en
Feedback
Uog zena

Uog zena

Open in Telegram

Uog news 🙏

Show more
5 799
Subscribers
-224 hours
+127 days
+11730 days
Posts Archive
ጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎቹን ጠርቷል ? በርካታ ተማሪዎች አሁንም የሚጠይቁን ጥያቄ ነው። ተማሪዎች አሁንም ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሳችሁን ጠብቁ ጥሪ የተደረገው ለጤና ሳይንስ ተማሪዎች ብቻ ነው። ቴዲ - ማራኪ - እና ፉሲል ካምፓሶች በተመሳሳይ ሰዐት ጥሪ የሚያደርጉ ይሆናል። መቼ ለሚለው ጥያቄ በቀጣይ 5 ቀናት ውስጥ መልስ የምታገኙ ይሆናል። @uogzena

💥 የዚህ ወቅት የአፍላ ፍቅር ምን አይተው ወቅታዊ ድራማዬን አገኘኝ? ይህ አይነት ድራማ አገኘኝ የጋብቻ መፍትሔዎችን እና የአገር ወቅታዊ ጉዳዮችን ምስራቅ መክወይ ፍጥነት እንዳንቀሳቀስ ከሚሉበት ቅ
💥 የዚህ ወቅት የአፍላ ፍቅር ምን አይተው ወቅታዊ ድራማዬን አገኘኝ? ይህ አይነት ድራማ አገኘኝ የጋብቻ መፍትሔዎችን እና የአገር ወቅታዊ ጉዳዮችን ምስራቅ መክወይ ፍጥነት እንዳንቀሳቀስ ከሚሉበት ቅዱስ ዝግጅት! 🌀 ይህ የአዲስ ክፍል ለእርስዎ ይታወቃል፣ ይዘን ነገር እንዳይወጣ ቻናሉን ይገብሩ! 👉 ለመግባት ይድገም #ad 📢 InsideAd

ቴዲ ካምፓስ / ማራኪ ካምፓስ/ ፋሲል ካምፓስ ተማሪዎቻቸውን በግልፅ አልጠሩም ግን የግድ በጊዜ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል ምክንያቱም የplane Ticket በጊዜ book መደረግ ስለሚኖርበት ፡፡ ተማሪዎች ለአለስፈላጊ ወጪ እንዳይዳረጉ ፡፡ የሚመለከተው አካል በአፋጠኝ ምላሸ የሚሰጥበት ይሆናል፡፡ @uogzena

ከዚህ ቀደም ይሄንን መረጃ ማድረሳችን አይዘነጋም አሁን ደግሞ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎቻቸዉ ከመስከረም 5 ጀምሮ ጥሪ እንዲያደርጉ አቅጣጫ አስቀምጧል ጎንደር ዩኒቨርስቲም መስከረም 4 እና 5 ተማሪዎቹን መጥራቱ አይዘነጋም ፡፡ ለዋናው ካምፓስ ተማሪዎችም የተለየ ጥሪ ለይኖር ይችላል ፡፡ አዲስ መረጃ ካለ አጣርተን እናደርሳለን፡፡ @uogzena

ዛሬ ሌሊት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚከሰተው አስደናቂው "የደም ጨረቃ" እና የጠፈር ምስጢር በጥንታውያን ዘንድ ብዙ ፍርሃትና ግርምት ይፈጥር የነበረው፣ በሳይንሱ ደግሞ እጅግ አስደናቂው የጠፈር ትዕይ
ዛሬ ሌሊት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚከሰተው አስደናቂው "የደም ጨረቃ" እና የጠፈር ምስጢር በጥንታውያን ዘንድ ብዙ ፍርሃትና ግርምት ይፈጥር የነበረው፣ በሳይንሱ ደግሞ እጅግ አስደናቂው የጠፈር ትዕይንት ተብሎ የሚገለጸው የጨረቃ ግርዶሽ ዛሬ ሌሊት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ይከሰታል:: ሐሙስ ለዓርብ አጥቢያ በሚደረገው በዚህ ሁነት፣ ሙሉ ጨረቃ በመሬታችን ጥቁር ጥላ ውስጥ አልፋ እስከ 96 በመቶ የሚሆነው ገጽታዋ ሲሸፈንና ወደ ዝገት ቀይ ቀለም ስትቀየር የማየት እድል ይገጥመናል :: በህይወት ዘመን ድጋሚ የማይገኝ እድል፡፡ @uog zena

photo content

የሁሉም ጊቢ መግቢያ ቀን ተመሳሳይ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው ፡፡ መሉ መረጃ ነገ የምናደርስ ይሆናል፡፡

ሰበር
ሰበር

"በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰየመ ":: ******** በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም ለተቋሙ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሀገር
"በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ በዶ/ር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰየመ ":: ******** በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም ለተቋሙ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሀገር ባለውለታዎችና ዩኒቨርሲቲውን በኃላፊነት መርተው ለዚህ ደረጃ ላበቁ መሪዎች በስማቸው ህንፃዎችንና መሰረተ-ልማቶችን ስያሜ መስጠት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተለመደ የምስጋና ባህል ነው። ይህንኑ አሰራር በመከተል፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴዎድሮስ ግቢ የሚገኘው ትልቁ ፓርክ ዛሬ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዶክተር አሥራት አፀደወይን ስም ተሰይሟል። ስያሜው ዶ/ር አሥራት አፀደወይን በተቋሙ ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታን ለመፍጠርና ግቢው እጅግ ሳቢ የምርምር ማዕከል እንዲሆን ላደረጉት ሁለንተናዊ አስተዋፅኦና ላሳዩት የላቀ አመራር እውቅና ለመስጠት የተደረገ ነው። ፓርኩ በ3.22 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ በውስጡ ሦስት ውብ ፋውንቴኖች (Fountains)፣ ዘመናዊ ስማርት ካፌቴሪያ፣ የትዕይንትና ዝግጅት ማቅረቢያ ስፍራ (Amphitheater) እና የተለያዩ ማረፊያ ቦታዎችን ያካተተ ነው። በተጨማሪም፣ ፓርኩ የተማሪዎችን የንባብ ባህል የሚያዳብር ምቹ አካባቢ ከመፍጠሩም በላይ ለተለያዩ ማህበራዊ ኩነቶች ማካሄጃነት ያገለግላል። @uogzena

እንኳን ደስ አለን! "የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የየጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ"። ********* የጎን
+1
እንኳን ደስ አለን! "የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ  ትምህርት ቤት እና የየጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ"********* የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የተፈተኑት ሁሉም ተማሪዎቻቸው የማለፊያ ነጥብ በማስመዝገብ አንጸባራቂ ድል አስመዝግበዋል። ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ  ረድኤት ሳሙኤል 574.4 ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ እንዲሁም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ደግሞ ተማሪ ናትናኤል ሙላት 570.16 ውጤት በማስመዝገብ አስደናቂ ስኬት ተጎናፅፈዋል። ለዚህ ታሪካዊ ውጤት መመዝገብ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣  የትምህርት ቤቶቹ የማኔጅመንት አባላት፣ የመምህራንና የወላጆች ያልተቋረጠ ድጋፍ እንዲሁም የተማሪዎቹ ጥረት  ከፍተኛው ድርሻ አላቸው። ተማሪዎቻችን ነገ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በብቃት የሚያገለግሉ፣ ለታላቅ ቁምነገር የሚበቁ ዜጎች እንዲሆኑልን መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን። ለልህቀት እንተጋለን! የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን  ሥራ አስፈጻሚ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም @uogzena

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል። ውጤት ለማየት ፦ 👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et 👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram 👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል። @uogzena

ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @uogzena

የሀዘን መግለጫ ********* በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የነበሩት አቶ ሙሉጌታ አያሌው በድንገተኛ ሕመም ምክንያት የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ከቆዩ
የሀዘን መግለጫ ********* በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሕክምናና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የነበሩት አቶ ሙሉጌታ አያሌው በድንገተኛ ሕመም ምክንያት የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ከቆዩ በኋላ ዛሬ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በመሆኑም በአቶ ሙሉጌታ አያሌው ህልፈተ ሕይወት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው፣ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን። ************* ለልህቀት እንተጋለን! የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ነሐሴ 16 / 2018 ዓ.ም. @uogzena

Repost from Kelemat Ads
"ሠልጥነው ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡ ተመራቂዎችን በ(Paid Internship) እየቀጠርን ነው!" የ Oriix AI Income Lab የሁለተኛው ዙር (Cohort 2) ምዝገባ አሁን ተከፍቷል! 20,00
"ሠልጥነው ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡ ተመራቂዎችን በ(Paid Internship) እየቀጠርን ነው!" የ Oriix AI Income Lab የሁለተኛው ዙር (Cohort 2) ምዝገባ አሁን ተከፍቷል! 20,000 ብር የሚያወጣውን ሥልጠናችንን በ Oriix AI Lab ስፖንሰር ስለተደረገ በ 999 ብር ብቻ ለአጭር ጊዜ ሥልጠናውን እየሰጠን ነው። በሥልጠናው መጨረሻ ላይ የብዙ ልምድና እውቀት ባለቤት ይሆናሉ፦ 👉 የኮዲንግ ዲግሪ ሳይኖርዎት AIን በመጠቀም ሶፍትዌሮችንና ዌብ አፖችን ከዜሮ መገንባት 👉 የገነቧቸውን አፖች በአግባቡ አዘጋጅተው፣ ዋጋ ተምነው ለደንበኞች ማቅረብና መሸጥ 👉 ለ(CV) ዝግጁ የሆነና ተግባራዊ የ AI ክህሎትዎን የሚያረጋግጥ የተረጋገጠ ሰርተፊኬት መያዝ 👉 እርስዎ የሠሯቸውን ሶፍትዌሮች መግዛት የሚፈልጉ 20,000+ የኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ የንግድ ድርጅቶች አድራሻ እና ስልክ ቁጥር (Contact List) ማግኘት 🎁 ቦነስ (Bonus): የዚህ ዙር ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡ 2 ሠልጣኞች በቀጥታ ክፍያ ወዳለው የልምድ ልምምድ (Paid Internship) የሥራ ዕድል ይሸጋገራሉ። ⏳ ምዝገባው የሚዘጋበት ቀን: ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም (August 25, 2026) 👉 እዚህ ይመዝገቡ: oriix.net/student-edition

ትምህርት ሚኒስትር ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን እስከ መስከረም አጋማሽ ባለው ጊዜ ጥሪ እንዲያደርጉ በማሰብ ወደ እንቅስቃሴ ገብቷል። መረጃውን የ ትምህርት ሚኒስትር ነው። @uogzena

የራስገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ሒደቱን እንዲጀምሩ የሚፈቀድላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር በቅርቡ ይፋ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች ራስገዝ ለመሆን የሚያስችላቸውን ሒደት ለመጀመር የራሳቸውን
የራስገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ሒደቱን እንዲጀምሩ የሚፈቀድላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር በቅርቡ ይፋ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች ራስገዝ ለመሆን የሚያስችላቸውን ሒደት ለመጀመር የራሳቸውን ግለ-ግምገማ ያደረጉ ሲሆን፣ ትምህርት ሚኒስቴር አቋቁሞ ወደ ተቋማቱ የላካቸው ገለልተኛ የባለሙያ ቡድኖች ባለፈው ግንቦት በየዩኒቨርሲቲዎቹ በመገኘት ምዘና ማከናወናቸው ይታወሳል። ዩኒቨርሲቲዎቹ የራስገዝነት ሒደቱን ለመጀመር ያቀረቡት ጥያቄ በትምህርት ሚኒስቴር እየታየ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ዩኒቨርሲቲዎቹ ከሦስት ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ራስገዝ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሏል፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን 10/11/2018 ዓ.ም ራስገዝ ለመሆን ሒደት ለጀመሩ ዘጠኝ ዩኒቨርሲዎች በጻፉት ደብዳቤ፤ እነዚህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በራስገዝነት ዝግጁነታቸው ላይ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ከመደበኛ የተቋሙ ተግባር ባለፈ ዩኒቨርሲቲውን ተጠያቂነት ውስጥ ከሚያስገቡ ውሳኔዎችና ድርጊቶች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ በዚህም የዩኒቨርሲቲውን መሬት፣ ንብረት እና መብት በውሰትም ሆነ በሽያጭ ለሌላ ወገን ማስተላለፍ እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ በስተቀር ከፍተኛ የግንባታና ንብረት ግዢ ውሳኔዎችን መስጠት የተከለከሉ መሆኑን ሚኒስትሩ አሳስበዋል፡፡ የራስገዝነት ሒደትን ለመጀመር የመንግሥትን ውሳኔ እየጠበቁ ከሚገኙ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በሦስቱ ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዝዳንት ለውጥ በቅርቡ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡ በራስገዝነት የሽግግር መመሪያ ተገምግመው 60 በመቶና ከዚያ በላይ የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች በ2019 ዓ.ም ወደ ራስገዝነት ይሸጋገራሉ መባሉ ይታወቃል። @Uogzena

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ዛሬ መሠጠት ጀምራል፡፡ ፈተናው በ31 የመፈተኛ ጣቢያዎች እየተሠጠ ሲሆን፣ እስከ አርብ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል። ፈተናው ነገ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ሲቀጥል፤ የMedical Laboratory Science, Public Health, Midwifery, Medical Radiology Technology, Paediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing, Surgical Nursing ሙያ ተመዛኞች ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰዓት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ፈተናቸውን የሚወስዱ ይሆናል። @uogzena

photo content

ዶርሞች ሊታደሱ ይገባል ፡፡ ከዚህ ቀደም ጉዳት የደረሰባቸው ዶርሞች እድሳት ያስፈልጋቸወዋል 1 በር 2 ቀለም 3 መብራት 4 መፀዳጃ ክፍሎች አምባሳደሩን ጎንደር ዩኒቨርስቲ በሚመጥን መልኩ ሊታደስ ይገባል ፡፡ ተማሪዎች በተደጋጋሚ የላኩልን መልዕክት፡፡ @uogzena

ማስታወቂያ ***** #NGAT አገር አቀፍ የድህረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ በመሆኑም ተመዝጋቢዎች Username፣ Password እና Entrance Ticket ለማግኘት የኢ-ሜይል አድራሻችሁን መጎብኘት አንዳትዘነጉ እናሳስባለን። ************************ ለልህቀት እንተጋለን! ጎንደር ዩኒቨርሲቲ @uogzena