cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

🔮ምክር📝ለሰለፊያ ወጣቶች! وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ وَارْكَعُوا مَعَ الرَّاكِعِينَ

➩ኢብኑ ኡሰይሚን አሏህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ፦ 📚➷ቀብር የጨለማ ሀገር ነው። ቀብር ውስጥ የሚታይ ፀሀይም ሆነ ጨረቃ የለም። ነገር ግን አንድ ሰው ከሰጋጆች ከነበረ አሏህ ቀብሩን ብርሀን ያደርግለታል። https://t.me/UMUHuzaifa2666

Show more
Advertising posts
793
Subscribers
-124 hours
No data7 days
+2630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

☑️ መተኛትህ ካልቀረ በሱና ላይ ሁነህ ተኛ !! ➰➰➰➰➰➰➰➰➰➰➰➰ ✅ ቻት እያደረክ ከዛም ከዚህ ትርፍ ወሬ እየተላላክ አልፎም ከአጅ ነብይ ጋር በሀራም እያወራህ ከምትተኛ፦ የመኝታ ዚክር ብለህ ውዱእ አድርገህ ወደ አላህ ተመልሰህ የበደለህን ይቅር ብለህ ↪️ በመተኛት ሱናውን ህያው አድርግ። ✅ ልብ በል እንቅልፍ ትንሹ ሞት መሆኑን አስታውስ ተኝተህ በዛው ልትቀር ትችላለህ። የውመል ቂያማ በሞትክበት ሁኔታ ነው የምትቀሰቀሰው በሀራም ተግባር ላይ ሞተህ በሚያስጠላ ሁኔታ ከምትቀሰቀስ በሱና ላይ ተኝተህ በሱና ላይ መቀስቀስን ምረጥ። ➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘ https://t.me/abushuayb1
Show all...
Abu shuayb (Channel)

القناة الرسمية للأخ أبي شعيبٍ السلفيِّ

✍በጋብቻ ዙሪያ የተደረገ ዳሰሳ 🎙 በኡስታዝ አቡ ፊርዶወስ አላህ ይጠብቃው! 🗒 ዛሬ እሁድ ምሽት ሰኔ  2016 E.C በአልፋሩቅ የሰለፍዮች መድረሳ የተደረገ ሙሐደራ ➴➘➴➘ https://t.me/alfarukmedrasa
Show all...
4_6035222576152712112.mp313.55 MB
👍 1
«ሴት እንዳትበልጥህ ከፈለክ ጠንክረህ ተማር  !    አንዳንዱ ወንድም ሴት አታስተምረኝም ይላል አቦ አትጃጃልብኝ ታዳ ሴት እንድታስተምርህ ካልፈለክ መማርነዋ ተምረህ ብለጣት ምን ሁነሃል   ጠንካራዋን ፈልገህ እንዳበልጥህ ፈርተህ እረግ ሁለት ወዶ ይሆናልን ?እረ በጭራሽ  ወይ ቀጥ ብለህ ተምረህ ማሳየት ነው ወይ  የመረጥካትን መምሰል ነው!?    #የምን መቀዋለል   ነው ?
Show all...
👍 3
00:36
Video unavailableShow in Telegram
📝رَبِّ هَبْ لِي حُكْمًا وَأَلْحِقْنِي بالصَّالِحِينَ وَاجْعَلْ لِي لِسَانَصِدْقٍ فِي الآخِرِينَ وَاجْعَلْنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ النَّعِيمِ
Show all...
4.55 MB
Photo unavailableShow in Telegram
📝በዚች አለም ላይ ምትክ የሌላት እናት ብቻ ነች ሌላው ሁሉም ተተኪ ሲኖረው እሷ ብቻ ነች ምትክ የሌላት እናት ልዩ የአሏህ ስጦታ ናት እናትን የመሰለ ማን አለ እንደሷ የሚረዳ እንደሷ የሚከባከብህ እንደሷ ከነ ጎዶልህ ከነ ስህተትህ ከነ ጥፋትህ የሚወድህ በሁሉም ነገር ከጎንህ የሚሆን ማን አለ? Soእናትህን በደብ ተከባከብ በሃያት እያለች ተከባከባት አስደስታት ኡሚ አብሽሪ በላት አሳርፋት በቻልከው ሁሉ እገዛት ልብ በል ከነ ችግርህ ከነ ስህተትህ የምትወድህ ምንም ሳትሰት ፍቅር የምትሰጥህ እሷ ብቻ ነች ከማንም ጋ አታወዳድራት ከማንም ጋ እኩል አታድርጋት!! ✍️መንገደኛዋ ከመገዷ! https://t.me/UMUZekeriya3519 https://t.me/UMUZekeriya3519
Show all...
👍 1
🚫  እህቶችን መሰረት ያደረገ የሿሿ ጥቃት       ሿሿ ማለት የሚታወቀው በአንድ ሚኒ ባስ ታክሲ ላይ ከስብእና የወጡ ሴቶች የሽማግሌ ቀላሎችና ወሮበላ ወጣቶች ተሰባስበው የሶስት ሰው ቦታ ከፊት ከመሀልና ኋላ ክፍት አድርገው ከተሳፋሪ ውስጥ የሚፈልጉትን ሲያገኙ አንድ ሰው ብቻ ብለው ያስገባሉ ። በክብር ቦታ የተለቀቀለት በማስመሰል የሚፈልጉት ቦታ እንዲቀመጥ ይደረጋል ። ያ ቦታ ማለት የተዋጣለት ፈታሽ የተዘጋጀበት ቦታ ነው ። ፈታሹ ስራውን ሲጀምር ውስጥ ያለው የውርጋጦች ስብስብ ረብሻ ይፈጥራል ። ሹፌሩ መኪናውን የሚገለብጠው ይመስላል ። በዚህ መሀል ግራ በመጋባት ምን እንደተፈጠረ ሳይገባው በፍተሻው የተራቆተው እንግዳ ተሳፋሪ እንዲወርድ ይደረጋል ። ወደራሱ ሳይመለስ ግራ እንደተጋባ ቆሞ ታክሲውን ያያል ። ታክሲው ትቶት ይፈተለካል ።   ወደራሱ ሲመለስና ኪሱን ሲፈትሽ ተራቁቷል ። ለመደወል ስልክ የለም ለመሳፈር ሳንቲም የለም ። የዚህን ጊዜ ነው የድራማው ሚስጢር የሚገባው ። ይህ ነው ከዚህ በፊት በሿሿ የሚታወቀው ።      የአሁኑ ሿሿ የረቀቀና ከውጭ የመጡ ወይም የውጭ ሀገር እድል ያገኙ እህቶችን መሰረት ያደረገ ነው ። በአብዛኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አካባቢና እንዲሁም ኤምባሲዎች አካባቢ ነው የወጥመዱ አካባቢዮች ።     ይህን በድራማ መልኩ የሚሰራ ትእይንተ ዘረፋ የሚያካሄዱ ዋልጌዎች በተቀናጀ መልኩ ስፍራ ስፍራቸውን ይይዛሉ ። በቅርብ ርቀት ቦታና የስራ ድርሻ ይመዳደባሉ ። የተንጣለለ ጊቢ ተከራይተው ለእኩይ ተግባራቸው ያዘጋጃሉ ።      በአብዛኛው ሒጃብ የለበሱ ሴቶችና ፂም ያስረዘሙ ሱሪ ያሳጠሩ ኮፍያ ያጠለቁ የሙስሊም ገፀባህሪ ተደርገው የተዘጋጁ የድራማው ተሳታፊ ይሆናሉ ። በዚህም በቀላሉ የሙስሊም እህቶችን ዐይን ይስባሉ ።      ከቀረጥ ነፃ ወረቀት ውክልና ሰጥተው ለማረጋገጥ ወደ ውጪ ጉዳይ የሚሄዱ , የጋብቻ ወይም የልደት አሊያም የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥም ወደዚያ የሚያመሩ እህቶች በተለይ ከተማውን የማያውቁ ከሆኑ ቶሎ ይታወቃሉ ። ወዲያው በእነዚያ በተዘረጋ ሰንሰለት አቀባበል ይደረግላቸዋል ።       ሙስሊሞች ከሆኑ በባለ ሒጃቧ ወዴት ነው ?  ተብለው ይጠየቃሉ ያለ ምንም መጠራጠር ለምን ጉዳይ ወዴት መሄድ እንደሚፈልጉ ይናገራሉ ። እኔም ወደዛው ነኝ አብረን እንሄዳለን ይባላሉ ።  ጉዞ ይጀመራል ። ከደቂቃ በኋላ መኪና ይዞ የቆመ የሰንሰለቱ ተዋናይ ጋር ይደርሳሉ ።  ባለ ሂጃቧ ውጪ ጉዳይ በየት በኩል ነበር የሚያስገባው ?  ብላ ትጠይቃለች ። ተዋናዩም ግቡ ላድርሳችሁ ይላል ። ወደ ትወናው ቢሮ ጊቢ አድርሶ ያው ብሎ አውርዶ ይሄዳል ። በድራማው የተመለመሉ የወንድና ሴት ጥበቃዎች የት ነበር ብለው ይጠይቃሉ ይነገራቸዋል ።      እዚህ ጋር የሚሰራውን ድራማ ለመረዳት ወደ ተለያዩ በጣም ጥብቅ የሆኑ የመንግስት ተቋማት ሲገባ ያለውን ሁኔታ ላስታውሳችሁ ።      እንደ ሰላም ሚኒስቴር ፣ ደህንነትና መረጃ ፣ ኤር ፖርትና የመሳሰሉ ቦታዎች ሲገባ አንድ ሰው ወንድም ይሁን ሴት ወደ ውስጥ ለማለፍ ፍተሻ አልፎ ነው የሚገባው ። ፍተሻው ጋር ኤክስሬ ማሽን አለ ። ማንም ሰው በእጁም በኪሱም የያዘውን ማንኛውንም ብረት ነክ ነገር እንደ ሰአት ፣ ቁልፍ ጌጣጌጥ ፣ ቀበቶም ጭምር አውጥቶ በማሽኑ እንዲያልፍ አድርጎ ራሱም በሌላ ፈታሽ ማሽን አልፎ ይሄድና ያ በማሽን እንዲያልፍ ያደረገውን ንብረቱን ይወስዳል ። ከዚህ በኋላ ወደ መስሪያ ቤቱ ቢሮ ያመራል ።      ይህ ታዲያ እነዚህ ድራማ ሰሪዮች እንዴት እንደሚጠቀሙበት እንይ : – ይህች ድራማ የሚሰራባት ምስኪን እህት በእነዚህ ተልእኮ በተሰጣቸው ሴት ፈታሾች ምንም ብረት ነክ ነገር ይዞ መግባት አይፈቀድም ስለዚህ ሰአት ፣ ሞባይል ፣ ጌጣ ጌጦችን በሙሉ አውጥተሽ በቦርሳሽ ውስጥ አድርጊ ትባላለች ። ምስኪኗ እህትም የተባሉትን በሙሉ በቦርሳው ውስጥ ያለውን ብርም ጭምር ታስረክባለች ። ምናልባት ፓስፖርትና የሚረጋገጠው ወረቀት ቦርሳው ውስጥ ካለ በፓስፖርቱ ውስጥ መቶ ብር ተደርጎ ይሰጣታል ። ወደ ተባለው ቢሮ ስትገባ ማንም የለም ትንሽ ቆዪ ይመጣሉ ትባላለች ። ይሁን እንጂ የሚመጣ የለም ለመጠየቅ ስትወጣ ዘበኛው ተቀይሮ ሌላ ነው ።  ስትጠይቀው ቢሮ ገና ሰው ያልገባበት ባዶ ነው ። የምን የውጪ ጉዳይ ነው እንዲህ የሚብል ነገር አላቅም ይላል ። ‼      ኤምባሲ ከሆነ ድራማ ሰሪዮቹ በታክሲ ወደ ኤንባሲ የመጡ እህቶችን አዛኝ መስለው ኤምባሲው ከዚህ ለቋል ተብለን ነው ኑ ወደ አዲሱ ቢሮ አብረን እንሄዳለን በማለት የተለመደውን ድራማ ይሰራሉ ። ሴቶችን መሰረት ያደረገው ሿሿ ይህን ይመስላልና እህቶች ራሳችሁን ጠብቁ ።     ወጪ ለመቀነስ ብላችሁ በታክሲ ከመሳፈር በሚታወቁ ታማኝ ራይዶች ሄዳችሁ ጉዳያችሁን ፈፅማችሁ በሰላም ተመልሳችሁ ተመጣጣኝ ዋጋ ብትከፍሉ ከአስደንጋጭ ዘረፋ ትድናላችሁና ለማንኛውም ተጠንቀቁ ።           http://t.me/bahruteka
Show all...
የኒካሕ ፕሮግራም ጥሪ ➹➹➹➹➹➹➹ اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎ የፊታችን እሁድ  2015 ዓ.ል     ⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️        ወር  ቀን አመት ሰኔ (10) 16      2016 አል      June  [6] 23  2024  እአአ ▱▪️▱▪️▱▪️▱▪️▱▪️  ذو الحجة    ١٧    الاحد   ١٢     ١٤٤٥ ሂ  1445 ሂ     12       እሁድ      17     ዙል ሂጂሪህ የወንድማችን ሙሀመድ እና የእህታችን አዒሻ ኡሙ መርየም በአላህ ፍቃድ ስለሚደረግ #የኒካሕ #ፕሮግራም 📩ውድ የሱንና ወንድም እህቶቻችን ሆይ! ሁላችሁም የዚህ የደስታ ቀን ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ ከወዲሁ በአክብሮት ተጋብዛችሃል። በእለቱ ከኒካህ ፕሮግራሙ ደስታ ጎን በኡስታዝ  ምክር የሚሰጥ ይሆናል። ተጋባዥ ኡስታዛችን 🎙ኡስታዝ አቡ ፊርደውስ አብዱ ሶመድ ሙሀመድ ሀፊዛሁሏህ " " #በእለቱ ከዒሻ ሶላት በኋላ በኢትዮ 🇪🇹 3 :00ሰዓት ከምሽቱ በሳኡዲ 🇸🇦9 :00 ሰዓትከምሽቱ መልካም              ጋ                 ብ                        ቻ 👇👇👇👇 https://t.me/alfarukmedrasa
Show all...
📚📚የአል ፋሩቅ መድረሳ ኦድዮዎች የሚለቀቁበት ቻናል📚📚

‏قال العلامة الفوزان - حفظهُ الله-: "من انحرف عن طريقة الرسول ﷺ فإنه لا يُتَّبع ولا يُقْتَدى به ولو كان عالماً" 📚أهمية التوحيد - صف36

🎤  ለአረፋ ተጓዘዦች    የተከበራችሁ በየአመቱ ለዒደል አድሓ ቤተሰብ ዚያራ የምትጓዙ ሙስሊም ወንድምና እህቶች በመጀመሪያ ጉዟችን ከሓራም የራቀ ሊሆን ይገባል ። አጅ ነብይ ወንድና ሴት ተቀላቅሎ ከመሄድ ፣ ከሙዚቃ ፣ ከጫት ፣ ከሲጋራ ፣ ካላስፈላጊ ቀልድና ንግግሮች የተጠበቀ ከተቻለ ሐዲስ እየሰማን ወይም እርስ በርሳችን እየተዋወስን አላህ አድረሶን ለቤተሰብ ዝያራ ስላበቃን እያመሰገንን መሆን አለበት ።     ሌላው ዲናችን ወላጅን ማስደሰት በጣም ትልቅ ቦታ ሰጥቶ መለኮታዊ በሆነው የአላህ ቃል ከሱ ሐቅ ቀጥሎ አውስቶታል ። በመሆኑም ወላጅን ለማስደሰት የሚሰሩ ነገሮች መጀመሪያ አላህ የፈቀዳቸውና የሚወዳቸው ሊሆኑ ይገባል ። አላህ እርም ( ሐራም ) ባደረገው ነገር ወላጅን ማስደሰት በራሱ ሐራም ስለሆነ ።      ወላጆቻችን ዱንያ ላይ እንዳይቸገሩ ፣ እንዳይራቡ ፣ እንዳይጠሙ ፣ እንዳይታረዙ ልብስና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ይዘን እነደምንሄደው ሁሉ አኼራ ላይ እንዳይቸገሩ ፣ እንዳይበዝኑ ፣ ከከሳሪዎች እንዳይሆኑ አኼራን የሚያጠፉ ነገሮችን በማሳወቅ እንደ ሽርክና ወደ ሽርክ የሚያዳርሱ ተግባሮችን በመንገር እንዲርቁና እንዲጠነቀቁ ፣ ከተለያዩ ወንጀሎች እንዲርቁ ማስታወስ ፣ ሐዲስ እንዲሰሙ መንገር ፣ የሽርክን አደገኝነት በጥሩ አገላለፅ በአስተማሪነት ስሜት ሳይሆን በጣም በተጨነቀ ልጅነት ስሜት ማስረዳት ያስፈልጋል ። በፍፁም የበላይነትና አውቃለሁ የሚል ስሜት ከኛ እንዳያዩ ማድረግ ።      ከጎረቤት ጋር ከአካባቢ ጋር ሊኖር የሚገባውን መልካም አኗኗር ማስታወስ ። የተቸገረ ሰው ከረዱ ያን ነገር እንዳያስታውሱት ፣ እንዳይመፃደቁ ፣ የተረዳው ሰው ለእነሱ እንዲተናነስላቸው እንዳይፈልጉ መርዳታቸውን እንዲረሱት መንገር ። ስለ ጎረቤት ሐቅ ፣ ስለ ዘመድ ሐቅ ፣ ስለባልና ሚስት ሐቅ ማስታወስ በጣም አስፈላጊ ነው ። በተቻለ መጠን እነዚህን ለመፈፀም ከጣርንና ከወንጀል ነገሮች ርቀን በዒባዳ ላይ ጠንክረን ለሰዎች በተግባር አሳይተን ዒዱን ካሳለፍን በአላህ ፈቃድ እጥፍ ድርብ ምንዳ ይዘን እንመለሳለን ።          አላህ ከተጠቃሚዎች ያድረገን ። በድጋሚ የተለቀቀ። http://t.me/bahruteka
Show all...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

በጀመዐህ ተክቢራ ማድረግ እንደማይፈቀድ ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል ዑሰይሚን እና ሸይኽ ሙቅቢል (አላህ ይርሃማቸው) ይናገራሉ የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን👇👇 #join  በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
Show all...
ما_حكم_التكبير_الجماعي_يوم_العيد؟_1.mp31.95 KB
حكم_التكبير_الجماعي_في_العيد_الشيخ.mp33.13 KB
አጥፍተሽ ወጥተሽ አምላክሽን አላህን አወድሰሽና አልቀሽ ለእርሱም ሰግደሽ ተመለሺ። ይህን ማድረግ ካልቻልሽ ግን አላህን ፈርተሽ ቤትሽ ይስፋሽ!!። »-» ወደ ዒድ ቦታ ሲኬድ ድምፅን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማለት ተደንግጓል። አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል:- وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ «ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡» አል-በቀረህ 185 ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ተይዞ፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺ በሁለቱ ዒዶች ከፈድል ኢብኑ ዐባስ፣ ከዐብደላህ፣ ከዐባስ፣ ከዐሊይ፣ ከጀዕፈር፣ ከሀሰንና ሁሰይን፣ ከኡሳማ ኢብኑ ዘይድ፣ ከዘይድ ኢብኑ ሃሪሰህ፣ ከአይመን ኢብን ኡሙ አይመን (ረዲየላሁ ዐንሁም) ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ተክቢርና ተህሊል እያሉ ይወጡ ነበር። [በይሀቂይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በኢርዋእ አልገሊል 3/123 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።] የተክቢራውን አደራረግ በተመለከተ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ሶሂህ የሆነ ዘገባ የለም። ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ግን የሚከተለውን የተክቢራ አይነት ይጠቀም እንደነበር ተረጋግጧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ ላ! ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ” [ኢብኑ አቢ ሸይባ በሶሂህ ሰነድ ዘግበውታል።] ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስም እንደሚከተለው ይል እንደነበር ተዘግቧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ፣ አላሁ አክበር ወ አጀልሉ፣ አላሁ አክበር ዐላ ማ ሐዳና” [በይሀቂይ ሶሂህ በሆነ ሰነድ ዘግበውታል።] »-» የተክቢራ ጊዜን በተመለከተ የዒደል ፊጥር ተክቢራ የዒዱን ቀን ተሰግዶ እስኪያበቃ ነው። የዒዱል አድሃ ተክቢራ ደግሞ ከዐረፋ ንጋት ሶላት ጀምሮ በተከታታይ አያሙ ተሽሪቅ እስኪጠናቀቅ ድረስ ነው። (የውሙ ዐረፋ ማለት ከዙል ሒጃ 9ኛው ቀን ነው።) ይህ አጠቃላይ ሰለፎች፣ ሶሃባዎች፣ አራቱ መሪዎችና ፉቅሃዎች የተጓዙበት መንገድ ነው። [ሶሂህ ፊቅህ አስ-ሱና አቡ ማሊክ ከማል] »-» አንዳንድ ሰዎች ዒድ ሚሰገድበት ቦታ ሲደርሱ ሱና ብለው ይሰግዳሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ለሁለቱም ዒዶች ከፊታቸውም ሆነ ከኋላቸው ሱና ሶላት የላቸውም። ነገር ግን ነቢዩ ﷺ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ 2ረከዓ ይሰግዱ ነበር። ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከዒድ በፊት ምንም አይሰግዱም ነበር፣ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ሁለት ረከዓ ይሰግዱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ 1076 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ነው ብለውታል።] ለሁለቱም ዒዶች አዛንም ሆነ ኢቃም ማለት የለም። »-» የዒድ ሶላት የአሰጋገድ ሁኔታን በተመለከተ እንደሚከተለው ነው:- የዒድ ሶላት 2ረከዓ ነው። ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብሏል:- “የተጓዥ (የጉዞ) ሶላት 2ረካዓ ነው። የዒደል አድሃ ሶላትና የዒደል ፊጥር ሶላትም ሁለት ሁለት ረከዓ ነው። እርሱም አጥሮ ሳይሆን ሙሉው ነው 2ረከዓ በነቢያችሁ አንደበት የተደነገገ ነው።” [ነሳኢይ እና ኢማሙ አህመድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] » የመጀመሪያውን ረከዓ ልክ እንደሌላው ሶላት  በኢህራም ተክቢራ ይጀምራል። ከዚያ በኋላ ሰባት ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል። ሰባቱ ተክቢራ በሚደረግበት ወቅ እጅ ማንሳቱ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ነገር ግን ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር የነቢዩን ﷺ ሱንና አጥብቆ የሚከተል ከመሆኑም ጋር በሰባቱም ተክቢራ ጊዜ እጁን ያነሳ ነበር ይላል። ሌላው በየ ተክቢራው መሃል የሚባል ዚክር ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ነቢዩ ﷺ በየ ተክቢራው መሃል "አላህን ያወድሱም ያመሰግኑም ነበር” ብሏል። [በይሀቂ የዘገቡት ሲሆን ሰነዱ ሀሰን ነው።] ከሰባቱ ተክቢራዎች በኋላ ፋቲሃ ይቀራል ከዚያም ሱራዎች ይቀራሉ። ተወዳጅ ሱራዎች "ቃፍ፣ ወል ቁርኣኒል መጂድ፣ የሚለውና ኢቅተረበቲ ሰኣቱ… እንዲሁም ሰቢህ እስመ ረቢከል አዕላና ሐል አታከ ሀዲሱል ጋሺየህ…" ሱራዎች ናቸው። [ሙስሊምና ነሳኢይ ሌሎችም ዘግበውታል።] ከዚያም በሁለተኛው ረከዓ ተነስቶ ለመቆም ከሚለው ተክቢራ ውጭ አምስት ተክቢራዎችን ይላል። ከዚያ በኋላ ልክ በመጀመሪያው ረከዓ እንዳደረገው ፋቲሃን እና ሌሎችን ሱራዎች ይቀራል። ከዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ተይዞ፣ “የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዒደል ፊጥርና በዒደል አድሃ ሶላት በመጀመሪያው ረከዓ ሰባት ተክቢራዎችን በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ አምስት ተክቢራዎችን ይሉ ነበር።” ብላለች። [አቡዳውድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] በመጨረሻም ከተሸሁድ በኋላ ያሰላምታል። »-» ወደ ዒድ ቦታ ከተጓዙባቸው መንገዶች በተቃራኒ መንገድ መመለስ ሱንና ነው። ከጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ የዒድ ቀን ከሆነ በተቃራኒ መንገድ ይጓዙ ነበር።” [ቡኻሪ ዘግበውታል] አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ ወደ ዒድ መስገጃ ቦታ ከወጡ መጀመሪያ ከወጡበት መንገድ በተቃራኒው ይመለሱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ ዘግበውታል] አላህ ዒዳችንን አላህን የምንታዘዝበትና አላህ በሚፈቅደው መልኩ የምንደሰትበት ዒድ ያድርግልን!! ✍🏻ኢብን ሽፋ: (t.me/ibnshifa) የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን👇👇 #join  በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
Show all...
[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.