en
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Open in Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Show more
3 309
Subscribers
-224 hours
-97 days
-3630 days
Posts Archive
የገና ስጦታ ለየኔታ ማኅበረ ቅዱሳን ገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶችን ለማጠናከር የሚውል የገና ስጦታ ለየኔታ በሚል ልዩ የድጋፍ ማሰባሰቢያ እና የስጦታ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም በዚህ ድ
የገና ስጦታ ለየኔታ
ማኅበረ ቅዱሳን ገዳማትና አብነት ትምህርት ቤቶችን ለማጠናከር የሚውል የገና ስጦታ ለየኔታ በሚል ልዩ የድጋፍ ማሰባሰቢያ እና የስጦታ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል፡፡ እርስዎም በዚህ ድጋፍ በመሳተፍ የድርሻዎትን እንዲወጡ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ኑ አብረን እንስራ ለውጥም እናመጣለን ማኅበረ ቅዱሳን ድጋፍዎን፡- 👉 ኢ/ን/ባንክ ፡- 1000003549805 👉 አሐዱ ባንክ ፡- 0025344310901 👉 አቢሲኒያ ባንክ ፡- 15376007 👉 ወጋገን ባንክ ፡- 0042921130101 ለበለጠ መረጃ 0963010101 ይደውሉ!!

📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን [የነገረ ፡አበውን]፡ ትምህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መ
📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን [የነገረ ፡አበውን]፡ ትምህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መጽሐፍ ፡ነው። #እኔ፡በበኩሌ፡ እንዲዘጋጁ ከምመኛቸው፡መጻሕፍት፡መካከል፡ አንደኛው፡ይህ ፡#መጽሐፍ  ፡ነበር ።ስለኾነም ብዙ ፡ምንጮችን  ፡መመልከት፡ የሚያሻውንና፡ ለይቶ፡ ጨምቆ ፡ለማቅረብ ብዙ ድካም ፡የሚጠይቀውን ፡ሥራ  በመሥራት፡ይህን መጽሐፍ  ፡አዘጋጅቶ ስላቀረበልን ወንድማችን #ዲያቆን_አቤል_ካሳሁንን ፡ከልብ ፡እያመሰገንኩ፡ እኛም፡ አንብበን ፡እንጠቀምበት ፡ዘንድ፡ #እግዚአብሔር ፡ይርዳን ፡እላለሁ ። #መምህረ_ቤተክርስቲያን_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ➮ለተወሰነ ጊዜ ጠፍቶ የነበረው ይህ እጅግ ተፈላጊ እንዲኹም አስፈላጊ መጽሐፍ በድጋሚ የታተመ ቢኾንም ጥቂት ኮፒ ብቻ ስለኾነ የታተመው እንዳያመልጠን ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

❝#ሰላም_ለእራኃቲከ። #ተክለ_ሃይማኖት ሆይ፤ ልዩ ትሩፋተ ሀብትን ለመስጠት እንደ ሁለት አክናፍ ለተዘረጉ መዳፎችህ ሰላም እላለሁ። ቅዱሱ አባት ሆይ፤ መሥዋዕቱ የሠመረለት አቤል የተባልክ አንተ #ተክ
+1
❝#ሰላም_ለእራኃቲከ#ተክለ_ሃይማኖት ሆይ፤ ልዩ ትሩፋተ ሀብትን ለመስጠት እንደ ሁለት አክናፍ ለተዘረጉ መዳፎችህ ሰላም እላለሁ። ቅዱሱ አባት ሆይ፤ መሥዋዕቱ የሠመረለት አቤል የተባልክ አንተ #ተክለ_ሃይማኖት ነህ እኮን። አቤቱ ዘወትር በምትወጣበት ጊዜ በጠላቶቼ ላይ ክንድህን አንሣ። ይልቁንም ወደ ቤትህ በምትመለስበት ሰዓት ዕጥፍ በዕጥፍ በተቃሚዎቼ ላይ ኃይልህን ግለጽ።❞ #እንኳን ለቅዱስ አባታችን ፀሐየ ጽድቅ አቡነ ተክለ-ሃይማኖት እንዲኹም ለሃያ ዐራቱ ካህናተ ሰማይ  ቅዱሳን ሱራፌል ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል አደረሰን!! ➥ በዚህች ዕለት #ቅዱሱ አባታችን አቡነ ተክለ-ሃይማኖት ተነጥቀው ከሃያ ዐራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሃያ አምስተኛ ኾነው መስዋዕተ ዕጣን ያቀረቡበት ዕለት ታስቦ ይውላል !!! #ከቅዱሳኑ_በረከት_ይክፈለን..!🙏 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔ
📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን ማደሪያዎቹ በሆኑ በቅዱሳን ኑሮ ላይ እናገኛቸዋለን፡፡ ያ የመንፈስ ፍሬም ነገረ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቢሰሙት የማይሰለቹት ቢያወሩት የማይጠግቡት ሁልጊዜ መንፈስን የሚያድስ ህሊናን የሚያለመልም ንግግር ነው። #በመምህር_አብርሃም_ፈቃዴ ተተርጉሞ የቀረበልን ዜና አበዊነ ቅዱሳን የሚለው መጽሐፍም ይሄው የአባቶች ጥልቅ ድንቅ የሕይወት ጣዕመ ንግግር ነው᎓᎓ በዘመናቸው ደርሰን በአካለ ሥጋ የማናያቸው አባቶቻችን ዕለት ዕለት እንዲመክሩን የሕይወት ጣዕማቸው ይሄው ደርሶናል፡፡ ወንጌል በሕይወት ስትገለጥ ምን እንደምትመስል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው፡፡በጣዕመ መንፈስ ቅዱስ ከታሹ አባቶች ጋራ ማውራት ምን ያህል ጥቅም እንዳለው ለመረዳት እስከ መጨረሻው ማንበብ ነው። #የኔታ_ገብረ_መድኅን_እንየው 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔ
📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን ማደሪያዎቹ በሆኑ በቅዱሳን ኑሮ ላይ እናገኛቸዋለን፡፡ ያ የመንፈስ ፍሬም ነገረ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቢሰሙት የማይሰለቹት ቢያወሩት የማይጠግቡት ሁልጊዜ መንፈስን የሚያድስ ህሊናን የሚያለመልም ንግግር ነው። #በመምህር_አብርሃም_ፈቃዴ ተተርጉሞ የቀረበልን ዜና አበዊነ ቅዱሳን የሚለው መጽሐፍም ይሄው የአባቶች ጥልቅ ድንቅ የሕይወት ጣዕመ ንግግር ነው᎓᎓ በዘመናቸው ደርሰን በአካለ ሥጋ የማናያቸው አባቶቻችን ዕለት ዕለት እንዲመክሩን የሕይወት ጣዕማቸው ይሄው ደርሶናል፡፡ ወንጌል በሕይወት ስትገለጥ ምን እንደምትመስል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው፡፡በጣዕመ መንፈስ ቅዱስ ከታሹ አባቶች ጋራ ማውራት ምን ያህል ጥቅም እንዳለው ለመረዳት እስከ መጨረሻው ማንበብ ነው። #የኔታ_ገብረ_መድኅን_እንየው 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔ
📖#ዜና_አበው 📖 [ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ] #የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን ማደሪያዎቹ በሆኑ በቅዱሳን ኑሮ ላይ እናገኛቸዋለን፡፡ ያ የመንፈስ ፍሬም ነገረ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቢሰሙት የማይሰለቹት ቢያወሩት የማይጠግቡት ሁልጊዜ መንፈስን የሚያድስ ህሊናን የሚያለመልም ንግግር ነው። #በመምህር_አብርሃም_ፈቃዴ ተተርጉሞ የቀረበልን ዜና አበዊነ ቅዱሳን የሚለው መጽሐፍም ይሄው የአባቶች ጥልቅ ድንቅ የሕይወት ጣዕመ ንግግር ነው᎓᎓ በዘመናቸው ደርሰን በአካለ ሥጋ የማናያቸው አባቶቻችን ዕለት ዕለት እንዲመክሩን የሕይወት ጣዕማቸው ይሄው ደርሶናል፡፡ ወንጌል በሕይወት ስትገለጥ ምን እንደምትመስል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው፡፡በጣዕመ መንፈስ ቅዱስ ከታሹ አባቶች ጋራ ማውራት ምን ያህል ጥቅም እንዳለው ለመረዳት እስከ መጨረሻው ማንበብ ነው። #የኔታ_ገብረ_መድኅን_እንየው 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ሰላም_ለዓምደ_ቤትከ ❝ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ የገዳም እንስሳት ባሕታውያን በተሰማሩባት የአያትም መንገደኛ ኹሉ በሚመገብባት ጸሎትህ ልምላሜዋ የኾነላት ዓምደ ቤትህን በብቃት ፡፡ የጥበበኛ
#ሰላም_ለዓምደ_ቤትከ ❝ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ የገዳም እንስሳት ባሕታውያን በተሰማሩባት የአያትም መንገደኛ ኹሉ በሚመገብባት ጸሎትህ ልምላሜዋ የኾነላት ዓምደ ቤትህን በብቃት ፡፡ የጥበበኛ ጥበቡ የሚደነቀው በሚያነጥረው የወርቅ ቅርፅ ነውና ፡፡ #አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ እዘንልን ፡፡ አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ ራራልን ፡፡ አቤቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ ይቅር በለን ፡፡🙏❞ #እንኳን_አደረሰን!! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧በድጋሚ ታትሟል ... #የነገረ_መለኮት_መግቢያ [በቀሲስ ግርማ ባቱ] #ተማሕልሏዊ ነገረ መለኮት ማለት ከመስማትና ከማገናዘብ ተነሥቶ በጸሎትና በምሥጢራት ወደሚደረሰበት ፍጹም የመገለጥ እምነት መድ
💧በድጋሚ ታትሟል ... #የነገረ_መለኮት_መግቢያ [በቀሲስ ግርማ ባቱ] #ተማሕልሏዊ ነገረ መለኮት ማለት ከመስማትና ከማገናዘብ ተነሥቶ በጸሎትና በምሥጢራት ወደሚደረሰበት ፍጹም የመገለጥ እምነት መድረስ ማለት ነው። ስለዚህ "መንገድ ነኝ" ሲል ጌታችን ያስተማረውን ትምህርት በትክክል እንድንረዳው የሚጋብዘንን ይህን መልካም መጽሐፍ በመጠቀም ከስሜት ከዚያም ከዐውቃለሁ ባይነት ተገብዞ ተላቅቀን ወደ ሕይወት መንገድ እንድንደርስ #ይህን መልካም መጽሐፍ አንብበን እናስነብበው ዘንድ በአዝመራው ባለቤት በመልካሙ ገበሬ ስም አሳስባለሁ።” [ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ] (MA) 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ዜና እረፍት! ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ➾ዐራት ዐይና ቆሞስ አባ ይባቤ በላይ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ የአቡሻኽር፣ የፍትሐ ነገሥት እና የቅኔ መምህር፤ የክብረ ደናግል ናዳ ቅድስት ማርያም ገዳም አበ
ዜና እረፍት! ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ➾ዐራት ዐይና ቆሞስ አባ ይባቤ በላይ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ የአቡሻኽር፣ የፍትሐ ነገሥት እና የቅኔ መምህር፤ የክብረ ደናግል ናዳ ቅድስት ማርያም ገዳም አበምኔት ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰማ። #ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ ወንበር ተክለው በማስተማር በርካታ ሊቃውንትን ወልደዋል። ገዳሙን በማስተዳደርም ጭምር ብዙ አልምተዋል። አሁን ሁሉንም ጥለውት ሔዱ። ናዳ ማርያም ገዳም ላይ ታላቅ ሐዘን ወደቀ። ➥ከዚህ ቀጥሎ ያለው ጽሑፍ የመልአከ ምሕረት ግሩም አለነ ነው። 👇 #ለካ ገዳሙን የሚመራ መሪ - በጉባኤ ቤቱ የሚያስተምር መምህር ፈልጉ! ያሉን የስንብት ቃል ነበርን⁉️ እርሳቸው የተናገሩት እኛም በማስታወሻችን ላይ የጻፍንበት የብርዕ ቀለም ሳይደርቅ ዜና እረፍታቸውን ከመስማት በላይ ምን የሚገርምና የሚከብድ ነገር አለ⁉️ የኔታ ባደረባቸው ፅኑእ ህማም ምክንያት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። #በየኔታ ይባቤ በላይ እረፍተ ሥጋ የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው፣ ለገዳሙ መነኮሳትና መነኮሳይት መጽናናትን እንመኛለን። #ሥርዓተ ቀብራቸው ነገ በ23 የሚፈፀም ! በረከታቸው ይደርብን።ለእውነት ኖሮ ማረፍ የሊቅ መገለጫ ነው!! 📚ግዮን መጻሕፍት https://t.me/GhionBookStore1623

♦ ኅዳር 21 #ጽዮን_ማርያም የምናከብርበት ምክንያት በጥቂቱ 🙏 "ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማኅደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ
+1
♦ ኅዳር 21 #ጽዮን_ማርያም የምናከብርበት ምክንያት በጥቂቱ 🙏 "ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማኅደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል። 👉 ኅዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው ብለን በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት በጥቂቱ፦ 🍀 ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን፣ 🍀 ታቦተ ጽዮን በምርኮ በሄደችበት በሀገረ ፍልስጤም ዳጎን የተባለ የአህዛብን ጣኦት አድቅቃ በድል የተመለሰችበትን ዕለት በማሰብ፣ 🍀 ቀዳማዊ ምኒሊክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገድ እስራኤል የበኩር ልጅ ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛሪያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበትን ዕለት በማሰብ፤ 🍀 በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታልና ይህንንም በማሰብ፤ 🍀 አብርሃ ወአጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተ መቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ፤ 🍀 በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያንን ስታቃጥል ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሀይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ ነው ። ✨🍀✨🍀✨ ለቅድስተ ቅዱሳን ንጽዒተ ንጹዓን ድንግል ማርያም ታላቅ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን! የእናትነት ፍቅሯ ፣ በረከቷ ፣ ጥበቃ እና ምልጃዋ አይለየን 🙏

💧✨💧 እነኾ አዲስ የመጽሐፍ ችሮታ #ከመምህር_በትረ_ማርያም_አበባው 📚#ኦርቶዶክሳዊ_ተዋስኦ [መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠየቁ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው] #በእግረ ሥጋም በእግረ ልቡናም ወደ ጉባኤ ቤ
💧✨💧 እነኾ አዲስ የመጽሐፍ ችሮታ #ከመምህር_በትረ_ማርያም_አበባው 📚#ኦርቶዶክሳዊ_ተዋስኦ [መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠየቁ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው] #በእግረ ሥጋም በእግረ ልቡናም ወደ ጉባኤ ቤት፣ ዐይኖቻቸውን ወደ መጻሕፍት ካቀኑ ወንድሞች መካከል አንዱ መምህር በትረ ማርያም ነው። ዘመኑ ያስገኘውን መገናኛ መረብ ተጠቅሞ ወንጌልን ለሕዝብ በማድረስ የሚደክመው ድካም የልጅ ቁም ነገረኛ አድርጌ በትኩረት እንድመለከተው አድርጎኛል። ዛሬ ደግሞ በዚህ መጽሐፍ በምዕመናን መካከል ለሚመላለሱ ጥያቄዎች አስቦ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ከርሠ መጻሕፍትን በርብሮ መልስ አዘጋጅቶ ማቅረቡ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ሥራ ሆኖ ስላገኘሁት ጥያቄ ቢኖርብንም ባይኖርብንም የሚያነሣቸው ጥያቄዎችና የሚመልሳቸው መልሶች የዕውቀት ዳርቻችንን ስለሚያሰፉልን እንድታነቡ እጋብዛለሁ። ✍️ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ [በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢና የአራቱ ጉባኤያት መምህር] 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#ኅዳር_ሚካኤል #በዚህች ቀን የሰማይ ሰራዊት ሁሉ አለቃቸው መልአከ ምክሩ የምክሩ አበጋዝ ይለዋል የቅድስት ሥላሴ መንጦላእትን የሚከፍትና የሚዘጋ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
#ኅዳር_ሚካኤል #በዚህች ቀን የሰማይ ሰራዊት ሁሉ አለቃቸው መልአከ ምክሩ የምክሩ አበጋዝ ይለዋል የቅድስት ሥላሴ መንጦላእትን የሚከፍትና የሚዘጋ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ቀን ነው። #በኅዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ኅዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡ #ከበዓሉ_ረድኤት_ያሳትፈን_አገራችንን_ኢትዮጵያን_ሰላም_ያድርግልን!🙏 -- በእውነቱ ሀገራችን እንዲኹም ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን እንዲኹም እኛ ከባድ ሐዘን ላይ ነው ያለነው ቸሩ አምላክ ቁጣውን በትእግስቱ መአቱን በምሕረቱ ይመልስልን!!ከእግዚአብሔር በታች የእኛ ብሔራዊ ንስሐ፤ ልባዊ ጸሎትናብርታት ግድ ነውና፥እግዚአብሔር ተነሳኢ ልብን እንዲሰጠን ደግሞም የልብ ንጽሕና እንዲኹም ቅን የኾነ አስተሳሰብ ያድለን ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ምልጃ አይለየን አሜን።+🙏 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#አንድ ወንድም በውስጥ መስመር ስለ መጽሐፉ የደረሰን አጠር መጠን ያለ መጣጥፍ ይህን ይመስላል ተጋበዙልን.......👇 መጽሐፉን ገና እንደተቀበልኩት እስኪ ቆይ መጀመሪያ አባ ጊዮርጊስን እንዴት ጽፎት ይሆን ብዬ ቀጥታ የገለጥኩት እሱ ላይ ነበር (ሰው ወደሚወድደው ነዋ ቀድሞ የሚሮጠው - አትታዘቡኝ እንግዴ -_- )። እንደው ደስ ቢለኝ ላጋራችሁ ፈለግሁ። ገና ዛሬ ነው የወጣው መጽሐፉ። እኔ እጅ ላይ ደግሞ የገባው ከደቂቃዎች በፊት። በጣም ደስ ብሎኛል፤ ለእኔ ከበቂ በላይ ምክንያት ነው መጽሐፉን ለማንበብ። ስለ አባ ጊዮርጊስ የተፃፈውን ከስር ቃል በቃል ጽፌላችኋለሁ ራሳችሁ አንብባችሁ ፍረዱ። (👇🏿): አባ ጊዮርጊስ ዘሰግላ/ጋሥጫ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ የጥበብ ሰማይ ላይ እንደ ንጋት ኮከብ ደምቆ የበራ፣ የእውቀቱ ጥልቀት እንደ ውቅያኖስ የማይመረመር፣ የመንፈሱ ግርማ እንደ ደብረ ታቦር ብርሃን የሚያንጸባርቅ አንድ ታላቅ ሊቅ ተነሥቶ ነበር እርሱም አባ ጊዮርጊስ ዘሰግላ፣ ወይም በሌላ ስሙ ዘጋሥጫ (በግምት ከ፲፫፻፶፯ - ፲፬፻፲፯ ዓ.ም.) በመባል የሚታወቀው የዘመኑ የዕውቀት ፀሐይ ነው:: ሕይወቱ፣ ለዕውቀት ጥማትና ለመንፈሳዊ ከፍታ የተሰጠ ሕያው መሥዋዕት የነበረ ሲኾን፤ በብዕሩ ያፈስሰው የጥበብ ጎርፍ የኢትዮጵያን የአበው ጥናት ወደማይደረስበት የልህቀት ጫፍ አድርሶታል፡፡ ከከበሩ ወላጆቹ ከካህኑ ሕዝበ ጽዮንና ከትውልደ-መኳንንቷ እምነ ጽዮን የተገኘው ይኽ ብርቅዬ ፍሬ የዕውቀት ጉዞው መጀመሪያ እሾኽ የበዛበት ነበር፡፡ የአባቱ ትምህርት እንደ ተራራ ከብዶት፣ የእውቀቱ በር እንደተዘጋበት ሲሰማው፣ ልቡ በሐዘን ተሰብሮ ነበር። ይኽ የመጀመሪያ ፈተና ግን ለታላቅ ጸጋ መቅድም፣ ለሰማያዊ ጥበብም የትሕትና በር መክፈቻ ነበር። በእምነት ወደ ደብረ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ተላከ ይኽ ገዳም የዘመኑ የሊቃውንት መፍለቂያና የመንፈስ ቅዱስ መገኛ። በደብረ ሐይቅ ፀጥታ ውስጥ፣ በዕንባ በታጠበ ጽኑ ጸሎትና እንደ ቅዱስ ትውፊቱ በእናቱ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ምልጃ፣ የሰማይ መስኮቶች ተከፈቱለት፤ የጸጋ ጥበብም እንደ ፏፏቴ ከልዑል ዙፋን ፈሰሰለት:: ከዚህች የተቀደሰች ዕለት ጀምሮ የተዘጋው አእምሮው የጥበብ ማኅደር ኾነ። የቅዱሳት መጻሕፍትን ውቅያኖስ ያለመርከብ የሚሻገር፣ የግእዝን ሥነ-ውበት ምሥጢር የሚመራመር፣ የሥርዓተ አምልኮን ውበት የሚተነትን፣ የቀደምት አበውን ድርሳናት (በተለይ ሃይማኖተ አበውን) የሚጠጣ፣ የአንድምታን ጥልቅ ትርጓሜ የሚፈታ መለኮታዊ ኃይል ተሰጠው፡፡ በዚኽም በዘመኑ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት፣ በጸጋ የተቃኘ የዕውቀት ማዕበል ኾኖ ወጣ። የጥበቡ መዓዛና የዕውቀቱ ዝና ብዙም ሳይቆይ የንጉሡን ደጅ አወደው:: የዐፄ ዳዊት ቀዳማዊ ዙፋን ለዚኽ የዕውቀት ብርሃን እጆቹን ዘረጋ፡፡ አባ ጊዮርጊስም በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ እንደ ቄሰ ገበዝና መምህር ኾኖ ሲያገለግል፣ ዋነኛ ተልእኮው ግን የነገሥታትን ነፍስ መቅረፅ ነበር። በተለይም፣ ለወደፊቱ የኢትዮጵያ ታሪክ ደማቅ ምዕራፍ ለሚጽፈው ለታላቁ ሊቅ ንጉሥ ለዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ የጥበብን ወተት ጋተው፤ የመንፈስን እንጀራም መገበው፡፡ በዚኽም የንጉሡን ልብ በሃይማኖት ቅናት፣ አእምሮውንም በመንፈሳዊ ጥበብ በማነጽ፣ ለሚመጣው ወርቃማ ዘመን የማይናወጥ መሠረት ጣለ፡፡ ክብሩና ሥልጣኑ ከፍ ከፍ እያለ ሄዶ፣ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ገዳማት እናት ወደኾነችው ወደ ጥንታዊቷ ደብረ ዳሞ በንቡረ እድነት ተሹሞ የመንፈሳዊ መሪነትን ጫፍ በመያዝ አገለገለ:: የእርሱ ታሪክ በሰው ድካም ውስጥ መለኮታዊ ኃይል እንዴት እንደሚገለጥ፣ በጨለማ ውስጥም የጥበብ ብርሃን እንዴት እንደሚፈነጥቅ የሚያሳይ ሕያው ምስክር ኾኖ ለዘለዓለም ይኖራል! ... .. . እያለ ይቀጥላል። 📖 ነገረ አበው ኢትዮጵያውያን 📖 ከገጽ ፻፰፩ - ፻፷፬ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧💧💧ወጥቷል !!! በጉጉት ስንጠብቀው የከረምነው #መምህር_ያረጋል_አበጋዝ 📖ኢቮሊዩሺን የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት ? የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ ውሏል..! # ደብተራ_በአማን_ነጸ
💧💧💧ወጥቷል !!! በጉጉት ስንጠብቀው የከረምነው #መምህር_ያረጋል_አበጋዝ 📖ኢቮሊዩሺን የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት ? የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ ውሏል..! # ደብተራ_በአማን_ነጸረ እንዳሉት ...👇 ድሮ፣ የነገሥታት መልእክት ሲደርስህ ባለህበት ቆመህ እጅ ትነሣለህ። የተክለ ጻድቅ መኩሪያ (ተጻመ) ግለ ታሪክ ላይ፥ ጃንሆይ ሲደውሉ ተጻመ እጅ ነሥተው ነው ስልኩን የሚያነሡት። ወጉ ሥርዓቱ ነው። ወገኛ ሆኜ ነው መሰል እኔም ትልቅ ሰው ሲደውል ቁጭ ብዬ አላናገርም። መቆም የማልችበት ቦታ ከሆንኩ ስልኩን አላነሳም። ያረጋል በዚህ ልክ ከማከብራቸው ወንድሞች መካከል ነው። መንፈሳዊ ሕይወትን ከዘመናዊ ንባብ ጋራ በመቃኘት ሁለት ዓይኖች አሉን። አንዱ ያረጋል ነው። ንግግሩንም መጽሐፉንም መንፈሴን ሰበር አድርጌ ነው የምሰማው የማነበው። የምንወድህ Yaregal Abegaz Kebede ስለችሮታህ እናመሰግናለን። --- ➮እኛም እጅ ነስተን አመስግን በልዩ ቅናሽ አቅርበናልና እናንተም መጥታችኹ ሳያልቅ ሸማምቱ...! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

💧አዲሱ መጽሐፍ "#ነገረ_አበው"ወጥቷል.... ➾ስለ መጽሐፉ ከደባትር ግንባር የተሰጠ አስተያየት የሚከተለውን ይመስላል..... "ጨርቆስ ጨርቆስ" ይላል ረዳት። የሕፃኑ ልጆች ግሩማን ወላጆች እየሆኑ
💧አዲሱ መጽሐፍ "#ነገረ_አበው"ወጥቷል.... ➾ስለ መጽሐፉ ከደባትር ግንባር የተሰጠ አስተያየት የሚከተለውን ይመስላል..... "ጨርቆስ ጨርቆስ" ይላል ረዳት። የሕፃኑ ልጆች ግሩማን ወላጆች እየሆኑ ነው። ከቅዱስ ቂርቆስ ቀሲስ መብራቱን፣ መምህር ሰሎሞንን (የክርስቶስ ያለህ! የመጽሐፍ ክምችቱና ለጋስነቱ...)፣ አሁን ደግሞ መምህር በኃይሉ በመጽሐፍ ተከሥተዋል። የሕፃኑ ልጆች በቀለም እየወለዱ ነው። ትሑታንና ቅኖች ለመሆናቸው ምስክሮች ነን። መምህር በኃይሉ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ የነገረ አበው መምህር ነው። Patrology ያስተምራል። ያስተምራል። በመካከል ይነደዋል። የነገረ አበው ብይኖችና ታሪኮች ውጫዊ ተፅዕኖ አይሎባቸው ሲያይ ቅንዓት መንፈሳዊት ትጎበኘዋለች። ያው ምንጩ አለኮ፣ ግን "ሲስተሚክ" ሆኖ ለሥርዓተ ትምህርት እንዲመች ሆኖ አልተስተጋባም፣ compiled ያለመሆን ነገር። ደግሞ አንዳንድ ፈረንጆች የሚሉት ነገር ያናድዳል። ለዓለም ሳትሰጡ ከዓለም ተጠቀማችሁ ይላሉ - ፕሮፌሰር ጌታቸው እንደነገሩን። እነዚህ ተደራራቢ ንግግሮች የቂርቆሱን ፍሬ፣ የቅድስት ሥላሴውን መምህር ለቁጭት ዳረጉት። ብርዑን አሹሎ በየመጻሕፍቱ ፊት ቆመ። መዘገበ። ዘገበ። ተጠራቀመ። ነገረ አበው ኢትዮጵያውያን ከዩኒቨርሲቲው ደቀ መዛሙርት እኩል ትደርሰን ዘንድ በማዕደ ንባብ ከፊታችን ቆመች። አሻግረን ምጽአቷን እየጠበቅን ነው። በመምህርነት ላይ ጽሕፈት ትልቅ ለጋስነት ነውና መምህራችንን ከሩቅ እጅ እንነሳለን። ✍️ደብተራ በአማን ነጸረ 📚ግዮን_መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

† እንኳን ለቅዱስ "ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" " ዓመታዊ በዓል #ኅዳር_7 በሰላም አደረሳችኹ ታውቁ ኖሯል..... #ቅዱስ_ጊዮርጊስ #ቅዱሱ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው
†  እንኳን ለቅዱስ "ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" " ዓመታዊ በዓል #ኅዳር_7 በሰላም አደረሳችኹ ታውቁ ኖሯል.....  #ቅዱስ_ጊዮርጊስ #ቅዱሱ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም [ልዳ] ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን አስተምረውት አባቱ ይሞታል:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ፳ ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት [የአሁኗ ቤይሩት - ሊባኖስ] ሰዎች ዘንዶ [ደራጎን] ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና ፸ ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ ደረሰ:: ከዚያም ለተከታታይ ፯ ዓመታት ብዙ ጸዋትወ መከራዎችን ተቀበለ:: ፫ ጊዜ ሙቶ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ "የሰማዕታት አለቃቸው" ይጠራል። ከ፯ ዓመታት መከራ በሁዋላም ከብዙ ተዓምራት ጋር ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: ፯ አክሊላትም ወርደውለታል:: #ኅዳር 7ም ''ለቅዱስ ጊዮርጊስ'' ቅዳሴ ቤቱ ናት:: እርሱ በ፫፻፺ዎቹ አካባቢ ሰማዕት ከሆነ በሁዋላ በዚያው በሃገሩ ደብር አንጸው: አጽሙን አፍልሠው #በዚህች_ቀን_ቀድሰዋታል:: #ታድያ ከወዲኹ ፕሮግራማችኹን ከእኛ ጋር #በገነተ_ጽጌ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እንድታደርጉ ጋብዘናል..! ከሰማዕቱ ከበረከቱ ይክፈለን::🙏 📚ግዮን መጻሕፍት  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] https://t.me/GhionBookStore1623