኔ አጠገብ ሲቀመጥ ይደሰታል፡ ጭንቁን ይረሳል አንተ ግን ትተክዛለህ ለምን?" አሉት። አብደላህ እስከዛሬ ያላወራውን ሰቅዞ የያዘውን ጭንቀት አዋያቸው "አንቱ የአላህ መልእክተኛ፡ እኔ ነጋዴ ነበርኩ። አንድ ጊዜ ለንግድ ከወጣሁ ለረጅም ጊዜ ሳልመለስ እቆይ ነበር። የሆነ ወቅት ባለቤቴ እርጉዝ ነበረች። ስመለስ ሴት ልጅ ወልዳ አገኘኋት፡ ልጅቱ አድጋለች። 'በፍፁም ይህን ነውር መሸከም አልችልም' ስል ከራሴ ጋር ተዋይቼ ወሰንኩና ባለቤቴን 'ልጅቱን አሰማምሪያት' አልኳት። ልጥላት እንደሆነ ገብቷት 'ተው ባክህ ነውር ፈርተህ አምላካችን የሰጠንን አደራ አታጥፋ' እያለች ትማፀነኝ ጀመር 'በጭራሽ ሊሆን አይችልም' ብዬ ልጃችንን ይዤ ወጣሁ፡ ሩቅ ስፍራ እየጎተትኩ ወሰድኳት። ከአንድ የገደል አፋፍ ላይ ደረስን። በዚያ ሁኔታ እንኳ 'አባዬ ፂምህ ላይ አቧራ' እያለች ታራግፍልኝ የነበረው ከአይነ-ህሊናዬ ልፍቀው አልቻልኩም። ወርውሬ ገደል ውስጥ ጨመርኳት፡ ልጄን ገደልኳት። ይህን ስራዬን ሳስበው ነው የምጨነው ያ ረሱለሏህ" ከሰው ልጆች ሁሉ ቀልባቸው ያማረው ነብይ ይህን ታሪክ ሰምተው ክፉኛ አዘኑ፡ ለልጅ ቀርቶ ለእንስሳት የሚራራው ልባቸው ምን ይሉት ክፋት ያሳምመዋል "እስልምና በድንቁርና ዘመን ስራ የሚቀጣ ቢሆን ኖሮ ከአንተ ነበር የሚጀምረው" አሉት። የድንቁርና ዘመን (ዘመነ ጃሂሊያ) ፅንሰ-ሀሳቡ የእውቀት ተቃራኒ መሀይምነት ሳይሆን የእምነት ተቃራኒ የሆነውን ክህደት አመላካች ነው። በዝያ ፅልመታማ ዘመን ሰዎች አላህን አያውቁም ነበር፡ የሰማያትና የምድር ብርሃን በአላህ ማመን ነው። እምነት ልቦናን ካልተቆጣጠረ መንፈሶች ጭለማ ይወርሳቸዋል። ዓለማትን ያስገኘውን፣ ሰዎች እሱን ብቻ እንዲገዙት የፈጠረውን አላህ አለማወቅ ሲታከልበት ድቅድቁ ጭለማ ይበልጥ አስፈሪ ይሆናል። ዓለም ላይ የሚነግሱ ስርአቶች ሁሉ ጨቋኝ ይሆናሉ። ሀብታም ድሃውን፣ ወንዱ ሴቷን፣ ባለስልጣን ተገዢውን፣ ጉልበተኛ አቅመ ደካማውን ይበዘብዛል። ሰዎች አላህን ሲረሱ፣ ዓለም አስቀያሚነቷ ቀን ከቀን ሲከፋ፣ ሰዎች ማን ላይ ተስፋ ማድረግ እንዳለባቸው ግር ሲላቸው አላህ ወደ'ርሱ ይመጡ ዘንድ ነብያትን ይልካል። የአላህ መልእክተኞች "አላህን ብቻ ተገዙ በእሱ ምንንም አታጋሩ" እያሉ ወደ አንድዬ ፈጣሪ ይጣራሉ። መልእክተኞች የተላኩበትን ከማድረሳቸው በተጨማሪ የአንድን ነብይ መላ'ክ ይናገራሉ። የመጨረሻው ነብይ፣ 'የአላህ ወዳጅ ወደፊት ይመጣል፡ ለምርጥ ህዝቦች ይላካል' ብለው ይህን ነብይ ያነሳሉ። ዓለም ላይ ኖሮ ስለ ታላቅነታቸው ያልሰማ አንድ የለም። አላህ በ'ርሳቸው ያምኑና ይረዷቸው ዘንድ ቃልኪዳን አስገብቷቸዋል። "አላህ የነብያትን ቃልኪዳን ከመጽሐፍና ከጥበብ ሰጥቻችሁ ከዚያም " ከእናንተ ጋር ላለው (መጽሐፍ) የሚያረጋግጥ መልክተኛ ቢመጣላችሁ በርሱ በእርግጥ እንድታምኑበት በእርግጥም እንድትረዱት ሲል በያዘ ጊዜ (አስታውስ)። አረጋገጣችሁን በዚህም ላይ ኪዳኔን ያዛችሁምን?" አላቸው። "አረጋገጥን" አሉ። "እንግዲያስ መስክሩ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከመስካሪዎቹ ነኝ" አላቸው። ይህችን ቃል ለመሙላት ነብያት ሲጓጉ ቆይተው አይነታው ነብይ ወደ ሰማይ ባረጉ ጊዜ ሁሉም ከኋላቸው ሆነው ሰግደዋል። እኒህን ታላቅ ሰው አላህ ለዓለማት እዝነት አድርጎ መረጣቸው። ለትልቅ ተልእኮ በመታጨታቸው የገጠማቸው ማህበረሰብ ድንቁርናው ከባድ ነበር፡ ከላይ ያነሳነው አንድ ታሪክ ማሳያ እንጂ በዛን ዘመን ሰዎች የገቡበትን ጭለማ የሚያመላክት አይደለም።

Repost from ABX
ባጠፉ ቁጥር "አጥፍቻለሁ፣ ኅጢአተኛ ሆንኩ" የሚለው ስሜት ኅጢአትን በሠራንና በተላመድነው ቁጥር በውስጣችን እየሞተ የሚሄድ ነው። ተከላከሉ፣ እጅ አትስጡ፣ ያ እስኪሆን አትጠብቁ። በወደቃችሁ ቁጥር መውደቃችሁን እሺ ብላችሁ አትቀበሉ። ከወደቃችሁበት ተነሱ። "ያ አጥፍቻለሁ፣ ነፍሴን በድያታለሁ" የሚለው የቁጭት ስሜት በዉስጣችሁ ከሚሞት እናንተ ራሳችሁ ብትሞቱ ይሻላችኋል ። https://t.me/MuhammedSeidAbx

Repost from Tofik Bahiru
የታላቁ ኢማም ኢብኑል‐ጀውዚይ [ረሒመሁላህ] ባለ ለዛ ተግሳፅን ላካፍላችሁ፤ ምክርን ዐረብኛውን አበላሽቼም ቢሆን… : «አንተ ሃሳብህን ደመነፍስ [ሀዋ] የተጫወተበት ሰው ሆይ! የፅናት ግንባርህን ስሜት ያጠቆረብህ ከንቱ! ስጋህ በሚበጫጨቅበት መርከብ የተሳፈርክ ሞኝ! የአጥንትህ መሳሳት አያስጠነቅቅህም?!… አንተ ስትርቅ ስንቴ አቀረብንህ?! ሰነፍ ነህ እንጂ ከፍ እንድትል ዘንድ ስንቴ አነቃንህ?! ስንቴ አግባባንህ፤ ለሚያግዝህ እጃችን አልተባበር ብለህ እንጂ?! በዛዛታ እንቅልፍ ስታሸልብ ስንቴ ቀሰቀስንህ?!… አንተ የህሊና እውር፣ መሪ አልባ፣ ደንባራ! በምኞት የተከዳህ፣ የተስፋ ግዳይ፤ ዘልዐለም የማትኖር ጠፊ!… አንድ መዳረሻ ብቻ እያለህ ሃሳብህን የበተንክ ድንዙዝ! ዱንያ ስትባርቅልህ አመፀኛ ሰይጣን!… ለርሷ የምትፋለም፤ ለርሷ የምታሳድድ! ደግሞም የምትሳደድ ጨካኝ! ሶላት ስትመጣ ባለ ሩቅ ልብ፣ ከነኦናው የተገተረ በድን!… ሰገድኩኝ ትላለህ?! ውስጥን ተመልካች ተቆጣጣሪህን ታታልላለህ?!… ደግሞም በችግርህ ጊዜ እንጂ አታውቀውም?! ወንጀልህ አእላፍ ነው፤ ግን ለምንድን ነው ዐይንህ የደረቀው?!… ደመነፍስ ነግሶብሃል! ስሜት ተቆጣጥሮሃል! የኛ ልፋት የመከነውም ለዚህ ነው። የምንቀጠቅጠው ቀዝቃዛ ብረት ነው!»