en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 159
Subscribers
-124 hours
-37 days
+230 days
Posts Archive
ክብሩን የመረጠ ! ትናንት በአደባባይ... አላውቅህም ብሎ መብቱን የረገጠ ፤ መፍትሄውን ትቶ አማራጭ የሰጠ :: ለስሜት ጥላቻ እጁን የለጠጠ ፤ "ተሸፍና እንዳላይ" ብሎ የቀወጠ ፤ ዛሬ ምን ተገኝቶ ... "ላክብራችሁ" አለ ምንኛ ቀበጠ :: ጥሪያችንን ሰምቶ ልቡ እንዳላበጠ ፤ ይጣራ ጀመረ ነገር ገለበጠ :: የሰማህ ይመጣል ሆዱን ያበለጠ ፤ እኛ ግን ቀሪ ነን ክብሩን የመረጠ :: ©️ Sefere Selam Jemeah @aaumsu

እህቶች ዛሬ ሙሉ የግቢው ሙስሊም ተማሪ ነው የኮራባችሁ! ኢንሻላህ ለጥያቀያችን መልስ እስኪሰጡ ድረስ ያሉበት ሁሉ ሄደን ድምጻችንን ማስማታችንን እንቀጥላለን። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን
እህቶች ዛሬ ሙሉ የግቢው ሙስሊም ተማሪ ነው የኮራባችሁ! ኢንሻላህ ለጥያቀያችን መልስ እስኪሰጡ ድረስ ያሉበት ሁሉ ሄደን ድምጻችንን ማስማታችንን እንቀጥላለን። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

የእህቶቻችን ID ተመልሷል! ወንድሞች እና እህቶች የእህቶቻችን id ሳይመለስ ንቅንቅ አንልም በማለታቸው የእህቶችን መታወቂያ ለመመለስ ተገደዋል። ነገር ግን የስም ዝርዝራቸውን ይዘዋል፤ እህቶችን ለማስፈራራት የሚደረግን ሙከራ በምንም መልኩ አንቀበልም!! @aaumsu

መልስ እንፈልጋለን!! ቢሮ ተመላልሰው አልሰማም ያለውን አካል ኢፍጣር ላስፈጥር ብሎ በመጣበት "ጥያቄ አለን!" ብለው እንዲሰማ አድርገውታል። እነኚህ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። ይህ አዲሱ ትውልድ ነው። የጀመረውን ሳይጨርስ የማያርፈው። ስለመብቱ መጠየቅን የማያፍረው: የማይፈራው። በመመሪያ የተረገጠው መብት በመመሪያ እስኪፀና ድረስ ጥያቄው ይቀጥላል። ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም! ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!! ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም! @aaumsu

ጥያቄ አለን ብለው የፍትህ ጥያቄያቸውን ያቀረቡ እህቶችን ID ተቀብሎ በዚህ ምሽት ማጉላላት ተቀባይነት የለውም!! በአሁን ሰዓት የእህቶቻችን ID እስኪመለስ አንቀሳቀስም ያሉ እህቶች እና ወንድሞች ልደት ካፌ አካባቢ ተሰባስበዋል። @aaumsu

+3
ጭቆና በቃ ያሉ እህቶችን ለመጨቆን እየተሞከረ ነው! ጥያቄ አለን ብለው ድምጻቸው ያሰሙ እህቶች Id ተቀብለዋል እያጉላሉ ነው። የጀመዓ ተወካዮችም በቦታው አሉ! ልደት ካፈ! @aaumsu

+3
አላውቃችሁም እያለ የነበረው ዩኒቨርሲቲያችን ራሱ ባዘጋጀው ኢፍጣር፤ አመራሮቹ ባሉበት ጅግና እህቶቻችን ጥያቄ አለን! ብለው ከፍ ብለዋል። @aaumsu

የእህቶቻችን ID ተመልሷል! ወንድሞች እና እህቶች የእህቶቻችን id ሳይመለስ ንቅንቅ አንልም በማለታቸው የእህቶችን መታወቂያ ለመመለስ ተገደዋል። ነገር ግን የስም ዝርዝራቸውን ይዘዋል፤ እህቶችን ለማስፈራራት የሚደረግን ሙከራ በምንም መልኩ አንቀበልም!! @aaumsu

ለ4 ኪሎ፣ 5ኪሎ እና ልደታ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች፤ ለ18 ወራት ጥያቄያችንን ችላ ላለውና 1,141 ተማሪዎችን "አናውቃችሁም" ብሎ በደብዳቤ ላይ ለሰረዘው አካል፣ ተማሪው ክብሩን በምግብ እንደማይለውጥ በተግባር የምናሳይበት ጊዜ ነው። ለእኛ እውነተኛው ኢፍጣር መብታችን ተከብሮ፣ ድምፃችን ተሰምቶና ወንድማማችነታችን ጎልቶ የሚታይበት ነው። የማንነታችን ማረጋገጫ ፊርማችንን "በቀይ ስርዝ" ከሚያጠፋው መድረክ ይልቅ፣ በእውነተኛ ፍቅርና እውቅና ወደተዘጋጁት የጀመዓችሁ ማዕዶች ሁላችሁንም እንጋብዛለን። 📍 ለ5 ኪሎ ተማሪዎች፦ ጀመዓችሁ 4 ኪሎ አምባሳደር ሞል መስጂድ ከ11፡30 ጀምሮ የዳዕዋ እና የኢፍጣር ፕሮግራም ስላዘጋጀ እንድትገኙ ተጋብዛችኃል። 📍 ለ4 ኪሎ ተማሪዎች፦ 4 ኪሎ ተማሪዎች መስጂድ የሚዘጋጀው የተለመደው ኢፍጣር ዛሬም ይኖራል እና እንድትገኙ ተጋብዛችኃል። 📍 ለልደታ (EiABC) ተማሪዎች፦ ጀመዓችሁ ሁለተኛውን የዳዕዋ እና ኢፍጣር ፕሮግራም ስላዘጋጀ 11፡30 ላይ አህመድ መስጂድ እንድትገኙ ተጋብዛችኃል። ኑ! ወንድማማችነታችንን እናድስ። ኑ! መብታችንን ለማስከበር በምናደርገው ጉዞ ላይ ብርታትን እንሰንቅ። እኛን የሚያውቁንና የሚያከብሩን ወንድሞቻችን ባዘጋጁት ማዕድ ላይ መገኘት፣ ከግብዝነት ግብዣዎች ሁሉ ይበልጣል። @aaumsu

🌙 RAMADAN SPECIAL EVENT 🌙 ✨ 4th Dawah & Ramadan Iftar Program ✨ With great joy, we invite you to join us today for our 4th Dawah and Iftar gathering in this blessed month of Ramadan. This special program brings together a beneficial Dawah session and the blessings of Iftar, offering us a valuable opportunity to listen, reflect, and strengthen our unity and brotherhood. We warmly encourage everyone to attend the Dawah program on time and not miss these important moments before we gather to break our fast together. Your presence from the beginning of the program will make this gathering more meaningful and beneficial for all. ✨ Program Highlights ⚜️ Inspiring Dawah Program ⚜️ Brotherhood & Sisterhood Gathering ⚜️ Iftar Together ⚜️ Open Discussion 📅 Today 🕰 Time:11:30 LT 📍 Venue:Ambassador 🤝 A beautiful time of brotherhood and sisterhood awaits. 💠 We want every one of you to be part of this special day. Your presence matters do not miss it.

It is truly a fascinating administrative miracle at Addis Ababa University: 📌 One moment, 1,141 students are "unknown": their names and signatures crossed out with a red pen as if they don't exist. 📌 The next moment, these same "non-existent" students are cordially invited to an official University Iftar. We have to ask the Administration: * If you don't know who we are when we ask for our rights, who exactly are you inviting to dinner? * Do we only become "students" when there is a photo-op for a PR event, but remain "unknown entities" when we demand justice? You cannot claim to honor our faith in the dining hall while dismissing our dignity in the Registrar's office. 1,141 signatures are 1,141 human beings, not a "club" you can erase with a stroke of a pen. Respect isn't served on a plate. It is written in policy and proven by the 18 months of justice you still owe us. We have a question! and We want the answer! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በግቢው የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ፊርማቸውን አሰባስበው ላስገቡት የመብት ጥያቄ አሰራርን የጣሰ፤ አሳፍሪ እና ለተማሪዎቹ ቦታ እንደሌለው የሚያሳይ ምላሽ ሰጠ! በቁጥር 1,14
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በግቢው የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ፊርማቸውን አሰባስበው ላስገቡት የመብት ጥያቄ አሰራርን የጣሰ፤ አሳፍሪ እና ለተማሪዎቹ ቦታ እንደሌለው የሚያሳይ ምላሽ ሰጠ! በቁጥር 1,141 የሚሆኑ፣ ማንነታቸው በውል የሚታወቅና በዩኒቨርሲቲው መዝገብ ላይ ያሉ ተማሪዎች፤ መብታችን ይከበር ብለው ያቀረቡትን አቤቱታ አስተዳደሩ በፌዝ መልሶታል። በደብዳቤው ላይ በጥቁር ስክሪቢቶ ስርዝ በማድረግ "እንደዚህ የሚባል ክበብ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ አናውቅም። ተመላሽ ይደረግ!" የሚል አሳፋሪ ምላሽ ሰጥቷል። አስተዳደሩ የሰረዘው የወረቀት ላይ ፅሁፍ ሳይሆን የ1,141 ተማሪዎችን ህያው ድምፅ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች ፒቲሺን ፈርመው ሲያስገቡ የመጀመሪያቸው አይደለም። ከበፊት ጀምሮ ቅሬታ ሲኖራቸው ከዩኒቨርሲቲው ጀምሮ አስከ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ድረስ አስገብተው ያውቃሉ። አሁን ላይም የተፈረመውን ፒቲሽን አልቀበልም ብሎ የመለሰው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ነው። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ጨምሮ የሐይማኖት ተቋማት ድረስ ገብቷል። በሁለተኛ ደረጃ 1141 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች መብታችን ተነካ ብለው ስለመብታቸው ቅሬታ ያስገቡት በክበብ ደረጃ ተደራጅተው አይደለም። ክበብ ነኝ ብሎ ያልሄደን አካል እንዲህ የሚባል ክበብ አላውቅምና ምላሽ አልሰጥም ማለት ከግንዛቤ የራቀ ነው። መጅሊስን ጨምሮ የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት፤ ዩኒቨርሲቲው የያዘው ይህ ግትርና ተማሪን አግላይ አካሄድ እንዲቆም፣ እንዲሁም የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚያከብር መመሪያ እንዲያወጣ የበኩላችሁን እንድታደርጉ እንጠይቃለን። እኛ "ክበብ" አይደለንም፤ እኛ የዚህ ተቋም ግማሽ አካል የሆንን ተማሪዎች ነን! ጥያቄያችን ህያው ነው፣ መልስም እንፈልጋለን! ጥያቄ አለን! መልስ እንፈልጋለን! @aaumsu

ለዩኒቨርሲቲያችን አመራሮች፤ የኢፍጣር ዝግጅታችሁን ተመልክተነዋል። ተምሩ ተደርድሯል፣ ውሃውም ቀርቧል። "ለሙስሊም ተማሪዎች አሳቢ" ሆናችሁ ለመታየት የሄዳችሁበት ርቀት "የሚደነቅ" ነው። ግን አንድ እውነታ አለ፦ ፀሐይ ስትጠልቅ እንደምንራብ ትዝ ያላችሁ አስተዳዳሪዎች፣ ለ18 ወራት ሙሉ የመብት ጥያቄ ስናነሳና "ፍትህ" እያልን ስንጮህ ግን ጆሮአችሁ እንዴት እንደተደፈነ ይገርማል። ለ540+ ቀናት ያህል መልስ አጥተው አቧራ የለበሱ ጥያቄዎቻችንን ችላ ብላችሁ፣ ዛሬ በአንድ ሳህን ምግብና በአንድ ብርጭቆ ውሃ ልታባብሉን መሞከራችሁ ለተማሪው ንቀት ነው። መልእክታችን ግልጽ ነው፦ * እኛን የራበን ፍትህ እንጂ የእናንተ ዳቦ አይደለም! * እኛን የጠማን መከበር እንጂ የእናንተ ውሃ አይደለም! ዩኒቨርሲቲው ሙስሊሙን ተማሪ በእውነት "ያከብራል" የሚባለው በጀት መድቦ ምግብ ሲያቀርብ ሳይሆን፣ ለአንድ አመት ከመንፈቅ ሙሉ መልስ የነፈጋቸውን የመብት ጥያቄዎች ሲመልስ ብቻ ነው። ያለ ፍትህ የሚቀርብ ማዕድ "ግዴታን ለመወጣት" የቀረበ ድራማ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም። የእውነት ሙስሊሙን ተማሪ የምታከብሩ ከሆነ የነፈጋችሁትን መብቱን መልሱለት! @aaumsu

ለዩኒቨርሲቲያችን አመራሮች፤ የኢፍጣር ዝግጅታችሁን ተመልክተነዋል። ተምሩ ተደርድሯል፣ ውሃውም ቀርቧል። "ለሙስሊም ተማሪዎች አሳቢ" ሆናችሁ ለመታየት የሄዳችሁበት ርቀት "የሚደነቅ" ነው። ግን አንድ እውነታ አለ፦ ፀሐይ ስትጠልቅ እንደምንራብ ትዝ ያላችሁ አስተዳዳሪዎች፣ ለ18 ወራት ሙሉ የመብት ጥያቄ ስናነሳና "ፍትህ" እያልን ስንጮህ ግን ጆሮአችሁ እንዴት እንደተደፈነ ይገርማል። ለ540+ ቀናት ያህል መልስ አጥተው አቧራ የለበሱ ጥያቄዎቻችንን ችላ ብላችሁ፣ ዛሬ በአንድ ሳህን ምግብና በአንድ ብርጭቆ ውሃ ልታባብሉን መሞከራችሁ ለተማሪው ንቀት ነው። መልእክታችን ግልጽ ነው፦ * እኛን የራበን ፍትህ እንጂ የእናንተ ዳቦ አይደለም! * እኛን የጠማን መከበር እንጂ የእናንተ ውሃ አይደለም! ዩኒቨርሲቲው ሙስሊሙን ተማሪ በእውነት "ያከብራል" የሚባለው በጀት መድቦ ምግብ ሲያቀርብ ሳይሆን፣ ለአንድ አመት ከመንፈቅ ሙሉ መልስ የነፈጋቸውን የመብት ጥያቄዎች ሲመልስ ብቻ ነው። ያለ ፍትህ የሚቀርብ ማዕድ "ግዴታን ለመወጣት" የቀረበ ድራማ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም። ምግባችሁን ለራሳችሁ አቆዩት፤ እኛ ግን የነፈጋችሁንን መብታችንን እንፈልጋለን! @aaumsu

ግልፅ ማብራሪያ: አቅጣጫ እና ጥሪ ከመጋቢት 1 ቀን ፕሮግራም እና አጠቃላይ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ --- ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !    የሙስሊሙ ተማሪ የመብት ጥያቄዎች ትላንት የነበሩ: በዛሬ ውስጥ ያሉ እንዲሁም መብቱን የሚጥሱ እና የሚገፉ እስካሉ እና እስከቀጠሉ ድረሱ የሚኖሩ እና የሚቀጥሉ ናቸው። እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የነበሩ መሠረታዊ የመብት ጥሰቶችን በመጠየቅ: በመታገል እና እንዲስተካከሉ በማድረግ ሙስሊም ተማሪዎች ብዙ ታሪክ አሳልፈዋል: ሰርተዋልም። ያለፉበት ታሪክ እንደሚያስረዳንም የተጓዙበት መንገድ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ከክላስ እና ትምህርት ጊዜን ቆርሶ ከመስጠት ጀምሮ ብዙ ችግሮች እና ውጣ ውረዶች ነበሩ። ሆኖም ግን በሁሉም የትግል መስመሮች ውስጥ የምንረዳው አንድ ጥሬ ሐቅ ቢኖር ቀደምቶቻችንን ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በማስከበር ረገድ ተምሳሌታዊ ስብዕና እንደነበሩ ነው።   እንዳለመታደል ሆኖም ትላንት በቀደምቶቻችን ላይ ሲደርስ የነበረው የመብት ጥሰት ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ሆኖ ሊሻሻል በሚሞክርበት ሰዓት እንኳ አልቀረም። ይባስ ብሎም የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ: ሕገ-መንግስታዊ መብት የሚንድ እንዲሁም ሐይማኖታዊ መብት የሚገፍ መመሪያ አወጣ። ሕገ-ወጥነትን ሕጋዊ ለማድረግ በመሞከርም መንገዱን ጀመረ።   የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚገፈውን መመሪያ የመቃወም እና እንዲስተካከል የማድረግ ሐላፊነት የሁሉም ኢትዮጵያዊ  ቢሆንም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት እንደ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካይ ባለቤት ሆኖ ጥያቄውን ለሚመለከታቸው አካላት እያደረሰ ለ18 ወራት ያክል ዘልቋል። በዚህ ጉዞውም ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሕብረት ጽ/ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፤ ከመጅሊስ እስከ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ ፤ ከሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እስከ ብልፅግና ጽ/ቤት ፤ ከሰላም ሚኒስቴር እስከ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ድረስ ተኪዷል። ለሁሉም አካላት የገቡት ደብዳቤዎች ይዘት ሲጠቃለል "በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰቶች እየደረሱ ነው። በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ፍትሐዊ መፍትሔ ይምጣ።" የሚል ነበር። ሆኖም ከዩኒቨርሲቲው በኩል የሗላሗላ ሲሰጡ የነበሩት ምላሾች "አናውቃችሁም! አንወያይም!" የሚሉ ሲሆን ለሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እና መሠረታዊ መብቶች እውቅናን የነፈገ እንዲሁም ክብር የጎደለው ነበር። የአብዛኛው መስሪያ ቤት ምላሽም ዝምታ እና ቸልተኝነት ነበር።     ከዚህም ባሻገር በዳይ ከሳሽ ሆኖ ዩኒቨርሲቲው የሙስሊም ተማሪዎችን አመራሮች "የዩኒቨርሲቲውን ስም በማጥፋት!" በሚል ርዕስ ስለመብት መጠየቅ እና መሞገትን ከስም ማጥፋት በመቁጠር የዲስፕሊን ክስ ከፍቶባቸዋል። በተለያየ ጊዜም የሕብረቱ አመራሮች ላይ ማስፈራሪያ አከል ማስጠንቀቂያዎችን ሲሰጧቸው ነበር። የመብት ጥያቄዎቹ ሲነሱ እና በደንብ እየተጠየቁ ሲሄዱ ብሎም የሁሉም ሙስሊም ተማሪ አጀንዳ እንደሆኑ በግልፅ እየታወቀ ሲመጣ ደግሞ ሙስሊም ተማሪዎች ተሰባስበው እንዳይወያዩ እስከመከልከል ድረስ ተዘልቋል። በመጋቢት አንድ ቀን የተፈጠረውም ይሄው ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን መልዕክቶች ለማስተላለፍ እንወዳለን። ለተማሪዎቻችን፦ ስንነሳ እንዳሳወቅነው ይህ ሁሉ ረጂም ጉዞ እና ትግል ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መመሪያ ምክንያት ነው። ስንነሳ ስለመመሪያው፣ ስለ ሰብዓዊ መብቶቻችን፣ ስለ ሐይማኖት ነፃነታችን ፣ ስለ ሕገ-መንግስታችን ፣ ስለ ዩኒቨርሲቲያችን እና ስለ ሀገራችን የነገ እጣፋንታ ጥያቄ አለን በማለት ነው። ፍላጎታችንም ሕገ- መንግስታዊ እና ፍትሐዊ መልስ ብቻ ነው። ለዚህ ሲባል ብዙ ለፍተናል፣ ከፍለናልም። ልናረጋግጥላችሁ የምንፈልገው ነገር ቢኖር ፍትሕ ሰፍኖ መመሪያው እስኪሻሻል ድረስ በምንም መንገድ ጥያቄያችን እንደማይቆም ነው። ለሚወሩ እና ለሚነዙ አሉባልታዎች ጆሮ አትስጡ። አጀንዳ ለማስቀየር ለሚራወጡ አውርቶ አደሮች ልባችሁን ክፍት አታድርጉ። የያዝነው የትውልድ አደራ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ከዚህ ትውልድ አይሻገርም። መነሻችን እንደሆነው ሁሉ እስከመጨረሻውም በዚሁ እንፅና። በአላህ ፈቃድ ድሉ ቅርቡ ነው። እስከዚያው ግን ምንም አይነት መረጃዎች እና ማምታቻዎች ሲያጋጥሟችሁ ለካምፓስ ጀመዓ አሚሮች ታሳውቁና መረጃዎችን በማጥራት ለምናደርገው ሰላማዊ የመብት ጥያቄ አስተዋፅዖ ታደርጉ ዘንድ ጥሪያችን ነው። ቀጣይ ሂደቶችን እና የሚጠበቁ እንቅስቃሴዎችንም በቶሎ የምናሳውቅ ይሆናል። ለሚመለከታቸው ሁሉ፦ አጀንዳችን የመብት እና መብት ብቻ እና ብቻ እንደሆነ እወቁ። የተማሪ አመራሮችን ማስፈራራት፣ መውቀስ ብሎም ስም መስጠት አላስፈላጊ የሕዝብ ጊዜ እንዲባክን ከማድረግ ውጪ መፍትሔ አይሆንም። እየተነሳ ያለው ስለ ሕገ- መንግስታዊ መብት ነውና በውይይት መፍትሔ መጥቶ የተሻለ ልምምድ እንዲኖረን ለማድረግ እና ተማሪዎች ትኩረታቸውን በትምህርታቸው እና በሌሎች ሀገራዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ እንዲያደርጉ በማገዝ ሀላፊነታችሁን በመወጣት ለሀገር ሊደረግ የሚችለውን ትንሹን ነገር ታደርጉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ጥያቄ አለን! መልስ እንፈልጋለን!! አላህ ለሀገራችን የተሻለ ጊዜን ያምጣ!!! @aaumsu

For those who do not know the location.