5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 159
Subscribers
-124 hours
-37 days
+230 days
Posts Archive
Repost from AAU - Muslim Students Union
+5
በታላቁ መሪ ንጉስ አባጅፋር ስም የተሰየመውን "ቻሌንጅ 7" በመቀበል፣ መብታችሁን ለማስከበርና ድምፃችሁን ለማሰማት እያሳያችሁት ያለው ቁርጠኝነት እጅግ የሚያስመሰግን ነው። በፌስቡክ ገጹ ላይ እየሰጣችሁት ያለው አስተያየትና መረጃዎችን የማጋለጥ ተግባር፣ ለውጥ የሚመጣው በተደራጀና በሰላማዊ ትግል መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል።
እስካሁን አስተያየታችሁን የሰጣችሁና ስክሪንሾት በመላክ ተሳትፏችሁን ያረጋገጣችሁ ጀግኖች፣ ለፍትህ የምታደርጉት ጉዞ የብዙዎችን ልብ እያነሳሳ ነው። ይሁን እንጂ ትግላችን ግቡን እንዲመታ ድምፃችን ከዚህ በላይ መጎላት ይኖርበታል። ሌሎች ተማሪዎችና የፍትህ ፈላጊዎችም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም፣ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የመብት ረገጣና የአመራር ብቃት ጉድለት ለአለም እንዲታወቅ በማድረግ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናድሳለን። ዝምታ ለበደል እውቅና መስጠት በመሆኑ፣ አሁኑኑ ሊንኩን በመጫን "ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!" የሚለውን ድምፃችሁን አሰሙ። አስተያየታችሁን ስክሪንሾት በማንሳት በቦታችን መላክ አትርሱ፤ የእናንተ ተሳትፎ የነገውን ብሩህና ፍትሃዊ የዩኒቨርሲቲ ህይወት ይወስናል።
ድል ለፍትህ!
@aaumsu
💥የአያሙል ቢድ ጾም ነገ ረቡዕ ይጀምራል!💥
➡️ ነቢዩ (ﷺ) በየወሩ ሶስት ቀናትን መጾም ለሚፈልግ ሰው፤ በጨረቃ አቆጣጠር 13ኛ፣ 14ኛ እና 15ኛ ቀናትን እንዲጾም መክረዋል። [ቲርሚዚና ነሳኢ]
🖊 እነዚህ ቀናት ጨረቃ ሙሉ ሆና በምትታይበት ብርሃናማ ሌሊቶች ምክንያት "አያሙል ቢድ" (ነጭ ቀናት) ይባላሉ። በእነዚህ ቀናት መጾም በሱና ደረጃ እጅግ የተወደደና ትልቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው።
☑ የሸዋል ወርም ግማሽ ልንደርስ ነው ፤ የስድስቱ ቀናት ጾም በሮች ግን አሁንም ክፍት ናቸው።እስካሁን 6ቱን የሻዋል ቀናት ያልጾመ ከነዚህ አያሙል ቢድ ቀናት ጋር አንድ ላይ ነይቶ በመጾም የተደራረበ ምንዳን ሊያገኝ ይችላል ። በረመዳን ያገዘን ጌታ ኒያ ካለን አሁንም ያግዘናል። የአላህን ውዴታ ለማግኘት እነዚህ ቀናት ጥቂት ናቸው!
አላህ በሐዲሰል ቁድሲይ እንዲህ ይላል፦ "ባሪያዬ በትርፍ ስራዎች (በነዋፊል) ወደ እኔ መቃረቡን አይተውም፣ እኔ እስክወደው ድረስ።"✨💫ክቡራት ሆይ! የአላህን እገዛ ጠይቁ፤ እነዚህን ታላቅ ቀናት መጾም እንዳትዘነጉ። አላህ ለታዛዥነቱ ይምራን! አላህ ይወፍቀን!
💥 ደርስ ማስታወሻ :::::::::::::::::::::::
🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋
✅ ኢንሻአላህ ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል ::
📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ
⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/672
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/Qirat4k
🔖አንድ ሰው ወደ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ መጥቶ "እከሌ እንዲህ ስሰድብህ ነበር" አለው። እርሳቸውም፦ "ያ የሱ መዝገብ ነው፤ በፈለገው ነገር ይሙላው" አሉ።
👉አንድ ሰው ወደ ወህብ ኢብኑ ሙነቢህ መጥቶ "እከሌ ይሳደብህ ነበር" አለው። እርሳቸውም፦ "ሼይጣን ካንተ ዉጭ ሌላ መልዕክተኛ አላገኘም ነበር ወይ?!" አሉት ።
🎯አንድ ሰው ለአንድ ሰው "እከሌ ሰደበህ" ቢለው ስነግረው ፣ እንዲህ ሲል መለሰ፦ "እሱ ቀስት ወርውሮብኝ ነበር፤ ነገር ግን አልመታኝም፤ ታዲያ ለምን ቀስቱን አንስተህ ልቤ ውስጥ ትሰካዋለህ?"
✍አንድ ሰው ወደ ኢማሙ ሻፊዒይ መጥቶ "እከሌ በክፉ ያነሳሃል" አለው። እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦ "እውነት ከሆነ (አሚያማ) ሰው ነህ፤ ውሸት ከሆነ ደግሞ ወንጀለኛ (ፋሲቅ) ነህ።" ያ ሰውም አፍሮ ተመለሰ።
🤲አላህ ከወሬና ከነገር (ከቂል ወል-ቃል) ይጠብቀን።
👋👋اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
እስከ አሁን ቴምር ያልወሰዳችሁ እህት፣ወንድሞች የፊታችን እሁድ, መጋቢት 27 (April 05) የመጨረሻ ቀን ስለሆነ እስከ እሁድ ድርስ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለወንዶች
👉ዶርም ያላችሁ B block ዶርም ቁጥር 302 መታችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እንዲሁም የማይመቻችሁ በዚ ስልክ ደውሉ
0905877461
ለሴቶች
👉ዶርም ያላችሁ የሴቶች ዶርም C block ዶርም ቁጥር 115 ወይም 407 መጣችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እና ለማይመቻችሁ በዚህ ቦት @fivekjemaa_bot አናግሩን ።
ቻሌንጅ 7 — የንጉስ አባጅፋር ልጆች ለዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ!
ንጉስ አባጅፋር ለፍትሕ ፀንተው በመቆም እና በጥበብ በመታገል የሚታወቁ ታላቅ መሪ ናቸው። ዛሬም በእርሳቸው ስም በሰየምነው በዚህ ቻሌንጅ፤ ፍትሕን በማጓደልና ሃይማኖታዊ መብታችንን በመጣስ ላይ ስላሉት የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ድምፃችሁን በንቃት ታሰሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና መላው የፍትህ ፈላጊዎች ሆይ!
በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲያችን ከፍተኛ አመራር ደረጃ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ከሀገሪቱ ሕገ-መንግሥትም ሆነ ገዥው ፓርቲ በይፋ ከሚያራምደው "መደመር" እና የውይይት ባህል ጋር በእጅጉ የሚጋጩ ሆነው አግኝተነዋል። የዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አመራር የተማሪዎችን ሃይማኖታዊ መብቶች የሚጥስ መመሪያ ከማውጣት ባለፈ፣ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የሚቀርቡ አማራጮችን ሁሉ በዝግተኝነትና በእምቢተኝነት አልፏቸዋል። እንዲህ ዓይነት የውይይት በር የዘጉ እና መሠረታዊ የዜጎችን መብት የረገጡ ግለሰቦች ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ሆነው መቅረባቸው እጅግ የሚያስገርም ብቻ ሳይሆን፣ ፓርቲው ለዜጎች መብትና ለሙስሊም ተማሪዎች ያለውን ትክክለኛ አቋም ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ነው።
ስለሆነም ዝምታ መፍትሄ አይሆንም! መብታችን የሚከበረው ድምፃችንን በአንድነት ስናሰማ ብቻ በመሆኑ፣ ሁላችሁም የቀረበውን የፌስቡክ ሊንክ https://www.facebook.com/reel/1529200765593420/?app=fbl በመጫን በቪዲዮው ስር እየተፈጠረ ያለውን የመብት ጥሰት እና የአመራር ብቃት ጉድለት በማጋለጥ፣ "ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!" የሚል አስተያየታችሁን (Comment) እንድታሰፍሩ እናሳስባለን። ፍትህ እንዲሰፍንና ብሶታችን ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ! በመጨረሻም የጻፋችሁትን አስተያየት ስክሪንሾት (Screenshot) በማንሳት በቦታችን @Niqab_issueBot በኩል ላኩልን። ድል ለፍትህ!
©aaumsu
@fivekjemaa
👋👋اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
እስከ አሁን ቴምር ያልወሰዳችሁ እህት፣ወንድሞች የፊታችን አርብ, መጋቢት 25 (April 03) የመጨረሻ ቀን ስለሆነ እስከ አርብ ድርስ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለወንዶች
👉ዶርም ያላችሁ B block ዶርም ቁጥር 302 መታችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እንዲሁም የማይመቻችሁ በዚ ስልክ ደውሉ
0920151033
ለሴቶች
👉ዶርም ያላችሁ የሴቶች ዶርም C block ዶርም ቁጥር 115 ወይም 407 መጣችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እና ለማይመቻችሁ በዚህ ቦት @fivekjemaa_bot አናግሩን ።
🍂ያልተቋረጠው ሰንሰለት🍂፦ ከረመዳን ጾም ወደ እውቀት ብርሃን
••አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ••
📢 ልዩ የዳዕዋ ጥሪ (Special Daewa Call)
💭..የእውቀት ማዕድ ተዘርግቷል፤ የሂዳያ መንገዶችም ተከፍተዋል። የረመዳን ወር በታላቅ ትውስታ ተሸኝቷል፤ ነገር ግን ለአማኝ ሙስሊም የአንዱ ዒባዳ መጠናቀቅ የሌላኛው ዒባዳ መጀመሪያ ነው!! ነፍሳችንን በጾምና በሶላት ስናንጻት እንደቆየን ሁሉ፣ አሁን ደግሞ አቅላችንንና ልባችንን በኪታቦች ብርሃን የምናክምበት ወቅት ላይ ደርሰናል። የጀነት መንገድ እውቀትን ከመፈለግ ይጀምራል!!
በመሆኑም የስድስት ኪሎ ጀምዓ የዳዕዋና ቂርኣት ዘርፍ መጪው ማክሰኞ ታላቅና ልዩ የሆነ የሴሚስተር ደርስ መክፈቻ ፕሮግራም በማሰናዳት በደስታ ጋብዟችኋል።
🎙 የዳዕዋ ፕሮግራም፦ የመንፈስ ስንቅ
🍃በተወዳጁ ሸይኻችን ሸይኽ ዓብዱረሒም ስለ እውቀት ሚና ልዩ ዳዕዋ ይጠብቀናል ኢንሻአላህ።
📚 የቂርኣትና የኪታቦች ማስተዋወቂያ
በዚህ ሴሚስተር ምን ኪታቦችን እንቀራለን? የትምህርት ይዘቶች በዝርዝር የምናስተዋውቅበትና ለተማሪዎች የምዝገባ ሁኔታዎችን የምናመቻችበት ልዩ ዝግጅት ነው።
📅 ቀን፦ ማክሰኞ፤ ሸዋል 12/ 1447 ዓ.ሒ
⏰ ሰዓት፦ ከመጝሪብ እስከ ኢሻ
📍 ቦታ፦ አል አቅሷ መስጂድ
👉እንኳን መቅረት ማርፈድ አይታሰብም!
©Qireat6k
@fivekjemaa
✅ ከሰለፎች አንደበት
አንድ ቀን ዑመር ቢን አብዱልዓዚዝ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ የሚል ኹጥባ (ንግግር) አደርጉ፦
﴿أيها الناس، أصلحوا آخرتكم تصلح لكم دنياكم، وأصلحوا سرائركم تصلح لكم علانيتكم﴾
“እናንተ ሰዎች ሆይ! የአኼራ ጉዳያችሁን የተስተካከለ አድርጉ፤ ለናንተ ደግሞ ዱኒያችሁ የተስተካከለ ይሆንላችኋል። ውስጣችሁን አስተካክሉ፤ ለናንተ ደግሞ ላያችሁ የተስተካከለ ይሆንላችኋል።”
📚አል‐ቢዳያ ወኒሃያ፡ 12/692
©
🔥 ከ ሙተነቂቦች መንደር~4🔥[የመጨረሻ ክፍል]
••ግቢው ፊቱን አዙሯል!!
የ presidentu መግለጫ ግልጽ እና ጎዶሎ ሃሳብ ይታወቃል፣ የጥበቃዎች የፊት መቀያየር ከዱላ በላይ ይጋረፋል(አሏህ ከፊቶች መቀያየር ይጠብቃቹ 😊ያየው ያውቀዋል)።
"Ict officeru•• አው, Ict officeru" አልኩኝ በውስጤ, ከአሏህ በታች ብቸኛ ጊዜያዊ መፍትሄ ምናገኝበት እንደሆነ ስላሰብኩ ምን እንደምንለው እያሰላሰልኩ ፈተናዬን ጨርሼ ወጣው። ከ 2 እህቶች ጋር ገባን፣ officerum ነጻ ሰው ይመስላል፣ ቢያስተካክልልን እንኳን ውለታ እንደዋለ ሳይሆን መብቴ እንደሆነ እንዲሰማው.....እንደገባን ከሰላምታ ቡሃላ scanneru እየሰራልን እንዳልሆነ ነገርኩት አትሉም😄
"ለምን ??!" ሲል ..
እህቶች ጨማመሩበት! በ አይን ብቻ እንዲው scan ተደርጎ እንድንገባ አድርግልን፣ ጥበቆች ጋ ክርክር ውስጥ እየገባን ነው አልነው፣ 1,1 ጥያቄ ጨማምሮልን መጨረሻ ላይ አስተካክሎልን ከነ ኒቃባችን ዐይን ብቻ scan እያረግን ገባን። ያም ለጊዜው temporary መፍትሄ ሆነ። still ግን ማሽኑ ዐይን scan የማረግ አቅም የለውም ያስቸግራል..
እንደው ታሪክ ቢዘረዘር አያልቅም አይደል ??! እኔም ከማስረዝም እናንተንም ጠይቁ፦ ውድ የኢስላም ወገኖች!!
🍂ምን ተማርሽ? ምን ተሰማሽ እያላቹ ነው አይደል?
1⃣ የእሳት ፍም እያጋላቹ የናንተ ውድ ሰው እሳት ውስጥ ገብቶ ሲቃጠል አይቶ ማዘንና ለመርዳት መሞከር ሰብኣዊነት ነው!!! ከፍሙ በላይ ግን ውስጥ ገብታቹ እየተቃጠላቹ እንደሆነ አስቦ መላ መፈለግ ደሞ ሰብኣዊነትን ማድመቅ ሚችለው ኢስላማዊነት ነው !!!!
አደራ በሁሉም እንቅስቃሴያችን ሙስሊምነታችን ትዝዝዝ ይበለን!! ማድረግ ምንችለው ምንም ትንሽ ነገር እንዳያመልጠን ይቆጨናል!!
2⃣ ስለ ኒቃብ ግር ላለው ሁሉ it is all about thinking and humanity እንዲህ ተሸፋፍና በዚህ ጸሃይ አይሞቅሽም ወይ ብሎ ሚያስብ ሁሉ እንዲህ ተገላልጠሽ በዚህ ብርድ አይበርድሽም ወይ ብሎ ቢያስብስ??🧐
ድሮ በጣም ድሮ •• 😄
አንዷ ጥቁር ምትለብሱት ሴቶች በኢስላም ሁሌ ሃዘን ላይ ስለሆናቹ ነው ስትለኝ፣ አይ እንደ ባለጋወን ተመራቂዎች ደስታ ላይ ስለሆንን ነው ያልኩት ትዝዝ አለኝ.......
3⃣ አንዱ እንዳለው niqab is psychological fence ✨ አው ኒቃብ አጥር ነው; ሰው ከውበት በላይ አስተሳሰብን ይመርጥ እንደሆነ መለያ አጥር!! ሰው ከስሜታዊነት በላይ ሰበኣዊነትን ሚለይበት አጥር !!
ሻይ ☕️ ከቅጠሉ እንደሚጠለለው ሁሉ ኒቃብ ማጥለያም ነው!! በዚህ ሰውን መለየት ከባድ በሆነበት ዘመን ሰዉን ለይቶ ፊትህ ያቀርብልሃል። ቅጠል የሆነውን አስወግዶ ሃሳብህን እንጂ ሌላ ነገርህን ማይፈልገውን ሰብኣዊ ሰው ፊትህ ያቆምልሃል!!
እንደዛ ባይሆን ኖሮ ባለፈው አንዱ ጥበቃ ልብስሽን አስተካክለሽ ነይ እንዲህ አይገባም ሲለኝ፣ አንዷ ጥበቃ ዝም ብለሽው ግቢ ባላለችኝ ነበር !!
እንደዛ ባይሆን ኖሮ taxi ውስጥ አንዱ ምስኪን ሃሳቡ በወላጆች ስራ የተመረዘበት ህጻን ከኔጋ ሊጫወት ዞር ሲል መሸፋፈኔን አይቶ ሲፈራኝ አንዷ ማላቃት ሌላ ምስኪን እዛው taxi ውስጥ ሊወልቅ የቀረበውን ጓንቴን ባላለበሰችኝ ነበር !!
አዎ ኒቃብ ሃይማኖታዊ መብቴ ነው ግን እንዳንረሳ ሰዋዊ የሆነ መብቴም ጭምር ነው !!
ኒቃብ የሰብኣዊነት መብቴ ነው!! ሲበርዳት ያልደረበላት ግድ የለም ይሙቅሽና ላውልቅልሽ ብሎ አደለም ሊጠጋኝ ሊያስብም አይገባም⚠️
አዎ ጥያቄ አለን !!
ጥያቄያችን ደግሞ ሃይማኖታዊም ሰብኣዊም መብታችን ነው‼️‼️
©aaumsu
✴️ኢማሙ አል-ፉደይል ቢን ኢያድ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
🔵«ትዕግስትን ከአንድ ትንሽ ልጅ ተማርኩ!
አንድ ቀን ወደ መስጂድ እየሄድኩኝ ሳለ አንዲት ሴት በቤቷ ውስጥ ልጇን ስትመታው አገኘሁ፤ ልጁም እየጮኸ በሩን ከፍቶ አመለጣት፣ እሷም በሩን ዘጋችበት።
🔵ከዚያም ስመለስ ተመለከትኩ፤ ልጁ ጥቂት ካለቀሰ በኋላ የእናቱን እዝነት በመፈለግ በቤቱ ደፍ (መግቢያ) ላይ ተኝቶ አገኘሁት። የናትየውም ልብ ተራርቶ በሩን ከፈተችለት።»
🔴በዚህ ጊዜ ፉደይል ፂማቸው በእንባ እስኪርስ ድረስ አለቀሱና እንዲህ አሉ። «ሱብሐን አላህ! የአላህ ባሪያ በአላህ በር ላይ ቢታገስ ኖሮ፣ አላህ በእርግጥ ይከፍትለት ነበር...!»
✴️አቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል፦
«በዱዓእ በርቱ፤ የጌታውን በር ደጋግሞ የሚያንኳኳ ሰው ሊከፍትለት ይቀርባል።»
(ሙሰነፍ ኢብኑ አቢ ሸይባህ፡ 6/22)
©IbnAbidunyaa
📢 Today's program is not just a dawah program…🔥🔥🔥
👉 It’s knowledge.
👉 It’s a reset for your iman.
👉 And yes… there’s more.
🎁 Bonus:
• Q&A session
• 🎉 Mobile card prizes for winners
• 🍽 Refreshments available
❗ Missing this is not an option.
🤝 Be there.
📢🌟 🌟FINAL REMINDER – TODAY🌟🌟
Don’t miss this opportunity.
Allah says:
“So remain steadfast as you have been commanded…”
(Qur’an 11:112)
The Prophet ﷺ said:
“The most beloved deeds to Allah are those that are consistent, even if small.”
📚 (Sahih al-Bukhari, Sahih Muslim)
👉 After Ramadan… this is your test.
👉 Will you stay firm… or fall back?
🎙 Grand Dawah Program – TODAY
• Our Mission as a Muslim Student— Ustaz Hussein Yousef
• Istiqamah After Ramadan — Ustaz Zanjabil
📍 4 Kilo Masjid
🕔 After Zuhr
🤝 Be there. Don’t miss what your heart needs.
🤲 May Allah keep us steadfast.
Repost from AAU - Muslim Students Union
+4
በሙጃሂድ ጦልሃጀዕፈር ስም ያቀድነውን የሚዲያ ዘመቻ ጀምረናል ! ! !
በመጀመሪያው ዙር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የሰብዓዊ እና ሀይማኖታዊ መብት ጥሰት ለአልጀዚራ አረብኛ፤ ለአልጀዚራ እንግሊዝኛ፤ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ (VOA)፤ ለአምኔስቲ ኢንተርናሽናል ( Amnesty International ) እና ለDocumenting Oppression Against Muslims (DOAM) በኢሜይል ድምፃችንን አሰምተናል።
እየጀመርን ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሁላችሁም የምትሳተፉበት መድረክ ይኖራል። በቅርቡም እናሳውቃለን። እስከዚያው ግን ዝግጁ ሆናችሁ ጠብቁን። ተጀምሮ የሚቀር፤ ተሸፋፍኖ የሚታለፍ ጥያቄ የለንም። እየደረሱ ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በሁሉም መድረክ እያጋለጥን ስለ ፍትሕ ከፍ ባለ ድምፅ እንጠይቃለን። ይህንን ማድረግ የዚህ ትውልድ ሀላፊነት ሆኗልና እንደጀመርነው የምንጨርስ ይሆናል።
አይደለም ወይ ያኡመተ ሙሐመድ? አይደለም ወይ እህቴ? አይደለም ወይ ወንድሜ?
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
📢 Grand Dawah Program
As we continue our journey as students and reflect after the blessed month of Ramadan, the 5 Killo Jamma’ah warmly invites you to a special program focused on spiritual growth and purpose.
This gathering aims to strengthen our faith, renew our intentions, and help us remain steadfast throughout the year.
🎙 Sessions & Speakers
Topic I: Our Mission as a Muslim Student
• Speaker: Ustaz Hussein Yousef
• Balancing academic excellence with Islamic identity and responsibility toward the Ummah.
Topic II: Istiqamah (Steadfastness) After Ramadan
• Speaker: Ustaz Zanjabil
• Practical ways to maintain the روح of Ramadan in our daily lives.
🪧 Event Details
📅 Date: Saturday, March 28
🕔 Time: After Zuhr Prayer
📍 Venue: 4 Kilo Masjid (UPDATED)
⚠️ Please note the change of venue. We sincerely apologize for any inconvenience caused.
🤝 All brothers and sisters are warmly invited to attend.
🤲 May Allah grant us beneficial knowledge and steadfastness.
﴿رَّبِّ ٱغۡفِرۡ لِی وَلِوَ ٰلِدَیَّ وَلِمَن دَخَلَ بَیۡتِیَ مُؤۡمِنࣰا وَلِلۡمُؤۡمِنِینَ وَٱلۡمُؤۡمِنَـٰتِۖ وَلَا تَزِدِ ٱلظَّـٰلِمِینَ إِلَّا تَبَارَۢا﴾ [نوح ٢٨]
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም አማኝ ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው፤» (አለ)፡፡ [ሱረቱ ኑሕ: 28]
👉ይህ አንቀጽ አማኞች ለራሳቸው፣ ለቤተሰቦቻቸዉና ለጠቅላላው የሙስሊም ማህበረሰብ ሁልጊዜ ዱዓ ማድረግ እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት ይሰጣል።
👉ከረመዳን በኃላ መች ይሁን ዱዓ ያደረግነው??? ዛሬ ጁምዓ ነው ከአስር በኃላ በዱዓ እንበርታ!!
@fivekjemaa
