ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፳፪ (22) ቀን።
❤ እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ዑራኤል ለሢመቱ (ለተሾመበት) ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ የዚህ ሳንምት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፮ "እሙነ ኮነ ልደቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ አዝ፣ እምሰማያት ወረደ ወእመላእክት ተአኵተ ወእማርያም ተወልደ፤ አዝ፣ በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ወአስተርእየ ገሃደ፤ አዝ፣ ውእቱ እክሊለ ሰማዕት ውእቱ መድኃኔ ነገሥት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ እሙነ ኮነ ልደቱ ብርሃነ ኮነ መጽአቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ። ትርጉም፦ የጌታችን የመድኃኒታችን የክርስቶስ ልደት እውነት ነው ከሰማያት ወረደ በመላእክት ዘንድ ተመሰገነ ከማርያም ተወለደ እርሱም የሰማዕታት አክሊል ነው ነገሥታት መድኃኒት ነው የአሕዛብ እረኛቸው ነው የመድኃኒታችን የክርስቶስ ምጽአቱ ብርሃን ልደቱ እውነት ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ "እምርተ ዕለት በዓለ ሢመትከ ዛቲ። ድኅረ ዕረፍተ እም ኪዳነ እስመ ተወከፍከ ባቲ። ዑራኤል ሥዩም ካህነ መስቀል አሐቲ። ማኅበረነ ዕቀብ ኵለሄ እምቅኔተ ሰይጣን መስሐቲ ወጽዋዓ እዴከ ፈኑ ጽሙዓነ ታስቲ"። ትርጉም፦ ቅዱስ ዑራኤል ሆይ ይህች የበዓል ሢመትህ ዕለት እጅግ የከበረች የተመረጠች ዕለት ናት። ከድንግል ዕረፍት በኋላ ቃል ኪዳን የተቀበልክባት ቀን ናትና። ቅዱስ ዑራኤል ሆይ በምዕመን መስቀል ላይ የተሾምክ ታማኝ አገልጋይ ካህን ነህና። አሳሳች ነፃ አውጥተህ። ማኅበራዊ አድነታችንን ለሁል ጊዜ ጠብቅ። ሃይማኖት ጥመኖችንም ታጠጣ ዘንድ የእጅህን ጽዋ ላክልን። መልክአ ቅዱስ ዑራኤል።
+ + +
❤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል፡- ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር የተባሉ ሦስት የመላእክት ከተሞች አሉ፡፡ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክት ከፈጠራቸው በኋላ በነገድ 100 በአለቃ 10 አድርጎ በሦስቱ ሰማያት አስፍሯቸዋል፡፡ ኢዮርን በ4፣ ራማን በ3፣ ኤረርንም በ3 ከፍሎ ነው በዓሥሩ ከተማ ያሰፈራቸው፡፡
❤ በዚህም መሠረት ኢዮርን ላይና ታች አድርጎ በ4 ከተማ ከፍሏታል፡፡ በእርሷ ያሉትን መላእክትን በ40 ነገድ 4 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያው ነገድ "አጋእዝት" ይባላሉ፡፡ አለቃቸው ሣጥናኤል ነበር፤ እርሱም የመላእክትን ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርግ ነበር፡፡ ከክብሩ ሲዋረድ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ ተሹሞበታል፡፡ ሁለተኛው ነገድ "ኪሩቤል" ይባላሉ፡፡ እነርሱም መንበረ ሥላሴን ይሸከማሉ፡፡ የቀሳውስት አምሳል ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ሰብና ገጸ አንበስ ናቸው፡፡ በሦስተኛው ከተማ በኢዮር ያሉት "ሱራፌል" ይባላሉ፡፡ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፡፡
❤ በትንቢተ ኢሳያስ በምዕራፍ 6 ላይ የተገለጹትና ኢሳያስን ከለምጹ እንዲፈወስ ያደረጉት ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ላህምና ገጸ ንስር ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ "ከሩቤል" ወይም "ሱራፌል" የሚባሉ የግለሰብ መጠሪያ ስሞች ስህተት ናቸው፡፡ አንደኛ እነዚህ ስሞች የብዙ መላእክት መጠሪያን የሚወክሉ ናቸው፡፡ ለአንዱ ሲሆን "ኪሩብ፣ ሱራፊ" ይባላል፡፡ "ኪሩቤል" ወይም "ሱራፌል" ማለት ግን የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የቅዱሳን መላእክትን ስም እንዳለ በቁሙ ወስዶ ለግል መጠሪያ ስም ማዋል ተገቢ አይደለም፡፡ "ወለተ ሚካኤል፣ ክብፈ ገብርኤል…." እየተባሉ ይሰየማሉ እንጂ ቀጥታ "ሚካኤል"፣ "ገብርኤል" እያሉ ሰዎችን መሰየም ስህተት ነው፡፡ 4ኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ኃይላት ይባላሉ፡፡ የእሳት ሰይፍ ይዘው በሥሉስ ቅዱስ ፊት የሚቆሙ ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የዛሉና የደከሙ ክርስቲያኖችን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
❤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በራማ ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ "አርባብ" ይባላሉ፡፡ የሥላሴ እልፍኝ አስከልካዮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ሁለተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት "መናብርት" ይባላሉ፡፡ ለእግዚአብሔርን እጅግ ቅርብ የሆኑ ናቸው፡፡ የመብረቅ ጋሻቸውን የእሳት ጦራቸውን ይዘው የሥላሴ ጋሻ ጃግሬዎች ሆነው በተጠንቀቅ ይቆማሉ፡፡ የሰውን ችግር ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፡፡ መዝ 88፡6፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሦስተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት "ሥልጣናት" ይባላሉ፡፡ መላውን ፍጥረት ለመጠበቅ ሥልጣን የተሰጣቸውና የምጽአት ዕለት አዋጅ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ ዳን 12፡1፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ነው፡፡
❤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በኤረር ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ "መኳንንት" ይባላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ባለ ቀስት ናቸው፡፡ የሰው ልጅ ልዩ ጠባቂዎች ናቸው፤ በተለይ በአደጋ ጊዜ ሎጥን እንዳዳኑት ፈጥነው ይደርሳሉ፡፡ በዕለተ ምጽዓት የሰውን ሁሉ ዐፅም ሰብስበው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ያበቃሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ነው፡፡ ሁለተኛዎቹ "ሊቃናት" ይላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ፈረሶች ናቸው፡፡ በእሳት ፈረስ ይመላለሳሉ፡፡ እነዚህም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሲሆኑ አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል ነው፡፡ በኤረር ከተማ የሰፈሩት ሦስተኛዎቹ "መላእክት" ይባላሉ፡፡ ፍጥረትን ሁሉ የሚጠብቁ ናቸው፡፡ አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል ነው፡፡ በእነዚህ የማይጠበቅ ፍጥረት የለም፡፡ ከአዝርእት ጀምሮ ሁሉን ይጠብቃሉ፡፡
❤ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ "በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ" (ራዕ 8፥2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል እና ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡ "ዑራኤል" የሚለው ስም "ዑር" እና "ኤል" ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፡፡ "ዑራኤል" ማለት ትርጉሙ "የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን" ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው፡፡
❤ በመሆኑም መጽሐፈ ሄኖክ እንደሚገልጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል፡፡ ምሥጢረ ሰማይንና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ መጽሐፈ ሄኖክ 28፡13፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨው ይኸው ገናና መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
❤ ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ "ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ"፡፡ መጽሐፈ ዕዝራ 2፡1፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
1 161
ዓዲ
ጥር 21
በቅዳሴ ጊዜ
#ምስባክ
መዝ ፻፲፯ ቊ፳፯
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ
ግበሩ በዐለ በትፍሥሕት በኅበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ
#ትርጉም
እግዚአብሔር አምላክ ነው፥ ለእኛም በራልን፤ እስከ መሠዊያው ቀንዶች ድረስ የበዓሉን መሥዋዕት በገመድ እሰሩት።
1 161
❤ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
*******************
ጥር ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም
""""""""""""""""""""""""""
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
**********
የመግለጫው ሙሉ ቃል እነሆ፦
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ለሚመለከተው ሁሉ
❤ እሁድ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሦስት ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት በተፈጸመው የሕግ ጥሰት 26 ኤጲስ ቆጶሳት በመሾማቸው፣ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ቋሚ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ላሉት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊቃነ ጳጳሳት አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
❤ ጥሪ የተደረገላቸው አባቶችም በቅጽበት ደርሰው ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አድርገው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት ከላይ በተጠቀሰው ኢሕጋዊ ድርጊት ላይ ውሳኔ ማሳለፋቸው በዚያው ዕለት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም በተላለፈው የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ በሰፊው ተገልጿል፡፡
መግለጫውን ያዳመጡ በውስጥም በውጭም ያሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ሁሉ ብርቱ ድጋፋቸውን ገልጸዋል፡፡
❤ እንዲሁም የዓለም አብያተ ክርስቲያናት እና መንፈሳውያን ተቋማት ድጋፋቸው ከመግለጻቸው በላይ የታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ኅብረት ተጠብቆ እንዲኖርም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
❤ እኛም ድጋፋቸውንና መልካም ምኞታቸውን ስለገለጹልን የላቀ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን፤ ምስጋናችን በያሉበት ይድረሳቸው፡፡ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂዎች የክርስትናና የእስልምና መሪዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ድንገተኛ ክስተት ተደናግጠውና ተጨንቀው መጥተው የችግራችን ተካፋይ መሆናቸውን በመንፈሳዊ ስሜት ገልጸውልናልና ምስጋናችን ይድረሳቸው፤ እግዚአብሔርም ያክብራቸው እንላለን።
❤ አሁንም በድጋሚ ለመንግሥትና ለሰፊው ሕዝባችን የምናስተላልፈው የአደራ መልእክት አለን፤ እሱም፡-
1. የታሪካዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት (ቀኖና) እንዲከበርልን፤
2. ጸጥታ እንዳይደፈርስና የንጹሐን ክርስቲያን ደም እንዳይፈስ ከወዲሁ ብርቱ ጥንቃቄ የተመላበት ጥበቃ እንዲደረግ በእግዚአብሔር ስም በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
❤ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥር 21 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
። https://t.me/Eotcw
1 161
😭 "እግዚአብሔር ከሰማይ እስኪጐበኝና እስኪመለከት ድረስ ዓይኔ ሳታቋርጥ ዝም ሳትል እንባ ታፈስሳለች"። ሰቆ. ኤር 3፥49-50
❤ ጥር 20 ቀን 2015 ዓ.ም የጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በሌሉበት አይመረቅም!።
❤ የጅማ ኦርቶዶክሳውያን በዛሬው ዕለት ለዓመታት የለፉባትንና ቅዳሴ ቤቷ ይከበራል ተብሎ በተጠበቀው የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ሲጠብቁ ቢውሉም ከአባታቸው ጋር ሳይገናኙ ቀርተዋል።
❤ የጅማ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በስፍራው ስለማይገኙ ቆሞሳት ባርከው ቤተ ክርስቲያኗ ትመረቅ ቢባሉም ምዕመናኑና ማኅበረ ካህናቱ እሳቸው የደከሙበትን ቤተ ክርስቲያን በሌሉበት አናስመርቅም፤ ይህ የኛ ቀን ነው፤ በእግዚአብሔር ቀን አባታችን ባሉበት እናስመርቃለን፤ የሠራነው የእግዚአብሔርን ቤት ነው ለምን ተፈተንን አንልም ብለዋል።
❤ የቤተ ክርስቲያኑ ምርቃት ወደ ሌላ ቀን መዘዋወሩንም የደብሩ አስተዳዳሪና አሠሪ ኮሚቴው ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይፋ አድርገዋል። ነገ በዓለ ንግሷ በቀድሞ ቤተ ክርስቲያን (በመቃኞ) ተከብሮ ይውላል።
❤ በተያያዘ ብፁዕነታቸው በዚህ ሰዓት አዲስ አበባ ገብተዋል። ምንጭ፦ ተዋሕዶ ሚድያ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" ትርጉም፦ ሞት(ማ) ለሟች ይገባል የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።
+ + +
❤ "ሰላም ለፀዐተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወጻማ። ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ። ማርያም ክልልተ ሞገስ ወግርማ። አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ። እምሕይወትዘተ ኄራን አበው ኢትሕጽጺ ዐቅማ"። ትርጉም፦ እመቤተ ማርያም ሆይ ያለመጨነቅ ያላፃር ከሥጋዋ ለተለየች ነፍስሽ ሰላምታ ይገባል አነዋወሯም በልጅሽ ቀኝ ጐን በክብር ነው። ድንግል ሆይ ከፈጣሪ ዘንድ የባለማልነትን ግርማ የተጐናፀፍሽ ነሽ። በረድኤትሽ ሰውነቴን ከድካሟ አሳርፊያት። ክብሯም (ኃይሏም) ከድጋግ አባቶቿ ክቡር (ኃይል) ያነሰ አይሁን። መልክአ ቅድስት ድንግል ማርያም።
https://t.me/Eotcw
1 161
አረጋ ጽፈዋል። ከአቡነ ኤልያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።
+ + +
❤ አቡነ ተስፋ ኢየሱስ ዘጎጃም፡- የትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ሲሆን የታላቁ ጻድቅ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ዘግሽ ዓባይ ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ እንደ ወንድማቸው የተወለዱት በመልአክ ብስራት ነው፡፡ አቡነ ተስፋ ኢየሱስን መልአክ እየመራ ወስዶ ጣና ሐይቅ ገዳም አደረሳቸውና በዚያ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓቷን ሁሉ በሚገባ ተማሩ፡፡ የዋሸራን ገዳም በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ከመሠረቱት 300 ቅዱሳን መነኰሳት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በ300ው መነኰሳትም ተመርጠው የገዳሟ ባራኪ ሆነው ተሹመው አገልግለዋል፡፡
❤ ሱባኤ ገብተው ስለ ዋሸራ ገዳምና ስለ አካባቢው ሕዝብ ምሥጢር ገለጠላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ገዳሟ ፈለፈ ሊቃውንት እንደምትሆን ተገልጦላቸዋል፡፡ ደግመው ሱባኤ ቢገቡ ገዳሟ በስተኋላ እንደምትቀዘቅዝ ተገለጠላቸው፡፡ ለ3ኛም ጊዜ ሱባኤ ቢገቡ ገዳሟ እስከ ዕለተ ምዕዓት ጸንታ እንደምትኖር ተገልጦላቸው በዚህም ደስ ተሰኝተዋል፡፡ ዋሸራ ገዳም በመጀመሪያ በባሐር የተከበበች ብትሆንም አቡነ ተስፋ ኢየሱስ ባሕሩን ቢባርኩት ተስተካክሎ እንደ ጸበል ሆኖላቸዋል፡፡ እመቤታችንም ዕለት ዕለት እየተገለጠችላቸው ትባርካቸው ነበር፡፡ ጻድቁ በተጋድሎ ብዙ ካገለገሉና ከጌታችን ታላቅ ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ጥር 21 ቀን ዐርፈው በዚያው ተቀብረዋል፡፡ ከአቡነ ተስፋ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!።
+ + +
❤ ቅድስት ማርያም ክብራ ዘጽላልሽ፡- ትውልዷ ሸዋ ደብረ ጽላልሽ ሲሆን በወቅቱ የትልቅ ባለስልጣን የመስፍን ልጅ ነበረች፡፡ ወደ ደብረ በግዕ ገዳም ገብታ መነኮሳቱን በብዙ ድካም ስታገለግል ከኖረች በኋላ በአቡነ ሕፃን ሞዐ እጅ መንኵሳለች፡፡
❤ አቡነ ሕፃን ሞዐ ማለት የደብረ በግዕህ ገዳምን የመሠረቱት ታላቅ አባት ሲሆኑ እንደበሬ በመታረስ ሰማዕትነት የተቀበሉ ናቸው፡፡ ጻድቁን ከአንድ በሬ ጋር ጠምደው ቀኑን ሙሉ ሲያርሷቸው በድካም ሆነው በኋይል የተነፈሱበት ቦታ ላይ ምድሪቱ ዛሬም ድረስ እንደእርሳቸው ስትተነፍስ የእስትንፋሷ ድምጹና ሙቀቱ ይሰማል፡፡ ለአስም ሕመም መድኃኒት ነው፡፡ ቦታውም ከደብረ ብርሃን በእግር የሁለት ሰዓት ተኩል መንገድ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን የጻድቁ ቤተ ክርስቲያኑ ከወይንዬ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አጠገብ ይገኛል፡፡
❤ ቅድስት ማርያም ክብራ በጻድቁ ሕፃን ሞዐ እጅ ከመነኮሰች በኋላ ወደ አቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም ገብታ በታላቅ ተጋድሎ ስትኖር ሰይጣን ብዙ ጊዜ በሰው አምሳል እየተገለጠ በፈተና ሊጥላት ይሞክር ነበር፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ እየተገለጠ ያበረታት ነበር፡፡ እርሷም በበትረ መስቀሏ ሰይጣንን እያሳደደች ታባርረው ነበር፡፡ ከቅድስት ማርያም ክብራ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷ ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
+ + +
❤ አቡነ ማማስ፡- ይኽም ቅዱስ የታላቁ አባት የአቡነ በጸሎተሚካኤል ረድእ የነበሩ ሲሆን ያመነኰሷቸውም እሳቸውናቸው፡፡ የአቡነ አሞኒ ሦስተኛ ልጅ ናቸው፡፡ ትውልዳቸው ወሎ አምሐራ ሳይንት ነው፡፡ አቡነ ማማስ በተለያዩ ቦታዎች ሰባት ገዳማትን ያቀኑ ሲሆን ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው በስብከተ ወንጌል ብዙ አገልግለዋል፡፡በስማቸው የተሠራው አስደናቂ ገዳም በትግራይ አጋሜ አውራጃ ይገኛል፡፡
❤ ኤርትራ አካለ ጉዛይ ውስጥም አቡነ ማማስ የሚባል ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ትግራይ ውስጥ
ከእዳጋ አርቢ ወደ ጥንታዊቷ ውቅሮ ማርያም ገዳም
በሚወስደው መንገድ ላይ ነበለት ከምትባለው ትንሽ
የገጠር ከተማ በስተሰሜን አቅጣጫ በሚገኘው አስደናቂ ገዳማቸው ውስጥ ለየት ያለ የማኅሌት ሥርዓት ይካሄድበታል፡፡ የማኅሌቱ ድምጽ እጅግ የተለየ ሲሆን ማኅሌቱን ቅዱሳን መላእክት እንደሚሳተፉበት በቦታው ላይ ያሉ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ በማኅሌቱም ወቅት ከዋሻው ጣራ ላይ ልዩ ጣዕም ያለውና ፈውስ የሚሰጥ ልዩ ጠበል ይፈልቃል፡፡ ስለትንሳኤ የሚናገረው ተአምረ ማርያም ላይ ስለዚህ ታላቅ ቦታ እንደተጻፈ አባቶች ያስረዳሉ፡፡ ጻድቁን በመጀመሪያ ወደዚህ ታላቅ ቦታ እየመራ ያመጣቸው የታዘዘ መልአክ ነው፡፡ ገዳሙ ሁለት ቤተ መቅደስ ያለው ሲሆን ቀድሞ በመነኩሴ ብቻ ይገለገል ነበር፡፡
❤ የአቡነ ማማስ መካነ መቃብራቸው ካለበት ተራራ ላይ የበቀለ የተለየ የዕፅ ተክል አለ፡፡ ይኽንንም ተክል የአካባቢው ነዋሪ ለእምነትነት በመጠቀም ከተለያዩ ሕመሞች ይፈወስበታል፡፡
❤ የአቡነ ማማስ የዕረፍታቸው ዕለት ጥር 21 ቀን ቢሆንም የአካባቢው ነዋሪ ተአምራት ባደረጉበት ዕለት ታኅሣሥ 30 ቀን በገዳማቸው በደማቅ ሁኔታ ያከብራቸዋል፡፡ የልደትበዓላቸውም ነሐሴ 7 ነው፡፡ ከአቡነ ማማስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፳፩ 21 ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያውያኑ ጻድቃን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአክስት ልጅ በሸዋ ክፍለ አገር ፈንታሌ ተራራ ላይ ሰሪቲ ለምትባ ጠንቋይ እየተላላኩ ሕዝቡን የሚያስቱና የሚያሰቃዩ አራት መቶ ሰባ ሽህ ሦስት መቶ አጋንንትን እንደ ነቢዩ ኤልያስ እሳት ከሰማይ አውርደው ላጠፋ ለታላቁ አባት ለአቡነ ቀውስጦስ ለዕረፍታቸው፣ ያጥኑባት የነበረችው ጽንሐ እንደ ሰው አፋ አውጥታ "አባታችን ዐረፈ" ብላ ለመነኰሳቱ ለተናገራለች ለታላቁ አባት ለአቡነ ኤልያስ ዘመርጦ ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለአቡነ ተስፋ ኢየሱስ ዘጎጃም ለዕረፍት በዓል፣ ለታላቁ አባት ለአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ረድእ ለነበሩ ለታላቁ አባ ለአቡነ ማማስ ለዕረፍት በዓልና ቅድስት ማርያም ክብራ ዘጽላልሽ ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ አቡነ ቀውስጦስ፦ ጻድቁ የተወለዱት ሸዋ ክፍለ አገር በወግዳና ቡልጋ ውስጥ ሲሆን አባታቸው ቅዱስ ገላውዴዎስ እናቸው ቅድስት እምነ ጽዮን ይባላሉ። የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እናት እግዚእ ኃርያ እና እምነጽዮን ታናሽና ታላቅ እህትማማቾች ናቸው።
❤ ቅዱስ ገላውዴዎስና ቅድስት እምነ ጽዮን እግዚአብሔር የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ለዓመታት በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል ፊት ሲጸልዩና ሲለምኑ እመቤታችን በስዕሏ ላይ አድራ አናገረቻቸው፤ እንዲህም አለቻቸው፦" አንድ ልጅ አስቀድማችሁ ትወልዳላችሁ፤ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ግንቦት1 ቀን ዕረፍቱም በእኔ ዕረፍት ቀን ጥር21 ነው እሱም የሰማያዊ ንጉሥ ጭፍራ ይሆናል" አለቻቸው። በቃሏ መሰረትም ግንቦት1 ቀን ጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ ተወለዱ።
❤ ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ የዚህን ዓለም ተድላ፣ ደስታና ጠዐም ንቀው ፈለገ ሐዋርያትን ተከትለው በሸዋ፣ በከፋና በጅማ ዞረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በማስተማር አረማውያን፣ ነገሥታትና ባላባቶች የሚደርስባቸውን መከራና እንግልት በመታገስ በተጋድሎ ፀንተው ብዙውን ሕዝብ ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ከኃጢያት ወደ ጽድቅ መልሰዋል። በተለይም በሸዋ ክፍለ አገር ፈንታሌ ተራራ ላይ ሰሪቲ ለምትባ ጠንቋይ እየተላላኩ ሕዝቡን የሚያስቱና የሚያሰቃዩ፬፻፸ሺ፫፻(አራት መቶ ሰባ ሽህ ሦስት መቶ) አጋንንትን እንደ ነቢዩ ኤልያስ በጸሎታቸው ከሰማይ እሳት አውርደው ተራራውን ደምስሰው አጋንንቱን አቃጥለዋል። ሕዝቡንም ለጣዖትና ለጠንቋይ ከመገዛት አድነውታል።
❤ ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ በብዙ ተጋድሎ ሲኖሩ በሰማዕትነት ያርፉ ዘንድ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚተጉ እንጂ የዚህን ዓለም መንግሥት ሀብትና ስልጣን የማይሹ እውነተኛ መናኝ ነበሩና የታናሽ ወንድማቸው የአፄ ይኩኖ አምላክ ልጅ አፄ አምደ ጽዮን የአባቱን እቁባት በማግባቲ "ይህንን ልታደርግ አይገባህም"። ብለው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥጥምቅ ቢገስጹት ዐሥራ አንድ አሽከሮቹን በሌሊት ልኮ ከበዩ ወደ እንሳሮ አገር ካስወሰዳቸው በኋላ ኮሶ አረህ ከሚባለው አፋፍ ላይ በእኩለ ሌሊት በጦር ጎናቸውን አስወግቶ ደማቸውን አስፈሰሰ። ደማቸውም እስከ ታላቁ ወንዝ ጀማ ድረስ ሆነ። የፈሰሰው ደማቸውም ቀይ ብርሃን ሲሆን የሌሊቱ ጨለማ ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚበልጥ ብርሃን በአውራጃዎቹ ሁሉ ታየ።በዚህ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ አገሩ ቀን ተብሎ ይጠራል።
❤ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ሳትለይ በስቃይ ላይ ሳሉም በዘመናቸው ሁሉ ስለነበራቸው ተጋድሎ፣ ንፅህናና ምናኔ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምንና ቅዱሳን መላእክትን አሰከትሎ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት መጣና ቃል ኪዳን ሰጣቸው። እንዲህም አላቸው፦ "እኔ ለአንተ አይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጀውልህ። በዘመንህ ስላሳለፍከው ክርስቲያናዊ ፍፁም ተጋድሎህ ሰባት የብርሃን አክሊል (ዘውዶችን) ያዘጋጀውልህ ሲሆን ሁለቱ እንደ እነ ነቢዩ ኤልያስና ነቢዩ ሳሙኤል ለሆነ ንጽህናህ፣ ሁለቱ እንደ እነ ቅዱስ ጴጥሮስና ጳውሎስ ለሆነ የወንጌል ስብከትህ፣ ሁለቱ እንደ እነ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ፊቅጦር በትዕግሥት ስለተጋደልክ፣ አንዷ ስለ ልብህ ርህራኄ ናት ብሎ አጎናፅፏችኋል። እንዲሁም ስለ እኔ ምስክርነት የሞትክባት ምድር እንደ ዳዊት አገር እንደ ኢየሩሳሌም ትሁንል ወደእርሷ የሄደውንም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ወደ መቃብሬ ጎልጎታ እንደሄደ እቆጥርለታለሁ። ብዙ ኃጢያት የሥራ ሰው ንስሐ ገብቶ በዚያች አገር በስምህ ጥቂት ምጽዋት ቢሰጥ እኔ ኃጢያቱን እደመስስለታለሁ፤ በጠበልህም ቢጠመቅ በደሉን አጠፋለታለሁ ደምህ በምድሪቱ ፈሷልና፤ በዕረፍትህ ዕለት ለቤተ ክርስቲያንህ ኖኗቅዱ ቁርባን ስንዴ፣ ወይንና ዕጣን ያቀረበ ኃጢያት የሰራ ተነሳሂ(ንስሃ የገባ) ሰው ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን እንደተቀበለ ንፁህ ሰው አደርገዋለሁ፣ ለስምህ መታሰቢያ በታነጸው ቤተ መቅደስ በንጽህና ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን የሚቀበል (የሚቆርብ) ሰው ራሱን፤ ቤተነሰቡን ባልንጀሮቹን ያድናል"።
❤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ይህንን ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው ዐረገ። ቅዱሳን መላእክትም ነፍሳቸውን ከስጋቸው በክብር ለዩ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በሰማይ መካከል ነፍሳቸውን በፈገግታ ተቀበለች። የዕረፍታቸውም ዕለት እመቤታችን ባለፈችበት ጥመ21ማቀ በመሆኑ እመቤታችንም "መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ በልጄ በረከት እበርካቸዋለሁ" ብላ ቃል ኪዳን ገባችላቸው። ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ባረፉበት ዕለትም ብዙዎች ከዴዌአቸው ተፈውሰዋል። የጻድቁ አባታችን በረከትና ፈውስ አሁንም ድረስ መደማቸ በፈሰበትና አፅማቸው ባረፈበት ቦታ ሁሉ እየታየ ብዙ ምዕመናን ፈውስ ነፍስና ፈውሰ ሥጋ እያገኙበት ነው።
❤ ገዳመ ቀውስጦስ የሚገኘው ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 120ኪ.ሜ ርቀት ላይ ሲሆን ወደ ደብረ ሊባኖስ በሚወስደው መንገድ ሙከጥሪ ከተማ ሲደርሱ ወደቀኝ በመታጠፍ ሜጤና ባዩ በሚባለው አካባቢ ልዩ ስሙ ተግባሬ(መገንጠያ) ከሚባል ቦታ ነው። ከጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ቀውስጦስ (በአጭሩ) ከሚለው መጽሐፍ።
+ + +
❤ አቡነ ኤልያስ ዘመርጦ፦ ትውልድ አገራቸው ጎጃም መርጡ ለማርያም ነው። አባታቸው መሠረተ ጽዮን መርጡ ለማርያምን በሹመት ብዙ ዘመን አገልግለዋል። አቡነ ኤልያስ 7ዓመት ሲሆናቸው ለታላቁ ጻድቅ መቋሚያቸው እንደ ሰው አፍ አውጥታ ለምትናገረው ለአቡነ ተክለ አልፋ ሰጧቸው። አቡነ ተክለ አልፋም ብሉያቱን፣ ሐዲሳት፣ ዶግማውንና ቀኖናውን ሁሉ በሥርዓት ካስተማሯቸው በኋላ አመንኩሰዋቸዋል። ጻድቁ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ሄደው 14ዓመት በገዳም አገልግለዋል።
❤ አቡነ ኤልያስ በሚያጥኑበት ጊዜ የዕጣኑ ሽታ እስከ ጣና ቂርቆስ ድረስ ይሸት ነበርና ቅዱሳን ሲሸታቸው "ዛሬ አባ ኤልያስ ቅዳሴ ገባ" ይላሉ። ጻድቁ ባረፉ ጊዜ በሞት መለየታቸውን ለመነኰሳቱ የነገረችው ያጥኑባት የነበረችው ጽንሐ ናት። እንደ ሰው አፋ አውጥታ "አባታችን ዐረፈ"ብላ ተናግራለች መነኰሳቱም ወስደው በተድባበ ማርያም ቀብረዋቸዋል። በስማቸው የተቀረጹ ታቦታት በተድባበ ማርያም፣ በቸር ተከል ማርያምና በየህላ ቅዱስ ሚካኤል እንደሚገኝ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ
1 161
...ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው። ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው። ገናም ሲናገር እነሆ፥ ሰዎች መጡ፤ #ከአሥራሁለቱ_አንዱም #ይሁዳ የሚባለው ይቀድማቸው ነበር፥ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ቀረበ። ኢየሱስ ግን። #ይሁዳ_ሆይ፥ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህን? አለው። ሉቃ 22: 45-48
'ኢየሱስም ደቀመዝሙሩ ይሁዳን ተጠግቶ አቅፎ በሳመው ጊዜ "ስለምን የሰው ልጅን በመሳም አሳልፈህ ተስጣለህ አለው" ሉቃ 22:48
እነሆ ዛሬም የሰው ልጅን አሳልፍችሁ የምትሰጡ ወዮላችሁ አሟሟታችሁ በእጅጉ የከፋ ቀባሪም የሌላችሁ ትሆናላችሁና ።
1 161
አስተርዮ ማርያም
አስተርዮ ማርያም ስልሽ ደስ ይለኛል
የመገለጥ ሚስጢር ተከናውኖልኛል
ገና ልጅም ሆኜ አስተርዮ ሲባል
እሰማ ነበረ እስኪደርስ ያጓጓል፡፡
አሁን ትልቅ ሆኜ ታሪኩ ሲገባኝ
ለካስ እናቴ ነሽ አምላኬ የሰጠኝ
የመድሃኔ ምክንያት ተስፋዬ የሆንሽኝ፡፡
የሆነውም ሆነ እሱ የወሰነው
የአምላክ እናት ሆነሽ ሞትን እንድትቀምሽው፡፡
የአዳም ልጆች ጠላት አስደናቂው ሞትም
ወረደ ወደ አንቺ ግዳጁን ሊፈጽም
እረፍት እንጅ ላንቺ ሞት ባይስማማሽም፡፡
ሞተች ሲባል ሰምተው የአንቺ ጠላቶችሽ
መጡ ከያሉበት በእሳት ሊያቃጥሉሽ፡፡
መሆንሽን እረስተው የፈጣሪ እናት
ክብር እንደ መስጠት በስተት ላይ ስህተት፡፡
ነገሩንም ጭረው ወደ ኀላ ሲሉ
ቅደም ታውፋንያ አንተ ጀግና እያሉ
ታውፋንያ ሞኙ በእሳት ሊያቃጥላት
የተዘጋጀውን ስጋዋ እንዲያርፍበት
የአልጋውን ሸንኮር ሲነካ በድፍረት
ምንም ሳያስበው መላኩ በቅፅበት
ሁለቱን እጆቹን በሰይፍቆረጠለት፡፡
ይህ ነው መጨረሻው ማን አለብኝ ማለት
ያ ሁሉ ፉከራ መሬት ገባ ድንገት
አይ የሰው ልጅ አቅም ያሳዝናል በእውነት፡፡
እጆቹንም ሲያጣ ጀግና የተባለው
የቀረው አማራጭ ወደ እሷ ማልቀስ ነው
እጆቹ እንዲድኑም አማልጅኝ ማለት ነው፡፡
እሱ መቼ አወቀ የእሷን ሕያው መሆን
ሞተች ሞተች ሲሉ ሲሰማ ወሬውን
መጣ እንጅ ዝም ብሎ ሊያቃጥል ስጋዋን፡፡
የእኛም እናት ድንግል የማታሳፍረው
የሞተች ብትመስልም ህያው የሆነችው
አማላጅነቷን አሳየችው ወዲያው እጆቹን ቀጥላ ስለ ሆኑህያው፡፡
እንዲህ ናት የእኛ እናት ጠላቶቷን የማትወድ
ማርያምን ይወቃት የማያውቃት ትውልድ
በጦር የወጋውን አይኑን እንዳበራ
ልጇ መድሃኔ አለም
ልጇ እንዳደረገ አደረገች እርሷም፡፡
ስሟ ማር ወለላ ፍቅር ናት የእኛ እናት
የማያውቅ ይወቃት የሚያውቅም ያክብራት🙏
1 161
ማኅሌቱን ለምቶሙ ማኅሌታውን መልካም አገልግሎት 🤲🤲
እንኳን አምላክን ለወለደች ለእናትችን
ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም
ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
1 161
Repost from ሰዋስው ☘☘☘☘
🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸
ስርዓተ ማህሌት ዘአስተርእዮ
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፣ በአሐቲ ቃል።
መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።
ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋህድ፤ ዕፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ፤ ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ፤ ዮሐንስ በልብሱ ከደነ ገፃ።
@EOTCW
ወረብ
እፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ በከየት እመ አምላክ/፪/
ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ በከየት/፪/
@EOTCW
ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።
@EOTCW
ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ወዓለሙኒ ኢክህለ ፀዊሮቶ፤ ፆረቶ ወአግመረቶ ማርያም።
@EOTCW
ነግሥ
ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ፤ ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ፤ ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ።
@EOTCW
ዚቅ
እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ኢያደሉ፤ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኲሉ፤ አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ።
@EOTCW
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።
@EOTCW
ዚቅ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ፤ ወአግአዛ እምእኩይ ውስተ ሠናይ፤ እሞት ውስተ ሕይወት፤ ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ዓለም።
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ/፪/
ወአግአዛ እምእኩይ ውስት ሠናይ እሞት ውስተ ሕይወት/፪/
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤ ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤ በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት።
@EOTCW
ዚቅ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ፤ ኃደረ ቃል ላዕሌሃ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ወይቤላ ለድንግል፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሰሎሞን ይቤላ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት፤ ፍናወ ዚአኪ ገነት፤ እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ፤ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ ለልዑል።
@EOTCW
ወረብ
'አንጺሆ ሥጋሃ'/፪/ ላዕሌሃ ኃደረ/፪/
ቀዲሶ ኪያሃ 'ሃሌ ሉያ'/፪/ ይቤላ ለድንግል/፪/
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ፤ በከመ ዳዊት ይዜኑ፤ ማርያም ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ፤ በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ፤ እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ።
@EOTCW
ዚቅ
እምሰማያት ወረደ ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፤ ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ ወረደ ስኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ፤ ወስኑሰ ለያዕቆብ ዘይቤ ይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ፤ መድኅን እማርያም።
@EOTCW
ወረብ፦
ወስኑሰ ለያዕቆብ 'ዘይቤ'/፪/ ያዕቆብ/፪/
'ይእቲ ሥጋ'/፪/ እማርያም እንተ ነሥአ መድኅን/፪/
@EOTCW
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ
ፃዕር ወፃማ፤ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ሞገስ ወግርማ፤ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፤ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።
@EOTCW
ዚቅ
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና፤ ጠሊላነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና።
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ጊዜ ዕረፍታ ለማርያም 'ጊዜ'/፫/ ዕረፍታ ለማርያም/፪/
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ/፪/
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ፤ ዘተመሰለ ባሕርየ፤ ማርያም ድንግል ዐጸደ ወይንየ፤ ንስቲተ ለዕበየኪ እንተ አቅረብኩ ግናየ፤ ኢይትኃደግ ዲበ ምድር ምሥጢ ሰማየ።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ኦ ትቤ ማርያም እወጽእ እምዝንቱ ሥጋየ፤ ወአሐውር ውስተ ሕይወት ዘለዓለም፤ ኦ ተዘከርኬ ዮሐንስ ዘይቤለከ ሊቅ አመ ትረፍቅ ዲበ ዕንግድዓሁ።
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፤ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ፤ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ፤ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ፤ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ።
@EOTCW
ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት፤ ብፁዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሃ፤ በሰላም አምኁ ኪያሃ፤ በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ።
@EOTCW
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለጌቴሴማኒ በመርኅባ፤ እንተ ይእቲ ለኢየሩሳሌም ቅሩባ፤ ማርያም ድንግል ለሀገረ መንግሥት ርግባ፤ ትትሜጦ ወረቀ እምአፌር ወጸበለ አፈው እምሳባ፤ ጌቴሴማኒ ለሥጋኪ ምስካባ።
@EOTCW
ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ዓውዳኒ ዘጽድቅ ወመርኅባኒ ዘዕንቊ፤ አንቀጸ አድኅኖ ሐዳስ ንጽቅ።
@EOTCW
መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለኢየሩሳሌም በአድያማ፤ እንተ ይእቲ ጌቴሴማኒ ስማ፤ ማርያም ሰንበት ዕረፍተ ጽዑራን እምፃማ፤ አመ ኀደረ ላዕሌኪ ፀሐየ ቅዱሳን ዘራማ፤ ኃይለ ልዑል ጸለለኪ በመንክር ግርማ
@EOTCW
ዚቅ
ኢይሜንንዋ ኪያሃኒ ወአድያሚሃኒ ነያ ጽዮን ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር።
@EOTCW
ማኅሌተ ጽጌ
እግዚአብሔር ጽጌ ትንቢት ለቢሶ ሥጋኪ ሥጋ ዚአነ፤ አመ አስተርአየ በምድር ወተአምረ ለነ፤ ንዌድሰኪ እንዘ ንብል ምክሃ ዘመድነ፤ ዮም በፍሥሃ ለማርያም እምነ፤ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ።
@EOTCW
ዚቅ
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርእዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ እምድንግል ተወልደ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በሥጋ ረቂቅ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ በበህቅ ልህቀ።
@EOTCW
አንገርጋሪ
ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን፤ ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ፤ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተአቊረ፤ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ፤ ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂዎ፤ ዘኪሩቤል ኢርእዮ።
@EOTCW
አመላለስ
ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂሆ/፪/
ኢያርኂሆ ዘኪሩቤል ኢርእዮ ኢያርኂዎ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/
@EOTCW
ወረብ
'አምላክ ኀደረ'/፪/ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ አምላክ ኀደረ/፪/
ዘድንግል መናሥግተ 'ኢያርኂዎ'/፪/ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/
@EOTCW
እስመ ለዓለም ዘሰንበት፦
ዮም ንወድሳ ለማርያም፤በእንተ ዘተወልደ እምኔሃ፤መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ።ፆረቶ በከርሳ፤ውእቱኒ ቀደሳ፤መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ፤እግዚአ ለሰንበት፤ወአቡሃ ለምሕረት፤ማ፦መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ፤አማን መላእክት ይኬልልዋ
@EOTCW
@EOTCW
አመላለስ፦
መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ/2/
አማን መላእክት ይኬልልዋ/4/
https://t.me/Eotcw
@EOTCW
#Join & share
1 161
#ጥር 21
#ምስባክ_ዘነግህ
መዝ ፻፵፯ ቊ ፩
ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር
ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን
እስመ አፅንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ
#ትርጉም
ኢየሩሳሌም ሆይ እግዚአብሔርን አመስግኚ
ጽዮንም ሆይ አምላክሽን አመስግኝ
የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቶአልና
https://t.me/Eotcw
1 161
#ምስባክ_ዘነግህ
መዝ ፻፵፯ ቊ ፩
ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር
ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን
እስመ አፅንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ
#ትርጉም
ኢየሩሳሌም ሆይ እግዚአብሔርን አመስግኚ
ጽዮንም ሆይ አምላክሽን አመስግኝ
የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቶአልና
በቅዳሴ ጊዜ
#ምስባክ
መዝ ፵፯ ቊ ፰
በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ
በሀገረ እግዚእ ኃያላን በሀገረ አምላክነ
እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም
#ትርጉም
እንደሰማን እንዲሁ አየን
በሠራዊት ጌታ ከተማ በአምላካችን ከተማ
እግዚአብሔር ለዘለዓለም ያጸናታል
#ወንጌል
የሉቃስ ወንጌል ም ፩ ቊ፵፯-፶፯
#ቅዳሴ
ቅዳሴ እግዝእትነ (የማርያም ቅዳሴ)
