en
Feedback
ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ M.O.R Hawassa Branch

ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ M.O.R Hawassa Branch

Open in Telegram

ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

Show more
3 302
Subscribers
+124 hours
+97 days
+5630 days
Posts Archive
· የታክስ ማስታወቂያ ግዴታውን ያልተወጣ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ የታክስ ጊዜ ያልተከፈለውን ታክስ 5%፤ 25% እስኪሞላ ድረስ ይቀጣል፤ · ለመጀመሪያው የሒሣብ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ ያላቀረበ ሰው
·   የታክስ ማስታወቂያ ግዴታውን ያልተወጣ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ የታክስ ጊዜ ያልተከፈለውን ታክስ 5%፤ 25% እስኪሞላ ድረስ ይቀጣል፤ ·   ለመጀመሪያው የሒሣብ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ ያላቀረበ ሰው ቅጣት ከብር 50ሺ አይበልጥም፡፡ ·  በማንኛውም ሁኔታ የሚጣለው ቅጣት ቀጥሎ ከተመለከቱት ከዝቅተኛው ያነሰ አይሆንም፤   I. ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር)፣  II.   በታክስ ማስታወቂያ ላይ መመልከት ከነበረበት የታክስ መጠን መቶ በመቶ፡፡  ታክስ ከፋዩ በታክስ ጊዜው ሊከፍል የሚገባው ታክስ የሌለው እንደሆነ የታክስ ማስታወቂያ ሳያቀርብ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ የታክስ ጊዜ 10 ሺህ ብር ቅጣት ይከፍላል፡፡ ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

ማስታወቂያ ለቅ/ጽ/ቤታችን ግ.ከፋዮች በሙሉ    በታክስ ደረሰኝ አጠቃቀምና አስተዳደር ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 188/2017 መሰረት unique QR Code የተካተተበት የማንዋል ደረሰኝ ህትመት ጠይቃችሁ  ለ22 ኛ ዙር የመጣላችሁ ከላይ በተያየዘው ዝርዝር መሰረት የድርጅቱ ስም መኖሩን በማጣራት ሥራ አስኪያጅ ወይም ተወካይ ከሆነ  የውክልና ደብዳቤና መታወቂያ ኮፒ፣ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን ለህትመት የተፈቀደበት ዋናውንና ኮፒ እንዲሁም በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ሂሳብ የተከፈለበትና ቅድመ ግብር የተቀነሰበት ደረሰኝ እንዲሁም ነባሩን ደረሰኝ መወገድ ስላለበት በመያዝ  1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 13  በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የደረሠኝ አስተደደር ቡድን በአካል መጥታችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ያስታውቃል፡፡ በገቢዎች ሚ/ር ሐዋሳ ቅ/ጽ/ቤት

ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ግብርን ቀንሶ ማስቀረትዎን እንዳይዘነጉ! 1. ነዋሪ ለሆነ ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት ለሚሰራ ድርጅት የማስከፈያ መጣኔ ፡- Ø ሮያልቲ………… 10% Ø የሮያልቲ ገቢው የተገ
ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ግብርን ቀንሶ ማስቀረትዎን እንዳይዘነጉ! 1.   ነዋሪ ለሆነ ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት ለሚሰራ ድርጅት የማስከፈያ መጣኔ ፡- Ø  ሮያልቲ………… 10% Ø  የሮያልቲ ገቢው የተገኘው ከኪነጥበብ ወይም ከባህላዊ ስራ ከሆነ 5% (አምስት በመቶ)፤ የገቢ ግብር የመክፈል ግዴታ አለበት። Ø  የትርፍ ድርሻ……. 15% Ø  በሌላ ማናቸውም ሁኔታ ከሚገኝ ወለድ ግብር …..10%  Ø  ከዕድል ሙከራ የሚገኝ ገቢ ግብር ………… 25% 2.  በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ሰው/ድርጅት ግብር የማስከፈያ መጣኔ ፡- Ø  ከመድን አርቦን  ---------15% Ø  ከሮያሊቲ ጠቅላላ ክፍያ ላይ ---------10% Ø  ከትርፍ ድርሻ --------- 15% Ø  ከወለድ ጠቅላላ ገቢ ላይ ---------- 10% Ø  ከስራ አመራር ክፍያና ከቴክኒክ አገልግሎት ጠቅላላ ክፍያ ላይ ----------15% Ø  የመዝናኛ አገልግሎት ሰጪዎች ግብር ---------- 15% Ø  የዓለም አቀፍ አየር ትራንስፖርት ድርጅቶች ግብር --------- 3% Ø  የማዕድንና ፔትሮሊየም ገቢ ግብር -------------  25%

1. ምርት ተረክበው የሚያከፋፍሉ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ ፋብሪካው ወይም አስመጪው የምርቱን የመሽጫ ዋጋ በሚተምንበትና አክፋፋዮቹ የትርፍ ህዳጋቸውን ከፍተኛ ወይም ዝቅተኛ ማድረግ የማይችሉ በሚሆንበት ጊዜ ግብር ከፋዮች ላይ አማራጭ አነስተኛ ግብር የሚሰላው በኮሚሽኑ ዋጋ ወይም ጠቅላላ ገቢ ላይ ይሆናል፡፡ 2. የንግድ ወኪሎች በተመለከተ የንግድ ወኪሎች የዋናውን ነጋዴ ዕቃ በውክልና ተረክበው የሚሸጡ ከሆነ የሸጡበትን ዋጋ ለወካያቸው ገቢ የሚያደርጉ እና ደረስኝ የሚቆረጠውም በወካዩ ነጋዴ ስም ሲሆን፣ ለወኪሎቹ የሚከፈላቸው የኮሚሽን ክፍያ ብቻ ነው :: ስለሆነም የንግድ ወኪሎችን በተመለከተ አማራጭ አነስተኛ ግብሩ የሚሰላው በሚያገኙት የኮሚሽን ክፍያ ላይ ብቻ ይሆናል ማለት ነው፡፡ 3. ጅምላ ሻጮች ወይም አከፋፋዮች በተመለከተ ጅምላ ሻጮች ወይም አከፋፋዮች በስማቸው የማከፋፈል የጅምላ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ከአምራቹ ወይም ከአስመጪው የዕቃዎችን ግዢ ፈጽመው ለሌሎች ጅምላ ሻጮች ወይም ቸርቻሪዎች የሚሽጡ ከሆነ ፤ በስማቸው ደረሰኝ የሚቆርጡ እና ክፍያ የሚቀበሉ ከሆነ የአማራጭ አነስተኛ ግብር ማስከፈያ መሰረቱ አመታዊ ጠቅላላ ገቢው ላይ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ጅምላ ሻጩ/አከፋፋዩ ከአምራቹ ወይም ከአስመጪው ጋር ባደረገው ውል የገዛቸውን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ለሌሎች ጅምላ ሻጮች ወይም ቸርቻሪዎች የሚሸጥበት ዋጋ እና ጅምላ ሻጩ የሚያገኘው መቶኛ የተወሰነ ከሆነ  የአማራጭ አነስተኛ ግብሩ ተፈጻሚ የሚሆነው በአዋጁ አንቀጽ 23(2(መ) መሰረት በጠቅላላ የሽያጭ ገቢው ላይ ሳይሆን ለጀምላ ሻጩ  ከላይ በተጠቀሰው ውል ወይም በህግ ስልጣን በተሰጠው አካል በተፈቀደለት መቶኛ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡ 4.  አማራጭ አነስተኛ ግብር እና የገቢ ግብር እፎይታ በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያ በኢንቨስትመንት ህግ የግብር እፎይታ በተሰጠው ሰው ላይ አማራጭ አነስተኛ ግብር ተፈጻሚ እንደሚሆንና አማራጭ አነስተኛ ግብሩ የሚሰላው የተሰጠው ማበረታቻ ተቀናሽ ተደርጎ ሊከፈል በሚገባው የገቢ ግብር ላይ እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ በሥራ ላይ ባለው  የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሕግ የገቢ ግብር እፎይታ የተሰጣቸው ግብር ከፋዮች መብቱ ጸንቶ ለሚቀይበት ጊዜ የንግድ ትርፍ ግብር እንዲከፍሉ አይጠበቅባቸውም፡፡ የማሻሻያ አዋጁ ታሳቢ ያደረገው አዲስ በሚወጣው  የኢንቨስትመንት  ማበረታቻ ደንብ  መሠረት ማበረታቻ ለተሰጣቸው ግብር ከፋዮች ተፈጻሚ የሚሆነውን ከመደበኛው የማስከፈያ መጣኔ አነስ ያለ የማስከፈያ መጣኔ ነው፡፡ በመሆኑም  በሥራ ላይ ፀንቶ በሚገኘው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሕግ መሰረት የገቢ ግብር ነፃ መብት የተሰጣቸው ኢንቨስተሮች ላይ አማራጭ አነስተኛ ግብር ተፈፃሚ አይደረግም፡   5.የቤት ኪራይ ገቢ ግብር እና አማራጭ አነስተኛ ግብር ተፈፃሚነት በአዋጁ  አንቀጽ 23(1) የተጣለው አማራጭ አነስተኛ ግብር የሚሰላው ግብር ከፋዩ በግብር አመቱ ከተለያዩ የንግድ ሥራ ገቢ ምንጮች ባገኘው ትርፍ ላይ ሊከፈል የሚገባውን ግብር ከጠቅላላ አመታዊ ገቢው ጋር ሲነፃፀር ከ2.5 በመቶ በታች ሲሆን ነው፡፡ ከንግድ ሥራ ገቢ የሚገኝ ትርፍ ላይ ግብር የሚከፈለው ደግሞ በሰንጠረዥ "ሐ" መሰረት በመሆኑ አማራጭ አነስተኛ ግብር ተፈፃሚ የሚሆነው በሠንጠረዥ"ሐ" መሰረት በሚከፈል የንግድ ትርፍ ግብር ላይ ብቻ ነው። በመሆኑም በሰንጠረዥ  "ለ"  የቤት ኪራይ ገቢ ላይ አማራጭ አነስተኛ ገቢ ግብር ተፈፃሚ አይደረግበትም፡፡

5. በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ ክሊራንስ ü የግብር/ታክስ ዕዳ ያለባቸው ነገር ግን በክርክር ላይ ያሉ ወይም የክፍያ ስምምነት የፈጸሙ ታክስ ከፋዮች የንግድ ፈቃድ ለማደስ፤ በጨረታ ለመሳተፍና ብ
5.  በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ ክሊራንስ   ü  የግብር/ታክስ ዕዳ ያለባቸው ነገር ግን በክርክር ላይ ያሉ ወይም የክፍያ ስምምነት የፈጸሙ ታክስ ከፋዮች የንግድ ፈቃድ ለማደስ፤ በጨረታ ለመሳተፍና ብድር ለማግኘት የሚያስችላቸው "በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ የምስክር ወረቀት"ማግኘት የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቷል። 6. የታክስ ከፋዮች ምደባ ኢትዮጵያ በተቀበለችው የዓለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ምደባ ደረጃ (ISIC) መሠረት የግብር/ታክስ ከፋዮች ምዝገባ እንዲከናወንና ግብር ከፋዮች በተለያዩ ምድቦች እንዲመደቡ ተደንግጓል። 7. የቅጣት ማስተካከያዎች ✅ የታክስ ደረሰኝ ሳይሰጥ ሲቀር የሚጣለው አስተዳደራዊ ቅጣት በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) እንዲሆን ተሻሽሏል። 8. የድርጅት ኃላፊዎች ተጠያቂነት፡ አንድ ድርጅት የታክስን ህግ በመተላለፍ ወንጀል ሲፈጽም የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም የፋይናንስ ኃላፊ ወንጀሉ እንዲፈጸም የፈቀደ፤ያዘዘ  ወይም የተባበረ እንደሆነ ተጠያቂ ይሆናል።

የታክስ ክሊራንስ ከመሰጠቱ በፊት ኦዲት የሚያስፈልጋቸው አገልግሎቶች 1.  የሚሸጠው ወይም የሚተላለፈው የንግድ ስራ ሀብት ከሃምሳ በመቶ  ያነሰ ከሆነ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት ዴስክ ኦዲት ወይም ውስን የኦዲት ስራ ይከናወናል፡፡ 2.  በከፍተኛ እና በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የሚስተናገድ ታክስ ከፋይ በሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት አጠቃላይ ኦዲት ይደረጋል፡፡ -   ከሃምሳ በመቶ ላይ የንገግድ ስራ ሀብት ለመሸጥ ወይም ለማስተላለፍ፣ -  ድርጅትን በከፊል ሆነ በሙሉ ለመዝጋት፣ -  የንግድ ዘርፍ ለመቀየር ወይም ለመቀነስ ከሆነ፣ -  ድርጅቶች በአንድ ላይ ለመደራጀት ወይም ለመዋሀድ በውህደት የሚፈጠረው ድርጅት የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳን ለመክፈል ግዴታ ገብቶ የሚዋሃድ ስለመሆኑ የሚያስረዳ ሰነድ  ወይም - የንግድ መደብሩ ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ ፣ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ አገልግሎት ሲጠየቅ      3.  በየትኛውም የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኝ አነስተኛ ቅ/ጽ/ቤት ታክስ ከፋዩ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት  እንዲሰጠው ሲጠይቅ ከሀምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ስራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ስራውን ለማቋረጥ ካልሆነ በስተቀር በዴስክ ወይም ውስን ኦዲት ብቻ የሚስተናገድ ይሆናል፡፡ 4.  ከላይ በተራ ቁጥር 3 መሰረት የተገለፀው ቢኖርም አነስተኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ታክስ ከፋይ ከሃምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ስራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ፣በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ስራውን ለማቋረጥ የሚያቀርብበት ጊዜ በአጠቃላይ ኦዲት ተከናውኖ ዕዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ የታክስ ምስክር ወረቀት ይሰጠዋል፡፡ 5. ታክስ ከፋይ ጥያቄውን ባቀረበበት ጊዜ በፋይል ስምሪት አሰራር ሥርዓት ይመራል፡፡

የታክስ ክሊራንስ ከመሰጠቱ በፊት ኦዲት የሚያስፈልጋቸው አገልግሎቶች 1.  የሚሸጠው ወይም የሚተላለፈው የንግድ ስራ ሀብት ከሃምሳ በመቶ  ያነሰ ከሆነ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት ዴስክ ኦዲት ወይም ውስን የኦዲት ስራ ይከናወናል፡፡ 2.  በከፍተኛ እና በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የሚስተናገድ ታክስ ከፋይ በሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት አጠቃላይ ኦዲት ይደረጋል፡፡ -   ከሃምሳ በመቶ ላይ የንገግድ ስራ ሀብት ለመሸጥ ወይም ለማስተላለፍ፣ -  ድርጅትን በከፊል ሆነ በሙሉ ለመዝጋት፣ -  የንግድ ዘርፍ ለመቀየር ወይም ለመቀነስ ከሆነ፣ -  ድርጅቶች በአንድ ላይ ለመደራጀት ወይም ለመዋሀድ በውህደት የሚፈጠረው ድርጅት የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳን ለመክፈል ግዴታ ገብቶ የሚዋሃድ ስለመሆኑ የሚያስረዳ ሰነድ  ወይም - የንግድ መደብሩ ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ ፣ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ አገልግሎት ሲጠየቅ      3.  በየትኛውም የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኝ አነስተኛ ቅ/ጽ/ቤት ታክስ ከፋዩ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት  እንዲሰጠው ሲጠይቅ ከሀምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ስራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ስራውን ለማቋረጥ ካልሆነ በስተቀር በዴስክ ወይም ውስን ኦዲት ብቻ የሚስተናገድ ይሆናል፡፡ 4.  ከላይ በተራ ቁጥር 3 መሰረት የተገለፀው ቢኖርም አነስተኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ታክስ ከፋይ ከሃምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ስራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ፣በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ስራውን ለማቋረጥ የሚያቀርብበት ጊዜ በአጠቃላይ ኦዲት ተከናውኖ ዕዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ የታክስ ምስክር ወረቀት ይሰጠዋል፡፡ 5. ታክስ ከፋይ ጥያቄውን ባቀረበበት ጊዜ በፋይል ስምሪት አሰራር ሥርዓት ይመራል፡፡

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  በ2018 በጀት ዓመት   ዕቅድ  አፈጻጸም  ላይ ውይይት አካሄደ                ሀምሌ 14/2018 ዓ.ም (በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ ጽ/ቤት)  በገቢዎች ሚኒሰቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት በ2018  በጀት ዓመት  ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ያካሄደ ሲሆን   በበጀት ዓመቱ 8.33  ቢሊዮን  ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ  8.36  ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱን 100.29%  ማሳካት መቻሉን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዕቅድ አፈፃፀምና ክትትል  ጀማሪ ባለሙያ አቶ መቅደስ ባዩ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  የማኔጅመንት አባላት ፣ቡድን አስተባባሪዎች እና  የስድስቱ ታክስ ማዕከላት አስተባባሪዎች  በተገኙበት  ከሀምሌ 13-14/2018 ዓ.ም በተደረገ ውይይት ላይ ባቀረቡት ሪፖርት መመልከት የተቻለ ሲሆን የገቢ አሰባሰቡ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር  ብር 3.00  ቢሊዮን ወይንም  56.01% በብልጫ መከናወን መቻሉን ገልጸዋል።   የዕለቱን ውይይት መድረክ  ሲመሩ የነበሩ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ  በበኩላቸው የ2018  በጀት ዓመት  ዕቅድ እንዲሳካ ለማድረግ   ከዕቅድ ዝግጅት  ጀምሮ  በእያንዳንዱ ጉዳዮች ላይ ክትትልና ድጋፍ  በማድረግ በቁርጠኝነት  ያገለገሉ  አመራሮችና ባለሙያዎች ፣  የታክስ ግዴታቸውን በወቅቱ  በመወጣት ግብራቸውን የከፈሉ ግብር ከፋዮችን እና ባለድርሻ አካላትን  በማመስገን  ያስጀመሩት ሲሆን የ2019 በጀት  ዓመት   ዕቅድ  ለማሳከት በባለፈው  ዓመት የታዩ  ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ ስርዓታችንን አጠናክረን በማስቀጠል፣ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለገቢ አሰባሰቡ ማነቆ የሚሆኑ ችግሮችን  በመለየት እርምት እርምጃ በመውሰድ፣ ለግብር ከፋዮች  ተገቢ  ምላሽና አገልግሎት በመስጠት ፣ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ  ስርዓትን በማዘመን ሁሉም  ግብር ከፋዮች ግብርን በኢ-ፋይልንግ ማሳወቂ እንድችሉ በማስተማር ፣  ለተገልጋይ የሚገባውን ክብር በመሰጠትና ከተቋሙ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በኦን-ላይን አገልግሎት መገልገል የሚችሉ አገልግሎቶችን ለይተን በማሳወቅ  ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባ እና ለታክስ ከፋዮች በታክስ ህጎች ላይ  በቂ ስልጠና በመስጠት  ግብር ከፋዮች ለታክስ ህግ ተገዥ እንዲሆኑ በማድረግ በዕቅድ የተያዘው ገቢ  የተሳካ እንድሆን ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በትኩረት  መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥቶ  በማንሳት  የቀጣይ ስራ አቅጣጫ  የሰጡ ሲሆን  ታክስ ማዕከላትን ጨምሮ ከተለያዪ  ስራ ክፍሎች  የተሳታፉ አመራሮች ላቀረቡት  አሰተያየቶችና ጥያቄዎች  ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  በ2018 በጀት ዓመት   ዕቅድ  አፈጻጸም  ላይ ውይይት አካሄደ                ሀምሌ 14/2018 ዓ.ም (በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ ጽ/ቤት)  በገቢዎች ሚኒሰቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት በ2018  በጀት ዓመት  ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ያካሄደ ሲሆን   በበጀት ዓመቱ 8.33  ቢሊዮን  ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ  8.36  ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱን 100.29%  ማሳካት መቻሉን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዕቅድ አፈፃፀምና ክትትል  ጀማሪ ባለሙያ አቶ መቅደስ ባዩ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  የማኔጅመንት አባላት ፣ቡድን አስተባባሪዎች እና  የስድስቱ ታክስ ማዕከላት አስተባባሪዎች  በተገኙበት  ከሀምሌ 13-14/2018 ዓ.ም በተደረገ ውይይት ላይ ባቀረቡት ሪፖርት መመልከት የተቻለ ሲሆን የገቢ አሰባሰቡ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር  ብር 3.00  ቢሊዮን ወይንም  56.01% በብልጫ መከናወን መቻሉን ገልጸዋል።   የዕለቱን ውይይት መድረክ  ሲመሩ የነበሩ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ  በበኩላቸው የ2018  በጀት ዓመት  ዕቅድ እንዲሳካ ለማድረግ   ከዕቅድ ዝግጅት  ጀምሮ  በእያንዳንዱ ጉዳዮች ላይ ክትትልና ድጋፍ  በማድረግ በቁርጠኝነት  ያገለገሉ  አመራሮችና ባለሙያዎች ፣  የታክስ ግዴታቸውን በወቅቱ  በመወጣት ግብራቸውን የከፈሉ ግብር ከፋዮችን እና ባለድርሻ አካላትን  በማመስገን  ያስጀመሩት ሲሆን የ2019 በጀት  ዓመት   ዕቅድ  ለማሳከት በባለፈው  ዓመት የታዩ  ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ ስርዓታችንን አጠናክረን በማስቀጠል፣ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ለገቢ አሰባሰቡ ማነቆ የሚሆኑ ችግሮችን  በመለየት እርምት እርምጃ በመውሰድ፣ ለግብር ከፋዮች  ተገቢ  ምላሽና አገልግሎት በመስጠት ፣ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ  ስርዓትን በማዘመን ሁሉም  ግብር ከፋዮች ግብርን በኢ-ፋይልንግ ማሳወቂ እንድችሉ በማስተማር ፣  ለተገልጋይ የሚገባውን ክብር በመሰጠትና ከተቋሙ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በኦን-ላይን አገልግሎት መገልገል የሚችሉ አገልግሎቶችን ለይተን በማሳወቅ  ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባ እና ለታክስ ከፋዮች በታክስ ህጎች ላይ  በቂ ስልጠና በመስጠት  ግብር ከፋዮች ለታክስ ህግ ተገዥ እንዲሆኑ በማድረግ በዕቅድ የተያዘው ገቢ  የተሳካ እንድሆን ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በትኩረት  መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥቶ  በማንሳት  የቀጣይ ስራ አቅጣጫ  የሰጡ ሲሆን  ታክስ ማዕከላትን ጨምሮ ከተለያዪ  ስራ ክፍሎች  የተሳታፉ አመራሮች ላቀረቡት  አሰተያየቶችና ጥያቄዎች  ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

የፌደራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የወጣው ማሻሻያ አዋጅ መሰረታዊ ዋና ዋና የሚባሉት ለውጦች የሚከተሉት ናቸው። 1. አዳዲስ ትርጓሜዎችና የተቋም ስም ለውጥ v መስማማት (Settlement)፡ የታክስ አለመግባባቶችን በውይይትና በስምምነት ለመፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በትርጓሜ ደረጃ ተካቷል። v የታክስ ማጭበርበር፡ ታክስን ለመሰወር የሚደረጉ እንደ ሐሰተኛ ደረሰኝ ማቅረብና ገቢን መደበቅ ያሉ ተግባራት በዝርዝር ተተርጉመዋል። 2. የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ሥርዓት Ø  ይህ  አዋጁ ይዞት የመጣው ትልቁ ለውጥ፤ ክርክሮችን በፍርድ ቤት ወይም በይግባኝ ኮሚሽን ከመጨረስ ይልቅ በባለሥልጣኑና በታክስ ከፋዩ መካከል በሚደረግ ስምምነት እንዲቋጩ የሚያስችል ነው። ü  የታክስ ባለሥልጣኑ ነጻና ገለልተኛ "አስማሚ" በመመደብ ሂደቱን ያመቻቻል። ü  መስማማት የሚቻለው በታክስ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ከቀረበ በኋላ ሲሆን፣ በዚህ ወቅት ለይግባኝ የተቀመጡ የጊዜ ገደቦች ታግደው ይቆያሉ። ü  የሚደረሰው ስምምነት በጽሁፍ ሆኖ በሁለቱም ወገኖች ከተፈረመ አስገዳጅና ተፈጻሚነት ይኖረዋል። 3.  በአዲስ ማስረጃ አቀራረብ ላይ የተጣለ ገደብ   v ግብር/ታክስ ከፋዮች የታክስ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በቅሬታ ወይም በይግባኝ ወቅት አዲስ ማስረጃ የማቅረብ መብታቸው ተገድቧል። v  አዲስ ማስረጃ ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ማስረጃው የታወቀው ከውሳኔ በኋላ ከሆነ፤ ወይም አቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልቀረበ ብቻ ነው። v  በዚህ መልክ የሚቀርብ አዲስ ማስረጃ በግብር/ታክስ ዕዳው ላይ 20% ቅጣት እንዲከፈል ያደርጋል። 4.  የግብር/ታክስ ስሌት ማሻሻያና የይርጋ ጊዜ v ባለሥልጣኑ የታክስ ማጭበርበር መኖሩን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ካገኘ፣ የታክስ ስሌቱን የማሻሻያ ጊዜ (ይርጋ) እስከ 10 ዓመት እንዲራዘም ተደርጓል።   v መደበኛው የታክስ ስሌት ማሻሻያ ጊዜ ግን በነበረበት 5 ዓመት ቀጥሏል።  ይቀጥላል------

የኤክሣይዝ ታክስ የሚጣልባቸው ዕቃዎች ሐምሌ 10/2018 ዓ. ም ( የገቢዎች ሚኒስቴር ) 👉የቅንጦት ዕቃዎች፡- መሠረታዊ ያልሆኑ የኢኮኖሚ ደረጃን ለማሳየት ጥቅም ላይ የሚውሉ፣ያለነዚህ ዕቃዎች መኖ
የኤክሣይዝ ታክስ የሚጣልባቸው ዕቃዎች ሐምሌ 10/2018 ዓ. ም ( የገቢዎች ሚኒስቴር ) 👉የቅንጦት ዕቃዎች፡- መሠረታዊ ያልሆኑ የኢኮኖሚ ደረጃን ለማሳየት ጥቅም ላይ የሚውሉ፣ያለነዚህ ዕቃዎች መኖር ስለሚቻል፣ ቁጠባን አያበረታቱም ምሳሌ፡- ኮስሞቲክስ፣ ሽቶ 👉ጉዳት የሚያስከትሉ ዕቃዎች፡- በተጠቃሚው ጤና ማህበራዊ ኑሮ እና ኢኮኖሚ ላይ ችግር የሚያስከትሉ ዕቃዎች፡- ሲጃራ፣ አልኮል መጠጥ 👉ፍጆታቸው የማይቀንስ ዕቃዎች:- ዋጋቸው በመጨመሩ ምክንያት እምብዛም የፍላጐት/የፍጆታ መቀነስ የማይታይባቸው ዕቃዎች ምሳሌ፡- ጨው

የታክስ ስርዓት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሄደ፤ (ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት) በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
+5
የታክስ ስርዓት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም  ላይ  ውይይት አካሄደ፤ (ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም  በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ  ቅርንጫፍ ጽ/ቤት) በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የታክስ  ስርዓት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዘርፉ ስር የሚገኙ አመራሮችና  ባለሙያዎች  በተገኙበት የዘርፉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ  አቶ መሀመድአወል ወዳጆ ቀርቦ ሰፊ ውይይት  የተደረገ ሲሆን በሪፖርቱ የበጀት ዓመቱ የዘርፍ አፈፃፀም በዝርዝር ቀርቦ በተለያዩ የሥራ ክፍሎች  የነበሩ ጠንካራ  አፈጻጸሞች ፣ ውስንነቶች እና በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ  ገለጻ አድርገዋል። አቶ መሀመድአወል አክለውም  ለተሳታፊዎች  እንደገለጹት  በባለፈው በጀት  ዓመት የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት ፣የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት በማሻሻልና እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ስራ በመስራት የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ የተሳካ እንድሆን የተለየ  ተነሻሽነት በማሳየት ኃላፊነታችን መውጣት  አለብን  ብሏል። በመጨረሻም ከተለያዩ ስራ ክፍሎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች  ምላሽ በመስጠት  የቀጣይ  ስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል። ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

•  የማንኛውም የንግድ ማህበር፤ የህብረት ሥራ ማህበር ወይም የማንኛውም ዓይነት ማህበር መመስረቻ ጽሑፍና መተዳደሪያ ደንብ ፤ •  ግልግል፡- የተፈጸመበት ሰነድ በሚረጋገጥበት ጊዜ የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልበት ነው፤የቀረጡ አተማመን ስልትም በዋጋው መሠረት የሚከፈል ነው ፡፡ •  ማገቻ (bonds)፡- ሰነድ በሚረጋገጥበት ጊዜ እና በሚመዘገብበት ጊዜ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ በንግድ ህጉ ማገቻ ወይም ቦንድ የአክሲዮን ማህበራት ካፒታላቸውን ለማሳደግ የሚያወጧቸው የግዴታ ወረቀቶችን ይጨምራል ፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ወይም የውል ማስከበሪያ የሚጠይቅ ሰው ዋስትናውን የሚሠጠው በሰነድ ከሆነ   የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል ፡፡ •  የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ/ውል በጽሑፍ የሚደረግ ውል በመሆኑ በሰነዱ ላይ በሚፈጸመው ውል ምክንያት የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ •  ውል፣ ስምምነትና  የእነዚህ መግለጫ፡- በጽሑፍ በሚደረጉበት ጊዜ መብት ወይም ግዴታ የተመሠረተበት፣የተመዘገበበት ወይም የተላለፈበት ወይም የተወገደበት እና የመሳሰሉት መብት እና ግዴታዎች የተመሠረቱበት ሰነድ በጽሑፍ ሲደረግ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ •  የመያዣ ሰነዶች  (ከባንክ ብድር ለመውሰድ መያዣ ሰነድ …)  •  የህብረት ስምምነት •  የሥራ ውል /ቅጥር/ የተለየ የውል አደራረግ ባይኖረውም አሠሪው ከሠራተኛው ጋር የሥራ ውል በሚፈጽምበት ወቅት ሠራተኛው በውሉ መሠረት የተቀጠረበትን ጽሑፍ የመሥጠት ግዴታ ያለበት በመሆኑ የቅጥር ውሉ በጽሑፍ ቢደረግም ባይደረግም አሠሪው በሠራተኛው የቅጥር ፋይል ወይም መዝገብ መሠረት የቴምብር ቀረጥ የመክፈል ግዴታ አለበት ፡፡ •  የኪራይ፣የተከራይ አከራይ እና መሰል መብት የማስተላለፊያ ሰነዶች ፤ •  ለማስረጃነት ማረጋገጫ የሚያስፈልጋቸው ሰነዶች የሚደራጁበትን እና የሚረጋገጡበትን አግባብ በፍትሐብሔር ህግ ከአንቀጽ 146 እስከ 153 ድረስ ተደንግጓል፡፡ •  የውክልና ሥልጣን •  የንብረት ባለቤትነትን  ማሰመዝገቢያ  ሰነድ  ናቸው ፡፡