en
Feedback
'' لَا تَكُنِ مِثْلَهُمْ كُنِ مَثَلًا لَهُمْ .''

'' لَا تَكُنِ مِثْلَهُمْ كُنِ مَثَلًا لَهُمْ .''

Open in Telegram

°• احـذرْ صفحـاتِ وجهِـك، فأعيـنُ النَّـاسِ تقـرأ.🍂

Show more
251
Subscribers
No data24 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
~ብልህ ሴት ዋጋዋን ስለምታዉቅ  የራስ መተማመኗን እንደ ዘዉድ ትለብሳለች ! =

አስሩ የዙል ሂጃ የፆም ቀኖች ! ሮብ........... 1 ሀሙስ....... 2 ጁሙዓ....... 3 ቅዳሜ....... 4 እሁድ........ 5 ሰኞ.......... 6 ማክሰኞ.... 7 እሮብ......
አስሩ የዙል ሂጃ የፆም ቀኖች ! ሮብ........... 1 ሀሙስ....... 2 ጁሙዓ....... 3 ቅዳሜ....... 4 እሁድ........ 5 ሰኞ.......... 6 ማክሰኞ.... 7 እሮብ....... 8 ሀሙስ..... 9 ሼር አድርጋት በአንተ ሰበብ ቢፆሙ ምን ያህል አጅር እንደምታገኝ አታውቅም! 👉 t.me/Abdurhman_oumer/9981

''‏اجعلوا أحلامكم كحمام الحرم محرم قتلها ،'' በአሏህ በመመካት የአሏህን ውሳኔ እየተቀበልሽ ህልምሽን ለማሳካት ሞክሪ ማንም ህልምሽን እንዲጠፋው አትፍቀጂ ¡¡
''‏اجعلوا أحلامكم كحمام الحرم محرم قتلها ،''         በአሏህ በመመካት  የአሏህን ውሳኔ እየተቀበልሽ   ህልምሽን ለማሳካት ሞክሪ ማንም ህልምሽን እንዲጠፋው  አትፍቀጂ ¡¡

~ሂጃብ (ኒቃብ)ሱና ነዉ ለምትሉ ....! 🔖 ሸህ ሷሊህ አልፈውዛን "አላህ ይጠብቃቸው" እንዲህ አሉ። ሴት ልጅ ፊቷን ገልጣ የምትወጣ ቢሆን ኖሮ ሊያጫት ለሚፈልግ ሰው ሂድና ተመልከታት የሚል ፍቃድ ባላስፈለገ ነበር። 📓اتحاف الطلاب | ٣٨٥

بَارَكَ اللَّهُ لَكَ وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ🌸
بَارَكَ اللَّهُ لَكَ وَبَارَكَ عَلَيْكُمَا وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ🌸

ቶሎ ልብሽን ለምትከፍችው እህቴ የተናገረ ሁሉ አዋቂ አይደለም አዋቂ ሁሉ አሏህን ፈሪ አይደለም ያገኘሽውን ሁሉ አትውደጂ ✅ቁርአን ሲቀራ የሰማሽውን ሁሉ እሱን ያገባች ታዲላ አትበይ በውስጥ ያለውን አታውቂም እና #ቃለ አሏህ ቃለ ረሱል ያለን ሁሉ የልጆቸ አባት ይሆነኛል አትበይ #አስተውይ መርምሪ ጠይቂ ዘለሽ ገብተሽ መውጫው ከባድ ይሆን እና ህይወትሽ ይበላሽብሻል ያከሆነ ደግሞ ለእውነተኛው ባልሽ ሚስት ለመሆን ይከብድሻል አስተውይ!! https://t.me/alfrkatu_anajeya

‏ በትዳር ስም አታላዮች ⁉️ ሸይኻችን ❝አንዳንድ ወንድሞች የሱና እህቶቻችንን በትዳር ስም የሚሸነግሉ ወጣቶች አሉ❞ ምን ይመክራሉ? ⁉️ በነዚህ አጭበርባሪ ሰዎች የሚሸወዱ እህቶችንስ ምን ይመክሩልናል? ✅ ወላሂ ሰው አይቀመስ እንደሚባለው ሰዎች የተለያዩ ባህሪዎች ስላሏቸው ተጠንቀቁ! ✅ በእህቶቻችን ገንዘብ፣ ጊዜ እና ስነ-ልቦና ላይ የምትጫወቱ ሰዎች ሆይ! አላህን ፍሩ! አላህ አይለቃችሁም! ✅ አንድ ሴትን ከመበደልህ በፊት እናትህን እህትህን አስታውስ! ✅ እህቶቻችን ደግሞ ገንዘባችሁን ክብራችሁን ጠብቁ! ✅ አገባሻለሁ እያሉ ከሚዘርፉ አደገኛ አጭበርባሪ ሰዎች ራቁ!!! 🎙 በሸይኽ ዐ/ሐሚድ حَفِظَهُ الله https://t.me/abdulham

«ጣፋጭ የሚባሉ ነገሮችን ሁሉ ቀመስኩ… ከጤና በላይ የጣፈጠ ነገር አላገኘሁም። መራር የተባሉ ነገሮችን ሁሉ ቀመስኩ…  ከሰዎች ፈላጊ ከመሆን በላይ መራር ነገር አላገኘሁም።» 📜ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ

የኢኽዋን አልሙስሊሚን ኢስልምና የሟሟ እስልምና ነው ። اسلام الاخوان اسلام مائع وقد ناصروا الخميني የኢኽዋን ደዕዋ የእስልምና ደዕዋ ሳይሆን ህዝብ የማብዛት የፓርላማ የወንበር ሲሆን መርሃቸውም ሰብስብ ከዛ አንፅ ነው ከዛ ማነፅ ምንም የለም በኢኽዋን ቤት በቁርዓን በሀዲስ በመነሀጅ አሰለፍ ማነፅ የለም ። የሸይኹን ድምፅ እንስማ 👇 🎙ታላቁ አሊም ሙሀመድ ቢን ናሲሩዲን አል አልባኒይ ረሂመሁሏህ join #telegram ቻናል https://t.me/abuabdurahmen

ህንፃዎች በአንድ ቀን አልተገኙም በብዙዎች ድካም እና ትግል ቢሆን እንጂ ~ ጥሩነት እና አስተዋይነት ~ በምኛት እና በአንዴ አይመጣም በመታገል ቢሆን እንጂ።
ህንፃዎች በአንድ ቀን አልተገኙም በብዙዎች ድካም እና ትግል ቢሆን እንጂ ~ ጥሩነት እና አስተዋይነት ~ በምኛት እና በአንዴ አይመጣም በመታገል ቢሆን እንጂ።

የነሲሓዎች የመጅሊስን ስልጣን የዜግነትን መብት ለመንጠቅ መጠቀም ። በጉራጌ ዞን የጌቶ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ( የጌቶ ወረዳ መጅሊስ) የቁርኣን ት/ቤት እንዲዘጋ ካልሆነ የግለሰቦችን ቤት እንደሚያሽግ አስጠንቅቆ ደብዳቤ ፃፈ ። በጣም የሚገርመው ም/ቤቱ በፃፈው ደብዳቤ ቤታቸውን ለቁርኣን ቤት ላከራዩት ወ/ሮ ሂዳያ ያሲን በፃፈው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እስከ ግንቦት 11/2017 ድረስ ቁርኣን ቤቱን አዘግተው ሪፖርት ካላደረጉ የመንግስትን መመሪያና ደንብ በመከተል ቤቶን በህግ አግባብ ታሽጎ እርሶም በህግ የሚጠየቁ መሆኑን እንገልፃለን ይላል ። ‼ ገርሞ ገርሞ የሚገርም ነው ። ስለየትኛው የመንግስት መመሪያና ደንብ ነው የሚያወሩት በየትኛው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ነው ወ/ሮ ሂዳይ በህግ ተጠያቂ የሚሆኑትስ ? ለመሆኑ የትኛው የመንግስት ህግ ነው ግለሰብ በንብረትህ ላህ እኔ ነኝ የማዘው አንተ በንብረትህ ማዘዝም ሆነ በምትፈልገው መልኩ ማስተዳደር አትችልም የሚለው ? እንዲህ አይነት መመሪያና ደንብ ካለ ለምን መጠጥ ቤቶችን ፣ ጭፈራ ቤቶችን ፣ ቁማር ቤቶችንና ጫት መቃመያና ሺሻ ማጨሻዎችን አያሽጉም ? ነው ወይስ ሰላም የሚነሳቸው ልጆችን በቁርኣንና ሐዲስ በመልካም ስነምግባር ማነፅ ነው ? ጌቶ ወረዳ ላይ የዚህ አይነቱን መጅሊስ የሚመሩት አዲሶቹ ኢኽዋኖች ( የነሲሓ ሙሪዶች) ናቸው ። ዛሬ ላይ አሕባሽ በስልጣን ሲመጣባቸው ስለዐቂዳው ብልሹነት ሊተርቱልን ይዳዳቸዋል ። ለመሆኑ ኢኽዋኖች ህዝቡ ከዳር እስከዳር አስነስተው ሲነዱት መፈክራቸው አሕባሽ መስጂዶችህንና መድረሳህን ሊቀማህ ነው የሚል አልነበረም ? ታዲ ዛሬ እነርሱ መስጂድና መድረሳን የሚቀሙትና በደብዳቤ የሚያዘጉት ምን ስለሆኑ ነው ? የአቡ በከርና የዑመር ምትኮች ወይስ የሰይድ ቁጥብና የሙሐመድ ሱሩር ዘይኑል ዓቢዲን ምትኮች ? ያኔ አሕባሽን ሲያወግዙ አንድም ቀን ስለዐቂዳው አላነሱም ። ምክንያቱም ትግላቸው ለዐቂዳ ሳይሆን የመጅሊሱን ስልጣን መረከብ ስለነበር ነው ። የድምፃችን ይሰማ ንቅናቄ መፈክር የነበረው " አሽሻዕብ ዩሪድ ኢስቃጠል መጅሊስ " ህዝቡ መጅሊስን መጣል ይፈልጋል የሚል ነበር ። እንሆ ከከፊል አሕባሽ ጋር ስልጣን ተጋርተው ሲያወግዙት የነበረውን ማወደስ ጀምረው ሳሉ ስምምነቱ አይወክለንም የሚሉ በቀብር አምልኳቸው ሙኽሊስ የሆኑ አሕባሾች ባደረጉት ንቅናቄ የመጅሊሱን ምርጫ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ሲከቱት አሕባሽን መኮነን ጀምረዋል ። ይህ በራሱ የመርህ መጣረስ መኖሩን ነው የሚያሳየው ። እገሌ እንዲህ ነው ማለት የለም ሁሉም የኢትዮዽያ ሙስሊም ነው የሚለው መርህ ዛሬ አሕባሾች ካፊሮች ሆነው ነው የተቀየረውና ማውገዝ የተጀመረው ወይስ የእነርሱን ጥቅም የሚነካ ሲመጣ መርሃቸው አይሰራም ። ከርእሴ እንዳልወጣ የጌቶ ወረዳ መጅሊስ የመንግስት መመሪያና ደንብ በሚል የግለሰቦችን መብት ለመርግጥ እየዳዳው ነውና በሳት ባይጫወት ይሻለዋል ። ግለሰቦች በንብረታቸው ላይ የመወሰን መብታቸው እንደተጠበቀ ነው ። ለፈለጉት ማከራየት ለፈለጉት መስጠጠትም ሆነ መሸጥ የሚከለክላቸው ህግ የለም ። ሌላ አካል ገብቶ በንብረታችሁ ማዘዝ አትችሉም ሲል ራሱ ነው ተጠያቂ የሚሆነው ። ከዚህ ባለፈ ጊዜው ያለፈበትን ፋሽን ተከትዬ አሸባሪ ፅንፈኛ እላለሁ ማለት ለሚሉት ነገር ማስጃ የማያቀርቡ ከሆነ ተጠያቂ እንደሚያደርጋቸው ሊያዉቁት ይገባል ። ሌላው በወ/ሮ ሂዳያ መሬት ላይ የተሰራው መስጂድ የአላህ ቤት ነው በሚል የታለፉ ነገሮች መኖራቸውን ማወቁ ጥሩ ነው ። አይ ብለው በዚሁ አካሄዳቸው የሚቀጥሉ ከሆነ የቆጡን አወርድ ብላ … የሚል ተረት ውስጥ እንዳይገቡ ቢያስቡበት ይሻላል ። መልእክት ለወ/ሮ ሂዳያና ቤተሰቦቻቸው በንብረታችሁ ላይ የምታዙት እናንተ ናችሁ ። የተከራዩት ወንድሞች በናንተ ቤት ላይ የሰሩት ወንጀል ካለ በመረጃ መረጋገጥ ይኖርበታል ። ወንጀለኞች መሆናቸው በመረጃ ከተረጋገጠ የወንጀል ተባባሪ ስለሚያደርግ ለወንጀለኛ ወንጀል ሊሰራበት ቤት ማከራየት አይፈቀድም ። ነገር ግን ቁርኣን ማስቀራትም ሆነ ተውሒድና ሱናን ማስተማር ህገመንግስታዊ መብት እንጂ ወንጀል አይደለም ። ወንጀል ነው የሚል አካል ካለ እሱ ነው በወንጀል የሚከሰሰው በመሆኑም መብታችሁን ማስከበራችሁ ህገመንግስታዊ አካሄድ ነውና ወደኋላ እንዳትሉ ። ቁርኣን ለማስቀራት ቤት የተከራያችሁ ወንድሞች ለእንደዚህ አይነት ተራ ውንጀላ ቦታ ሳትሰጡ ልጆችን በቁርኣንና ሐዲስ እንዲሁም በተውሒድና መልካም ስነምግባር የማነፅ ሀላፊነታችሁን ተወጡ ። በዚህ መብታችሁ ፊትለፊት የሚቆም የህግ አካል ካለ ወደ ፍርድቤት በመሄድ መብታችሁን አስከብሩ ። በዚህ ሂደት ስሜታዊ ሆናችሁ አላስፈላጊ ቃላት እንድትናገሩና ፀብ ውስጥ እንድትገቡ ለማድረግ የሚሰሩ ሊኖሩ ስለሚችሉ ተጠንቀቁ ። በፍፁም ፀብ ውስጥ እንዳትገቡ እላፊም እንዳትናገሩ በሰላማዊ አካሄድ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርባችሁ መብታችሁን አስከብሩ ። ይህን የምለው አብዛኛ አካባቢ ላይ ያሉ የተቋማት አመራሮች የመንግስትን ስልጣን ለግል አመለካትና ስሜት ማስፈፀሚያ ስለሚጠቀሙ ዜጎች መብታቸውን ፍ/ቤት ቀርበው እንዲጠይቁ ለመጠቆም ነው ። የወረዳው መጅሊስ የፀፈውን ደብዳቤ በዚህ ሊንክ ገብታችሁ ተመልከቱት ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://drive.google.com/file/d/1gXDrGCmGVoY5SBovjcjl_fsFlAkvagjy/view?usp=drivesdk http://t.me/bahruteka

🟢ኹጥባ አታርዝሙ የጁመዓህ ኹጥባ ማስረዘም እንዴት ነው❓ 🎤ፈታዋውን የሰጡት ዓሊም አሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን قَالَ أَبُو وَائِلٍ : خَطَبَنَا عَمَّارٌ–أي : ابن ياسر - فَأَوْجَزَ ، وَأَبْلَغَ ، فَلَمَّا نَزَلَ قُلْنَا : يَا أَبَا الْيَقْظَانِ لَقَدْ أَبْلَغْتَ وَأَوْجَزْتَ فَلَوْ كُنْتَ تَنَفَّسْتَ – أي : أطلتَ - ، فَقَالَ : إِنِّي سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ : ( إِنَّ طُولَ صَلَاةِ الرَّجُلِ وَقِصَرَ خُطْبَتِهِ مَئِنَّةٌ مِنْ فِقْهِهِ ، فَأَطِيلُوا الصَّلَاةَ ، وَاقْصُرُوا الْخُطْبَةَ ، وَإِنَّ مِنْ الْبَيَانِ سِحْراً ) . رواه مسلم ( 869 ) . አቡ ዋኢል አለ፡ "አማር ኢብኑ ያሲር ኹጥባ አደረገልን።አሳጥሮት እና አሳመሮት ነበርና ሲወርድ እንዲህ አልነው አንት የየቅዛን አባት ሆይ በእርጎጥም አሳመረክ አሳጠርክም። ምነው አስረዝመኀው በነበር።" አለ፡"እኔ ረሱልን(ﷺ)ሲሉ ሰምቻለሁ፡ {የሰውየው ሰላት መርዘም እና የኹጥባው ማጠር ከግንዛቤ ደረጃው ከፍ ማለት ምልክት ነው። ሰላትን አርዝሙ ኹጥባን አሳጥሩ። ከማብራሪያም ሲህር (ድግምት) አለ።} قلت ኸጢቦች ሆይ ✏️ ኹጥባና ሙሃደራን ለዩ ✏️ ሁሉን ለማደረስ አትዳክሩ ✏️ ሰው አታሰልቹ ✏️ ብዙሃኑ እያንቀላፋ እናንተ ለማነው የምታብራሩት❓ ✏️ጉዳዩ የኢኽዋን እና ሙመይዓህ ኸጢቦች ጋ የከፋ ነው።ማምታቻና ፖለቲካ ሲነዙ ያረዝሙታል። በምረጡን ቅስቀሳቸው ጊዜ ደግሞ ጁመዓ ምን የክል እንደሚረዝም አላህ ያውቃል። https://t.me/FATTAWAS

❝ ለፖለቲካ የአህባሽን መጥፎነት ደጋግሞ ገልፆ ኢኽዋንን መልካም እንደሆነ አስመስሎ ለመቅረፅ መሞከር ፦ “ኺንዚር” ብቻ ነው ነጃሳው እንጅ “ውሻ” አይነጅስም እንደማለት ነው። የአህባሽና የኢኽዋን ልዩነት በኺንዚር ነጃሳና በውሻ ነጃሳ መካከል እንዳለው ልዩነት ነው። ❞