5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 157
Subscribers
-224 hours
-57 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from AAU - Muslim Students Union
ለዩኒቨርሲቲያችን አመራሮች፤
የኢፍጣር ዝግጅታችሁን ተመልክተነዋል። ተምሩ ተደርድሯል፣ ውሃውም ቀርቧል። "ለሙስሊም ተማሪዎች አሳቢ" ሆናችሁ ለመታየት የሄዳችሁበት ርቀት "የሚደነቅ" ነው።
ግን አንድ እውነታ አለ፦ ፀሐይ ስትጠልቅ እንደምንራብ ትዝ ያላችሁ አስተዳዳሪዎች፣ ለ18 ወራት ሙሉ የመብት ጥያቄ ስናነሳና "ፍትህ" እያልን ስንጮህ ግን ጆሮአችሁ እንዴት እንደተደፈነ ይገርማል። ለ540+ ቀናት ያህል መልስ አጥተው አቧራ የለበሱ ጥያቄዎቻችንን ችላ ብላችሁ፣ ዛሬ በአንድ ሳህን ምግብና በአንድ ብርጭቆ ውሃ ልታባብሉን መሞከራችሁ ለተማሪው ንቀት ነው።
መልእክታችን ግልጽ ነው፦
* እኛን የራበን ፍትህ እንጂ የእናንተ ዳቦ አይደለም!
* እኛን የጠማን መከበር እንጂ የእናንተ ውሃ አይደለም!
ዩኒቨርሲቲው ሙስሊሙን ተማሪ በእውነት "ያከብራል" የሚባለው በጀት መድቦ ምግብ ሲያቀርብ ሳይሆን፣ ለአንድ አመት ከመንፈቅ ሙሉ መልስ የነፈጋቸውን የመብት ጥያቄዎች ሲመልስ ብቻ ነው። ያለ ፍትህ የሚቀርብ ማዕድ "ግዴታን ለመወጣት" የቀረበ ድራማ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም።
ምግባችሁን ለራሳችሁ አቆዩት፤ እኛ ግን የነፈጋችሁንን መብታችንን እንፈልጋለን!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ግልፅ ማብራሪያ: አቅጣጫ እና ጥሪ ከመጋቢት 1 ቀን ፕሮግራም እና አጠቃላይ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ --- ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !
የሙስሊሙ ተማሪ የመብት ጥያቄዎች ትላንት የነበሩ: በዛሬ ውስጥ ያሉ እንዲሁም መብቱን የሚጥሱ እና የሚገፉ እስካሉ እና እስከቀጠሉ ድረሱ የሚኖሩ እና የሚቀጥሉ ናቸው። እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የነበሩ መሠረታዊ የመብት ጥሰቶችን በመጠየቅ: በመታገል እና እንዲስተካከሉ በማድረግ ሙስሊም ተማሪዎች ብዙ ታሪክ አሳልፈዋል: ሰርተዋልም። ያለፉበት ታሪክ እንደሚያስረዳንም የተጓዙበት መንገድ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ከክላስ እና ትምህርት ጊዜን ቆርሶ ከመስጠት ጀምሮ ብዙ ችግሮች እና ውጣ ውረዶች ነበሩ። ሆኖም ግን በሁሉም የትግል መስመሮች ውስጥ የምንረዳው አንድ ጥሬ ሐቅ ቢኖር ቀደምቶቻችንን ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በማስከበር ረገድ ተምሳሌታዊ ስብዕና እንደነበሩ ነው።
እንዳለመታደል ሆኖም ትላንት በቀደምቶቻችን ላይ ሲደርስ የነበረው የመብት ጥሰት ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ሆኖ ሊሻሻል በሚሞክርበት ሰዓት እንኳ አልቀረም። ይባስ ብሎም የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ: ሕገ-መንግስታዊ መብት የሚንድ እንዲሁም ሐይማኖታዊ መብት የሚገፍ መመሪያ አወጣ። ሕገ-ወጥነትን ሕጋዊ ለማድረግ በመሞከርም መንገዱን ጀመረ።
የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚገፈውን መመሪያ የመቃወም እና እንዲስተካከል የማድረግ ሐላፊነት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቢሆንም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት እንደ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ባለቤት ሆኖ ጥያቄውን ለሚመለከታቸው አካላት እያደረሰ ለ18 ወራት ያክል ዘልቋል። በዚህ ጉዞውም ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሕብረት ጽ/ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፤ ከመጅሊስ እስከ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ ፤ ከሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እስከ ብልፅግና ጽ/ቤት ፤ ከሰላም ሚኒስቴር እስከ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ድረስ ተኪዷል። ለሁሉም አካላት የገቡት ደብዳቤዎች ይዘት ሲጠቃለል "በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰቶች እየደረሱ ነው። በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ፍትሐዊ መፍትሔ ይምጣ።" የሚል ነበር። ሆኖም ከዩኒቨርሲቲው በኩል የሗላሗላ ሲሰጡ የነበሩት ምላሾች "አናውቃችሁም! አንወያይም!" የሚሉ ሲሆን ለሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እና መሠረታዊ መብቶች እውቅናን የነፈገ እንዲሁም ክብር የጎደለው ነበር። የአብዛኛው መስሪያ ቤት ምላሽም ዝምታ እና ቸልተኝነት ነበር።
ከዚህም ባሻገር በዳይ ከሳሽ ሆኖ ዩኒቨርሲቲው የሙስሊም ተማሪዎችን አመራሮች "የዩኒቨርሲቲውን ስም በማጥፋት!" በሚል ርዕስ ስለመብት መጠየቅ እና መሞገትን ከስም ማጥፋት በመቁጠር የዲስፕሊን ክስ ከፍቶባቸዋል። በተለያየ ጊዜም የሕብረቱ አመራሮች ላይ ማስፈራሪያ አከል ማስጠንቀቂያዎችን ሲሰጧቸው ነበር። የመብት ጥያቄዎቹ ሲነሱ እና በደንብ እየተጠየቁ ሲሄዱ ብሎም የሁሉም ሙስሊም ተማሪ አጀንዳ እንደሆኑ በግልፅ እየታወቀ ሲመጣ ደግሞ ሙስሊም ተማሪዎች ተሰባስበው እንዳይወያዩ እስከመከልከል ድረስ ተዘልቋል። በመጋቢት አንድ ቀን የተፈጠረውም ይሄው ነው።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን መልዕክቶች ለማስተላለፍ እንወዳለን።
ለተማሪዎቻችን፦ ስንነሳ እንዳሳወቅነው ይህ ሁሉ ረጂም ጉዞ እና ትግል ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መመሪያ ምክንያት ነው። ስንነሳ ስለመመሪያው፣ ስለ ሰብዓዊ መብቶቻችን፣ ስለ ሐይማኖት ነፃነታችን ፣ ስለ ሕገ-መንግስታችን ፣ ስለ ዩኒቨርሲቲያችን እና ስለ ሀገራችን የነገ እጣፋንታ ጥያቄ አለን በማለት ነው። ፍላጎታችንም ሕገ- መንግስታዊ እና ፍትሐዊ መልስ ብቻ ነው። ለዚህ ሲባል ብዙ ለፍተናል፣ ከፍለናልም። ልናረጋግጥላችሁ የምንፈልገው ነገር ቢኖር ፍትሕ ሰፍኖ መመሪያው እስኪሻሻል ድረስ በምንም መንገድ ጥያቄያችን እንደማይቆም ነው። ለሚወሩ እና ለሚነዙ አሉባልታዎች ጆሮ አትስጡ። አጀንዳ ለማስቀየር ለሚራወጡ አውርቶ አደሮች ልባችሁን ክፍት አታድርጉ። የያዝነው የትውልድ አደራ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ከዚህ ትውልድ አይሻገርም። መነሻችን እንደሆነው ሁሉ እስከመጨረሻውም በዚሁ እንፅና። በአላህ ፈቃድ ድሉ ቅርቡ ነው። እስከዚያው ግን ምንም አይነት መረጃዎች እና ማምታቻዎች ሲያጋጥሟችሁ ለካምፓስ ጀመዓ አሚሮች ታሳውቁና መረጃዎችን በማጥራት ለምናደርገው ሰላማዊ የመብት ጥያቄ አስተዋፅዖ ታደርጉ ዘንድ ጥሪያችን ነው። ቀጣይ ሂደቶችን እና የሚጠበቁ እንቅስቃሴዎችንም በቶሎ የምናሳውቅ ይሆናል።
ለሚመለከታቸው ሁሉ፦ አጀንዳችን የመብት እና መብት ብቻ እና ብቻ እንደሆነ እወቁ። የተማሪ አመራሮችን ማስፈራራት፣ መውቀስ ብሎም ስም መስጠት አላስፈላጊ የሕዝብ ጊዜ እንዲባክን ከማድረግ ውጪ መፍትሔ አይሆንም። እየተነሳ ያለው ስለ ሕገ- መንግስታዊ መብት ነውና በውይይት መፍትሔ መጥቶ የተሻለ ልምምድ እንዲኖረን ለማድረግ እና ተማሪዎች ትኩረታቸውን በትምህርታቸው እና በሌሎች ሀገራዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ እንዲያደርጉ በማገዝ ሀላፊነታችሁን በመወጣት ለሀገር ሊደረግ የሚችለውን ትንሹን ነገር ታደርጉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ጥያቄ አለን!
መልስ እንፈልጋለን!!
አላህ ለሀገራችን የተሻለ ጊዜን ያምጣ!!!
@aaumsu
We only have two hours remaining before the start of the Special Grand Da‘wah program, which will also include the introduction of the Jema, a discussion session, and the Iftar program.
Don't be late!!!
✨አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረከቱ
ቀጠሮአችን አልተዘነጋማ?????✨
🌙 RAMADAN SPECIAL EVENT 🌙
✨ 3rd Grand Iftar Program ✨
Join us for a special evening of Iftar, Dawah, and brotherhood & sisterhood as we come together in the blessed month of Ramadan.
📌 Program Highlights
🍁 Special Dawah Program
🍁 Welcoming Session
🍁 Jema Introduction
🍁 Jema Progress & Future Plans
🍁 Brotherhood & Sisterhood Gathering
🍁 Inspiring Talks from Senior Graduated Jema Members sharing their experience
📅 TODAY-DA‘WAH & IFTAR (Ramadan 22)
🕰 Time: 11:00 LT
📍 Venue: Ambassador
🤝 Come and strengthen the bonds of Iman, unity, and brotherhood & Sisterhood.
السلام عليكم ورحمت الله وبركاته
ጊዜው የረመዳን የመጨረሻ አስርቱ (አሽረልአዋሂር) ቀናት ላይ እንገኛለን::
ለይለተል ቀድር የሚከጀልባቸው ውብ ለሊቶች ( ለይለተል ቀድር :-ትልቅ ደረጃ ያላት ሌሊት ፍጡራንን የሚመለከቱ የአመቱ ውሳኔዎች የሚተላለፍባት የመወሰኛዋ ሌሊት ፣ የሰራነው ኢባዳ ከ1000 ወራት በላይ ማለትም ከ83 አመት ኢባዳ በላይ ተደርጎ የሚፃፍባት ለሊት) ግን እነዚ ለሊቶችን እንዴት መጠቀም አለብን።
👉እንደሚታወቀው ዛሬ 23'ተኛው ሌሊት ከፊታችን እየጠበቀን ነው::
🌐 ስለዚህ ጊዜ አጠቃቀማችንን ማስተካከል አለብን። እንዴት???
❇️ ለይለተል ቀድር በአስሩ ሌሊቶች በአንዱ ሌሊት መኋኑ ስለማይቀር እንዲህ አድርጉ
በመጀመሪያ ሁሉንም ተግባሮቻችንን ለአላህ ብቻ ብለን (በኢህላስ) መስራት አንዘንጋ ሪያ ልፋታችንን መና ታስቀራለች ና በንጹህ፣ ቅን ልቦና ኢባዳችንን እናከናውን።
"ጌታዬ ሆይ! ይህቺ ስራ/ኢባዳ ካንተ ዘንድ ተቀባይነት ታገኝ ዘንዳ ኢህላስን ወፍቀኝ ብለን አላህን እንማፀን"
1. በየሌሊቱ ቢያንስ 10 ብር ሰደቃ መስጠት
2. በየሌሊቱ ቢያንስ 1 ጁዝ መቅራት (ጥቂት አንቀጾችን ቢሆንም መቅራትና ትርጉማቸውን ማስተንተን )
3. በየሌሊቱ ቢያንስ 100 ጊዜ ዚክር (አላህን ማውሳት)
💠ሱብሀነላህ፣ አልሀምዱ ሊላህ፣ላኢላሀ ኢለ ላህ ፣ አላሁ አክበር ፣
💠ላሀውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ፣
ነቢያችን ﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድ ፣ኢስቲግፋር
💠ላኢላኢለላሁወህደሁ ላሸሪከለሁ ለሁልሙልኩወለሁል ሀምዱ ወሁወ አላኩሊሸይኢን ቀዲር
💠ሱብሀነላሂ ወቢሀምዲሂ ሱብሀነላሂል አዚም
💠10 ጊዜ ሱረቱል ኢኽላስ መቅራት (ሱረቱል ኢኽላስን በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ሦስት ጊዜ መቅራት ሙሉ ቁርኣንን የመቅራት (ኸትም) ያህል ምንዳ ያስገኛልና)
4.ዱዓ ማብዛት
ነቢያችን ﷺ ለእናታችን ዓኢሻ (ረ.ዐ) የነገሯት ዱዓ እና ሌሎችንም ሀጃዎቻችን መጠየቅ አላህ የባሮቹን ጥሪ ሰሚ ነውና የምንፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ ዘርዝረን እንጠይቀው። ለራሳችን፣ ለቤተሰባችንና ለወገኖቻችን ከልብ የመነጨ ዱዓ እናድርግ።
ነቢያችን ﷺ ለእናታችን ዓኢሻ (ረ.ዐ) የነገሯት ዱዓ
"اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عني"
5. የተወሰኑ ረከዐዎችን መስገድ
(ለሊት ሁሉም ሰው በተኛበት ሰዓት ተነስተን ጌታችን ፊት ቆመን የውስጣችንን እንንገረው)
6. ፆመኛ ማስፈጠር
እና ሌሎችንም የኸይር ስራዎች መስራት።
⚜️ ማሳሰቢያ :- ይህንን በየሌሊቱ ማድረግ የከበደው 23(ዛሬ) :25:27 እና 29 ላይ ያድርግ እና ቁጥሮቹን መጨመርም መቀነስም ይቻላል።
ኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-
“ለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን እንኳ እሷን ለማግኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር። በ(ረመዳን) አስር ሌሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? (እንዴት እንዘናጋለን?!)” [በዳኢዑል ፈዋኢድ፡ 1/55]
⚜️ ማሳሰቢያ ለእህቶቻችን::::
ለይለተል ቀድር ለሰጋጆች ብቻ አይደለችም!
የወር አበባ ላይ ወይም የወሊድ ደም ላይ ያሉ ሴቶች፣ መንገደኞች፣ … የዚች ሌሊት ትሩፋት አያልፋቸውም። ማስረጃው ጠቅላይ ነውና። ባይሆን ከሶላት ውጭ ባሉ ዒባዳዎች ላይ ልትበራቱ ይገባል። በዚያች ሌሊት ዱዓእ ማብዛት ጥሩ ነው። እንዲያውም ሱፍያኑ ሠውሪይ ረሒመሁላህ “በሌሊቷ ከሶላት ይልቅ ዱዓእ እኔ ዘንድ የተወደደ ነው” ይላሉ።
አላህ ለይለተል ቀድርን ይግጠማችሁ
والله اعلم
السلام عليكم ورحمت الله وبركاته
ጊዜው የረመዳን የመጨረሻ አስርቱ (አሽረልአዋሂር) ቀናት ላይ እንገኛለን::
ለይለተል ቀድር የሚከጀልባቸው ውብ ለሊቶች ( ለይለተል ቀድር :-ትልቅ ደረጃ ያላት ሌሊት ፍጡራንን የሚመለከቱ የአመቱ ውሳኔዎች የሚተላለፍባት የመወሰኛዋ ሌሊት ፣ የሰራነው ኢባዳ ከ1000 ወራት በላይ ማለትም ከ83 አመት ኢባዳ በላይ ተደርጎ የሚፃፍባት ለሊት) ግን እነዚ ለሊቶችን እንዴት መጠቀም አለብን።
👉እንደሚታወቀው ዛሬ 23'ተኛው ሌሊት ከፊታችን እየጠበቀን ነው::
🌐 ስለዚህ ጊዜ አጠቃቀማችንን ማስተካከል አለብን። እንዴት???
❇️ ለይለተል ቀድር በአስሩ ሌሊቶች በአንዱ ሌሊት መኋኑ ስለማይቀር እንዲህ አድርጉ
በመጀመሪያ ሁሉንም ተግባሮቻችንን ለአላህ ብቻ ብለን (በኢህላስ) መስራት አንዘንጋ ሪያ ልፋታችንን መና ታስቀራለች ና በንጹህ፣ ቅን ልቦና ኢባዳችንን እናከናውን።
"ጌታዬ ሆይ! ይህቺ ስራ/ኢባዳ ካንተ ዘንድ ተቀባይነት ታገኝ ዘንዳ ኢህላስን ወፍቀኝ ብለን አላህን እንማፀን"
1. በየሌሊቱ ቢያንስ 10 ብር ሰደቃ መስጠት
2. በየሌሊቱ ቢያንስ 1 ጁዝ መቅራት (ጥቂት አንቀጾችን ቢሆንም መቅራትና ትርጉማቸውን ማስተንተን )
3. በየሌሊቱ ቢያንስ 100 ጊዜ ዚክር (አላህን ማውሳት)
💠ሱብሀነላህ፣ አልሀምዱ ሊላህ፣ላኢላሀ ኢለ ላህ ፣ አላሁ አክበር ፣
💠ላሀውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ፣
ነቢያችን ﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድ ፣ኢስቲግፋር
💠ላኢላኢለላሁወህደሁ ላሸሪከለሁ ለሁልሙልኩወለሁል ሀምዱ ወሁወ አላኩሊሸይኢን ቀዲር
💠ሱብሀነላሂ ወቢሀምዲሂ ሱብሀነላሂል አዚም
💠10 ጊዜ ሱረቱል ኢኽላስ መቅራት (ሱረቱል ኢኽላስን በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ሦስት ጊዜ መቅራት ሙሉ ቁርኣንን የመቅራት (ኸትም) ያህል ምንዳ ያስገኛልና)
4.ዱዓ ማብዛት
ነቢያችን ﷺ ለእናታችን ዓኢሻ (ረ.ዐ) የነገሯት ዱዓ እና ሌሎችንም ሀጃዎቻችን መጠየቅ አላህ የባሮቹን ጥሪ ሰሚ ነውና የምንፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ ዘርዝረን እንጠይቀው። ለራሳችን፣ ለቤተሰባችንና ለወገኖቻችን ከልብ የመነጨ ዱዓ እናድርግ።
ነቢያችን ﷺ ለእናታችን ዓኢሻ (ረ.ዐ) የነገሯት ዱዓ
"اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عني"
5. የተወሰኑ ረከዐዎችን መስገድ
(ለሊት ሁሉም ሰው በተኛበት ሰዓት ተነስተን ጌታችን ፊት ቆመን የውስጣችንን እንንገረው)
6. ፆመኛ ማስፈጠር
እና ሌሎችንም የኸይር ስራዎች መስራት።
⚜️ ማሳሰቢያ :- ይህንን በየሌሊቱ ማድረግ የከበደው 23(ዛሬ) :25:27 እና 29 ላይ ያድርግ እና ቁጥሮቹን መጨመርም መቀነስም ይቻላል።
ኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-
“ለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን እንኳ እሷን ለማግኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር። በ(ረመዳን) አስር ሌሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? (እንዴት እንዘናጋለን?!)” [በዳኢዑል ፈዋኢድ፡ 1/55]
⚜️ ማሳሰቢያ ለእህቶቻችን::::
ለይለተል ቀድር ለሰጋጆች ብቻ አይደለችም!
የወር አበባ ላይ ወይም የወሊድ ደም ላይ ያሉ ሴቶች፣ መንገደኞች፣ … የዚች ሌሊት ትሩፋት አያልፋቸውም። ማስረጃው ጠቅላይ ነውና። ባይሆን ከሶላት ውጭ ባሉ ዒባዳዎች ላይ ልትበራቱ ይገባል። በዚያች ሌሊት ዱዓእ ማብዛት ጥሩ ነው። እንዲያውም ሱፍያኑ ሠውሪይ ረሒመሁላህ “በሌሊቷ ከሶላት ይልቅ ዱዓእ እኔ ዘንድ የተወደደ ነው” ይላሉ።
አላህ ለይለተል ቀድርን ይግጠማችሁ
والله اعلم
Repost from AAU - Muslim Students Union
ክፍል 5
ጀማዓው ምን ሰራ?
ጀማዓው በነበረው እንቅስቃሴ በመጀመሪያ ደረጃ እየተነሱ ያሉትን መብቶች አግባብነት ለመገምገም ሞክሯል:: በዚህም መሠረት ከዩኒቨርሲቲው እየቀረቡ ያሉ መመሪያዎችን እና ክልከላዎች ወጥነት የሌላቸው: በጊዜ እና ቦታ የሚለያዩ ሆነው አግኝቷል:: መስከረም ላይ ያልተከለከለን ነገር ጥር ላይ እንደሚከለከል አድርገው ያመጡታል:: ሚያዝያ ላይ ያልተከለከለን ነገር ሰኔ ላይ እንደተከለከለ ያደርጉታል:: ከዚህም አልፎ ዛሬ በአንዱ ካምፓስ ሰላም ሆኖ በሌላ ካምፓስ ተማሪ ይገላታል:: በር ላይ ሰላም ሆኖ ሲባል ካፌ ላይ ችግር ይፈጠራል:: ትላንት ሴኩላሪዝም ብለው ሳለ ዛሬ ደግሞ ደህንነት ከዚያም ነገ ስሜትን ለማንበብ ይላሉ::
ከዚህ እንደምንረዳው ዋነኛው ዓላማቸው ተማሪዎቹን መቼ የት እንዴት እንከልክላቸው እንጂ ሌላ አይደለም:: ይህ ደግሞ አግባብነት የሌለው: የሙስሊም ተማሪዎች ሃይማኖታዊ መብት የሚጥስ: በሕገ-መንግስቱ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን የሚፃረር አካሄድ ነው:: ዛሬ ላይ ዝም ተብሎ ቢታለፍ በእህቶች ላይ የሚደርሰው በደል በማህበረሰባችን ላይ ከሚያደርሰው አሉታዊ ተፅዕኖ ባሻገር ለነገው ትውልድ እዳን ማውረስ በመሆኑ ይህ አጀንዳ በዚህ ትውልድ ይዘጋ ዘንድ ጀማዓው እየተንቀሳቀሰ ይገኛል:: ለዚህም ከግቢው አመራሮች ጀምሮ መጅሊሱን ጨምሮ የሚመለከታቸውን አካላት ሁሉ ለማነጋገር: ተማሪውም ተናቦ እና ተቀናጅቶ መብቱን ይጠይቅ እና ያስከብር ዘንድ እየሰራ ነው:: በአላህ ፈቃድም እነዚህ ችግሮች ተፈትተው መፍትሔ እስከመጣ ድረስ የሚሰራ ይሆናል::
ዛሬስ ምን ይሰራ?
በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ባሻገር ስለ ሰብዓዊ መብት ግድ የሚሰጠውን አካል ሁሉ የሚመለከት ስለሆነ ሁሉም አካል የተቻለውን የማድረግ ሰብዓዊ ሀላፊነት አለበት:: ከእያንዳንዱ አካላት የሚጠበቁትን ነገሮች እንደሚከተለው እናቀርባለን፦
◊ መንግስት፦ ከሃይማኖታዊ መብቶች ጋር በተያያዘ የሚደረጉ መብቶችን ለመከላከል እና እየተፈጠሩ ያሉ ክፍተቶችን ለመድፈን ያስችል ዘንድ ለሁሉም መነሻ የሚሆን አዋጅ ሊያወጣ ይገባል:: አለዚያ ተቋማት እንዳሻቸው ሰብዓዊ መብቶችን የሚገድቡ ድንጋጌዎችን የሚያወጡ ከሆነ የዜጎች መብቶችን እንዲጣሱ በር ከመክፈቱም ባሻገር የሕግ ስርዓቱም ውስጥ መታወክን ይፈጥራል:: ስለሆነም ያለስልጣናቸው የዜጎችን መብት የሚገድብ መመሪያ የሚያወጡ ተቋማትን ተጠያቂ ከማድረግ ጎን ለጎን መፍትሔውን የሚያስቀምጡ አዋጆችን በማውጣት ለዜጎች ጥያቄ መልስ መስጠት አለበት::
@aaumsu
🌙 RAMADAN SPECIAL EVENT 🌙
✨3rd Grand Ramadan Iftar Program ✨
With great joy, we invite you to a special and memorable Ramadan gathering that brings together Dawah and Iftar, encouraging everyone to benefit from the Dawah program before sharing the blessings of Iftar together. Join us for a meaningful evening of reflection, unity, and brotherhood
📌 Program Highlights
🍁 Special Dawah Program
🍁 Welcoming Session
🍁 Jema Introduction
🍁 Jema Progress & Future Plans
🍁 Brotherhood & Sisterhood Gathering
🍁 Inspiring Talks from Senior Graduated Jema Members sharing their experience
✨ Special Guests:
We are honored to welcome Senior Graduated Shura Members who will join us and share their valuable experiences and advice with us.
It will be a beautiful opportunity to strengthen our brotherhood and sisterhood, reflect together, and build a stronger future for our Jema.
📅 Wednesday – Ramadan 22
🕰 Time: 11:00 LT
📍 Venue: Ambassador
🤝 Come and strengthen the bonds of Iman, unity, and brotherhood and sisterhood.
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግቢው ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች ሰብአዊ መብቶቻቸው ተከብረው፣ በዲናቸውና በዱንያቸው ስኬታማ እንዲሁም ለሀገራቸው ጠቃሚ ዜጎች እንዲሆኑ በቁርጠኝነት ሲሰራ ቆይቷል።
በተለይም ከ2017 ዓ.ል ጀምሮ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መመሪያ ምክንያት ኒቃብ ለባሽ እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን የአድልዎና የጭቆና ተፅዕኖ ለመፍታት ህብረቱ ላለፉት 18 ወራት ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም ሂደት ከግቢው የተማሪዎች ህብረት ጀምሮ እስከ ፌደራል መጅሊስ ድረስ ካሉ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይቶች ተካሂደዋል። ጉዳዩ የሁላችንም መሆኑን ለማሳየት ከ1,100 በላይ ተማሪዎች የፈረሙበት የቅሬታ ሰነድ ለሚመለከታቸው ወገኖች ቀርቧል።
ይህንኑ እንቅስቃሴ አሁን ያለበትን ደረጃ ለማሳወቅና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለመምከር ለነገ ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ል በአል-አቅሷ መስጂድ አጠቃላይ የተማሪዎች ውይይት መጥራታችን ይታወሳል። ህብረቱ ለፕሮግራሙ ስኬት አስፈላጊውን አስተዳደራዊ ቅድመ ሁኔታዎች ሲያሟላ ቆይቷል።
ሆኖም ፕሮግራሙ ይፋ ከተደረገበት ሰዓት ጀምሮ፣ እንቅስቃሴውን ለማደናቀፍና የህብረቱን አመራሮች ጨምሮ በተማሪው ላይ የተለያዩ ማስፈራሪያዎችን የማድረስ ሙከራዎች ተስተውለዋል። ሰላማዊ የመብት ጥያቄውንም ወደማይፈለግ አጀንዳ ለመቀየር ጥረቶች ተደርገዋል። በመሆኑም ህብረቱ በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ከመከረ በኋላ፤ በዝግጅቱ ምክንያት በተማሪው፣ በህብረቱና በአል-አቅሷ መስጂድ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ተጽዕኖና ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት የነገው ስብሰባ ለጊዜው እንዲሰረዝ ወስኗል።
ይሁን እንጂ፤ ህብረታችን የመብት ጥያቄውን በምንም መልኩ እንደማያቆም እና ተማሪውን የማስተባበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በግልጽ ለእነዚሁ አካላት በግልጽ አሳውቋል። የእምነት ነፃነትን ለማፈን ከመሞከር ይልቅ ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎችን በደል ሰምቶ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ግፊት እንዲያደርጉ ጥሪያችንን አቅርበናል። የዚህንም ውጤት በቅርቡ የምናየው ይሆናል ኢንሻላህ።
በቀጣይ መካሄድ ስላለባቸው እንቅስቃሴዎች ከሁሉም ካምፓስ ተወካዮች ጋር እየተወያየን ሲሆን፣ በቅርቡ አዲስ የትግል አቅጣጫ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።
ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግቢው ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች ሰብአዊ መብቶቻቸው ተከብረው፣ በዲናቸውና በዱንያቸው ስኬታማ እንዲሁም ለሀገራቸው ጠቃሚ ዜጎች እንዲሆኑ በቁርጠኝነት ሲሰራ ቆይቷል።
በተለይም ከ2017 ዓ.ል ጀምሮ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መመሪያ ምክንያት ኒቃብ ለባሽ እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን የአድልዎና የጭቆና ተፅዕኖ ለመፍታት ህብረቱ ላለፉት 18 ወራት ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም ሂደት ከግቢው የተማሪዎች ህብረት ጀምሮ እስከ ፌደራል መጅሊስ ድረስ ካሉ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይቶች ተካሂደዋል። ጉዳዩ የሁላችንም መሆኑን ለማሳየት ከ1,100 በላይ ተማሪዎች የፈረሙበት የቅሬታ ሰነድ ለሚመለከታቸው ወገኖች ቀርቧል።
ይህንኑ እንቅስቃሴ አሁን ያለበትን ደረጃ ለማሳወቅና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለመምከር ለነገ ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ል በአል-አቅሷ መስጂድ አጠቃላይ የተማሪዎች ውይይት መጥራታችን ይታወሳል። ህብረቱ ለፕሮግራሙ ስኬት አስፈላጊውን አስተዳደራዊ ቅድመ ሁኔታዎች ሲያሟላ ቆይቷል።
ሆኖም ፕሮግራሙ ይፋ ከተደረገበት ሰዓት ጀምሮ፣ እንቅስቃሴውን ለማደናቀፍና የህብረቱን አመራሮች ጨምሮ በተማሪው ላይ የተለያዩ ማስፈራሪያዎችን የማድረስ ሙከራዎች ተስተውለዋል። ሰላማዊ የመብት ጥያቄውንም ወደማይፈለግ አጀንዳ ለመቀየር ጥረቶች ተደርገዋል። በመሆኑም ህብረቱ በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ከመከረ በኋላ፤ በዝግጅቱ ምክንያት በተማሪው፣ በህብረቱና በአል-አቅሷ መስጂድ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ተጽዕኖና ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት የነገው ስብሰባ ለጊዜው እንዲሰረዝ ወስኗል።
ይሁን እንጂ፤ ህብረታችን የመብት ጥያቄውን በምንም መልኩ እንደማያቆም እና ተማሪውን የማስተባበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በግልጽ ለእነዚሁ አካላት በግልጽ አሳውቋል። የእምነት ነፃነትን ለማፈን ከመሞከር ይልቅ ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎችን በደል ሰምቶ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ግፊት እንዲያደርጉ ጥሪያችንን አቅርበናል። የዚህንም ውጤት በቅርቡ የምናየው ይሆናል ኢንሻላህ።
በቀጣይ መካሄድ ስላለባቸው እንቅስቃሴዎች ከሁሉም ካምፓስ ተወካዮች ጋር እየተወያየን ሲሆን፣ በቅርቡ አዲስ የትግል አቅጣጫ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።
ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
❗️አስቸኳይ❗️❗️
ለነገ ተይዞ የነበረው ውይይታችን ለጊዜው የተሰረዘ ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ምን እንደሚሆኑ ኢንሻላህ በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል።
ጥያቄ አለን!! መልስም እንፈልጋለን!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ክፍል 3
ግቢው ምን አለ?
መመሪያው በወጣ ሰሞን የተማሪዎቹን መብት የሚጥስ ድንጋጌ የወጣበትን ምክንያት በግልፅ ባያስቀምጥም፣ የሙስሊም ተማሪዎች አመራሮች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በነበራቸው ውይይት ለመረዳት እንደቻሉት ከግቢው በኩል ያለው መነሻ እንደሚከተለው ነው።
◊ ዩኒቨርሲቲው ሴኩላር ስለሆነ ኒቃብ መልበስ አይቻልም፦ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች በኩል በመጀመሪያ ደረጃ እንደ መከራከሪያ ነጥብ የተነሳው "ዩኒቨርሲቲው ሴኩላር ነው" የሚል ነበር። ሆኖም በኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት ውስጥ የተቀመጠው ሴኩላሪዝም ዜጎችን ሃይማኖት እና እምነት አልባ የሚያደርግ አይደለም። ሴኩላሪዝሙም ተማሪዎች ሃይማኖታቸውን ከበር አውልቀው እንዲገቡ የሚያስገድድ አልነበረም። ምክንያቱም ሕገ-መንግስቱ በአንቀፅ 27 ላይ በግልፅ ለዜጎች የሃይማኖት ነፃነት እውቅና የሰጠ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሌሎች የትምህርት ተቋማት እና የመንግስት ተቋማት በግልፅ እየታየ ያለ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እራሱ ከ2017 ዓ.ል በፊት የታየ እና የተተገበረ ነበር።ይህንን መሠረት ባደረገ መልኩ ውይይት ከተደረገ ቡሃላ ግን ሴኩላሪዝም እንደ መከራከሪያ ነጥብ ሆኖ አልቀረበም።
◊ ኒቃብ የደህንነት ስጋት ነው፦ እንደ መጀመሪያ መከራከሪያ ሆኖ የቀረበው ሴኩላሪዝም በኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት መሠረት መብትን መከልከል ሳይሆን ማስከበር እና መጠበቅ እንደሆነ ግልፅ እየሆነ ሲመጣ ጊዜ የመከልከያ ነጥባቸውን "ኒቃብ የደህንነት ስጋት ስለሆነ መልበስ አይቻልም!" ወደሚል ተሻገሩ። ለሕዝበ ሙስሊሙ መገለጫ የሆነን አለባበስ የደህንነት ስጋት ብሎ መፈረጅ የኢስላሞፎቢያ (ሙስሊም ጠልነት) መገለጫ ፡ አንድን ሕዝብ መሳደብ እና ለማጥቃት መሞከር ነው:: ኒቃብ ስለተለበሰ ብቻ የሚመጣ የደህንነት ስጋት የለም። ኒቃብ ስለተለበሰ ብቻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ላይ ተለይቶ የሚመጣ የደህንነት ስጋት የለም። ኒቃብ መለበስ የተጀመረውም
@aaumsu
🗣🗣 የኸይር ተካፋይ ይሁኑ!!!!
💚 በተቻለን አክል የተቸገሩትን እንርዳ!!!!
📖 " إِنَّ الْمُصَّدِّقِينَ وَالْمُصَّدِّقَاتِ وَأَقْرَضُوا اللَّهَ قَرْضًا حَسَنًا يُضَاعَفُ لَهُمْ وَلَهُمْ أَجْرٌ كَرِيمٌ"
📖 የመጸወቱ ወንዶችና፣ የመጸወቱ ሴቶች፣ ለአላህም መልካምን ብድር ያበደሩ ለእነርሱ መልካም ምንዳ አልላቸው፡፡
🌙 " ረመዳን የበረከት የደስታ የመሽቀዳደሚያ ወር ነው። ስራዎች በእጥፍ ድርበ የሚመነዱበት ወር ነው። አማኞች በረመዳን በመልካም ስራ ሊሽቀዳደሙ ይገባል። በተቻላቸው አቅም ወደ መልካም ሊበርቡ ይገባል። ጉልበታችን ሃብታችን እና ሃሳባችን በመልካም ስራ ልናውለው ይገባናል።በተለይ በዚህ ልዩ ወር።
🌙 ጀመዓችን 4ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ይህን ከግምት በማስገባት በማሕበራዊ ዘርፍ በኩል ለናንተ አንድን ስራ አዘጋጅቷል።
👍ጀመዓችን በአካባቢያችን ያሉ ብዙ ሰዎች ማያቁላቸው የተቸገሩ ቤተሰቦችን በተቻለን ያክል ትንሽም ቢሆን በዚህ በተከበረው ወር ለመርዳትና እንዲሁም ኢድን ሳይቸገሩ በደስታ እንዲያሳልፉ ከጎናቸው ለመሆን እቅድ ይዟል።ስለዚህ ሁላቹም በዚህ ኸይር ስራ እንድትሳተፍ ጥሪ ያቀርብላችኋል።
""የተቸገረ ሰውን ችግሩን ያቀለለ አላህ በቂያማ ችግሩን ያቀልለታል"" ረሱል ሰ.ዐ.ወ
""በቴምር ቁራጭ ቢሆን እንኳን ከእሳት ተጠበቁ"" ረሱል ሰ.ዐ.ወ
➡️ ድጋፉን በአካል ለመስጠት በወንዶች በኩል ለ
👉 Mesud Ali
👉 aymen Muhammed
በሴቶች በኩል ደግሞ ለአሚሮቻችሁ መስጠት ትችላላችሁ።
🌟በ Mobile Banking መላክ ለምትፈልጉ ከታች ባለው account አስገቡ።
ያስገባችሁበትን screen shoot በማድረግ በዚህ @fourkilojemeaBot ላኩልን።
CBE 1000729100173 (Abdulmalik Muhdin and/or Mesud Ali)
👍በመልካም ስራ በተከበረው ወር እንሽቀዳደም
🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌
https://t.me/aau4kilomsj
