5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 156
Subscribers
-224 hours
-57 days
No data30 days
Posts Archive
🗣🗣 የኸይር ተካፋይ ይሁኑ!!!!
💚 በተቻለን አክል የተቸገሩትን እንርዳ!!!!
📖 " إِنَّ الْمُصَّدِّقِينَ وَالْمُصَّدِّقَاتِ وَأَقْرَضُوا اللَّهَ قَرْضًا حَسَنًا يُضَاعَفُ لَهُمْ وَلَهُمْ أَجْرٌ كَرِيمٌ"
📖 የመጸወቱ ወንዶችና፣ የመጸወቱ ሴቶች፣ ለአላህም መልካምን ብድር ያበደሩ ለእነርሱ መልካም ምንዳ አልላቸው፡፡
🌙 " ረመዳን የበረከት የደስታ የመሽቀዳደሚያ ወር ነው። ስራዎች በእጥፍ ድርበ የሚመነዱበት ወር ነው። አማኞች በረመዳን በመልካም ስራ ሊሽቀዳደሙ ይገባል። በተቻላቸው አቅም ወደ መልካም ሊበርቡ ይገባል። ጉልበታችን ሃብታችን እና ሃሳባችን በመልካም ስራ ልናውለው ይገባናል።በተለይ በዚህ ልዩ ወር።
🌙 ጀመዓችን 4ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ይህን ከግምት በማስገባት በማሕበራዊ ዘርፍ በኩል ለናንተ አንድን ስራ አዘጋጅቷል።
👍ጀመዓችን በአካባቢያችን ያሉ ብዙ ሰዎች ማያቁላቸው የተቸገሩ ቤተሰቦችን በተቻለን ያክል ትንሽም ቢሆን በዚህ በተከበረው ወር ለመርዳትና እንዲሁም ኢድን ሳይቸገሩ በደስታ እንዲያሳልፉ ከጎናቸው ለመሆን እቅድ ይዟል።ስለዚህ ሁላቹም በዚህ ኸይር ስራ እንድትሳተፍ ጥሪ ያቀርብላችኋል።
""የተቸገረ ሰውን ችግሩን ያቀለለ አላህ በቂያማ ችግሩን ያቀልለታል"" ረሱል ሰ.ዐ.ወ
""በቴምር ቁራጭ ቢሆን እንኳን ከእሳት ተጠበቁ"" ረሱል ሰ.ዐ.ወ
➡️ ድጋፉን በአካል ለመስጠት በወንዶች በኩል ለ
👉 Mesud Ali
👉 aymen Muhammed
በሴቶች በኩል ደግሞ ለአሚሮቻችሁ መስጠት ትችላላችሁ።
🌟በ Mobile Banking መላክ ለምትፈልጉ ከታች ባለው account አስገቡ።
ያስገባችሁበትን screen shoot በማድረግ በዚህ @fourkilojemeaBot ላኩልን።
CBE 1000729100173 (Abdulmalik Muhdin and/or Mesud Ali)
👍በመልካም ስራ በተከበረው ወር እንሽቀዳደም
🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌
https://t.me/aau4kilomsj
Repost from AAU - Muslim Students Union
ክፍል 2
◊ ጥያቄዎቻችን ምንድን ናቸው?
ሕዝበ ሙስሊሙ በዘመናት ውስጥ ስለመብቱ እየጠየቀ እየታገለ የማለፋን ያህል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪም ስለመብቱ እየጠየቀ እየታገለ ለዘመናት አልፏል። ሰላት አትሰግዱም ተብሎ ተከልክሎ ከመስገድ ባሻገር የመስገጃ ቦታ ማግኘትም መብት ነው በማለት ታግሎ በካምፓሱ መስጂድ የተቀበለበት ወቅት ነበር። ይህ ከ1995 - 2005 የነበረ እውነት ነው። ሒጃብን መልበስ አትችሉም በረመዳን ለተሐጁድ መውጣት አትችሉም ተብሎ ሒጃብ / ኒቃብ መልበስ መብቴ ነው መስገድም መብቴ ነው ብሎ ታግሎ መብቱን ያስከበረበት ወቅት ነበር። ሌሎች የሙስሊም ተማሪዎች መብቶችንም በሰላማዊ መንገድ እየጠየቀ እያስከበረ እያስተካከለ ለውጥ እያመጣ አልፏል::
ሆኖም ግን በሰላማዊ መንገድ ጠይቆ እና ታግሎ ያስከበራቸውን ሰብዓዊ መብቶች የሚፈታተን ነገር ከአመታት በኋላ በ2017 ዓ.ል ተፈጠረ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዝዳንትነት እየተመራ አዲስ የስነ- ስርዓት መመሪያ በ2017 ዓ.ል ጥቅምት ወር ውስጥ አወጣ። በመመሪያው ውስጥም ከ2 አስርት አመታት በላይ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ተከብረው የነበሩ የሙስሊም ተማሪዎች መብቶችን የሚፈታተን ድንጋጌ መጣ:: መመሪያው በአንቀፅ 6.6 ላይ "በዩኒቨርሲቲው ከሚከናወኑ የመማር ማስተማር ተግባራትና ከሚሰጡ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ማንነትን ለመለየት ሲባል በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ፊትን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍኑ አለባበሶችን መልበስ የተከለከለ ነው።" በማለት የሕዝበ ሙስሊሙ እሴት እና የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሕይወት ክፍል የሆነውን ሒጃብ / ኒቃብ የሚከለክል መመሪያ አወጣ::
መመሪያዎች ሲወጡ መመሪያው በልዩነት የሚመለከታቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች በረቂቁ ላይ አስተያየታቸውን መስጠት እንዳለባቸው የተደነገገ ቢሆንም ይህ መመሪያ ሲወጣ ግን የተማሪው አስተያየት፣ መሰረታዊ መብት ብሎም ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ነገር ከግምት ውስጥ አልገባም:: ተማሪዎችም አገር አማን ብለው በተለመደው መልኩ ለመማር ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲያመሩ "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም!" - ተብለው ተከለከሉ። ከዚህም በተጨማሪ ካፌ ውስጥ "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ ምግብ መብላት አትችሉም!" - ተብለው ለ15 ቀናት ያህል በምግብ ተቀጡ:: በመማሪያ ክፍሎች ውስጥም ከአንዳንድ መምህራን "ይህንን ለብሳችሁ እንዴት ገባችሁ? አይቻልምኮ! አስቡበት!!" - የሚሉ ቃላቶች ይሰነዘሩባቸው ጀመር::
ይህ የሆነው በ2017 ዓ.ል በጥቅምት ወር ላይ ሲሆን ሙስሊሙ ተማሪ "ጥያቄ አለን!" - በማለት በመነሳቱ በውይይት እስኪፈታ ድረስ ተብሎ በጊዜያዊነት ክልከላው እንዲቆም ተደርጎ ሳለ የ2017 ዓ.ል ተጠናቆ 2018 ዓ.ል ገባ:: ሆኖም የተጀመረው ውይይት ከግብ ሳይደርስ በአዲሱ ዓመት አዲስ ፈተና ለሙስሊሙ ተማሪዎች ተጋረጠ:: በFBEE: Commerce: Main Campus እና ያሬድ በተለያዩ ጊዜያት በተለያየ ቦታ ሙስሊም ኒቃቢስት ተማሪዎች "አትገቡም" ተብለው ተንገላቱ::
ለዚህ ሁሉ መነሻው በ2017 ዓ.ል የወጣው መመሪያ ስለሆነ፣ የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ መመሪያው ተሻሽሎ ለመሰረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እውቅና እና ከለላ የሚሰጥ መመሪያ ይውጣ የሚል ነው። አሁንም ድረስ ሙስሊሙ ተማሪ "ጥያቄ አለን!" የሚለውን መፈክሩን እንደያዘ ነው። መልስን ይፈልጋል! መልስ እስኪመጣ ድረስ!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
መፍትሔ ያልተሰጠው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ
ከየት እስከ የት ? ዘላቂ መፍትሔውስ?
ክፍል 1
◊ መብቶቻችን ምንድን ናቸው?
የሰው ልጅ የመፈጠሩ ዓላማ ፈጣሪውን አላህን (ሱ.ወ) ሊገዛና ሊያመልክ እንደሆነ የእስልምና አስተምህሮ ያስረዳል :: ይህ አምልኮ ደግሞ እንደ ሰላት፣ ጾምና ዘካ ባሉ ማዕዘናት ብቻ ሳይወሰን፤ ማንነትና ታዛዥነትን በሚገልጹ እንደ ሒጃብ ባሉ ሃይማኖታዊ አልባሳትም ይገለጻል :: እነዚህን ትዕዛዛት በመፈፀም ውስጥ የሚገኘው መንፈሳዊ ነፃነት ሙስሊሞች በምድር ላይ ላላቸው ሕይወት መሰረታዊ ግዴታቸው ነው ::
ይህ ሃይማኖታዊ ግዴታ በሀገራችን በኩል ደግሞ በሕገ-መንግስት የተረጋገጠ መብት ነው :: ሀገር ማለት የዜጎቿ የእምነት፣ የባህል፣ የታሪክና የእሴት ድምር ውጤት በመሆኗ፤ ሙስሊሞችም ለሀገራቸው ከሚከፍሉት መስዋዕትነት ጎን ለጎን በእኩልነትና በፍትሐዊነት የመኖር መብት አላቸው::
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ባለፉት የታሪክ ሂደቶች ውስጥ መብትና ነፃነታቸውን ለማስከበር ሲታገሉ ቆይተዋል :: የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችም የዚህ ታላቅ ታሪክና የመብት ትግል ዋነኛ አካል ናቸው::
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከቤተሰብ ተነጥለን ከዩኒቨርሲቲው አገልግሎት ለማግኘት በምንመጣበት ወቅት የመጣንበትን አካባቢ ታሳቢ በማድረግ፣ ብዝሃነትን ከግምት በማስገባት፣ ሃይማኖቶች ተከባብረው ተከታዮቻቸውም መብታቸው ተጠብቆ ለሀገር እድገት የሚታተሩ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚሠሩ ልጆችን መብት በጠበቀ እና ባከበረ መልኩ እንዲሆን ጠብቀን ነው:: አንድ ተማሪ ለ18 ዓመታት ያህል ያደገበትን ሃይማኖት ከዩኒቨርሲቲው ደጃፍ አውልቀህ ግባ የሚባልበት አግባብ ሊኖር አይገባም:: አንዲት ሙስሊም ተማሪ ከልጅነት እስከ እውቀት ስትለብሰው የነበረውን ሃይማኖታዊ አልባሳት (ሒጃብ / ኒቃብ) ከዩኒቨርሲቲ ደጃፍ ስትደርስ አውልቂ የምትባልበት አግባብ የለም:: እንደ ሙስሊም ተማሪ ለዘመናት ሲሰግድ እና ሲጾም ኖሮ ከዩኒቨርሲቲ ሲገባ ስላያዘው አቋም የእምነትህንም ተው የሚባልበት አግባብ የለም:: ከሃይማኖቱ ጋር ተያይዘው ያሉ ማንነቶቹ ማለትም እንደ ሰላት መስገድ፣ ጾም መጾም፣ ሒጃብ / ኒቃብ መልበስ ወዘተ ... እንደ እስልምናው ግዴታ የሆኑ ጉዳዮች ሲሆኑ እንደ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ደግሞ ሊያገኛቸው የሚገቡ ሊከበሩለት የሚገቡ መብቶቹ ናቸው::
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
❝የትምህርት ስርዓቱን እንጂ ተማሪውን Secular ማድረግ አይቻልም!❞
መጋቢት #1 ከአሚሮቻችን ጋር ውይይት አለን
#አይቀርም #ጥያቄ #አለን
•~• የትምህርት ተቋማት Secular መሆን ቢችሉም፣ ተማሪዎች ግን የራሳቸው ሃይማኖታዊና ሥነ-ልቦናዊ ማንነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። ሆኖም ኒቃብን ጨምሮ ሌሎች የእምነት መገለጫዎች የተማሪው ሰብዓዊ መብቶች እንጂ የትምህርት እንቅፋቶች ሆነው አያውቁም! ለዚህ ደግሞ ታሪክ ምስክራችን ነው!። ተማሪውን ከማንነቱ ነጥሎ "ዓለማዊ" ለማድረግ መሞከር የእውቀት ሳይሆን የጥላቻን መንገድ መከተል ነው! ማንነትን መግፈፍ ነው! አግላይነት ነው!።
•~• የፊታችን ማክሰኞ መጋቢት 1/2018 (ረመዿን 21) ከዙሁር ሶላት በኋላ በአቅሷ መስጂድ አይቀርም!!
ሁላችንም ለዚህ አንገብጋቢ ሀጃ ቅድሚያ ሰጥተን፤ ለአሚሮቻችን ጥሪ 'አቤት' ብለን በሰዓቱ እንገኝ!
#ጥያቄ #አለን
6ኪሎ ጀመዓ ዳዕዋና ቂርዓት ሴክተር
@aaumsu
ይህ የሙዕተሲም ቢላህ ታሪክ ለእኛ ለዛሬዎቹ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሚሰጠው ትልቅ ትምህርት አለ። እሱም የእምነት ማንነትና የግል ድክመት የተለያዩ መሆናቸውን ነው። ሙዕተሲም በግል ሕይወቱ ስህተቶች የነበሩበት፣ እንዲያውም ታላቁን ኢማሙ አህመድን ያስገረፈ መሪ ቢሆንም፣ የአንዲት ሙስሊም ሴት ክብር ሲነካ ግን ሁሉንም የግል ጉዳዮች እና ድክመቶች ወደ ጎን አድርጎ ለዲኑ ክብር ዘምቷል።
ዛሬም በግቢያችን ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የተለያዩ የመብት ጥሰቶች ሲከሰቱ፣ "እኔ ኃጢአተኛ ነኝ" ወይም "እኔ ዲኔ ላይ ጠንካራ አይደለሁም" በማለት ወደ ኋላ ማለት አይገባም። እምነትንና የእህቶችን ክብር መጠበቅ የግል ማንነት ምንም ይሁን ምን በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ የወደቀ የጋራ ኃላፊነት ነው። ወንዶችም ሆኑ ሴቶች፣ ልክ እንደ ሙዕተሲም አንዲት እህት ስትበደል እንደ ራሳችን ህመም ሊሰማን ይገባል።
ኢማሙ አህመድ እንኳን ያንን ሁሉ ስቃይ አድርሶባቸው ፤ ለዲኑ ባሳየው ቆራጥነት ሙዕተሲምን ይቅር እንዳሉት ሁሉ፣ እኛም ዛሬ ለኒቃብ መከበር የምናደርገው ትግል የዲናችንን ክብር ለማስጠበቅ ምን ያክል ርቀት መጓዝ እንችላለን የሚለውን የሚያሳየን ይሆናል።
©AAU6kilojemea
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
🔥🔥ከሙተነቂቦች መንደር••
የመጀመሪያ አመት ተማሪ እያለሁኝ ነው:: Inclusive የሚባል ኮርስ እየወሰደን ነበር :: የቡድን አሳይንመንት ተሰጥቶን እሱን ልናቀርብ ነበር...ከዛ ያው ሁሉም ቡድን የሚወክለውን እየመረጠ መቀረብ ተጀመሮዋል...ሔዶ ሔዶ የኛ ቡድን ደረሰ:: እኔ እንዳቀርብ ተስማምተን ስለነበር ሰከም ሰከም እያልኩ ወደ ፊት ወጣሁ:: ልክ ለማቅረብ ስሜን ሳስተዋውቅ...
"ቆይ!ቆይ!ቆይ! እንደዚህ ለብሰሽ ነው የምታቀርቢው!?" አለኝ መምህሩ...እውነት ለመናገር ስለኒቃቤ እያወራ እንደነበር ለራሱ አልገባኝም ነበር::
"ማለት?" ብዬ ተመልሼ ወደራሴ መመልከት ጀምርኩ...እሱም በማፌዝ አስተያየት እያየኝ
"አይይይ...ይህ የተሸፋፈንሽውን ነገር ነው እያልኩሽ ያለሁት!" አለኝ...አበሳጨኝ አወራሩ: አናደደኝ!::
"እእእ...አዎ! እንደዚሁ ነው የማቀርበው!" አልኩት ትንሽ ቆጣ ብዬ:: ....ለመሳቅ እያዳዳው
" እንደዚህ ለብሶ መግባት እንደማይቻል አታውቂም?!" ....አለኝ
" አይ ይቻላል! ስለሚቻልም ነው እየገባሁ ያለሁት! " አልኩት ድፍረቱን አላህ ሰጥቶኝ....ተናደደ
" ስሚኝ....ተቻለም አልተቻለም እኔ እንደዚህ አይነት ነገር አይመቸኝም!" ....አለኝ በፈጣጣው!! በዚህም አላቆመም..." አለባበስሽን አስተካክዪ!" የሚለውንም አስከተለ....ወላሂ በጣም አበሸቀኝ!
" አንተ ተመቸህ አልተመቸህ አይመለከተኝም! ይህ ነው የተስተካከለው አለባበሴ! እና ምንም የማስተካክለው ነገር የለኝም!" አልኩት አንገቴን ቀና አድርጌ!" ከዛ ዝምምም አለ:: እኔም present ማድረጌን ቀጠልኩ:: አቅርቤ ስጨርስም አሪፍ ስለነበር በጭብጨባ ሸኙኝ! መምህሩ ግን ፊቱ እንዲያው ጭምድድ እንዳለ ነበር::...
ከፋይናል ቦሀላ ውጤቴን ለማየት portal ውስጥ ስገባ ያየሁትን ማመን ነበር ያቀተኝ:: 5/15 ነበር የሰጠኝ ፕረዘንቴሽኑን!! ግራ ስለገባኝ የቡድኔን ልጆች ጠየቅኳቸው:: ለሁሉም 14/15 እንደሰጣቸው ሲነግሩኝ ሸሩ ገባኝ!! እራሴ በሰራሁት paper••• እራሴው ባቀረብኩት presentation!.....
እንደዚህ አይነት ስንትና ስንት ያልተነገሩ የሙተነቂብ እህቶች ታሪኮች ይኖሩ ይሆን??
ማክሰኞ መጋቢት 1/2018 ከዙሁር በኋላ አቅሷ መስጂድ አይቀርም!!!
እምነትን መኖር መብት እንጂ ስጦታ አይደለም!!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
❗️አስቸኳይ የውይይት ጥሪ❗️❗️
ቀጠሯችን የፊታችን ማክሰኞ መጋቢት 1/2018 ከዙሁር ሰላት በኋላ በአቅሷ መስጂድ አይቀርም!!!
በሁሉም ካምፓስ ያላችሁ የግቢያችን ሙስሊም ተማሪዎች ሆይ፤
እምነትን መኖር መብት እንጂ ስጦታ አይደለም! ላለፉት ረጅም ወራት በእህቶቻችን ማንነት እና በኒቃባቸው ላይ እየተደረገ ያለው ተገቢ ያልሆነ ክልከላና ጫና ሁላችንንም እያሳመመን ይገኛል። ህብረታችን ይህንን ግልጽ የሃይማኖት ነፃነት ጥሰት በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ ለመፍታት ያልሄደበት ርቀት፣ ያላንኳኳው በርና ያላነጋገረው አካል ባይኖርም፤ እስካሁን የተሰጠን ምላሽ ግን የትዕግስታችንን ጥንካሬ የሚፈትን ሆኖ ቀጥሏል።
አሁን ግን ትዕግስት ገደብ አጥቷል፤ ዝምታም መፍትሔ አልሆነም! ማንነታችን ተደፍሮ፣ የእህቶቻችን ክብር ተገፍፎና የእምነት መብታችን ተገድቦ የምንቀጥልበት ምንም ዓይነት ምክንያት የለም!
በመሆኑም፣ ይህንን ነባራዊ ሁኔታ ለመቀልበስና የጋራ አቋም ይዘን የመጨረሻውን እርምጃ ለመወሰን፣ መጪው ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ል ከግቢው ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ወሳኝና ታሪካዊ ውይይት ይደረጋል።
የጥቁር አንበሳ፣ የሰፈረ ሰላም፣ የ6 ኪሎ፣ የ5 ኪሎ፣ የ4ኪሎ የልደታም ሆነ የቢሾፍቱ ካምፓስ ተማሪዎች ሆይ!
የዚህ ጥሪ ባለቤት አንተ/አንቺ ነሽ፤ የእህትህ መከፋት ያንተ ቁስል ነው፣ የእምነትሽ መገፋት ያንቺም ህመም ነው። በዚህች ዕለት የሚኖረን ተሳትፎ የነገውን የክብር ጉዟችንን ይወስናል፤ ስለዚህ ማንም ተማሪ ከዚህ ታሪካዊ ስብሰባ መቅረት የለበትም። ለአላህ ብለን የምንቆምለት እውነት አሸናፊ ነውና፣ በአንድነት ሆነን ድምፃችንን የምናሰማበት ጊዜው አሁን ነው!
መጋቢት 1 ቀን ሁላችንም በአንድ ልብ እንገናኝ!
ቀን፡ ማክሰኞ፤ መጋቢት 1 2018 ዓ.ል
ሰዓት፡ ዙህር ሰላት እንደተሰገደ
ቦታ፡ አል-አቅሷ መስጂድ
ከጥቁር አንበሳ፤ ሰፈረ ሰላም እና ልደታ ለሚመጡ ተማሪዎች ትራንስፖርት በህብረቱ ይመቻቻል።
@aaumsu
ዋ! ሙዕተሲማ❗️❗️❗️
ትዕቢትና ኩራት በወጠራት በባዛንታይን ስረወ መንግሥት ሥር በምትተዳደረው የዓሙሪያ ከተማ ሙስሊሞች በእሥር ቤት ታጉረዋል። ክብራቸው ተዋርዶ ወታደሮቹ በእስልምናቸው እየተሳለቁ ዘብጥያ ጥለዋቸዋል።
ሺራት አል ዓለውያ የተሰኘች ወጣት ወደዚህ እሥር ቤት ልትወሰድ በወታደሮች ታጅባ ትገፈተር ይዛለች። አንድ የሮማ ወታደር ሒጃቧን ገፍፎ በስድብና ግልምጫ እየገፈተራት ሳለ የክብሯ መደፈር የሒጃቧ መገፈፍአንገብግቧት “ዋ! ሙዕተሲማ ዋ ኢስላማ” በማለት ድምጿን ከፍ አድርጋ ተጣራች።
በወቅቱ የዓባሲያ ስረወ መንግሥትን ይመራ የነበረው ኸሊፋ ሙዕተሲም ቢላህ ይሰማት ዘንድ ጩኸቷን አሰማች። ምንም እንኳ ኸሊፋው በብዙ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ቢሆንም ይህ ዜና በአንድ አዕራቢ አማካኝነት የአንዲት ሙስሊም ሴት ክብር መነካቱና “ዋ! ሙዕተሲማ” በማለት የመጮዃ ዜና ደረሰው።
ኸሊፋው ሙዕተሲም ይህ ሲነገረው በውሃ ጥም የተንገበገበ ጉሮሮውን ሊያረጥብ ብርጭቆውን ወደ አፉ እያስጠጋ ነበር። ውሃ ለምኔ በማለት ብርጭቆውን ወደ መሬት ወረወረው “አንቺ ሙስሊም ሴት ሆይ ወላሂ እረዳሻለሁ!” ሲል ከተቀመጠበት ተነሳ። በንዴት ጦፎ ተቆጣ። ፊቱ ተቀያየረ “ከአሚሩል ሙዕሚኒን ለሮማው ውሻ...” ብሎ የሚጀምር ዛቻ አዘል መልእክት ሴቷን እንዲፈታ የሚጠይቅ፤ ካልሆነ ግን ቅጣቱ የከፋ መሆኑን የሚያትት ደብዳቤ ወደ ባዛንታይኑ ንጉሥ ላከ።
የባዛንታውያኑ ንጉሥ ግን መልስ ሳይሰጥ በመቅረቱ ሙዕተሲም ቢላህ ወደ ዓሙሪያ ከተማ ጦሩን በራሱ እየመራ ዘመተ። በቦታው ደርሶም የዓሙሪያን ግንብ ተሻግረው የሚያጠቁ እሳት ጎረስ ድንጋዮችን በወስፈንጥር አከታትሎ በመወርወር የከተማዋ ምሽግ ውስጥ ያሉትን ወታደሮች ደበደበ። ልክ በረመዳን 6ኛ ቀን በ223ኛው ዓመተ ሂጅራ እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር ጁላይ 31/838 ዓመት ከዛ በፊት ተደፍራ የማታውቀው እና ጠንካራዋን ዓሙሪያን በቁጥጥሩ ሥር አዋለ። የሴቷ ክብር መደፈርና ጥሪዋ የአንድ ከተማ መከፈት ምክንያት ሆነ፡፡
ያቺን ሴት አስጠርቶ “ሙዕተሲም ደረሰልሽን?” በማለት ጠየቃት እሷም “አዎ” ብላ መለሰች። ሒጃቧን ያወለቀውን ግለሰብ ይዞ ፊት ለፊቷ አቀረበው የፈለገችውን ማድረግ እንደምትችልም ነገራት። እርሷ ግን “ኢስላም ምህረትን ያስተምረናል እኔም ይቅር ብዬዋለሁ” በማለት ድንቅ ስነ ምግባር ለበስ መልስ መለሰች።
ሐለቃ ደርስ ላይ ተቀምጠው ሳለ ነበር ይህን የሙዕተሲም ድል ኢማሙ አህመድ ኢብኑ ሐንበል የሰሙት። ያ የገረፋቸው፣ቁርኣን መኽሉቅ ነው በሉ ብሎ የቀጣቸው፣ ጀርባቸው ሰንበር እስኪያወጣ፣ ራሳቸውን ስተው እስኪወድቁ የገረፋቸው ሙዕተሲም ይህን ዘመቻ ለኢስላምና ለሒጃብ ሲል መክፈቱ
አስደስቷቸው ከተቀመጡበት ተነስተው ስለኢስላም ባደረገው ተጋድሎ እኔም አውፍ ብዬዋለሁ አሉ።
©AAU6kilojemea
@fivekjemaa
ዋ! ሙዕተሲማ❗️❗️❗️
ትዕቢትና ኩራት በወጠራት በባዛንታይን ስረወ መንግሥት ሥር በምትተዳደረው የዓሙሪያ ከተማ ሙስሊሞች በእሥር ቤት ታጉረዋል። ክብራቸው ተዋርዶ ወታደሮቹ በእስልምናቸው እየተሳለቁ ዘብጥያ ጥለዋቸዋል።
ሺራት አል ዓለውያ የተሰኘች ወጣት ወደዚህ እሥር ቤት ልትወሰድ በወታደሮች ታጅባ ትገፈተር ይዛለች። አንድ የሮማ ወታደር ሒጃቧን ገፍፎ በስድብና ግልምጫ እየገፈተራት ሳለ የክብሯ መደፈር የሒጃቧ መገፈፍአንገብግቧት “ዋ! ሙዕተሲማ ዋ ኢስላማ” በማለት ድምጿን ከፍ አድርጋ ተጣራች።
በወቅቱ የዓባሲያ ስረወ መንግሥትን ይመራ የነበረው ኸሊፋ ሙዕተሲም ቢላህ ይሰማት ዘንድ ጩኸቷን አሰማች። ምንም እንኳ ኸሊፋው በብዙ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ቢሆንም ይህ ዜና በአንድ አዕራቢ አማካኝነት የአንዲት ሙስሊም ሴት ክብር መነካቱና “ዋ! ሙዕተሲማ” በማለት የመጮዃ ዜና ደረሰው።
ኸሊፋው ሙዕተሲም ይህ ሲነገረው በውሃ ጥም የተንገበገበ ጉሮሮውን ሊያረጥብ ብርጭቆውን ወደ አፉ እያስጠጋ ነበር። ውሃ ለምኔ በማለት ብርጭቆውን ወደ መሬት ወረወረው “አንቺ ሙስሊም ሴት ሆይ ወላሂ እረዳሻለሁ!” ሲል ከተቀመጠበት ተነሳ። በንዴት ጦፎ ተቆጣ። ፊቱ ተቀያየረ “ከአሚሩል ሙዕሚኒን ለሮማው ውሻ...” ብሎ የሚጀምር ዛቻ አዘል መልእክት ሴቷን እንዲፈታ የሚጠይቅ፤ ካልሆነ ግን ቅጣቱ የከፋ መሆኑን የሚያትት ደብዳቤ ወደ ባዛንታይኑ ንጉሥ ላከ።
የባዛንታውያኑ ንጉሥ ግን መልስ ሳይሰጥ በመቅረቱ ሙዕተሲም ቢላህ ወደ ዓሙሪያ ከተማ ጦሩን በራሱ እየመራ ዘመተ። በቦታው ደርሶም የዓሙሪያን ግንብ ተሻግረው የሚያጠቁ እሳት ጎረስ ድንጋዮችን በወስፈንጥር አከታትሎ በመወርወር የከተማዋ ምሽግ ውስጥ ያሉትን ወታደሮች ደበደበ። ልክ በረመዳን 6ኛ ቀን በ223ኛው ዓመተ ሂጅራ እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር ጁላይ 31/838 ዓመት ከዛ በፊት ተደፍራ የማታውቀው እና ጠንካራዋን ዓሙሪያን በቁጥጥሩ ሥር አዋለ። የሴቷ ክብር መደፈርና ጥሪዋ የአንድ ከተማ መከፈት ምክንያት ሆነ፡፡
ያቺን ሴት አስጠርቶ “ሙዕተሲም ደረሰልሽን?” በማለት ጠየቃት እሷም “አዎ” ብላ መለሰች። ሒጃቧን ያወለቀውን ግለሰብ ይዞ ፊት ለፊቷ አቀረበው የፈለገችውን ማድረግ እንደምትችልም ነገራት። እርሷ ግን “ኢስላም ምህረትን ያስተምረናል እኔም ይቅር ብዬዋለሁ” በማለት ድንቅ ስነ ምግባር ለበስ መልስ መለሰች።
ሐለቃ ደርስ ላይ ተቀምጠው ሳለ ነበር ይህን የሙዕተሲም ድል ኢማሙ አህመድ ኢብኑ ሐንበል የሰሙት። ያ የገረፋቸው፣ቁርኣን መኽሉቅ ነው በሉ ብሎ የቀጣቸው፣ ጀርባቸው ሰንበር እስኪያወጣ፣ ራሳቸውን ስተው እስኪወድቁ የገረፋቸው ሙዕተሲም ይህን ዘመቻ ለኢስላምና ለሒጃብ ሲል መክፈቱ
አስደስቷቸው ከተቀመጡበት ተነስተው ስለኢስላም ባደረገው ተጋድሎ እኔም አውፍ ብዬዋለሁ አሉ።
©AAU6kilojemea
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
የዛሬ መልዕክት - ቁጥርህን ሳይሆን ወኔህን መዝን!
ሙስሊሙ ተማሪ ሆይ!
ወንድሜዋ:- ቁጥሬ ትንሽ ነው አትበለኝ:: ካነስክም ቁጥር የተመናመነ እለት ሳይሆን ወኔህ የሞተ እለት እንደሆነ እወቅ:: ጌታህ በቅዱስ ቃሉ "ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት" ሲል ገልፇል:: ነብያችንም የበድር ጦርነትን ሲያሸንፉ በቁጥር በብዙ ተበልጠው ነበር:: ኻሊድም ያን ሁሉ አውደውጊያ ሲያሸንፍ በቁጥር በልጦ ሳይሆን በወኔ ልቆ በመገኘቱ ነው::
ወዲህ በታሪክ ፈረስ ብትጋልብ አንደሉስን ድል ያደረጓት ሙስሊሞች 12ሺህ ብቻ እንደሆኑ ትረዳለህ:: ከአንደሉስ ሲባረሩ ግን ከገርናጣ ብቻ የተፈናቀሉት ከሚልዬን በላይ ነበሩ:: ሐበሻዊው ኢማም አህመድ የልብነ- ድንግልን 200ሺህ ሰራዊት ድል ሲያደርግ 12ሺህ ሰራዊት ብቻ ይዞ ነበር:: ዛሬ ግን በቁጥር በልጠህ እንኳ ያለህበትን ሁኔታ ታውቀዋለህ:: ነብዩላህ ዳውድ ጃሉትን ድል ሲያደርጉ ገና ብላቴና ነበሩ::
በከፍታና በዝቅታ መካከል ያለው ርቀት የልብን ያክል ነው:: በድልና በሽንፈት መካከል ያለው ርዝመት የኢማንን ያክል ነው:: በክብር እና በውርደት መካከል ያለው ክፍተት የወኔን ያክል ነው:: በነፃነት እና በባርነት መካከል ያለው ቀዳዳ የትግልን ያክል ነው:: በፍትሕ እና በጭቆና መካከል ያለው ርቀት በተገፊው መካከል ያለውን ህብረት ያክል ነው:: እንጂማ "ብቻዬን ሆንኩ እንጂ...!" እያለ ከንፈሩን የሚመጠው ሙስሊም ሁለት ቢልዬንም አይደል?
ስለዚህ ልብህን ፈትሽ! ኢማንህን አጠንክር! ወኔህን ከፍ አድርግ! ስለ ነፃነትህ ታገል! ለፍትህ ስትል በህብረት ቁም! አለቀ!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ጥያቄ አለን!
ስለ እስልምናችን ጥያቄ አለን !!
ስለ መብቶቻችን ጥያቄ አለን !!
ስለኒቃቢስቷ ጥያቄ አለን!!
ለዩኒቨርሲቲያችን ጥያቄ አለን!!!
ሁላችሁም ፕሮፋይል ፒክቸር አድርጉት!
በስቶሪያችሁ ላይ አጋሩት!!
መልዕክታችን ይድርሳቸው ዘንድ!
አቋማችንን ያውቁ ዘንድ!
የክብራችንን ዋጋ ይረዱ ዘንድ!
ጥላቻቸውን ይተው/ይውጡ ዘንድ!
መከባበርን ያስቀድሙ ዘንድ ማለት ነው!!
ኒቃብ እና ሌሎች ሀይማኖታዊ እሴቶቻችን ለድርድር የሚቀርቢ ሸቀጦች አይደሉም:: እሴቶቻችን የነፃነት ዘውዶቻችን ናቸው!!!። እሴቶቻችን የእኩልነት መገለጫዎቻችን ናቸው። እሴቶቻችን ሕገ- መንግስታዊ መብቶቻችን ናቸው!!!።
Profile picturesque እና Story ያደረጋቹበትን screen shoot በ @Niqab_issueBot ላኩልን
@aaumsu
ረመዷን 17...
~
📅ዛሬ ረመዷን 17… የቀን መቁጠሪያው ላይ ያለ ተራ ቁጥር አይደለም። ከ14 ክፍለ ዘመናት በፊት፣ ፀሀይ አናት ላይ በወጣችበት፣ አሸዋው እሳት በለበሰበት በዚያ ጭው ባለ የበድር በረሃ ላይ የተፃፈ አንፀባራቂ የኢማን ታሪክ ነው።
313 ፆመኛ የነቢዩ ﷺ ባልደረቦች፣ በቁጥር ከ1000 በላይ ከሆኑ፣ እስከ አፍንጫቸው ከታጠቁና በዘመኑ የጦር ስልት በረቀቁ የቁረይሽ ሙሽሪኮች ጋር የተፋጠጡበት ዕለት ነው። ይህ ቀን አላህ በቁርኣኑ "የውመል ፉርቃን" (እውነትና ውሸት የተለዩበት ቀን) ብሎ የሰየመው ታላቅ ቀን ነው።
(يَوْمَ الْفُرْقَانِ يَوْمَ الْتَقَى الْجَمْعَانِ)
«እውነትና ውሸት በተለዩበት ቀን፤ ሁለቱ ጭፍሮች በተገናኙበት ቀን…» (አል-አንፋል)
ሶሀባዎቹ ከነቢያቸው ﷺ ጋር ሲወጡ ሀሳባቸው የሻምን የንግድ ቅፍለት ለመያዝ ነበር። አላህ ግን ከዚህ የላቀ፣ እስከ ቂያማ የሚወሳ ድልን ፈልጎላቸው ነበር። የጦር መሳሪያቸው ጥቂት፣ ፈረሶቻቸው ሁለት፣ ግመሎቻቸው ደግሞ ሰባ ብቻ ነበሩ። በየተራ እየተፈራረቁ ይጋልባሉ። ሆዳቸው በፆም ተቆራምዷል፣ ጉሮሯቸው በውሀ ጥም ደርቋል፤ ልባቸው ግን በአላህ ፍቅር እና በተውሂድ ብርሀን ርሶ ነበር።
📓አላህ ይህንን ሲገልፀው፡-
(وَإِذْ يَعِدُكُمُ اللَّهُ إِحْدَى الطَّائِفَتَيْنِ أَنَّهَا لَكُمْ وَتَوَدُّونَ أَنَّ غَيْرَ ذَاتِ الشَّوْكَةِ تَكُونُ لَكُمْ وَيُرِيدُ اللَّهُ أَن يُحِقَّ الْحَقَّ بِكَلِمَاتِهِ وَيَقْطَعَ دَابِرَ الْكَافِرِينَ)
«አላህም ከሁለቱ ጭፍሮች (ከንግዱ ወይም ከጦሩ) አንደኛይቱ ለእናንተ መኾኗን በተስፋ ቃል በሰጣችሁ ጊዜ (አስታውሱ)፡፡ የጦር መሣሪያ የሌላትንም (የንግዷን ጭፍራ) ለእርናንተ ልትኾን ትወዳላችሁ፡፡ አላህም እውነትን በቃላቱ ሊያረጋግጥና የከሓዲዎችንም ርባራብ ሊቆርጥ ይሻል፡፡» (አል-አንፋል 8፡7)
ጦርነቱ ሊጀመር ዋዜማው ላይ ሌሊቱን ሙሉ ነቢዩ ﷺ ድንኳናቸው ውስጥ ሆነው ወደ ጌታቸው ሲያለቅሱ አደሩ። ትከሻቸው ላይ የነበረው ሻል መሬት ላይ እስኪወድቅ ድረስ እጆቻቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው፣ የዚህ ዲን ህልውና እንዲቀጥል ጌታቸውን ይማፀኑ ነበር። በሶሂህ ሙስሊም ላይ እንደሰፈረው እንዲህ አሉ፡-
«اللَّهُمَّ أَنْجِزْ لِي مَا وَعَدْتَنِي، اللَّهُمَّ آتِ مَا وَعَدْتَنِي، اللَّهُمَّ إِنْ تُهْلِكْ هَذِهِ الْعِصَابَةَ مِنْ أَهْلِ الْإِسْلَامِ لَا تُعْبَدْ فِي الْأَرْضِ»
«ያ አላህ! የገባህልኝን ቃል ኪዳን ፈፅምልኝ። ያ አላህ! ቃል የገባህልኝን ድል ስጠኝ። ያ አላህ! ይህችን የሙስሊም ጭፍራ ዛሬ ካጠፋሃት በምድር ላይ ከእንግዲህ አትመለክም!»
ይህ ዱዓ የነቢዩን ﷺ ጭንቀት እና የዚያን ቀን ክብደት ያሳያል። አቡበክር ሶዲቅ ሻላቸውን አንስተው ትከሻቸው ላይ እያደረጉላቸው፣ «ያ ረሱለላህ! ይበቃል፤ ጌታህ የገባልህን ቃል በእርግጥ ይሞላልሃል»እያሉ ያፅናኗቸው ነበር።
ንጋቱ ላይ ጦርነቱ ሲጀመር፣ የፆመኞቹ 313 ሙእሚኖች ተክቢራ የበድርን በረሀ አናወጠው። በአላህ የተወከለ፣ አኼራን የናፈቀ ልብ፣ የጠላትን ብዛትም ሆነ የመሳሪያውን ክምችት አልፈራም። አላህም በሰማይ ያሉ መላእክትን ወደ በድር ምድር አዘመተ።
📓(إِذْ تَسْتَغِيثُونَ رَبَّكُمْ فَاسْتَجَابَ لَكُمْ أَنِّي مُمِدُّكُم بِأَلْفٍ مِّنَ الْمَلَائِكَةِ مُرْدِفِينَ)
«(በጦርነቱ ጊዜ) ጌታችሁን እርዳታ በለመናችሁ ጊዜ (አስታውሱ)፡፡ እኔ ከመላእክት ሺህ፣ ተከታታዮች ሲኾኑ አጠናክራችኋለሁ በማለት ለእናንተ (ጥሪያችሁን) ተቀበለ፡፡» (አል-አንፋል)
ነቢዩ ﷺ አንድ እፍኝ አሸዋ ዘግነው ወደ ጠላት ፊቶች ላይ ሲበትኑት፣ አላህ ያንን አሸዋ የያንዳንዱን ካሀዲ አይን ውስጥ እንዲገባ አደረገ። ሙስሊሞቹም ጠላትን በጀግንነት መከቱ።
(وَمَا رَمَيْتَ إِذْ رَمَيْتَ وَلَٰكِنَّ اللَّهَ رَمَىٰ)
«በወረወርክም ጊዜ አንተ አልወረወርክም፤ ግን አላህ ወረወረ።" (አል-አንፋል)
ዛሬ ላይ ሆነን ስናስበው…
ይህ ታላቅ ቀን ለእኛ ትልቅ ትምህርት ነው። ዛሬ እኛ ዘንድ ይህ ውብ የሆነ የኢስላም ዲን የደረሰው በምቾት እና በአልጋ ላይ ሆኖ አይደለም። እነዚያ ጀግና ፆመኛ ሶሀቦች፤ በጠራራ ፀሀይ፣ ትኩስ አሸዋ ላይ፣ በፆም የደረቀ ጉሮሯቸውን፣ በላባቸውና በደማቸው አርጥበው ባመጡልን ታላቅ መስዋዕትነት ነው።
እኛ ዛሬ አየር ማቀዝቀዣ (AC) ባለው መስጊድ ውስጥ ሆነን ቁርኣን ስንቀራ፣ በምቾት ተኝተን ፆማችንን ስንፆም፣ የዚህን ዲን ዋጋ እና እነዚያ ብርቅዬ ትውልዶች የከፈሉትን ዋጋ ማስታወስ አለብን።
በፆም ምክንያት «ደከመኝ፣ ሰነፍኩ»ስንል — በፆም አፍ ተዋግተው ያሸነፉትን የበድር ጀግኖችን እናስታውስ።
ዲናችንን ለመተግበር ስናፍር ወይም ስንሳቀቅ — ለዚህ ዲን ሲሉ አንገታቸውን የሰጡትን እነ ዑመይር ኢብኑ አቢ ወቃስን (ገና የ16 አመት ታዳጊ) እናስታውስ።
«ጥቂት ነን፣ አቅም አነሰን»ብለን ስንጨነቅ — 300 ሆነው 1000 የተጋፈጡትን፣ አላህም በመላእክት ያገዛቸውን ሶሀባዎች እናስታውስ።
ረመዷን 17 - የሙስሊሞች የክብር፣ የድል እና የኢማን ጥንካሬ ማረጋገጫ ቀን!
©
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
የዛሬው መልዕክት ለሙስሊሙ ተማሪ!
ጭቆናና ግፍ በተለያዩ ዘመናትና ቦታዎች መልካቸውን እየቀያየሩ መምጣታቸው የማይቀር ሀቅ ነው፤ አምባገነኖች እስካሉ ድረስ ደግሞ ይህ ፈተና ይቀጥላል። ከአለም አድማስ እስከ አድማስ በ"ሙስሊም ጠልነት" ስሜት ሰክረው እምነትህንና ማንነትህን ለመገፍተር የማይሞክሩበት ቀዳዳ የለም።
መብትህ በዜግነትህ ክብር ወይም በቁጥርህ መብዛት ብቻ ተከብሮ እንዲሰጥህ አትጠብቅ፤ ምክንያቱም ቁጥራቸው ጥቂት ሆኖ መብታቸውን ያስከበሩ እንዳሉ ሁሉ፣ ቁጥራቸው በዝቶ ሳለ የባርነትን ቀንበር የተከናነቡ መኖራቸውን ከታሪክ መማር ይገባሃል። መብት የሚገኘው ከአባቶችህ በወረስከው የቆራጥነትና የመስዋዕትነት መንፈስ እንጂ ዝም ብሎ በመጠበቅ አይደለም። እንደፈለጉ የሚጋልቡህና የሚጭኑህ ታዛዥ ፍጡር ከመሆን ይልቅ፣ "ለምን?" ብለህ የምትጠይቅ፣ የሚገባህን የምታውቅና ለማንም የማትሰጥ ጀግና መሆን ይኖርብሃል።
መብትህን ለማስከበር በቁርጠኝነት ዘብ ቁም፤ ይህች ሀገር የራሷ የሆነ እሴትና ታሪክ ያላት እንጂ የሌሎችን የተሳሳተ መንገድ የምትከተል ፈረንሳይ አለመሆኗን አስገንዝባቸው፤ የፈረንሳይን መንገድ ከመረጡ ግን አንተም እንደ አልጄሪያ ሙጃሒዶች ለነፃነትህ መስዋዕት ለመሆን ዝግጁ መሆንህን በተግባር አሳያቸው፤ ምክንያቱም ለአንድ አማኝ መስዋዕትነት እንጂ ሽንፈት መቼም ቢሆን አይመጥነውም።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ዋ! ሙዕተሲማ!
ዋይታዋን አሰማች! አንተ ባለህበት ደፍረው ክብሬን ነኩ!
ጦር አዘመተላት እ'ሱም አልጠፋውም የሒጃቧ ልኩ።
ዛሬ ደግሞ እኛ አለን!
ሙዕተሲምን ባንሆን 'ላገር የሚበቃ ጦር ባናሰማራ
በዝምታ አናልፍም ሒጃቧ ተነክቶ እህት ስትጣራ።
እንጠብቃታለን ነፍሳችንን ሰጥተን ቅንጣትም ሳንፈራ
አንደራደርም አለን እንላለን እኛ ስለክብሯ!!!
@aaumsu
.
╔════•| ✿ |•════╗
ልደታ ካምፓስ (SBE)
╚════•| ✿ |•════╝
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ
🍃ውድ ልደታ ካምፓስ የተመደባችሁ ፍሬሽ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወንድምና እህቶቻችን በቅድሚያ የልደታ ካምፓስ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመአ ጊቢውን በመቀላቀላችሁ ያለንን ደስታ ለመግለፅ እንወዳለን። ለሚኖራችሁ የጊቢ ቆይታና የትምህርት ጊዜም በተቅዋ የበለፀገ፣ በዲን ማንነት የታነፀ፣ የተሳካና ያማረ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
🧩ወደ ጊቢያችሁ ስትመጡ ለሚያስፈልጋችሁ መረጃዎች፤ ከመጣችሁም በኋላ ለሚኖራችሁ ቆይታና ለሚያስፈልጋችሁ እገዛዎች ለማቀላጠፍ ይረዳን ዘንድ ይህንን ፎርም አዘጋጅተናል።
https://docs.google.com/forms/d/1l63w206xiGrm3Bn3KFPBT_xktaKxR8fSCzwyTHmZtnI/edit
#EIABC(SBE)_MSJ.
╔════•| ✿ |•════╗
ልደታ ካምፓስ (SBE)
╚════•| ✿ |•════╝
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ
🍃ውድ ልደታ ካምፓስ የተመደባችሁ ፍሬሽ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወንድምና እህቶቻችን በቅድሚያ የልደታ ካምፓስ የሙስሊም ተማሪዎች ጀመአ ጊቢውን በመቀላቀላችሁ ያለንን ደስታ ለመግለፅ እንወዳለን። ለሚኖራችሁ የጊቢ ቆይታና የትምህርት ጊዜም በተቅዋ የበለፀገ፣ በዲን ማንነት የታነፀ፣ የተሳካና ያማረ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
🧩ወደ ጊቢያችሁ ስትመጡ ለሚያስፈልጋችሁ መረጃዎች፤ ከመጣችሁም በኋላ ለሚኖራችሁ ቆይታና ለሚያስፈልጋችሁ እገዛዎች ለማቀላጠፍ ይረዳን ዘንድ ይህንን ፎርም አዘጋጅተናል።
https://docs.google.com/forms/d/1l63w206xiGrm3Bn3KFPBT_xktaKxR8fSCzwyTHmZtnI/edit
#EIABC(SBE)_MS
Reminder from Yesterday’s Da‘wah – ‘Izzah of the Muslim
Allah gave honor (‘izzah) to the believers through Islam.
Real superiority is not wealth, houses, or worldly power - it is holding firmly to Islam.
The early Muslims understood this deeply.
👉When the Muslims fought Battle of Yamama, the companion Al-Bara ibn Azib bravely entered the fortress from the top of the wall while enemies surrounded him, just to open the gate for the Muslims.
👉In another example during the Battle of al-Qadisiyyah, the companion Ribi ibn Amir came as a messenger to the Persian leader Rostam Farrokhzad.
Though his clothes and mount were simple, his words carried such confidence that Rustum feared the strength of the Muslims behind him.
👉And in the Battle of Mu'tah, only 3000 Muslims stood against a huge Roman army.
When Zayd ibn Harithah was martyred, Ja'far ibn Abi Talib took the flag, and then Abdullah ibn Rawahah- showing courage and honor for Islam.
👉Another powerful example is Abdullah ibn Hudhafa al-Sahmi during the time of Umar ibn al-Khattab.
The enemy king tried to tempt him with food, wealth, and even his daughter, but he refused to leave Islam. His honor in faith amazed the king.
These stories teach us something important:
‘Izzah is not in worldly things.
‘Izzah is in holding firmly to Islam.
The early Muslims used to say:
“We are a people whom Allah honored through Islam.”
But when Muslims start looking at the dunya of others and take them as models, they begin to lose that honor.
As students, our honor should be in:
• Being serious about our salah
• Holding firmly to our Islamic identity
• Strengthening our aqidah
• Not being ashamed of our religion
• And today, when our niqabi sisters face disturbance in the university, this is also part of the struggle (ijtihad) for Islam. As brothers, we should feel responsible, support them with respect, stand for their rights in a wise and dignified way, and not remain silent when the symbols of our religion are pressured.
Honor does not come from dunya.
Honor comes from Islam.
