5killo Jem'a official Channel
رفتن به کانال در Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
نمایش بیشتر1 160
مشترکین
-124 ساعت
+27 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
👋👋اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
እስከ አሁን ቴምር ያልወሰዳችሁ እህት፣ወንድሞች የፊታችን አርብ, መጋቢት 25 (April 03) የመጨረሻ ቀን ስለሆነ እስከ አርብ ድርስ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለወንዶች
👉ዶርም ያላችሁ B block ዶርም ቁጥር 302 መታችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እንዲሁም የማይመቻችሁ በዚ ስልክ ደውሉ
0920151033
ለሴቶች
👉ዶርም ያላችሁ የሴቶች ዶርም C block ዶርም ቁጥር 115 ወይም 407 መጣችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
👉ዶርም የሌላችሁ እና ለማይመቻችሁ በዚህ ቦት @fivekjemaa_bot አናግሩን ።
🍂ያልተቋረጠው ሰንሰለት🍂፦ ከረመዳን ጾም ወደ እውቀት ብርሃን
••አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ••
📢 ልዩ የዳዕዋ ጥሪ (Special Daewa Call)
💭..የእውቀት ማዕድ ተዘርግቷል፤ የሂዳያ መንገዶችም ተከፍተዋል። የረመዳን ወር በታላቅ ትውስታ ተሸኝቷል፤ ነገር ግን ለአማኝ ሙስሊም የአንዱ ዒባዳ መጠናቀቅ የሌላኛው ዒባዳ መጀመሪያ ነው!! ነፍሳችንን በጾምና በሶላት ስናንጻት እንደቆየን ሁሉ፣ አሁን ደግሞ አቅላችንንና ልባችንን በኪታቦች ብርሃን የምናክምበት ወቅት ላይ ደርሰናል። የጀነት መንገድ እውቀትን ከመፈለግ ይጀምራል!!
በመሆኑም የስድስት ኪሎ ጀምዓ የዳዕዋና ቂርኣት ዘርፍ መጪው ማክሰኞ ታላቅና ልዩ የሆነ የሴሚስተር ደርስ መክፈቻ ፕሮግራም በማሰናዳት በደስታ ጋብዟችኋል።
🎙 የዳዕዋ ፕሮግራም፦ የመንፈስ ስንቅ
🍃በተወዳጁ ሸይኻችን ሸይኽ ዓብዱረሒም ስለ እውቀት ሚና ልዩ ዳዕዋ ይጠብቀናል ኢንሻአላህ።
📚 የቂርኣትና የኪታቦች ማስተዋወቂያ
በዚህ ሴሚስተር ምን ኪታቦችን እንቀራለን? የትምህርት ይዘቶች በዝርዝር የምናስተዋውቅበትና ለተማሪዎች የምዝገባ ሁኔታዎችን የምናመቻችበት ልዩ ዝግጅት ነው።
📅 ቀን፦ ማክሰኞ፤ ሸዋል 12/ 1447 ዓ.ሒ
⏰ ሰዓት፦ ከመጝሪብ እስከ ኢሻ
📍 ቦታ፦ አል አቅሷ መስጂድ
👉እንኳን መቅረት ማርፈድ አይታሰብም!
©Qireat6k
@fivekjemaa
✅ ከሰለፎች አንደበት
አንድ ቀን ዑመር ቢን አብዱልዓዚዝ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ የሚል ኹጥባ (ንግግር) አደርጉ፦
﴿أيها الناس، أصلحوا آخرتكم تصلح لكم دنياكم، وأصلحوا سرائركم تصلح لكم علانيتكم﴾
“እናንተ ሰዎች ሆይ! የአኼራ ጉዳያችሁን የተስተካከለ አድርጉ፤ ለናንተ ደግሞ ዱኒያችሁ የተስተካከለ ይሆንላችኋል። ውስጣችሁን አስተካክሉ፤ ለናንተ ደግሞ ላያችሁ የተስተካከለ ይሆንላችኋል።”
📚አል‐ቢዳያ ወኒሃያ፡ 12/692
©
🔥 ከ ሙተነቂቦች መንደር~4🔥[የመጨረሻ ክፍል]
••ግቢው ፊቱን አዙሯል!!
የ presidentu መግለጫ ግልጽ እና ጎዶሎ ሃሳብ ይታወቃል፣ የጥበቃዎች የፊት መቀያየር ከዱላ በላይ ይጋረፋል(አሏህ ከፊቶች መቀያየር ይጠብቃቹ 😊ያየው ያውቀዋል)።
"Ict officeru•• አው, Ict officeru" አልኩኝ በውስጤ, ከአሏህ በታች ብቸኛ ጊዜያዊ መፍትሄ ምናገኝበት እንደሆነ ስላሰብኩ ምን እንደምንለው እያሰላሰልኩ ፈተናዬን ጨርሼ ወጣው። ከ 2 እህቶች ጋር ገባን፣ officerum ነጻ ሰው ይመስላል፣ ቢያስተካክልልን እንኳን ውለታ እንደዋለ ሳይሆን መብቴ እንደሆነ እንዲሰማው.....እንደገባን ከሰላምታ ቡሃላ scanneru እየሰራልን እንዳልሆነ ነገርኩት አትሉም😄
"ለምን ??!" ሲል ..
እህቶች ጨማመሩበት! በ አይን ብቻ እንዲው scan ተደርጎ እንድንገባ አድርግልን፣ ጥበቆች ጋ ክርክር ውስጥ እየገባን ነው አልነው፣ 1,1 ጥያቄ ጨማምሮልን መጨረሻ ላይ አስተካክሎልን ከነ ኒቃባችን ዐይን ብቻ scan እያረግን ገባን። ያም ለጊዜው temporary መፍትሄ ሆነ። still ግን ማሽኑ ዐይን scan የማረግ አቅም የለውም ያስቸግራል..
እንደው ታሪክ ቢዘረዘር አያልቅም አይደል ??! እኔም ከማስረዝም እናንተንም ጠይቁ፦ ውድ የኢስላም ወገኖች!!
🍂ምን ተማርሽ? ምን ተሰማሽ እያላቹ ነው አይደል?
1⃣ የእሳት ፍም እያጋላቹ የናንተ ውድ ሰው እሳት ውስጥ ገብቶ ሲቃጠል አይቶ ማዘንና ለመርዳት መሞከር ሰብኣዊነት ነው!!! ከፍሙ በላይ ግን ውስጥ ገብታቹ እየተቃጠላቹ እንደሆነ አስቦ መላ መፈለግ ደሞ ሰብኣዊነትን ማድመቅ ሚችለው ኢስላማዊነት ነው !!!!
አደራ በሁሉም እንቅስቃሴያችን ሙስሊምነታችን ትዝዝዝ ይበለን!! ማድረግ ምንችለው ምንም ትንሽ ነገር እንዳያመልጠን ይቆጨናል!!
2⃣ ስለ ኒቃብ ግር ላለው ሁሉ it is all about thinking and humanity እንዲህ ተሸፋፍና በዚህ ጸሃይ አይሞቅሽም ወይ ብሎ ሚያስብ ሁሉ እንዲህ ተገላልጠሽ በዚህ ብርድ አይበርድሽም ወይ ብሎ ቢያስብስ??🧐
ድሮ በጣም ድሮ •• 😄
አንዷ ጥቁር ምትለብሱት ሴቶች በኢስላም ሁሌ ሃዘን ላይ ስለሆናቹ ነው ስትለኝ፣ አይ እንደ ባለጋወን ተመራቂዎች ደስታ ላይ ስለሆንን ነው ያልኩት ትዝዝ አለኝ.......
3⃣ አንዱ እንዳለው niqab is psychological fence ✨ አው ኒቃብ አጥር ነው; ሰው ከውበት በላይ አስተሳሰብን ይመርጥ እንደሆነ መለያ አጥር!! ሰው ከስሜታዊነት በላይ ሰበኣዊነትን ሚለይበት አጥር !!
ሻይ ☕️ ከቅጠሉ እንደሚጠለለው ሁሉ ኒቃብ ማጥለያም ነው!! በዚህ ሰውን መለየት ከባድ በሆነበት ዘመን ሰዉን ለይቶ ፊትህ ያቀርብልሃል። ቅጠል የሆነውን አስወግዶ ሃሳብህን እንጂ ሌላ ነገርህን ማይፈልገውን ሰብኣዊ ሰው ፊትህ ያቆምልሃል!!
እንደዛ ባይሆን ኖሮ ባለፈው አንዱ ጥበቃ ልብስሽን አስተካክለሽ ነይ እንዲህ አይገባም ሲለኝ፣ አንዷ ጥበቃ ዝም ብለሽው ግቢ ባላለችኝ ነበር !!
እንደዛ ባይሆን ኖሮ taxi ውስጥ አንዱ ምስኪን ሃሳቡ በወላጆች ስራ የተመረዘበት ህጻን ከኔጋ ሊጫወት ዞር ሲል መሸፋፈኔን አይቶ ሲፈራኝ አንዷ ማላቃት ሌላ ምስኪን እዛው taxi ውስጥ ሊወልቅ የቀረበውን ጓንቴን ባላለበሰችኝ ነበር !!
አዎ ኒቃብ ሃይማኖታዊ መብቴ ነው ግን እንዳንረሳ ሰዋዊ የሆነ መብቴም ጭምር ነው !!
ኒቃብ የሰብኣዊነት መብቴ ነው!! ሲበርዳት ያልደረበላት ግድ የለም ይሙቅሽና ላውልቅልሽ ብሎ አደለም ሊጠጋኝ ሊያስብም አይገባም⚠️
አዎ ጥያቄ አለን !!
ጥያቄያችን ደግሞ ሃይማኖታዊም ሰብኣዊም መብታችን ነው‼️‼️
©aaumsu
✴️ኢማሙ አል-ፉደይል ቢን ኢያድ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
🔵«ትዕግስትን ከአንድ ትንሽ ልጅ ተማርኩ!
አንድ ቀን ወደ መስጂድ እየሄድኩኝ ሳለ አንዲት ሴት በቤቷ ውስጥ ልጇን ስትመታው አገኘሁ፤ ልጁም እየጮኸ በሩን ከፍቶ አመለጣት፣ እሷም በሩን ዘጋችበት።
🔵ከዚያም ስመለስ ተመለከትኩ፤ ልጁ ጥቂት ካለቀሰ በኋላ የእናቱን እዝነት በመፈለግ በቤቱ ደፍ (መግቢያ) ላይ ተኝቶ አገኘሁት። የናትየውም ልብ ተራርቶ በሩን ከፈተችለት።»
🔴በዚህ ጊዜ ፉደይል ፂማቸው በእንባ እስኪርስ ድረስ አለቀሱና እንዲህ አሉ። «ሱብሐን አላህ! የአላህ ባሪያ በአላህ በር ላይ ቢታገስ ኖሮ፣ አላህ በእርግጥ ይከፍትለት ነበር...!»
✴️አቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል፦
«በዱዓእ በርቱ፤ የጌታውን በር ደጋግሞ የሚያንኳኳ ሰው ሊከፍትለት ይቀርባል።»
(ሙሰነፍ ኢብኑ አቢ ሸይባህ፡ 6/22)
©IbnAbidunyaa
📢 Today's program is not just a dawah program…🔥🔥🔥
👉 It’s knowledge.
👉 It’s a reset for your iman.
👉 And yes… there’s more.
🎁 Bonus:
• Q&A session
• 🎉 Mobile card prizes for winners
• 🍽 Refreshments available
❗ Missing this is not an option.
🤝 Be there.
📢🌟 🌟FINAL REMINDER – TODAY🌟🌟
Don’t miss this opportunity.
Allah says:
“So remain steadfast as you have been commanded…”
(Qur’an 11:112)
The Prophet ﷺ said:
“The most beloved deeds to Allah are those that are consistent, even if small.”
📚 (Sahih al-Bukhari, Sahih Muslim)
👉 After Ramadan… this is your test.
👉 Will you stay firm… or fall back?
🎙 Grand Dawah Program – TODAY
• Our Mission as a Muslim Student— Ustaz Hussein Yousef
• Istiqamah After Ramadan — Ustaz Zanjabil
📍 4 Kilo Masjid
🕔 After Zuhr
🤝 Be there. Don’t miss what your heart needs.
🤲 May Allah keep us steadfast.
Repost from AAU - Muslim Students Union
+4
በሙጃሂድ ጦልሃጀዕፈር ስም ያቀድነውን የሚዲያ ዘመቻ ጀምረናል ! ! !
በመጀመሪያው ዙር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የሰብዓዊ እና ሀይማኖታዊ መብት ጥሰት ለአልጀዚራ አረብኛ፤ ለአልጀዚራ እንግሊዝኛ፤ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ (VOA)፤ ለአምኔስቲ ኢንተርናሽናል ( Amnesty International ) እና ለDocumenting Oppression Against Muslims (DOAM) በኢሜይል ድምፃችንን አሰምተናል።
እየጀመርን ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሁላችሁም የምትሳተፉበት መድረክ ይኖራል። በቅርቡም እናሳውቃለን። እስከዚያው ግን ዝግጁ ሆናችሁ ጠብቁን። ተጀምሮ የሚቀር፤ ተሸፋፍኖ የሚታለፍ ጥያቄ የለንም። እየደረሱ ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በሁሉም መድረክ እያጋለጥን ስለ ፍትሕ ከፍ ባለ ድምፅ እንጠይቃለን። ይህንን ማድረግ የዚህ ትውልድ ሀላፊነት ሆኗልና እንደጀመርነው የምንጨርስ ይሆናል።
አይደለም ወይ ያኡመተ ሙሐመድ? አይደለም ወይ እህቴ? አይደለም ወይ ወንድሜ?
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
📢 Grand Dawah Program
As we continue our journey as students and reflect after the blessed month of Ramadan, the 5 Killo Jamma’ah warmly invites you to a special program focused on spiritual growth and purpose.
This gathering aims to strengthen our faith, renew our intentions, and help us remain steadfast throughout the year.
🎙 Sessions & Speakers
Topic I: Our Mission as a Muslim Student
• Speaker: Ustaz Hussein Yousef
• Balancing academic excellence with Islamic identity and responsibility toward the Ummah.
Topic II: Istiqamah (Steadfastness) After Ramadan
• Speaker: Ustaz Zanjabil
• Practical ways to maintain the روح of Ramadan in our daily lives.
🪧 Event Details
📅 Date: Saturday, March 28
🕔 Time: After Zuhr Prayer
📍 Venue: 4 Kilo Masjid (UPDATED)
⚠️ Please note the change of venue. We sincerely apologize for any inconvenience caused.
🤝 All brothers and sisters are warmly invited to attend.
🤲 May Allah grant us beneficial knowledge and steadfastness.
﴿رَّبِّ ٱغۡفِرۡ لِی وَلِوَ ٰلِدَیَّ وَلِمَن دَخَلَ بَیۡتِیَ مُؤۡمِنࣰا وَلِلۡمُؤۡمِنِینَ وَٱلۡمُؤۡمِنَـٰتِۖ وَلَا تَزِدِ ٱلظَّـٰلِمِینَ إِلَّا تَبَارَۢا﴾ [نوح ٢٨]
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም አማኝ ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው፤» (አለ)፡፡ [ሱረቱ ኑሕ: 28]
👉ይህ አንቀጽ አማኞች ለራሳቸው፣ ለቤተሰቦቻቸዉና ለጠቅላላው የሙስሊም ማህበረሰብ ሁልጊዜ ዱዓ ማድረግ እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት ይሰጣል።
👉ከረመዳን በኃላ መች ይሁን ዱዓ ያደረግነው??? ዛሬ ጁምዓ ነው ከአስር በኃላ በዱዓ እንበርታ!!
@fivekjemaa
🔥 Our Mission as a Muslim Student!!
You are not just a student.
You are a Muslim.
Allah says:
“My prayer, my sacrifice, my life and my death are for Allah…”
(Qur’an 6:162)
The Prophet ﷺ said:
“Whoever follows a path to seek knowledge, Allah will make a path to Paradise easy for him.”
📚 (Sahih Muslim)
Sufyan al-Thawri رحمه الله said:
“Nothing is harder on me than my intention.”
❓ What is your mission as a Muslim student?
* Dunya?
* Akhirah?
👉 Fix your mission… before your years pass.
📅 March 28 | After Zuhr
📍 Al Aqsa Masjid
🤝 Be there.
🎉ዛሬ ጁምአ ነው
በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉
إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّو
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﷺ
"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)
🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
"ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።"
ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልብአችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው።
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት ዱዓ ማድረግ (ከአስር በኋላ ኡማውን በዱዓ እናስታውስ)
በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️
اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
🔥ከ ሙተነቂቦች መንደር~4🔥 (ክፍል 2)
ግቢው ለዘመናዊ ቁጥጥሩ በቃ የታየው face scanner መግጠም ነበር።
እነ fingerprint የት ሄደው ??! እያላቹ ነው አደል?
በቃ ግቢዉ የታየው face scanneru ብቻ ነው no id , no fingerprint and ሌላም ምታስቡት አማራጮችን ማሰብ አልቻለም።
ከወደ ዋናው ግቢ ' ከላይ ሰፈር ' ከ6ኪሎ የ እህቶቼ የስቃይ ድምጽ ማስተጋባት ጀመረ። ታች 5ኪሎ ሆኜ ድምጻቸው ሲያስጨንቀኝ ትዝ ይለኛል። ከወጡ ስለማይገቡ መውጣት እንዳቆሙ ሰማሁ፣ ውስጤ እዝን; ድብር; እርር ይላል......
ደህና ነገር መቶ በቅርቡ ሰላም እንደሚሆኑ ሳስብ ጭራሽ cafe ላይም scanneru ተገጥሞ ገብቶ ለመጠቀም እየተቸገሩ እንደሆነ ስሰማ፣ ከዛ ደሞ ምንም አቅም እንደሌለኝ ሳስብ ልቤ ስብርርር እያለ ከአላህዬ መላው ይመጣ ዘንድ እጠብቅ ጀመርኩ።
እዛ ያለውን ሳስብ እዚህ ለካ ተደግሶልኛል፣ final እየተፈተንን ነበረ እዚህም face scanneru ተገጥሞ ስላለቀ ከነገ ጀምሮ መግባት አይቻልም ተባለ። እህቶቼ ቀኑን በትግል ረጅም ሰአት ተከራክረው እንደገቡ ነገሩኝ።
በሰአቱ ዶርም ውስጥ 3 ሆነን ለነገ ፈተና እያነበብን ነበር፣ ማን ማን አትሉኝም ?? ያቺ መጀመሪያ ያስተዋወኳቹ ኒቃቢስቷ ጓደኛዬ፣ እኔና፣ እኔ በለበስኩ በ 15 ቀኑ የለበሰችዋ እህቴ።
ሁለታችን አብረን ተቀምጠናል፣ pciw ደብተሩ ተከፍቷል ግን ውስጥ ያለው ለፈተና መዘጋጀት ሳይሆን ከነፍሲያ እና ሸይጧን ጋር እየታገልን ሃሳብ ስናወጣ ስናወርድ ነበር.....በጣም ሲብስብን ፈተናውን ረስተን እርስ በርስ ጭንቀታችንን እየተነጋገርን አብሽሪ!! አብሽሪ!! መባባል ጀመርን••
ራቅ ብላ ስታጠና የነበረችውም እህታችን መጣች፣ እኔም እኮ ስሜቴን ዋጥጥጥ!! አርጌ ለማንበብ እየሞከርኩ እንጂ ችዬ ሳነብ አልነበረም አለች፣ በዚህ ሰአት በሰላም ሚያነበው ህዝብ ትዝዝዝ አለኝ! ኒቃብ ሳለብስ እና ከለበስኩ ቡሃላ የተቀየሩብኝ የክላሥ ፊቶች በሰላም ተረጋግተው ሲያነቡ ውል አለብኝ, በቃ ከዛ ያረብብብ!!! አልኩኝ..
በጠዋቱ ያለመደብንን ካላስገቡን ፈተና እንዳያመልጠን አስበን ለመከራከሪያ ሚሆን ሰአት መድበን ቀደም ብለን ግቢ ሄድን፣ ከ እህቶች ጋር ተሰብስበን ግማሹ scanneru በሌለበት ግማሹ ደሞ scanneru በተገጠመበት በር እንደምንም እንድንገባ ተነጋገርን።
እኔ በscanneru በኩል ሊገቡ ካሉ እህቶች ጋ ነበርኩ ስሜቱን ልገልጽላቹ አልችልም ለምን አትሉም??!!ማስረዳት ከባድ ነው፣
እራሴን አመመኝ ሲሉ መስማትና ራስን መታመም እኩል ነው??!!
ብቻ scanneru ጋር ቆሜ አንድ ተለቅ ያሉ ጥበቃ መጡና እያጉረመረሙ id check እያረጉ "አስተካክሉ!! አሁን እናንተ ምንድነው ምትደረጉት?!!" እያሉ አስገቡን።
ሰውነቴ እሳት ውስጥ የገባ ያህል ተቃጠለ ውስጤ ያለው ንዴት ምንም ማረግ ካለመቻል ቢያንስ ጊዜያዊ መፍትሄ ማምጣት እንዳለብኝ አስረግጦ ነገረኝ!!! የclassun ፈተና ከጎን ብለን ለዚህ ዋና ፈተና ጊዜያዊ መፍትሄ ማሰብ ጀመርን፣ ከእህቶች ጋርም ተመራርጠን አነስ ብለን ICT officerun ለማግኘት እና እሱን ለማውራት ተነጋግረን ወደ ፈተና ክፍላችን ገባን!
••ሌላው 1 የፈተና ወረቀት ይዞ ሲፈተን፣ የኔ ፈተና ደሞ 2 ነበር። 1 የያዝኩት ወረቀት እና 1 ደሞ ስወጣ ምን እንደማረግ እያሰብኩት ያለው ፈተና .....
©aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
AAU የኮሜንት ሳጥኑን ዳግም ዘግቶታል። ትላንት በነበረው ፖስት ላይ ተማሪዎች ሐሳባቸውን ለማስፈር በመሞከራቸው በዛሬው እለት ያለው ፖስት ላይ የሐሳብ መስጫ ሳጥኑ ተዘግቷል። ይህ ስለ የሐሳብ ነፃነት፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት ከሚያስተምር የልሕቀት ማዕከል የማይጠበቅ እና ለተቋማችን ስም የማይመጥን ተግባር ነው። ሐሳብን በመሸሽ የሚመጣ ለውጥ የለም። ሐሳብን በሐሳብ በመሞገት ስልጡን በሆነ መንገድ የማህበረሰቡን ጥያቄ ማስተናገድ ግዴታ ነው።
በምንም መልኩ ቢሆን ጥያቄያችን አይቆምም። ዛሬም ነገም ጥያቄ አለን እንላለን። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ድረስ ጥያቄያችንን እንቀጥላለን።
አይደለም ወይ?!
@aaumsu
🔥 The Real Loss After Ramadan
The Prophet ﷺ said:
“The most beloved deeds to Allah are those that are consistent, even if small.”
📚 (Sahih al-Bukhari, Sahih Muslim)
Ramadan made you strong
You prayed.
You remembered Allah.
You felt alive again.
But after Ramadan?
👉 Many people collapse.
Not because they can’t continue…
But because they never built 'istiqamah'
Allah says:
“So remain steadfast as you have been commanded…”
(Qur’an 11:112)
Al-Hasan al-Basri رحمه الله said:
“The believer is not the one who worships Allah in Ramadan only, but the one who worships Him all year.”
❓ Are you Ramadan-only… or truly a servant of Allah?
And if you’re serious about the answer…
👉 Then your presence matters.
🤝 All brothers and sisters are expected to attend.
📅 March 28
🕔 After Zuhr
📍 Al Aqsa Masjid
"የሸዋል ዒድ"
~
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
( وأما اتخاذ موسم غير المواسم الشرعية كبعض ليالي شهر ربيع الأول التي يقال : إنها ليلة المولد , أو بعض ليالي رجب , أو ثامن عشر ذي الحجة , أو أول جمعة من رجب , أو ثامن من شوال الذي يسميه الجهَّال عيد الأبرار : فإنها من البدع التي لم يستحبها السلف , ولم يفعلوها. والله سبحانه )
"ሸሪዓዊ ካልሆኑ ወቅቶች (በዓላት) ውጭ ሌላ ወቅትን መያዝን በተመለከተ፤ ለምሳሌ የመውሊድ ሌሊት ነው ተብሎ የሚታሰበው ከፊል የረቢዕ አል-አወል ሌሊቶች፣ ወይም ከፊል የረጀብ ሌሊቶች፣ ወይም የዙልሒጃ አሥራ ስምንተኛው ቀን፣ ወይም የመጀመሪያው የረጀብ ጁሙዐ፣ ወይም መሀይማን 'የደጋጎች በዓል' ብለው የሚጠሩት #ስምንተኛው_የሸዋል_ቀን፦ እነዚህ ሁሉ ቀደምት ደጋግ አባቶች (ሰለፎች) ያልወደዷቸውና ያልፈጸሟቸው የፈጠራ ስራዎች (ቢድዓዎች) ናቸው።" [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 25/298]
በተጨማሪም እንዲህ ብለዋል፦
( وأما ثامن شوال : فليس عيداً لا للأبرار ولا للفجار , ولا يجوز لأحد أن يعتقده عيداً, ولا يحدث فيه شيئاً من شعائر الأعياد )
"ስምንተኛውን የሸዋል ቀን በተመለከተ፦ ለደጋጎችም ሆነ ለ አመፀኞች በዓል አይደለም። ማንም ሰው በዓል ነው ብሎ ሊያምን አይገባም፣ በውስጡም ምንም ዓይነት የበዓል ምልክቶችን (ስነ-ስርዓቶችን) ማከናወን አይፈቀድም።" [አልኢኽቲያራቱል ፊቅሂየህ፡ 199]
©IbnuMunewor
