5 660
订阅者
+824 小时
+27 天
+6230 天
帖子存档
5 660
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት exit exam result መመልከቻ ሊንክ ሰርቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ መስራት አቁሟል ተማሪዎች አሁንም በትግስት ጠብቁ ::🙏🏻
Uogzena መልካም ዉጤት ለሁላችውም ይመኛል ::
5 660
የመውጫ ፈተና ዉጤት ለማየት ዌብሳይቱ እያስቸገረ ይገኛል::
አሁንም በርካታ ተማሪዎች አልሰራልንም እያሉ ይገኛሉ system ሲስተካከል ወድያው መመልከት ትችላላችው system ለማስተካከል ትንሽ ጊዜ ይፈልጋል ሆኖም ግን አሁን ላይ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ደርሷል ስለሆነም ከጥቂት ሰዓታት በኃላ ዉጤት መመልከት ትችላላችው ::
እሰክዚያው ተማሪዎች በትግስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን ::
Portal ሲሰራ ወድያው ዉጤት እንዲታይላችው የምትፈልጉ direct message ላይ user name አስቀምጡልን ::
መልካም ዕድል 🙏🏻
@uogzena
5 660
ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የምናካሂደውን የተማሪዎቻችንን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በቀጥታ ስርጭት ለመከታተል ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ።
To watch the live broadcast of our students’ graduation ceremony, which will be held on June 25, 2026, use the link below.
https://youtube.com/live/Y6P--G3uI5w?feature=share
5 660
#update
የ መውጫ ፈተና ውጤት ተለቆ ተማሪዎች ውጤት ማየት ጀምረው ነበረ አሁን ላይ ሲስተሙ በመጨናነቁ ምክንያት ዌብሳይቱ not found ማለት ጀምሯል። ሰርቨሩ ዳግም መስራት እስኪጀምር በትግስት እንድጠብቁ አደራ እንላለን ሁልጊዜም ውጤት ሲለቀቀ መሰል ችግሮች እንደሚኖሩ ይታወቃል ።
ውጤት ሰኔ 16 እንደሚገለጸ ትላንት ተናግረን ነበር
https://result.ethernet.edu.et/usernamepage
ለታማኝ እና ፈጣን መረጃ ይቀላቀላሉን
5 660
‼️❗️ማስታወቂያ❗️‼️
ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህ.ሴ.ጣ.ኮ ግቢ ተመራቂ እና መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ፤
ለሁሉም ተመራቂ እና መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የዘንድሮው የትምህርት ዘመን እየተጠናቀቀ ስለሆነ፣ ተመራቂ ተማሪዎች በሪጅስትራል ኦፊስ በተገለፀው ቀን ፤ ተመራቂ ያልሆናችሁ ደግሞ ከነገ ጀምሮ እስከ "ሰኔ 19/2018 ዓ.ም" ድረስ የክሊራንስ ሂደታችሁን በአግባቡ አጠናቃችሁ ከወዲሁ ሻንጣችሁን እና ጉዟችሁን እንድታመቻቹ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ይህንን አስቀድመን ለማሳወቅ የወደድነው፣ ከ "ሰኔ 21/2018 ዓ.ም" ጀምሮ ግቢው ለተማሪዎች የሚሰጠውን ማንኛውንም አይነት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ የሚያቋርጥ ስለሆነ፣ ተማሪዎች ይህንን ተረድታችሁ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ከካፌ ውጪ (Non-Cafe) ለሆናችሁ ተማሪዎች ወርሃዊ የኑሮ መደጎሚያ (Cost-sharing) ገንዘባችሁን በተመለከተ፤ ምናልባትም በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት (ቢበዛ በሁለት ቀናት ውስጥ) ወደ የባንክ ሂሳባችሁ ገቢ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን።
ከህ.ጤ.ሳ.ኮ ተማሪዎች አገልግሎት ዲን
@uogzena
5 660
የማያልቁ የመሰሉ እነዚያ አመታቶች የማይነጉ የመሰሉ እነዚያ ምሽቶች በመጨረሻም ወደ ፍፃሜው ደረስን ምን አልባት አሁን ዳግም ግቢያችን ሊናፍቀን የሚችልበት ጊዜ እሩቅ አይደለም :: ስንት ዓመት አብረን ያሳለፍናቸው ወዳጆቻችንን የምንሰናበትበት ቀንም ቅርብ ነው አላልቅ ያሉን ቀናቶች አልቀው ለቀሩት ጥቂት ቀናቶች የምንሰስትበት ቀን ላይ ደርሰናል ::
ተማሪ አንተነህ ከ GC campus ለተመራቂ ተማሪዎች አድርሱልኝ ብሎ የላከልን መልዕክት 🙏🏻
@uogzena
5 660
ጎንደር ዩንቨርስቲ የ አመቱን ትምህርት ያጠናቀቀቁ ተማሪዎችን እየሸኘ ይገኛል
ተማሪዎች ወደየ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ሲሆን uogzena ዘንድሮም ለተማሪው ድምፅ እየሆነ ብዙ መረጃዎችንም እያደረሰ መልካም የትምህርት ዓመት አሳልፋችው ወደየ ቤተሰቦቻችው ለምትቀላቀሉ ዉድ ቤተሰቦቻችን መልካም የእረፍት ጊዜ እንዲሆንናልችው እንመኛለን ::
በጉዞ ላይ ያላችው ሰላም ያግባችው ለመሄድ ያሰባችው መልካም ጉዞ እንመኝላችዋለለን ::
አሁንም በግቢው የሚካሄዱ ሁነቶችን በጥራት እና በታማኝነት ማድረሳችንን እንቀጥላለን ::
@uogzena
5 660
ማስታወቂያ
ለመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች
የአመቱን ትምህርት የጨረሳችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ስትመጡ የፋይዳ መታወቂያና የቲን ቁጥር /TIN Number/ ይዛችሁ እንድትመጡ እያሳሰብን ምዝገባ ያለፋይዳ መታወቂያና ቲን ቁጥር /TIN Number/ እንደማይደረግ እናሳውቃለን።
5 660
27/09/2018
ለሬሜዲያል ተማሪዎች በሙሉ
ዛሬ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጠዋት 2:00 ላይ በነበረው ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ዘግይተው በመምጣታቸው በቀጣይ በነበረ ፈተና ላይ የተወሰነ ሰዓት ወስዷል። ስለሆነም ከነገ ጀምሮ የጠዋት 2:00 ሰዓት ተፈታኞች 1:30 ላይ በመፈተኛ ክፍሎች እንድትገኙ እያሳሰብን። በሰዓቱ ባለመገኘት ለሚፈጠረው የሰዓት መሸራረፍ ኃላፊነቱ የተማሪው መሆኑን እናሳውቃለን።
5 660
ውድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እና አጋሮች እንኳን ደስ አላችሁ!
********
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ ምዘና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቡ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ፣ መምህራንና ተመራማሪዎች ፣ ተማሪዎችና ሰራተኞት እንዲሁም አጋር አካላት እንኳን ደስ አላችሁ!
በ2026 የCenter for World University Rankings (CWUR) ዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር መሠረት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚከተሉትን ደረጃዎች አስመዝግቧል፦
በኢትዮጵያ ካሉት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ 2ኛ ደረጃን ፣ ከምስራቅ አፍሪካ ደግሞ የ4ኛ ደረጃን ሲያገኝ ከአፍሪካ 43ኛ ሲሆን እንዲሁም በዓለም ደረጃ 1,517 በአጠቃላይ 68.0/100 ውጤት በማስመዝገብ ከዓለም ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ከከፍተኛዎቹ 7.2% ውስጥ ሊካተት ችሏል።
ይህ ታላቅ ስኬት የዩኒቨርሲቲው ማ/ሰብ እና የአጋር አካላት በጋራ በመቀናጀት በመማር ማስተማሩ ፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎቱ እየተከናወነ ያለው ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና እየላቀ በመምጣቱ ይህ ከፍተኛ ውጤት ሊመዘገብ ችሏል።
ስለሆነም ለዚህ ያላሰለሰ ጥረታችሁ ለዚህ ልዩ ስኬት ደርሳችኃልና ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ!
ወደፊትም ከዚህ የበለጠና የላቀ ስኬት ለማስመዝገብ የሚያበረታታ ውጤት ነውና በአንድነት ተባብሮ በመስራት ለተሻለ ውጤት እንነሳ!
********
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ግንቦት 27/2018 ዓ.ም.
5 660
Global Recognition, National Pride.
***
University of Gondar Ranked 2nd in Ethiopia, 43rd in Africa, and is among the top 7.2% of universities globally. The University continues to make its mark on the world through excellence in research, innovation, and academic achievement.
****
Devoted to Excellence!
Public Relations Directorate
June 4, 2026
Follow us on:
Facebook:
https://www.facebook.com/TheUniversityofGondar?mibextid=9R9pXO
LinkedIn:
https://www.linkedin.com/school/university-of-gondar/
Twitter:
https://twitter.com/UoGondar?t=rgtSo_84UZRyWznpPej3-g&s=09
Telegram:
https://t.me/UofGondar
WhatsApp:
https://whatsapp.com/channel/0029VaKhoG11XquVQkSDPM3F
YouTube:
https://www.youtube.com/@UniversityofGondarOffici-lv9ml
5 660
Greetings,
All first-time Exit Exam candidates are required to complete identity verification using the National ID in order to sit for the exam.
Please visit the link below to verify your identity:
👉 https://verify.ethernet.edu.et
Video Guide:
🎥 https://youtu.be/6sH8UVac1Cg
If you have any questions, please leave your comments in the comment section.
Thank you.
---
ሰላም፣
ለመጀመሪያ ጊዜ የ መውጫ ፈተና የሚትወስዱ ተፈታኞች በሙሉ፣ ፈተናውን ለመውሰድ በብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የመለያ ማረጋገጫ ማረጋጋ ገጥ ይጠበቅባችኃል።
መለያዎን ለማረጋገጥ የሚከተለውን ዌብ ሳይት ይጎብኙ፡
👉 https://verify.ethernet.edu.et
@Uogzena
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
