en
Feedback
Abu abdullah Ibnu Areb-As Selefiy

Abu abdullah Ibnu Areb-As Selefiy

Open in Telegram

ለተፈጠርንበት አላማ(ለተውሂድ) ቅድሚያ እንስጥ.... 🍃ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿مَنْ يُرِدِ اللَّهُ بِهِ خَيْرًا يُفَقِّهْهُ فِي الدِّينِ﴾ “አላህ መልካም የሻለትን ሰው ዲኑን (እምነቱን) እንዲገነዘብ ያደርገዋል።” 📚 ቡኻሪ (3116) ሙስሊም (1037) ዘግበውታል http://t.me/Abuhibeti_bot አስታየት ካሎት👆👆

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
809
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ፀጉርሽን እንደ ግመል ሻኛ ቆልለሽ የምትሄጂው እህቴ ሆይ እስኪ ይህችን የአሽረፈል ኸልቅ ﷺ ንግግር በጥሞና ተመልከቺ! ፀጉርን ነበር እንዳይቆለል የተፈራው ዛሬ ግን ፀጉር ማስያዣ እየቆለሉ ነው ያስቸገሩት وقال صلي الله عليه وسلم صنفان من اهل النار لم اراهما. ‍.‍.. ونساء كاسيات عاريات، مائلات مميلات، رؤسهن كأسنمة البخت المائلة، لا يدخلن الجنة، ولا يجيدن ريحها. وإن ريحها ليوجد من مسيرة كذا وكذا. (صحيح مسلم) ጀነትን አይገቡም ሽታዋንም አያገኙትም! ➲ነብዩﷺ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፦ "ከእሳት ሰዎች መካከል ሁለት አይነት ሰዎች አሉ። እኔ ያላየኋቸው ወደፊት የሚመጡ! አንደኛቸው ለብሰው ያለበሱ(የለበሰቱ ልብስ ሰውነታቸውን የማይሸፍን) አካሄዳቸው እና እንቅስቃሲያቸው ወደ ፀያፍ ተግባር ያዘነበሉ፤ ሌሎችንም የሚያሳስቱ #ፀጉራቸው_ልክ_እንደ_ግመል_ሻኛ_የተከመረ_ሴቶች_ናቸው። " ➲እንደነዚህ አይነቶቹ ጀነትን አይገቡም ሽታዋንም አያገኙትም፡፡›› 📚ሙስሊም ዘግበውታል

አስደማሚ ታሪክ ~~ ኢስሓቅ ኢብኑ ዐባድ አልበስሪ ይባላሉ። በአንድ ወቅት ተኝተው ሳለ በህልማቸው የሆነ አካል መጥቶ "ችግረኛውን እርዳ!" አላቸው። ከእንቅልፋቸው ተነስተው በጎረቤት የተቸገረ ካለ ቢጠይቁ "አናውቅም" የሚል ምላሽ አገኙ። ተመልሰው ተኙ። አሁንም ለሁለተኛ፣ ከዚያም ለሶስተኛ ጊዜ መጥቶ "ችግረኛውን ሳትረዳ ትተኛለህ?" አላቸው። ተነሱ። 300 ዲርሃም ያዙ። በቅሏቸው ላይ ሆነው ወደ መስጂድ ወጡ። ሲደርሱ ሶላት የሚሰግድ ሰው አለ። ማጠናቀቁን ሲገምቱ ተጠጉና "አንተ የአላህ ባሪያ! ምነው በዚህ ሰዓት? በዚህ ቦታ? ምን አወጣህ?!" አሉት። ሰውየው:– "እኔ ወረቴ መቶ ዲርሃም የሆንኩ ሰው ነበርኩ። ግን ጠፋብኝ። ከዚያም የ200 ዲርሃም እዳ ተጫነኝ" አለ። ዲርሃሞቹን አውጥቶ "ይሄው እነዚህ 300 ዲርሃሞች ናቸው። ውሰድ" አሉት። ወሰደ። ከዚያም "ታውቀኛለህ?" አሉት። "አላውቅህም" አለ። "እኔ ኢስሓቅ ኢብኑ ዐባድ ነኝ። ችግር ከገጠመህ ከኔ ዘንድ ና" ብለው ቤቱ የሚገኝበትን አካባቢ ነገሩት። • ሰውየው በዚህም ጊዜ እንዲህ አለ:– "አላህ ይዘንልህ። ችግር ከገጠመን አንተን ከቤትህ አውጥቶ እኔ ዘንድ ወዳመጣህ ጌታ ነው የምሸሸው።" 📚 [ረሳኢሉ ኢብኒ ረጀብ: 3/128]   ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

☑️ የጠዋት ዚክር اللَّهمَّ إنا نسألُكَ خيرَ هذا اليومِ فتحه ونصرَهُ ونورَهُ وبرَكتَهُ وَهداهُ، ونعوذ بِكَ من شرِّ ما فيهِ وشرِّ ما بعدَهُ.

🌹እናታችን አዒሻ የሳቀች እለት 🌹 ➲እናታችን አዒሻ ረዲየላሁ ዓንሃ እንዲህ አሉ፦ ➲ከእለታት አንድ ቀን የረሱልን ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም መደሰት ባየሁ ግዜ እንዲህ አልኳቸው ➲"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ ! እስኪ ዱዓ አድርጉልኝ"? ከዚያም እንዲህ ብለው ዱዓ አደረጉልኝ ፡ "ጌታዬ አላህ ሆይ!የአዒሻን ኃጢያት ማርላት ያሳለፈችውንም ወደፊት የሚመጣውንም እንዲሁም በድብቅ የሰራችውንም በገሀድ በግልፅ የሰራችውንም ሁሉንም ማርላት" አሉ። ➲ከዚያም እናታችን አዒሻ ከደስታ ብዛት በጣም ሳቀች ፡ በጣም ከመሳቋ የተነሳ በጭንቅላቷ ከረሱል ታፋ ላይ እስክትወድቅም ድረስ ደረሰች ፡ ➲ከዚያም የአላህ መልዕክተኛ - ምነው ዱዓዬ አስደሰተሽ ? አሏት ፡ ➲ከዚያም እናታችን አዒሻ እንዴታ አያስደስተኝ ዱዓችሁ አንቱ የአላህ መልዕክተኛ አለች ፡ ➲ከዚያም የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ አሉ፦ በአላህ ስም እምላለሁ ይህ ለአንቺ ያደረግኩልሽ ዱዓ በእያንዳንዱ ሶላቴ ላይ ለሁሉም ለዑመቶቼ (ለህዝቦቼ) የማደርግላቸው ዱዓዬ ነው ። 📚ምንጭ፦ ሲልሲለቱ ሶሒሀህ [(5/324 https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy https://whatsapp.com/channel/0029VaANnkPCxoAu3seNcE1F

ክፍል 03 አጭር መልስ በአህባሾች ላይ ضربني وبكى سبقني واشتكى መታኝ እና አለቀሰ ቀደመኝ እና ስሞታን አቀረበ የአሏህን ስም እና ባህሪ በማንሸዋረር ለተጠመዱ አህባሾች አጠር ያለች መልስ خاصة لمن حاور الأستاذ عبد الملك حفظه الله 🎙በኡስታዝ ኸድር ቢን አህመድ (አል-ኬሚሴ) ''ሀፊዘሁሏህ'' t.me/UstazKedirAhmed t.me/UstazKedirAhmed

ሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም ክፍል - 05 የሱና ብርሃን ትምህርት ቤት ግሩፕ ላይ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር በየ ሳምንቱ የሚሰጥ ትምህርት። የቴሌግራም ቻናል፡‐ https://t.me/fejir_tube

sefinetu solah 07.mp39.80 MB

ኢብኑ_ረጀብ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ  : - «ድህነት ማለት ገንዘብ ማጣት እንዳይመስልህ፣ ነገር ግን ዲንን ማጣት ከድህነቶች ሁሉ የከፋውና ትልቁ ነው።» 📚 ۞ مجمـوع الرسائـل【1/65】

➥ሁሌም ቢሆን ጥቁር ብቻ መስሎ ከሚታይህ ቀን ጀርባ የታዘለ ደማቅ ብርሃን አለ ➥ሊገፈትሩህ ከበረቱ እልፍ ክንዶች ኋላ ሊያቀኑህ የቆሙ ልስልስ መዳፎች አሉ! ➥ አንሸራትተው ከሚደፉክ ሃሳቦች ባሻገር በተስፋ ሞልተው የሚያቆሙህ ቅን ሀሳቦች ተሰልፈዋል! ➥ያላየከው ነገ ብዙ አዲስ የህይወት ገፆችን ይዞ ይጠብቅሃል ካጎነበስክበት ቀና ትላለህ! ➥ ሀዘንህ በሳቅ ይተካል ጉስቁልናህን ወዝ ይሽረዋል ይህ እንዲሆን ግን ነገን ጠብቀው አልም ተስፋ አትቁረጥ ነገ ያንተ ሲሆን ብቻ አሸናፊ ነህ !! #ስለዚህ_ታገስ_ወዳጀ!! https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

እኛ እንደምናልፈው ሁሉ ህመሞቻችንም ያልፋሉ፤ አብሽሩ። የሚዘልቅ ህመምም ሆነ ችግር የለም። https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

ሳምንታዊ የሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም የደርስ ፕሮግራም 🗒 ሰኞ፣ ማክሰኞ እና እሮብ:- 📚 بلوغ المرام 🕛 ከሱብሒ ሶላት በኋላ 📚 شرح ابن عقيل على ألفية ابن مالك 🕓 ቀን ከ4:25 እስከ 5:00 📚 سنن أبي داود  🕔 ቀን ከ5:00 እስከ 6:00 📚 شرح السنة للبربهاري 🕐 ከመግሪብ እስከ ዒሻእ 🗒 ሐሙስ:- 📚 بلوغ المرام 🕛 ከሱብሒ ሶላት በኋላ 📚 شرح ابن عقيل على ألفية ابن مالك 🕓 ቀን ከ4:25 እስከ 5:00 📚 سنن أبي داود 🕔 ቀን ከ5:00 እስከ 6:00 🗒 ቅዳሜ እና እሁድ:- 📚 صحيح مسلم 🕐 ጠዋት ከ1:10 እስከ 2:30 📚 صحيح مسلم 🕙 ቀን ከዐስር ሰላት በኃላ አድራሻ:- ፉሪ (በፉሪ ሜዳ ፊት ለፊት ባለው ቅያስ ገባ ብሎ) አቡበክር መስጂድ Abubakar mesjid - አቡበከር መስጂድ http://maps.google.com/?cid=9777129393835294663&hl=en&gl=gb ____ * ትምህርቶቹን በቴሌግራም ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam

✍💦💦ዚክር → አላህን ማውሳት‼ =================== ✍ ጊዜ ከማይገድባቸው ዒባዳዎች መካከል አንዱ ዚክር ነው። የታክሲ ሰልፍ ላይ የምናሳልፈውን ጊዜ፣ የሆነ ጉዳይ ለማስፈጸም በአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት ወይም ሌላ ተቋም ወረፋ ስንጠብቅ የምናሳልፈውን ጊዜ፣ ወደ ሥራ ቦታ ስንሄድም ሆነ ስንመለስ መንገድ ሲዘጋጋ መንገድ ላይ የሚያልፈውን ጊዜ፣ ተማሪ ከሆንን የረፍት ሰዓትና መምህር እስኪገባ ድረስ የምናሳልፈውን ጊዜ፣ ነጋዴና ሠራተኛ ከሆንን ደንበኛ እስኪመጣ ድረስ የሚያልፈውን ጊዜ፣ የቤት ሠራተኛ የሆነ ሥራውን በአካሉ እየሠራ በምላሱ… ዚክር በማድረግ ብናሳልፈው እጅግ በጣም አትራፊዎች ነን። ከተለያዩ ወቅቶችና ሁኔታዎች ከተያያዙት ዚክሮች ባሻገር በየትኛውም ወቅት ዚክር ማድረግ እንችላለን። አላህን በማስታወስ ልቦች ይረጋሉ። አላህ እንዲህ ይለናል፦ (الَّذِينَ آمَنُوا وَتَطْمَئِنُّ قُلُوبُهُم بِذِكْرِ اللَّهِ ۗ أَلَا بِذِكْرِ اللَّهِ تَطْمَئِنُّ الْقُلُوبُ) «(እነሱም) እነዚያ ያመኑ ልቦቻቸውም አላህን በማውሳት የሚረኩ ናቸው፡፡ ንቁ! አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ፡፡» [አ-ር'ረዕድ: 28] * (… وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا) «… አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶችና አውሺዎች ሴቶችም፣ አላህ ለእነርሱ ምሕረትንና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡» [አል-አሕዛብ: 35] * (الَّذِينَ يَذْكُرُونَ اللَّهَ قِيَامًا وَقُعُودًا وَعَلَىٰ جُنُوبِهِمْ وَيَتَفَكَّرُونَ فِي خَلْقِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ رَبَّنَا مَا خَلَقْتَ هَٰذَا بَاطِلًا سُبْحَانَكَ فَقِنَا عَذَابَ النَّارِ) «(እነርሱም) እነዚያ ቆመው፣ ተቀምጠውም፣ በጎኖቻቸው ተጋድመውም አላህን የሚያወሱ በሰማያትና በምድር አፈጣጠርም የሚያስተነትኑ፡- «ጌታችን ሆይ! ይኸን በከንቱ አልፈጠርከውም፤ ጥራት ይገባህ፤ ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን» የሚሉ ናቸው፡፡» [ኣሊ ዒምራን: 191] * ውዱ ነቢያችንም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ (مَثَلُ الذي يَذْكُرُ رَبَّهُ والذي لا يَذْكُرُ رَبَّهُ، مَثَلُ الحَيِّ والمَيِّتِ.) «ጌታውን የሚያወሳና የማያወሳ አምሳያው፤ ልክ እንደ ሕያውና ሙት ነው።» [አል-ቡኻሪይ: 6407፣ ሙስሊም: 779] * 👉እርሱ ዚክር ከመቶ በላይ ጥቅሞች አሉት ከእነዚያም ውስጥ በጥቂቱ፦  *እርሱ ዚክር ሽይጧንን ያባርራል። *እርሱ ዚክር የአልረሕማን ውዴታ ያስገኛል። *እርሱ ዚክር ጭንቀትን እና መረበሽን ከቀልብ ላይ ያስወግዳል። *እርሱ ዚክር በልብ ውስጥ ደስታንና እርካታን ያስገኛል። *እርሱ ዚክር ቀልብን እና አካልን ያጠነክራል። *እርሱ ዚክር የሲሳይን በር ይከፍታል። *እርሱ ዚክር አላህን መፍራትን ያስወርሳል። *እርሱ ዚክር ለቀልብ ህያውነትን ያወርሳል። *እርሱ ዚክር ወንጀልን ለማራገፊያ ሰበብ  ይሆናል ፨ ሌሎችም ብዙ ጥቅምችን አሉት ስለዚህ አላህን የምናወሳ ሕያው እንሁን። አላህ ያግራልን‼

💦💦ሶላት በላጩ ስራ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿و اعلموا أنّ خيرَ أعمالِكم الصلاةُ﴾ “እወቁ! ከመልካም ስራዎቻችሁ ሁሉ በላጩ ሶላት ነው።” 📚 ሶሂህ አልጃሚዕ: 956 https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

ኡዱሒያ ጋር የሚያያዙ ተጨማሪ ነጥቦች ~ 1ኛ፦ የሚታረደው እንስሳ ወንድ ብቻ አይደለም የሚሆነው፣ ሴትም ማረድ ይቻላል። ይሄ የዑለማእ ወጥ ስምምነት (ኢጅማዕ) ያለበት ጉዳይ ነው። የታረደችው እንስሳ ሆዷ ውስጥ ፅንስ ካለ፣ ካልከበዳቸው መመገብ ይችላሉ። ነብዩ ﷺ ስለዚህ ጉዳይ ሲጠየቁ እንዲህ ብለዋል፦ كُلوه إنْ شِئتُم؛ فإنَّ ذَكاتَه ذَكاةُ أمِّه "ከፈለጋችሁ ብሉት። የእሱ (የሽሉ) እርድ የእናቱ እርድ ነው።" [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 2827] ማለትም የሷ ክፍል እንደመሆኑ እሷን ሐላል ያደረጋት እርድ እሱንም ሐላል አድርጎታል ማለታቸው ነው። "ከፈለጋችሁ" ነው ያሉት። ያልፈለገ ለሚፈልግ ሊሰጠው ካልሆነም ሊተወው ይችላል። 2ኛ፦ የሚታረደው እንስሳ ቀንድ ያለው መሆኑ ግዴታ አይደለም። በተፈጥሮው ቀንድ የሌለው ከሆነ ምንም ችግር የለውም። 3ኛ፦ ግልፅ ያልሆኑ ትንንሽ ነውሮች ያሉበትን ማረድ ይቻላል። በጣም አጥብቀን ራሳችንን ልናስቸግር ወይም የተሻለ እንስሳ ልናስመልጥ አይገባም። 4ኛ:- ውጭ ሃገር ለሚኖር ሰው በውክልና የምናርድ ከሆነ ባለ ኡዱሒያው አካል ዒድ ሳይሰግድ ቀድመን ማረድ የለብንም። ይቺን ፈትዋ ማየት ትችላላችሁ። https://t.me/ibnhezam/14606 ስለዚህ ባለ ኡዱሒያዎቹ አውሮፓና አሜሪካ የሚኖሩ ከሆኑ ከኛ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት ስለማይሰግዱ እናቆየው። እስከ 13ኛ ቀን ድረስ ማረድ ስለሚቻል ስጋት እንዳይገባን። 5ኛ፦ ስጋውን ከፊሉን ቤት ውስጥ ለእለት ምግብ ማዋል፣ ከፊሉን ማስቀመጥ፣ ከፊሉን ደግሞ ሶደቃ አድርጎ ለሰው መስጠት ይቻላል። 1/3ኛ ለእለት ምግብ፣ 1/3ኛ ለሚቆይ፣ 1/3ኛ ደግሞ ለሶደቃ የሚለው መረጃ የለውም። በዚህም ይሁን በሌላ በፈለገው መልኩ ማከፋፈል ይችላል። ከፊል ዓሊሞች ትንሽም ቢሆን ሶደቃ መስጠቱ ግዴታ ነው ይላሉ። ነገር ግን አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው ሙሉውን መጠቀምም ይቻላል። https://t.me/ibnhezam/14661 ስለዚህ ለምሳሌ ቤተሰብ የሚበዛበት ሰው እዚያው ሊጠቀመው ይቻላል ማለት ነው። = Ibnu Munewor የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor

➦የአረበኛ ፊደላቶች ባህሪያት ከጥንካሬያቸው እና ከደካማነታቸው አንፃር በሶስት ይከፈላሉ። 1) ጠንካራ (القوية) 2) መካከለኛ (المتوصط) 3) ደካማ (الضعيفة) -—-------------------------------------- ----------------------------------------- ◆ከአረበኛ ፊደላት ባህሪያቶች ውስጥ ጠንካራ የሚባሉት 1) ጀህር 2) ሺዳህ 3) ኢስቲዕላእ 4) ኢጥባቅ 5) ሶፊር 6) ቀልቀላህ 7) ኢንሒራፍ 8) ተክሪር 9) ተፈሺ 10) ኢስቲጧለህ 11) ጉና ናቸው። ◆ከአረበኛ ፊደላት ባህሪያቶች ውስጥ መካከለኛ  የሚባሉት (ደካማ ወይም ጠንካራ ያልሆኑ) 1) በይንያህ 2) ኢዝላቅ 3) ኢስማት ናቸው። ◆ከአረበኛ ፊደላት ባህሪያቶች ውስጥ ደካማ የሚባሉት 1) ሀምስ 2)ረኻዋህ 3) ኢስቲፋል 4) ኢንፊታህ 5) ሊን ናቸው። https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

የአሕባሾች መንዙማ ③.mp38.79 MB

ድንግል/ቢክራ አላገኘዉባትም ልጅ አገረድ አገባ ግን (ቢክራ) ድንግል አላገኘባትም ?? ሸይኽ ኢብኑ ባዝ (ረሂመሁላህ) ተጠየቁ :- ➪ ጥያቄ:- ሰውየው ልጅ አገረድ አግብቶ ድንግል ሁና ካላገኛት ምን ማድረግ ነው ያለበት ? ➪ መልስ:- ይሄ ብዙ ምክኒያቶች ይኖሩታል : ድንግሏ ምናልባት ያለ ዝሙት ሊፈርስ ይችላል። የልጂቱ ውጫዊ ስብዕናዋ መልካም ከሆነ እናም በዲኗ የተስተካከለች ከሆነች በሷ ላይ ጥሩ ግምትና መልካም ጥርጣሬን ማሳደር የግድ ነው። በዚያ ላይ ጥሩ ጥርጣሬን ማሳደር ግድ ይላል። - ወይንም አፀያፊውን ዝሙት ሰርታ ከዚያ አላህ መርቷት ከሰራችሁ መጥፎ ተግባር ተፀፅታና ቶብታም ሊሆን ይችላል። ከዚያም ወደ ጥሩነትና መልካምነት ከተቀየረች (ቢክራ) ድንግል አለመኖሯ እሱን አይጐዳውም። - ምናልባትም ድንግሏ በወር አበባ ብርታት ምከንያት ፈርሶ ሊሆን ይችላል። ጠንካራ (ሃይድ) የወር አበባ (ቢክራን)ድንግልን ያፈርሳል። ይሄህ ኡለሞች አውስተውታል። - ልክ እንደዚሁም በአንዳንድ ዝላዮች ድንግል ሊፈርስ ይችላል። ከሆነ ቦታ ወደሆነ ቦታ ስትዘል። ወይንም ከከፍተኛ ቦታ ወደ ዝቅተኛ ቦታ በምትወርድ ጊዜ በዚህ አጋጣሚ ድንግል ሊፈርስ ይችላል። ➪ ስለዚህ የድንግል መፍረስ የግድ በአፀያፊው ዝሙት ብቻ ሊሆን አይችልም። በጭራሽ። ከዝሙት ውጭ በሆነ ክስተት ነው ድንግል የፈረሰው ካለች ወይንም በዝሙት ነው ድንግሌ የፈረሰው ግን ተገድጄ እና ተደፍሬ ነው ካለች ይሄ እሱን አይጎዳውም። - ወይንም በፍላጎቷ ዝሙት ሰርታ ከሆነ ድንግሏ የፈረሰው ግን ያንን ያደረገችው በማታውቅበትና በመሃይምነቷ ጊዜ እንደሆነም እናም አሁን ከዚያ ቶብታና ተፀፅታ ከሆነ ይሄም እሱን አይጎዳውም። - ይሄን የሷን ሚስጥር ሊበትንባት እና ሊያሰራጭባት አይገባም ይልቁንስ ሊደብቅላት ይገባል። በእርሱ ግምት እውነተኛነቷንና ቅንነቷን እናም መስተካከሏን ካመነበት ከእርሱ ጋር ያስቀራታል። ካሎነ ግን በሷ ላይ ያደረበት ግምት ጥሩ ካልሆነ ይፈታታል የሷን ሚስጥር ከመደበቅና ከመጠበቅ ጋር በጭራሽ ሚስጥሯን ባደባባይ መግለፅ አይገባውም። ምንጭ፡- መጅሙዕ አል-ፈታዋ (287/286-30) https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy

sticker.webp0.63 KB