5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 157
Subscribers
No data24 hours
-47 days
No data30 days
Posts Archive
የAAU ሙስሊም ተማሪዎችን የሰብዓዊ መብት ጥያቄ አስመልክቶ ዶክተር ሳሙኤል በሰጡት መልስ ላይ የተነሱ ጥያቄዎች እና መጠነኛ ማብራሪያዎች:-
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን የሚገድብ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ፣ ለቀረቡ ጥያቄዎች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የሰጡት ምላሽ ከመንደርደሪያ እስከ መደምደሚያው መሠረታዊ የሕግ እና የፅንሰ-ሐሳብ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኖ ተገኝቷል። ፕሬዚዳንቱ ትምህርት ማህበራዊ ልማት ስለሆነ ከባህል፣ ከሃይማኖት እና ፖለቲካ ተፅዕኖ ውጪ ይፈፀማል በሚል መንደርደሪያ ንግግራቸውን ቢጀምሩም፣ አንዲት ሙስሊም ተማሪ ኒቃብ በመልበሷ በትምህርት ሂደት ላይ የምታሳድረው "ሃይማኖታዊ ተፅዕኖ" ምን እንደሆነ ግን ግልጽ አይደለም። ሴኩላር እንዲሆን የሚፈለገው የትምህርት ስርዓቱ እንጂ የተማሪው ማንነት አለመሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን መገደብና "ካላወለቃችሁ አትማሩም" ወይም "የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎት አታገኙም" ማለት ዓለምአቀፋዊ የሆነውን ሰብዓዊ መብት ከመጋፋትም በላይ፣ "ሃይማኖትህን ጥለህ ካልገባህ አትማርም" የሚል አግባብነት የሌለው ጣልቃ-ገብነት በመሆኑ የሴኩላሪዝምን መርህ ይጥሳል። ተማሪውንም ከሃይማኖቱ ነጥሎ ምን ዓይነት ትውልድ ለመፍጠር ታስቦ እንደሆነ የሚያጠያይቅ ሲሆን፣ ሃይማኖት አልባነትም ራሱን የቻለ እሳቤ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች የሚሰወር አይሆንም።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ሳይንስ ሰውን ከመጣበት የዝግመተ ለውጥ (Evolution) ታሪክ አንጻር እንደሚያስተምርና ተማሪውም ይህ ከሃይማኖቴ ጋር ይጋጫል ብሎ "አልፈተንም" ማለት እንደማይችል ጠቅሰዋል። ይህ ትክክለኛ ገለፃ ቢሆንም፣ ከተማሪዎቹ የእምነት ነፃነት ጥያቄ ጋር ግን በቀጥታ አይገናኝም። ተማሪዎች እያነሱ ያሉት ጥያቄ "ትምህርቱ ከእምነቴ ጋር ስለሚጋጭ አልማርም" የሚል ሳይሆን፣ ትምህርቱን እየተማሩ እምነታቸው የሚያዘውን መለኮታዊ አለባበስ በተለይም የኒቃብ አጠቃቀምን የመተግበር መብታቸው እንዲከበር ነው። ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሳይንሳዊ እውቀትን እንዲቀስሙ የማድረግ መብት እንዳለው ሁሉ፣ የአንድን ተማሪ ሃይማኖታዊ አለባበስ "አውልቅ" ብሎ የማስገደድ ስልጣን ግን የለውም። እዚህ ጋ ማነው ሕገ-መንግስቱን፣ ዓለምአቀፍ ሰብዓዊ መብቶችን እና ከመማርና ሃይማኖትን ከመተግበር ጋር የተደነገጉ ሕግጋትን እየጣሰ ያለው የሚለው ነጥብ ትልቅ ጥያቄ ያስነሳል።
በተጨማሪም ትምህርት ማንነትን በግልፅ እንዲታይ እና መምህር የተማሪን ስሜት ማንበብ የሚችልበትን የፊት ለፊት ግንኙነት እንደሚፈልግ፣ ለዚህም ሲባል የኒቃብ አለባበስን የመተግባር መብት ሊገደብ እንደሚችል የቀረበው መከራከሪያ በዘመናዊው የትምህርት ዓለም ተቀባይነት ያለው አይደለም። መምህር የተማሪን ስሜት ማንበብ ግዴታ ከሆነ፣ በአሁኑ ወቅት በስፋት እየተሰጡ ያሉ የርቀት ትምህርቶች ስህተት ናቸው ሊባል ነውን? በዓለም ዙሪያ ያሉና በትምህርት ጥራት ከዩኒቨርሲቲያችን የሚልቁ የልህቀት ማዕከላት እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ሳይከለክሉ ስኬታማ መሆናቸው እየታወቀ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይህንን እንደ ምክንያት ማቅረቡ አሳማኝ አይሆንም። ፕሬዚዳንቱ "ተማሪ Civic እንዲሆን እንፈልጋለን" በማለት የሰጡት መደምደሚያም ቢሆን፣ ሲቪክ መሆን ማለት ሃይማኖትን ከመተግበርና ከመከተል ነፃ መሆን ማለት ነው የሚል እሳቤ ካለው ወዴት እያመራን እንደሆነ ጥያቄ ያስነሳል። ሲቪክ መሆን እና አማኝ መሆን እርስ በእርስ የሚደጋገፉ እንጂ የሚቃረኑ እሴቶች አይደሉም።
ሰብዓዊ መብቶች ሊገደቡ የሚችሉት በፓርላማ በሚወጣ አዋጅ እንጂ ተቋማት በሚያወጡት መመሪያ ብቻ ሊሆን አይገባም። በዚህ ጉዳይ ፓርላማው አዋጅ ሳያወጣ ወይም ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ሳያፀድቅ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተለይቶ መብቶችን የሚገድብ መመሪያ ያወጣው ለምንድን ነው? ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ባወጣውና በያዝነው ዓመት ባሻሻለው የተማሪዎች ዲሲፕሊን መመሪያ መሠረት፤ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብን፣ የክርስትና እምነት ተከታዮች ደግሞ ነጠላን ለብሰው የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎት እንዳያገኙ የሚከለክል አንቀጽ መኖሩን ልብ ይሏል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ከትምህርታቸው የሚያዘናጋ አጀንዳ ከመስጠት ይልቅ፣ ዓለምአቀፍ ተሞክሮዎችን በመውሰድ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት በማክበር ለተሻለ የትምህርት ስርዓት ግብዓት እንዲሆኑ ማስቻሉ መልካም ነው።
©aaumsu
ለተፈጠረው መቁአረጥ ይቅርታ እንጠይቃለን
አሁን ተስተካክሏል የ "ኡስታዝ አቡል አባስ" "ኒእመተል ኢስላም" ዳእዋ መከታተል ችላላችሁ::
ቅጂውን እንለቃለን!!!!
የዳዕዋ ፕሮግራማችን ሊጀመር ነው!!!!🔥
አጅሩሚያ ክላስ
በአካል መገኘት ለማትችሉ በዚሁ ቻናል ላይ በቀጥታ የምናስተላልፈው ይሆናል::
⏳ FINAL DAWAH — TIME IS VERY SHORT
🕌 Make Zuhr Salah in Jama‘ah at Aqsa Masjid
➡️ Dawah program starts immediately after Zuhr
👉Ustaz Abu Sufyan
Softening hearts hardened by sin
👉Ustaz Abul Abbas
Ni‘matul Islam — the blessing we often forget
🎓 Certificates for course attendees
☕ Refreshment available
⚠️ No absence — be there
Pray together. Stay for the reminder.
إِذَا كُنْتَ بِاللَّيْلِ نَائِمًا، وَبِالنَّهَارِ هَائِمًا، وَفِي الْمَعَاصِي دَائِمًا، فَكَيْفَ تَرْجُو أَنْ تَكُونَ عِنْدَ اللَّهِ قَائِمًا؟»
ቀጠሯችን 1 ቀን ቀረው
📌 ከቀልብ ጋር በተያያዘ ጠቃሚ ምክሮችን በመስጠት የምናውቀው ኡስታዝ አቡ ሱፍያን የደረቁ ቀልቦቻችንን በምክሮቹ ያረጥብልን ዘንድ "ቀልብ እና ወንጀል" በሚል ርዕስ ጋብዘነዋል ::
📌 የተዘናጋንበትን እና አላህ ከሰጠን ፀጋወች ሁሉ በላጩን የእስልምና ፀጋ እናስተነትን ዘንድ ደግሞ ኮርሱን የሰጡንን ኡስታዝ ናሲር ሙሀመድ "ኒዕመቱል ኢስላም" በሚል ርዕስ ጣፋጭ ዳዕዋን ለመስማት ጋብዘናቸዋል ::
ሌላስ ምን አለ ❓
🖱 በቅርቡ የተሰጠውን ኮርስ ለተከታተሉ ተማሪዎች ሰርተፊኬት ይበረከትላቸዋል ::
🖱 የኪታብ ሽልማቶች
🖱 የሻይ ቡና ሰዐት
የት እና መቼ ❓
🗓 ነገ ቅዳሜ [ታህሳስ 25]
🕖 ከዙህር ሶላት በኋላ
📍 አል አቅሷ መስጂድ
@fivekjemaa
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉
إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﷺ
🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ከህፍ መቅራት
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
اللَّهُــمَّ صَلِ وَسَـــلِّمْ وَبَارِكْ على نَبِيِّنَـــا مُحمَّد ﷺ
@fivekjemaa
ቀጠሯችን 1 ቀን ቀረው
📌 ከቀልብ ጋር በተያያዘ ጠቃሚ ምክሮችን በመስጠት የምናውቀው ኡስታዝ አቡ ሱፍያን የደረቁ ቀልቦቻችንን በምክሮቹ ያረጥብልን ዘንድ "ቀልብ እና ወንጀል" በሚል ርዕስ ጋብዘነዋል ::
📌 የተዘናጋንበትን እና አላህ ከሰጠን ፀጋወች ሁሉ በላጩን የእስልምና ፀጋ እናስተነትን ዘንድ ደግሞ ኮርሱን የሰጡንን ኡስታዝ ናሲር ሙሀመድ "ኒዕመቱል ኢስላም" በሚል ርዕስ ጣፋጭ ዳዕዋን ለመስማት ጋብዘናቸዋል ::
ሌላስ ምን አለ ❓
🖱 በቅርቡ የተሰጠውን ኮርስ ለተከታተሉ ተማሪዎች ሰርተፊኬት ይበረከትላቸዋል ::
🖱 የኪታብ ሽልማቶች
🖱 የሻይ ቡና ሰዐት
የት እና መቼ ❓
🗓 ነገ ቅዳሜ [ታህሳስ 25]
🕖 ከዙህር ሶላት በኋላ
📍 አል አቅሷ መስጂድ
@ fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
“ሂጃብና ኒቃብ ምርጫ ሳይሆኑ ማንነታችን ናቸው! ”
ትምህርት በነፃነት የመማር መብታችን ይከበር። የAAU ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ድምፃችንን ለማሰማትና እውነታውን ለማብራራት በቲክቶክ ብቅ ብለናል! ተከታተሉን።
@aaumsu
https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7590465283408530708?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7504249112218240518
አሰላሙ ዐለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
✨እነሆ አጅር የማፈሻ ተከታታይ ቀናቶች መጡልን!!!✨
ረጀብ ወር አያመል–ቢض፣ኸይር ስራዎች በእጥፍ ድርብ አጅር የሚበዙበት ወር✨
ረጀብ 13-ጁመዓ
ረጀብ 14-ቅዳሜ
ረጀብ 15-እሁድ
እነዚህን ቀናቶች ከፆምን ወሩን ሙሉ እንደፆምን ይቆጠርልናል:: ምክንያቱም እያንዳንዱ መልካም ስራ በ10 የሚባዛ በመሆኑ ነው::አሁን ያለንበት ረጀብ ወር ላይ ሲሆን ደግሞ መልካም ስራዎች በእጥፍ ድርብ አጅሮች ይባዛሉ።
እነዚህን ቀናቶች እንፁም•••መፆም ካልቻልን እንኳ እህት ወንድሞቻችንን ወደዚህ ኸይር ስራ እንጋብዛቸው።
Repost from AAU - Muslim Students Union
"AAU ኒቃብን በመከልከሉ ምክንያት ለ15 ቀናት ከካፌ የታገዱ ሙስሊም ተማሪዎች ነበሩ:: በFBE: Commerce: ያሬድ ካምፓሶች አትገቡም ተብለው ከበር የቆሙበት ጊዜም ነበር:: መማሪያ ክፍል ውስጥም የተለያዬ እንቅፋት የተፈጠረባቸው ተማሪዎች አሉ:: ይህ ሁሉ የሆነው ሕገ- መንግስታዊ መብቶችን በማፈን በወጣው መመሪያ ምክንያት ነው:: እስካሁን የደረሰባቸው መበደልም ቆሞ ለመብታቸው ዋስትና የሆነን መመሪያ በማውጣት ሊካሱ ይገባል::" - ተማሪ ሙሐመድአሚን ካሳው ETV ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ከተናገረው
ሆኖም ግን ከተለቀቀው ፕሮግራም እንደተገነዘብነው ይህ እና መሠል የተማሪዎችን ጥያቄ የሚገልፁ መልዕክቶች ተቆርጠው ቀርተዋል:: ይህም በመሆኑ የጥያቄው ሙሉ መንፈስ ሊንፀባረቅ አልቻለም::
ለመሠል ፕሮግራሞች ሽፋን የሚሰጡ ሀገራዊ ሚዲያዎች ለተቋም ግንባታ ያላቸውን አስተዋፅዖ ታሳቢ አድርገው ተማሪዎች እየጠየቋቸው ያሉትን የመብት ጥያቄ ሀላፊነት በተሞላበት መልኩ እንዲያስተላልፉ እንጠይቃለን:: የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የሰጡት ምላሽም በተማሪዎች ዘንድ ሰፊ ጥያቄን በማስነሳት ላይ ያለ ከመሆኑም ባሻገር ለመልሳቸው በራሱ ብዙ ጥያቄዎች አሉን:: ስለሆነም ETVም ሆነ ከእርሱ ውጪ ያሉ የመንግስት ሚዲያዎች: ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የተቋቋሙ ሚዲያዎች እንዲሁም ስለ ሰብዓዊ መብት የሚጠይቁ አካላት ሁሉ ከፀደቀ ጀምሮ የሙስሊም ተማሪዎች መብት እንዲጣስ እያደረገ ስላለው የAAU መመሪያ እንዲጠይቁ እና ፍትሐዊ የሚዲያ ሽፋን እንዲሰጡ እንጠይቃለን::
@aaumsu
Repost from 5killo Jem'a official Channel
📚 Tutorial Program for Freshman Students!
🌟 As-salamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌟
We are back with our Mathematics Tutorial! ✨
Dear brothers and sisters taking Freshman courses, 😊
The 5 Kilo Muslim Students’ Jem’a Academic Sector is pleased to announce that the Freshman Tutorial Program will continue tomorrow with a dedicated Mathematics session:
📘 Subject: Mathematics
🕙 Time: 10:20 LT
📅 Date: 01/01/2026 . Thursday
📍 Venue: E-Block, Room E-131
✨ Let’s strengthen our understanding and excel in our studies — together, In shaa Allah!
📌 Don’t miss out!
📌 Invite your classmates too!
🔗 Join our Telegram channel for updates:
👉 t.me/fivekjemaa
"ሰሃባዎች (የነቢዩ ባልደረቦች) በአጋሪዎች (ሙሽሪኮች) በዓላት ላይ መገኘትንም ሆነ በሃይማኖታዊ በዓላቶቻቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ማስተላለፍን አይፈቅዱም ነበር።
ከሰለፎች አንደበት!
ዑመር ኢብኑል ኽጣብ (رضي ﷲ عنه) እንዲህ ይላሉ፦
﴿اجتنبوا أعداء الله في عيدهم، فإنّ السخط ينزل عليهم﴾
“የአላህን ጠላቶች በክብረበዓላቸው ጊዜ ራቋቸው፤ በርግጥ የአላህ ቁጣ በነሱ ላይ ይወርዳልና።”
📙 አል‐በይሀቂይ ሹዕበል ዒማን፡ 8940
