uk
Feedback
ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ M.O.R Hawassa Branch

ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ M.O.R Hawassa Branch

Відкрити в Telegram

ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

Показати більше
3 258
Підписники
Немає даних24 години
+97 днів
+7930 день
Архів дописів
•  የማንኛውም የንግድ ማህበር፤ የህብረት ሥራ ማህበር ወይም የማንኛውም ዓይነት ማህበር መመስረቻ ጽሑፍና መተዳደሪያ ደንብ ፤ •  ግልግል፡- የተፈጸመበት ሰነድ በሚረጋገጥበት ጊዜ የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልበት ነው፤የቀረጡ አተማመን ስልትም በዋጋው መሠረት የሚከፈል ነው ፡፡ •  ማገቻ (bonds)፡- ሰነድ በሚረጋገጥበት ጊዜ እና በሚመዘገብበት ጊዜ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ በንግድ ህጉ ማገቻ ወይም ቦንድ የአክሲዮን ማህበራት ካፒታላቸውን ለማሳደግ የሚያወጧቸው የግዴታ ወረቀቶችን ይጨምራል ፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ወይም የውል ማስከበሪያ የሚጠይቅ ሰው ዋስትናውን የሚሠጠው በሰነድ ከሆነ   የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል ፡፡ •  የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ/ውል በጽሑፍ የሚደረግ ውል በመሆኑ በሰነዱ ላይ በሚፈጸመው ውል ምክንያት የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ •  ውል፣ ስምምነትና  የእነዚህ መግለጫ፡- በጽሑፍ በሚደረጉበት ጊዜ መብት ወይም ግዴታ የተመሠረተበት፣የተመዘገበበት ወይም የተላለፈበት ወይም የተወገደበት እና የመሳሰሉት መብት እና ግዴታዎች የተመሠረቱበት ሰነድ በጽሑፍ ሲደረግ የቴምብር ቀረጥ ይከፈልበታል፡፡ •  የመያዣ ሰነዶች  (ከባንክ ብድር ለመውሰድ መያዣ ሰነድ …)  •  የህብረት ስምምነት •  የሥራ ውል /ቅጥር/ የተለየ የውል አደራረግ ባይኖረውም አሠሪው ከሠራተኛው ጋር የሥራ ውል በሚፈጽምበት ወቅት ሠራተኛው በውሉ መሠረት የተቀጠረበትን ጽሑፍ የመሥጠት ግዴታ ያለበት በመሆኑ የቅጥር ውሉ በጽሑፍ ቢደረግም ባይደረግም አሠሪው በሠራተኛው የቅጥር ፋይል ወይም መዝገብ መሠረት የቴምብር ቀረጥ የመክፈል ግዴታ አለበት ፡፡ •  የኪራይ፣የተከራይ አከራይ እና መሰል መብት የማስተላለፊያ ሰነዶች ፤ •  ለማስረጃነት ማረጋገጫ የሚያስፈልጋቸው ሰነዶች የሚደራጁበትን እና የሚረጋገጡበትን አግባብ በፍትሐብሔር ህግ ከአንቀጽ 146 እስከ 153 ድረስ ተደንግጓል፡፡ •  የውክልና ሥልጣን •  የንብረት ባለቤትነትን  ማሰመዝገቢያ  ሰነድ  ናቸው ፡፡

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ ሀምሌ 1/2018 ዓ.ም (በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ ጽ/ቤት) በገቢዎች ሚኒሰቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ
+3
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  የእንኳን ደስ ያላችሁ  መልዕክት  አስተላለፉ                ሀምሌ 1/2018 ዓ.ም (በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ ጽ/ቤት)  በገቢዎች ሚኒሰቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት በ2018  በጀት ዓመት  የገቢ ዕቅድ ከታቀዳው በላይ ማሳካት መቻሉን አስመልክቶ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ  እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የተሰማቸውን ደስታ  የገለጹ ሲሆን  ከመድረኩ  ባስተላላፉት መልዕክት  ለዕቅዱ መሳካት መላው  የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  ሰራተኞች ፣ ግብር ከፋዮች እና ባለድርሻ አካላት ላደረጉት አስተዋጽኦ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስም አመስግነዋል።    ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  በ2018 በጀት ዓመት  የዘጠኝ  ወር ዕቅድ  አፈጻጸም  ላይ ውይይት አካሄደ                ሚያዝያ 12/2018 ዓ.ም (በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ ጽ/ቤት)  በገቢዎች ሚኒሰቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት በ2018  በጀት ዓመት  በዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ያካሄደ ሲሆን   በሶስተኛ ሩብ ዓመት  5,814.08 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 5,924 ሚሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ የእቅዱን 101%  ማሳካት መቻሉን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዕቅድ አፈፃፀምና ክትትል  ጀማሪ ባለሙያ አቶ መቅደስ ባዩ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ  የማኔጅመንት አባላት ፣ቡድን አስተባባሪዎች እና  የስድስቱ ታክስ ማዕከላት አስተባባሪዎች  በዙም በተሳተፈበት በዛሬ ቀን በተደረገ ውይይት ላይ ባቀረቡት ሪፖርት መመልከት የተቻለ ሲሆን የገቢ አሰባሰቡ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር  ብር 2.50  ቢሊዮን ወይንም 73.24% በብልጫ መከናወን መቻሉን ገልጸዋል።  በዚህ መሰረት የዕለቱን ውይይት መድረክ  ሲመሩ የነበሩ የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ  በበኩላቸው የ2018 በጀት ዓመት  የዘጠኝ  ወር ዕቅድ እንዲሳካ ለማድረግ   አመራሮች እና ሰራተኞች  ከዕቅድ ዝግጅት  ጀምሮ  በእያንዳንዱ ጉዳዮች ላይ ክትትልና ድጋፍ  በማድረግ ፣በቁርጠኝነት  በመስራት ፣ ለታክስ ህግ ተገዥ በመሆን  ከራሳቸው የሚጠብቅባቸውን የታክስ ግዴታቸውን በወቅቱ  በመወጣት ግብራቸውን የከፈሉ ግብር ከፋዮችን እና ባለድርሻ አካላትን  በማመስገን  ያስጀመሩት ሲሆን የቀጣይ  ሶስት ወር   ዕቅድ  ለማሳከት በባለፈው  ዘጠኝ ወር ውስጥ   የነበረን ጥሩ የገቢ አሰባሰብ ስርዓታችንን አጠናክረን በማስቀጠል፣ ለገቢ አሰባሰቡ ማነቆ የሚሆኑ ችግሮችን  በመለየት እርምት እርምጃ በመውሰድ፣ለግብር ከፋዮች  ተገቢ ምላሽና አገልግሎት በመስጠት ፣ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ  ስርዓትን በማዘመን ሁሉም  ግብር ከፋዮች ግብርን በኢ-ፋይልንግ ማሳወቂ እንድችሉ በመደገፍ፣  ለተገልጋይ የሚገባውን ክብር በመሰጠትና ከተቋሙ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በኦን-ላይን አገልግሎት መገልገል የሚችሉ አገልግሎቶችን ለይተን በማሳወቅ  ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባ እና ለታክስ ከፋዮች በታክስ ህጎች ላይ  በቂ ስልጠና በመስጠት  ግብር ከፋዮች ለታክስ ህግ ተገዥ እንዲሆኑ በማድረግ በዕቅድ የተያዘው ገቢ  የተሳካ እንድሆን ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በትኩረት  መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥቶ  በማንሳት  የቀጣይ ስራ አቅጣጫ  የሰጡ ሲሆን  ታክስ ማዕከላትን ጨምሮ ከተለያዪ  ስራ ክፍሎች  የተሳታፉ አመራሮች ላነሱት  አሰተያየቶችና ጥያቄዎች  ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።   ገቢዎችን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ይጫኑ፦ በቴሌግራም https://t.me/MORHawassaBranch በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100080114927205 በዩትዩብ https://youtube.com/channel/UCtu9M68G_lQbTIsu1fzzjyw

የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ እንዲፈቀድለት የሚጠይቅ ታክስ ከፋይ ማሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታ v የክፍያ ጊዜ ስምምነት በሚገባባቸው ዕዳዎች 25%ቅድሚያ መክፈል አለበት፡፡(የቅድመ ክፍያው መሰረት ፍሬ ታክስ ፣ወለድ እና የማይነሳ መቀጫ ነው) v የክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ ጥያቄ የቀረበው ሀብት ከተያዘ በኋላ ሲሆን የታክስ ባለሥልጣኑ የታክስ ከፋዩን ሀብት ለመያዝና ለማስተዳደር ያወጣውን ወጪዎችን እና የታክስ ዕዳውን 25% ቅድሚያ ክፍያ መክፈል አለበት v ጉዳዩ በፍርድ ቤት ወይም በፍርድ አፈጻፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን ታክስ ከፋዩ የታክስ ባለሥልጣኑ የታክስ ዕዳ አሰባሰቡን ለመከታተል ያወጣቸውን ወጪዎችን በሙሉ በቅድሚያ መክፈል ይኖርበታል፤ v የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ደረሶት በውሳኔው ላይ ባለመሰማማት ለታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ የሰራ ክፍል ቅሬታውን ሲያቀርብ  አምኖ የከፈለው ታክስ ወይም ለታክስ ይግባኝ ኮሚሺን ወይም ወደ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ቅሬታውን ሲያቀርብ የከፈለው ታክስ የመክፈያ ጊዜ ስምምነት በሚገባበት ጊዜ አስቀድሞ ከዕዳው ላይ ተቀናሽ ይደረግለታ፤ v ወለድ የሚታሰበው ባልተከፈለው ወይም በሚቀረው ፍሬ ታክስ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡   በልዩ ሁኔታ የሚሰጥ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ Ø  በልዩ ሁኔታ የመክፈያ ጊዜ እንዲራዘም የሚቀርቡ ጥያቄዎች የሚቀርቡት ለቅ/ጽ/ቤቱ ይሆናል፤ Ø  ቅ/ጽ/ቤቱ ከታክስ ከፋዩ የሚፈለግ የታክስ ዕዳ መጠን፤ የታክስ ዓይነት፤ የታክስ ዕዳው ያለበት ሁኔታ(status)፤ የታክስ ከፋዩ አከፋፈል ታርክ፤ በልዩ ሁኔታ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የተጠየቀበትን ተጨባጭ ምክንያት (ማስረጃ) እና ከታክስ ከፋዩ ጥያቄ አንጻር የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን ዝርዝር የውሳኔ ሀሳብ በሥራ አስኪያጁ ተፈርሞ ለታክስ ዕዳ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ይላካል፡፡ Ø  የታክስ ዕዳ አስተዳደር ዳይሬክቶሬቱ ከቅ/ጽ/ቤቱ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ለሚኒስትሩ ወይም ለወከለው የሥራ ኃላፊ አቅርቦ በሚወሰነው መሠረት እንዲፈፀም ለቅ/ጽ/ቤቱ መልሶ ያስተላልፋል፡፡ Ø  ሚኒስትሩ ወይም ሚኒስተሩ ወከለው የሥራ ኃላፊ የክፍያ ስምምነት ለገባ ታክስ ከፋይ ያለበትን የእዳ ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት የቅድሚያ ክፍያውን እስከ 15 በመቶ ዝቅ ሊያደርግ ይችላል፡፡   የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ ጥያቄ አቀራረብ፣ ስለሚፈቅደው አካል እና አፈፃፀም ሥርዓት o   የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ በአንዴ የመክፈል አቅም የሌለው መሆኑን ገልጾ ጥያቄውን ለቅ/ጽ/ቤቱ የታክስ ዕዳ አስተዳደር ሥራ ሂደት ሲያቀርብ እና ምክንያቱ ተቀባይነት ሲያገኝ የሚስተናገድ ይሆናል፡፡ o   ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበ የክፍያ ጊዜ ስምምነት ከሆነ የታክስ ዕዳ አስተዳደር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ሊፈቅድ ይችላል፡፡ o    ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበ የክፍያ ጊዜ ስምምነት ከሆነ የታክስ ዕዳ አስተዳደር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ሊፈቅድ ይችላል፡፡ o   በድጋሚ የቀረበ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ ከሆነ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ የሚፈቅድ ይሆናል፡፡ o   ታክስ ከፋዩ ያቀረበው የታክስ ዕዳ አስተዳደር ባለሙያ የስምምነት ውል በማዘጋጀት ለሥራ ሂደት መሪው አቅርቦ እንዲፈረም ያደርጋል፡፡ o   የክፍያ ጊዜ ስምምነት ውል በ3 ኮፒ ተዘጋጅቶ ዋናው ኮፒ ከማህደር ጋር ይያያዛል፣ 2ኛው ኮፒ ለግብር ከፋዩ ይሰጣል፣ 3ኛው ኮፒ በታክስ ዕዳ ክትትል ሥራ ሂደት ለቀጣይ የክትትል ሥራ የሚያዝ ይሆናል፡፡ o    የክፍያ ጊዜ ስምምነት ውል በ3 ኮፒ ተዘጋጅቶ ዋናው ኮፒ ከማህደር ጋር ይያያዛል፣ 2ኛው ኮፒ ለግብር ከፋዩ ይሰጣል፣ 3ኛው ኮፒ በታክስ ዕዳ ክትትል ሥራ ሂደት ለቀጣይ የክትትል ሥራ የሚያዝ ይሆናል፡፡ o   የክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የተፈቀደለት ታክስ ከፋይ በውሉ መሠረት በየወሩ ካልከፈለ ታክስ ከፋዩ ክፍያውን ካቆመበት ጊዜ አንስቶ ያልተከፈለውን ቀሪ ክፍያ እና ቀሪ መቀጫ ተሰልቶ በሙሉ እንዲከፍል በታክስ ባለሥልጣኑ የዕዳ አሰባሰብ የሥራ ክፍል በታክስ ሕጉ መሠረት እርምጃ ሊወስድ ይችላል፡፡ o    ክፍያ ያቋረጠው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋገጠ አቋርጦት የነበረውን ታክስ በስምምነት ውል ጊዜ ውስጥ ያልከፈለውን ወራት አጠቃሎ እና የወጡ ወጪዎችን ጨምሮ የከፈለ ከሆነ የስምምነቱ ውል ሳይሰረዝ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡

ታክስ የሚከፈልበትን የስራ እንቅስቅሴ በማይንቀሳቀስ የስራ ቦታ የሚያከናውን ማናቸውም የተመዘገበ ሰው፡- . ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ በሚያካሂድበት ዋንኛ የስራ ቦታ በግልጽ በሚታይ ስፍራ ዋናውን የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የመለጠፍ፤ . የተሠጠውን የተጨማ ዕሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ቅጂ ታክስ የሚከፈልበት እንቅስቃሴ በሚያካሂድባቸው ሌሎች የስራ ቦታዎች ሁሉ በግልጽ በሚታይ ሥፍራ የመለጠፍ ግዴታ አለበት፡፡ . የተመዘገበ ሰው ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበበትን ዝርዝር መረጃ ታክስ የሚከልበትን ስራ በሚያከናውንበት ዌብሳይት እና የማህበራዊ ሚዲያ አድራሻ ላይ ማስፈር አለበት፡፡ . የተመዘገበው ሰው ከታች በተዘረዘሩት መረጃዎች ላይ ለውጥ ሲያጋጥም ይህንኑ ለውጥ በ30 ቀን ጊዜ ውስጥ ለታክሱ ባለስልጣን ማስታወቅ አለበት፡፡ • የተመዘገበው ሰው የስልክ ቁጥር፣ የፋክስ ቁጥር፣ የኤሌክትሮኒክ እና ሌሎች የግንኙት አድራሻዎች፤ • አዳዲስ ቅርንጫፎችን ወይም የሥራ ክፍሎችን መክፈትና መዝጋትን እንዲሁም የኢንተርኔት ወይም የማህበራዊ ሚዲያ አድራሻ መለወጥን ጨምሮ የተመዘገበው ሰው ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ በሚያከናውንበት ቦታ ወይም በሚያከናውንባቸው ቦታዎች፤ • የተመዘገበው ሰው የንግድ ሥራ ባህሪ፣ እና ስሙ፣ ቋሚ አድራሻው ወይም የፓስፖርት አድራሻ፣ የተቋቋመበት መተዳደሪያ ደንብ ወይም ዋንኛ የስራ እንቅስቃሴው፤ • ከባለስልጣኑ ጋር ግንኙነት የሚያርግበት የባንክ አድራሻ፤ • ከባለስልጣኑ ጋር ግንኙነት የሚደርግበት የኤልክትሮኒክ አድራሻ

የክፍያ ጊዜ ስምምነት ስለሚፈቅደው አካል እና የጊዜ ገደብ v ታክስ ከፋዩ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከተቀመጠው ከዝቅተኛው የታክስ ዕዳ  መጠን በታች ሆኖ ታክስ ከፋዩ በአንድ ጊዜ መክፈል የማይችል መሆኑ ከተረጋገጠ የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ለአንድ ጊዜ ከ3 ወር ላልበለጠ ጊዜ እንዲራዘምለት ሊፈቅድ ይችላል፡፡   v ታክስ ከፋዩ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ራሱ አስታውቆ የሚከፍለውን የንግድ ትርፍ ግብር መክፈል አለመቻሉን ጠቅሶ ሲያመለክት ጥያቄውን የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አሳማኝ ምክንያት መሆኑን ሲያረጋግጥ ከ3 ወር ላልበለጠ ጊዜ እንዲራዘምለት ሊፈቅድ ይችላል፡፡ v  ይህ ቢኖርም ታክስ ከፋዩ ለ3 የግብር ዘመን ተመሳሳይ ጥያቄ የሚያቀርብ ከሆነ የታክስ ዕዳ መክፈያ ጊዜ አይራዘምለትም፡፡   ü በከፍተኛ ታክስ ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ በሁሉም የታክስ ዓይነቶች የሚፈለግበት ጠቅላላ ዋና ታክስ፣ መቀጫ እና ወለድ ዕዳ:- o   ከብር 1,500,000 /አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ- 5,000,000 ሚሊዮን ከሆነ እስከ 6 ወር o   ከብር 5 ሚሊዮን አንድ- ብር 9 ሚሊዮን  ከሆነ እስከ 8 ወር፣ o   ከብር 9 ሚሊዮን  አንድ እስከ 15 ሚሊዮን ከሆነ እስከ 1ዐ ወር፣ o   ከብር 15 ሚሊዮን አንድ በላይ ከሆነ እስከ 12 ወር የክፍያ ጊዜ ሊሰጥ ይችላል፡፡   ü በመካከለኛ ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው በሁሉም የታክስ ዓይነቶች የሚፈለግበት ዋና ታክስ፣ መቀጫና ወለድ ዕዳ:-   o   ከብር 500ሺ- ብር 1,500,000/ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ/ ከሆነ 3 ወር፣ o   ከብር 1 ሚሊዮን 5 መቶ ሺ አንድ እስከ 3 ሚሊዮን ከሆነ እስከ 6 ወር፣ o   ከብር 3 ሚሊዮን አንድ እስከ 4 ሚሊዮን 75ዐ ሺ ከሆነ እስከ 8 ወር፣ o   ከብር  4 ሚሊዮን 75ዐሺ አንድ እስከ ብር 6 ሚሊዮን ከሆነ እስከ 1ዐ ወር፣ o   ከብር 6 ሚሊዮን  በላይ ከሆነ 12 ወር፣ የክፍያ ጊዜ ሊሰጥ ይችላል፡፡ o   በአነስተኛ ታክስ ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ በሁሉም የታክስ ዓይነቶች የሚፈለግበት ጠቅላላ ዋና ታክስ፣መቀጫ እና የወለድ ዕዳ:-   ü በአነስተኛ ታክስ ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ በሁሉም የታክስ ዓይነቶች የሚፈለግበት ጠቅላላ ዋና ታክስ፣መቀጫ እና የወለድ ዕዳ:- o   ከብር 50 ሺ እስከ 100ሺ ከሆነ እስከ 3 ወር፣ o   ከብር 100 ሺ  አንድ ብር እስከ 350 ሺ ከሆነ እስከ 6 ወር፣ o   ከብር 350 ሺ አንድ ብር  እስከ 75ዐ ሺ ከሆነ እስከ 8 ወር፣ o   ከብር 75ዐ ሺ አንድ ብር እስከ 2 ሚሊዮን ከሆነ እስከ 1ዐ ወር፣ o   ከብር 2 ሚሊዮን በላይ ከሆነ እስከ 12 የክፍያ ጊዜ ሊሰጥ ይችላል፡፡   ü  በጥቃቅን ታክስ ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የደረሰው ታክስ ከፋይ በሁሉም የታክስ ዓይነቶች የሚፈለግበት ጠቅላላ ዋና ታክስ፣ መቀጫ እና ወለድ ዕዳ:-   o   ከብር 10 ሺ እስከ 25 ሺ ከሆነ እስከ 3 ወር፣ o   ከብር 25 ሺ አንድ-5ዐ ሺ ከሆነ እስከ 6 ወር፣ o   ከብር 5ዐ ሺ አንድ-75 ሺ ከሆነ እስከ 8 ወር፣ o   ከብር 75 ሺ አንድ እስከ 10ዐ ሺ ከሆነ እስከ 1ዐ ወር፣ o   ከብር 100 ሺ በላይ ከሆነ እስከ 12 ወር የክፍያ ጊዜ ሊሰጥ ይችላል፡፡ Ø   የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የተሰጠው ታክስ ከፋይ ከታክስ ባለሥልጣኑ ጋር የክፍያ ጊዜ ስምምነት እንዲፈርም ይደረጋል፡፡

የራስ ታክስ ስሌት ጥያቄ አቀራረብና አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር181/2015 የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያ ማሻሻል” ማለት ታክስ ከፋዩ በራሱ ውሳኔ መጀመሪያ ባቀረበው የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ላይ የተገለፀውን የታክስ መጠን በመጨመር ወይም በመቀነስ ወይም ሌላ ለውጥ በማድርግ የሚያቀርበው ማሻሻያ ነው፡፡ 1. የራስ ታክስ ስሌት የሚሻሻልበት ምክንያት Ø  የሂሳብ ስሌት ስህተት ሲኖር፤ Ø  የገቢ እና የወጪ አመዘጋገብ ስህተት ሲያጋጥም፤ Ø  ከሒሳብ መደብ አመራረጥ (Chart of Account) ጋር የተያያዘ ስህተት ሲኖር፤ Ø   የጆርናል ምዝገባ ስህተት ሲኖር፤ Ø  ሂሳብ ወደ ሌጀር ሲተላለፍ የተከሰተ ስህተት ሲያጋጥም፤ Ø   ከሒሳብ ማስተካከያ (Adjusting Entry) ጋር የተያያዘ ስህተት ሲያጋጥም፤ Ø  በሒሳብ መዘገብ ላይ ሳይመዘገብ የተዘለለ የገቢና ወጪ ሰነድ ሲኖር፤ Ø  የመጀመሪያ ወይም የመጨረሻ ሀብት ቆጠራ አያያዝ ስህተት ሲኖር፤ Ø  በውጭ ኦዲተሮች እና በቦርዱ በቀረበ የኦዲት ምርመራ ሪፖርት የቀረበ ማስተካከያ ሲያጋጥም፤ Ø  ሦስተኛ ወገን በሚሰጠው ማረጋገጫ ወይም በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔ መሰረት በሂሳብ መዝገቡ ላይ ማስተካከያ ማድረግ ሲያስፈልግ፣    Ø  በታክስ ሕግ ያልተፈቀደ ወጪ በተቀናሽነት በመያዙ ምክንያት  የተፈጠረ ስህተት ሲኖር፤ Ø   የግልና የንግድ ሒሳቦች በመቀላቀላቸው የተፈጠረ ስህተት ሲያጋጥም፤ Ø  በታክስ ማስታወቂያ ቅፅ ላይ የአመዘጋገብ ወይም የአገላለጽ ስህተት ሲያጋጥም፣ Ø  ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ለታክስ ስሌት የሚያስፈልጉ ሰነዶች ሳይሟሉበመቅረታቸው ታክስ ከፋዩ በእጁ ያሉትን ሰነዶች ብቻ መሠርት በማድርግ ሌላውን ታክስ በግምት ባሰላው የራስ ታክስ ስሌት መሠርት አሳውቆ ከከፈለ በኋላ የተሟላ ሰነድ ማቅርብ በቻለበት ጊዜ፤  Ø  ከተጨማሪ እሴት ታክስ እና ከኤክሳይዝ ታክስ ጋር በተያያዘ በታክስ ማስታወቂያ ውስጥ ሳይካተት የቀረ ታክስ ወይም ከተቀናሽ ሂሳብ አያያዝ እና የተመላሽ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ስህተት ሲያጋጥም፣ 2. የራስ ታክስ ስሌት እንዲሻሻል የሚቀርብ ማመልከቻ ü ታክስ ከፋዩ ያቀረበው ማመልከቻ ላይ የታክስ ስሌቱን ለማሻሻል ምክንያት የሆኑትን ጉዳዮች በዝርዝር መጥቀስ አለበት፡፡ ü ታክስ ከፋዩ ያቀረበው ማመልከቻ ከቀረበበት ቀን በፊት ባሉ 5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ በነበሩ የራስ ታክስ ስሌቶች ላይ ለውጥ የሚያመጣ ከሆነ የሁሉም ዘመናት የታክስ ስሌት ማሻሻያ በአንድነት ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ü የታክስ ስሌት ማሻሻያ እንዲደረግ የተጠየቀበትን የታክስ ጊዜ እና ዓይነት፤ ü ማሻሻያ የሚደረግበትን ጉዳይ እና ምክንያቱን ፣ ü ማሻሻያ እንዲደረግበት የተጠየቀው ጉዳይ የሚያስከተለው የገንዘብ ወይም ሌላ ለውጥ፣ ü በሚሻሻለው የታክስ ስሌት የተገለፀው የታክስ መጠን ወይም ወደፊት የሚሸጋገር ኪሣራ ወይም በብልጫ የተከፈለ የግብዓት መጠን የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡ ü  የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያ እንዲሻሻል የሚቀርበው ማመልከቻ ከማሻሻያ ምክንያቶቹ እና አስፈላጊ ከሆኑ ሰነዶች ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡ ü ሚኒስቴሩ የራስ ታክስ ስሌት ማሻሻያ እንዲደረግበት የሚቀርብለትን ማመልከቻ ተቀብሎ ከተቀበለበት ቀን ጀምሮ ባሉት አንድ መቶ ሃያ ቀናት ውስጥ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል 3. የራስ ታክስ ስሌት ማሻሻያ ጥያቄ የሚከለከልባቸው ሁኔታዎች v ሚኒስቴሩ የመጀመሪያ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ(official assessment notice)  ከሰጠ በኋላ ወይም አጠቃላይ ኦዲት ወይም ኢንቨሰቲገሽን ኦዲት በመደረግ ሂደት ላይ የሚገኝ ከሆነ ታክስ ከፋዩ የሚያቀርበው የራስ ታክስ ስሌት ማሻሻያ (amendment of selfassessment) ጥያቄ ተቀባይነት አይኖረውም v አንድ ጊዜ የታክስ ስሌት ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ የቀረበበት የራስ ታክስ ስሌት በድጋሚ ማሻሻያ እንዲደረግበት ጥያቄ ሊቀርብበት አይችልም፡፡ v  ከላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ሚኒስቴሩ በራሱ አነሳሽነት የተሻሻለ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ ሊሰጠው ይችላል፡፡

የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ፡-ማለት ማንኛውም ታክስ ከፋይ በአዋጁ መሰረት የመክፍያ ጊዜ የደረሰ ወይም በወቅቱ ያልተከፈል የታክስ ዕዳን ለመክፍል ጊዜ እንዲራዘምለት ሲያመለክት ከመደበኛው የታክስ መክ
የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ፡-ማለት ማንኛውም ታክስ ከፋይ በአዋጁ  መሰረት የመክፍያ ጊዜ የደረሰ ወይም በወቅቱ ያልተከፈል የታክስ ዕዳን ለመክፍል ጊዜ እንዲራዘምለት ሲያመለክት ከመደበኛው የታክስ መክፍያ ጊዜ በተለየ ሁኔታ እንዲከፈል የሚሰጥ የክፍያ ጊዜ ነው፡፡ v ይህ የተፈቀደለት ታክስ ከፋይ በዘገየው ክፍያ ላይ ከመጀመሪያ የታክስ መክፈያ ቀን ጀምሮ የሚታሰብ ወለድ የመክፈል ግዴታውን አያስቀርም፡፡ v በቀረበ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ ማመልከቻ ላይ የታክስ ባለሥልጣኑ የሰጠውን ውሳኔ የሚገልፅ የጽሑፍ ማስታወቂያ ማመልከቻው በቀረበ በ3ዐ ቀናት ውስጥ ይሰጣል፡፡ v የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የሚፈቀድባቸው ሁኔታዎች Ø  ታክስ ከፋዩ የታክስ ዕዳውን በአንድ ጊዜ መክፈል የማይችል ሲሆን፣ Ø  ሀብት በዕዳ የተያዘበት ወይም ንብረት እንዲሸጥ ጨረታ የወጣበት ታክስ ከፋዩ ዕዳውን ለመክፈል ጥያቄ ያቀረበ እንደሆነ ለዕዳው ተመጣጣኝ የሆነ የባንክ ዋስትና ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል፡፡ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የማይፈቀድባቸው ሁኔታዎች Ø በታክስ ማስታወቂያ (በራስ ታክስ ስሌት ማስታዎቂያ) ጊዜ መከፈል ያለበት የታክስ ዕዳ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ወይም ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ ገቢ መደረግ ያለበት ሲሆን፣ Ø አስቀድሞ የክፍያ ጊዜ ስምምነት የተሰጠው ሆኖ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ከአቅም በላይ ባልሆነ ምክንያት ዕዳውን ያልከፈለ ሆኖ ሲገኝ፣ Ø የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የተጠየቀበት የታክስ ዕዳ መጠን እንደ ታክስ ከፋዩ አመዳደብ ከተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በታች ከሆነ፣  ለዕዳው ማስከፈያ ሃብት እና ንብረት የተያዘበት ከሆነ፣ በዕዳ  የተያዘበትን ንብረት ለመሸጥ የጨረታ ማስታወቂያ የወጣበት ከሆነ፣ የክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የሚሰጠው ለዕዳው ተመጣጣኝ የሆነ የባንክ ዋስትና ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል::

የታክስ_አስተዳደር_አዋጅ_የተሻሻለው.pdf5.57 KB

የታክስ_አስተዳደር_አዋጅ_የተሻሻለው_@Taxation_in_Ethiopia_Tax_Administration.pdf5.57 KB

21ኛ ROUND 17-10-2018.xlsx0.14 KB

ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ M.O.R Hawassa Branch - Статистика та аналітика Telegram каналу @morhawassabranch