en
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Open in Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Show more
1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከዚህም በኋላ ቅድስት ኢላርያ የታመመችውን ልጅ ወደ በዓቷ ወስዳ ጸሎት አደረገችላት፡፡ ሰይጣኑም ወዲያው ጥሏት ሸሸ፡፡ በጥቂት ቀንም ውስጥ ፈጽማ ዳነች፡፡ ቅድስት ኢላርያም እኅቷ እንደሆነች ታውቃለችና አቅፋ ትስማት ነበር ስለ ፍቅሯና ናፍቆቷም ወደ ውጭ እየወጣች ታለቅስ ነበር ነገር ግን ታማ የነበረችው እኅቷ አላወቀቻትም፡፡ ቅድስት ኢላርያም በጸሎቷ ከፈወሰቻ በኋላ ወደ አረጋውያኑ መነኰሳት ወስዳ "እነሆ በጸሎታች እግዚአብሔር ፈውሷታልና ወደ ንጉሡ አባቷ መልሷት" ብላ ሰጠቻቸው፡፡ እነርሱም እጅግ ደስ ብሏቸው ወደ አባቷ መለሷት፡፡ ❤ ሮሜ አገር በደረሰችም ጊዜ ልጃቸው ስለዳነችላቸው ንጉሡና መኳንንቱ የአገሩም ሰዎች ሁሉ ተደስተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህም በኋላ አባቷ በገዳም ስለነበራት ቆይታ ልጁን ጠየቃት፡፡ እርሷም "ያ በጸሎቱ ያዳነኝ አባ ኢላርዮን የሚባል መነኩሴ አብዝቶ ይወደኛል፤ አቅፎም ይስመኛል" አለችው፡፡ ንጉሡም ይህንን ሲሰማ ልቡ ታወከና "መነኵሴ እንዴት ሴትን ለመሳም ይገባዋል" አለ፡፡ በዚህም ጊዜ "በእኔ ላይ ይጸልይ ዘንድ አገሬንም ይባርክ ዘንድ ልጄን ያዳናትን አባ ኢላርዮንን ወደኔ ላኩልኝ" ብሎ ደብዳቤ ጽፎ ወደ አስቄጥስ ገዳም ላከ፡፡ አረጋውያኑም ቅድስት ኢላርያ ጠርተው ወደ ንጉሡ አገር ሄዳ እንድትባርከው አዘዟት፡፡ እርሷም ይተዋት ዘንድ እያለቀሰች ብትለምናቸውም እነርሱ ግን "ይህ ንጉሥ ክርስቲያኖችን የሚወድ ጻድቅ ነው፣ ቅዱሳት መጻሕፍትም እንደሚያዙን ትእዛዙን መተላለፍ የለብንም" ብለው አስገድደው ላኳት፡፡ ወደ ንጉሡም በደረሰች ጊዜ ሁሉም በክብር ተቀብለው ተሳለሟት፡፡ ንጉሡና ንግሥቲቱም ለብቻቸው ሆነው ወደ ውስጠኛ ክፍል አስገቧትና ንጉሡ እንዲህ ብሎ ጠየቃት፡- "ልጄን ትስማት እንደነበር በሰማሁ ጊዜ በሀሳቤ ታውኬያለሁ፤ መነኵሴ ሴትን መ ሳም አይገባውምና ይህን ነገር ትገልጥልኝ ዘንድ እወዳለሁ" አላት፡፡ ❤ የከበረች ቅድስት ኢላርያም "በነገርኳችሁ ጊዜ ወደ አስጥስ ገዳም መሄድን ላትከለክሉኝ የከበረ ወንጌልን አምጥታችሁ ማሉልኝ" አለቻቸው፡፡ እነርሱም ማሉላት፡፡ በዚህም ጊዜ እርሷ ማለት ልጃቸው ኢላርያ መሆኗን ነገረቻቸው፡፡ እንዴት ከቤተ መንግሥት እንደወጣችም አስረዳቻቸውና በአካሏ ላይ ያለውን ምልክት አሳየቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ በቤተ መንግሥቱ ታላቅ ጩኸት ሆነ፡፡ አቅፈውም እየሳሟት አለቀሱ፡፡ "ከእኛ ዘንድ እንድትሄጂ ከቶ አንተውሽም" አሏት፡፡ እርሷም "በከበረ ወንጌል የማላቸሁትን መሐላ አስቡ" አለቻቸው፡፡ እሺ ብለው ግን እስከ 40 ቀን አብራቸው እንድትቆይ ለመኗት 40 ቀን አብራቸው ቆየች፡፡ ❤ ቅድስት ኢላርያም ወደ አስቄጥስ ገዳም ከተመለሰች በኋላ ንጉሡ ዘይኑን ለገዳሙ መነኮሳት ለፍላጎታቸው ይሆን ዘንድ የግብጽን ምድር ግብር እንዲሰጧቸው አዘዘ፡፡ በዚያም ወራት በአባ መቃርስ ገዳም 400 የመነኮሳት ቤቶች ተሠሩ፡፡ በአባ ዮሐንስ ገዳም 700 በአባ ሙሴ ገዳም 300 ቤቶቸ ተሠሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅድስት ኢላርያ 5 ዓመት ኖራ በሰላም ዐረፈች፡፡ ከዕረፍቷም አስቀድሞ እርሷ ሴት እንደሆነች ያወቀ የለም፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኢላርያ ጸሎት ይማረን በከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 21 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር። ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን። እስመ አጽንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ"። መዝ 147፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ1፥27-ፍ.ም። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ። በሀገረ እግዚአ ኃያላን በሀገረ አምላክነ። እግዚአብሔር ሣረራ ለዓለም"። መዝ 47፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥1-12፣ 2ኛ ዮሐ 1፥1-7 እና የሐዋ ሥራ 7፥30-35። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥47-57። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

ዓለም በሚመጣውም ዓለም አይጠፋም"። ❤ እመቤታችንም ከአረፈች በኋላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሐዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ሥጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእርሳቸው አንዱ ስሙ ታውፋንያ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን ዐልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በዐልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ። ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ "የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ" በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ። ❤ በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሦስት ቀን ኖሩ ዕረፍቷም የሆነው እሑድ ቀን በጥር ወር በሃያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሃናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ሥጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በዕፀ ሕይወት ሥር አኖሩዋት። ❤ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም "ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሣ" አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኋላ ወደ ሐዋርያት ደረሰ። እነርሱም እመቤታችን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበሩዋትም ነገሩት ቶማስም "ሥጋዋን እስከማይ አላምንም" አላቸው። ሥጋዋንም ያሳዩት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ወስጥ ሥጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቅዱስ ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን ዕርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ሥጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኋላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ሰጣቸው እነርሱም እሰሰከ ነሐሴ ዐሥራ ስድስት በተስፋ ኖሩ። ❤ የእመቤታችን የዕድሜዋ ዘመን ስሳ አራት ዓመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሦስት ዓመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም ዐሥራ ሁለት ዓመት በዮሴፍ ቤት ሠላሳ አራት ዓመት ከሦስት ወር ከጌታችን ዕረገት በኋላ በወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ቤት ዐሥራ አራት ዓመት ነው። የሕይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በጸሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 21 ስንክሳር። + + + ❤ አቡነ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፡- ይኸውም የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም ነው፡፡ አገሩ ቂሳርያ ሲሆን የተሾመው ኑሲስ በተባለች ደሴት ላይ ነው፡፡ መናፍቁ ሰባልዮስ "አንድ ገጽ" በማለቱ ሌሎቹ መናፍቃንም መቅዶንዮስና አቡሊናርዮስ "መንፈስ ቅዱስ ህጹፅ" እና "ወልድ ሥጋ እንጂ ነፍስ አልነሳም" በማለታቸው በ381 ዓ.ም 150ው ሊቃውንት በቍስጥንጥንያ ተሰብስበው መናፍቃኑን ተከራክረው እረተው ሃይማኖትን ሲያጸኑ ከጢሞቲዎስ ጋር አንድ ላይ የጉባኤው አፈ ጉባዔ የነበረው ሊቁ ጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ ነበር፡፡ እርሱም በጉባኤው ላይ እነ መቅዶንዮስንና አቡሊናርዮስን ተከራክሮ በመርታት መልስ አሳጥቷቸዋል፡፡ ሃይማኖትንም አጽንቷል፡፡ ❤ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቅዳሴ ሲቀድስ ጌታችን በርግብ አምሳል ሲወርድ ያየው ስለነበር ዘወትር እያለቀሰ ይቀድሳል፡፡ ከተጋድሎውም ጽናት የተነሣ ታማሚ ሆኖ ነበር፡፡ በኤጲስ ቆጶስነት ተሹሞ 33 ዓመት ኖሯል፡፡ ከተጋድሎውም ብዛት ድካም አጋጥሞት ነበርና አንድ ቀን ወንድሙ ባስልዮስ ሊጠይቀው መጣ፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስም እንደልማዱ ሊቀድስ ወደ መሠዊያው በወጣ ጊዜ እመቤታችን ተገለጠችለትና "ዕረፍትህ በዕረፍቴ ቀን ነውና ዛሬ ወደእኔ ትመጣለህ" አለችው፡፡ ጎርጎርዮስም የቁርባኑን ቅዳሴ ሲጨርስ ሕዝቡን በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለመምከር ተነሣ ነገር ግን ከድካምና ሕመም ብዛት ሰውነቱ መቆም ስላልቻለ ወንደሙን ባስልዮስን "ዛሬ አንተ አስተምራቸው" አለው፡፡ ወዲያውም እንደሚያንቀላፋ ሆነና ዐረፍ አለ፡፡ በቀሰቀሱትም ጊዜ በሞት ዐርፎ አገኙት፡፡ ይኸውን ጥር 21 ቀን ነው፡፡ ❤ በስሙ የተጠራ አንድ ቅዳሴና ገድለ ዜና አለው፡፡ በትንቢት ተናጋሪነቱ፣ በደራሲነቱና በመምህርነቱ መጽሐፍ "ጎርጎርዮስ ዐቃቤ ሥራይ ቁስለ መድኃኒት ዘነፍስ" ይለዋል፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ወንድማማቾቹን ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በጸሎታቸው ሰዓት ደርሶባቸው እነርሱን ገድሎ መሥዋዕታቸውን ሊበላባቸው ሲመጣባቸው የቅዱስ መርቆሬዎስን ሥዕል በጸሎት ቢማጸኑ ሥዕሉ በገዘፈ ሥጋ ሆኖ በተአምራት ዑልያኖስን በጦር ወግቶ ገድሎላቸዋል፡፡ + + + ❤ ቅድስት ኢላርያ፡- ይኽችም ቅድስት የሮሜው አገር ንጉሥ የዘይኑን ልጅ ናት፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚወድ ሃይማኖቱ የቀና ነው፡፡ ልጁ ቅድስት ኢላርያንም ፈሪሃ እግዚአብሔርንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እያስተማረ አሳደጋት፡፡ ከሁለት ሴቶቹ ለጆቹ በቀር ወንድ ልጅ የለውም ነበር፡፡ ❤ ቅድስት ኢላርያም ዕድሜዋ ከፍ ሲል ዓለምን ፍጹም ንቃለችና የምንኵስናን ልብስ የመላእክትንም አስኬማ ትለብስ ዘንድ ወደደች፡፡ ከቤተ መንግሥትም ተደብቃ ወጥታ የወንድ ልብስ በመልበስ ወደ ግብጽ አገር ሄደች፡፡ ወደ አስቄጥስ ገዳምም ገብታ ስሙ አባ ባውሚን የሚባል ፍጹም ሽማግሌ ጻድቅ ሰውን አግኝታ የምንኩስና ሀሳቧን ነገረችው፡፡ እርሷም ሴት እንደሆነች ስትነግረው ምሥጢሯን ጠብቆ ለብቻዋ ከዋሻ ውስጥ አስገባት፡፡ እየጎበኛትም ልትሠራው የሚገባትን ሁሉ ያስተምራት ነበር፡፡ እንዲህም ሆና በዚያ ዋሻ ውስጥ 12 ዓመት ኖረች፡፡ ቅድስት ኢላርያ ፂም ስለሌላት ለአረጋውያን መነኮሳት ጃንደረባ ትመስላቸው ነበር፡፡ በወንድ ስም አጠራርም አባ ኢላርዮን ብለው ይጠሯት ነበር፡፡ ❤ ከአባቷ ዘንድ ያለችው ታናሽ እኅቷ ርኩስ መንፈስ አደረባትና ብዙ አሠቃያት፡፡ ያድኗትም ዘንድ አባቷ ብዙ በመድከም ገንዘቡን አወጣ ነገር ግን ልትድን አልቻለችም፡፡ መኳንንቶቹም ወደ ግብጽ አስጥስ ገዳም እንዲልካት ለንጉሡ ነገሩት-በዚያ ያሉ መነኮሳት ክብራቸውና ጸጋቸው በሮም አገሮች ሁሉ ታውቋልና፡፡ ንጉሡም የታመመችውን ልጁን ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደ ግብጽ ላካት፡፡ ለመነኮሳቱም "… ሁለት ሴቶች ልጆችን ወለድኩ ነገር ግን አንደኛዋ ጥላኝ ጠፋች፣ ሁለተኛዋንም ርኩስ መንፈስ ይዞ መጨወቻ አደረገብኝ፡፡ ቅዱሳን አባቶቼ ሆይ ልጄን በጸሎታቸሁ ትፈውሱልኝ ዘንድ ቅድስናችሁን እለምናለሁ" የምትል ደብዳቤ ጽፎ ላከላቸው፡፡ መነኮሳቱም የንጉሡን ደብዳቤ ካነበቡ በኋላ በልጅቱ ላይ ጸለዩ፡፡ ነገር ግን ያደረባት ርኩስ መንፈስ ሊለቃት አልቻለም፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አረጋውያኑ መነኮሳት ጃንደረባ የሚሏትን ኢላርያን ጠርተው እስካዳናት ድረስ የንጉሡን ልጅ ወስደህ "በላይዋ ላይ ጸልይ" ብለው ሰጧት፡፡ እርሷም "ይህ ለእናንተ እንጂ ለእኔ አይቻለኝም" ብትላቸውም ግድ አሏት፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳፩ 21 ቀን። ❤ እንኳን አምላክን ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታች ለቅድስት ድንግል ማርያም ለዕረፍቷ በዓል (ለአስተርእዮ ማርያም)፣ ለኑሲስ ኤጲስቆጶስ ለቅዱስ ባስልዮስ ወንድም ለከበረ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ዕረፍት በዓልና ለሮሜ አገር ንጉሥ ለዘይኑን ልጅ ለከበረች ለቅድስት ኢላርያ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ እመቤታችንንም ከመጥቁ ዮሐንስ ጋር በደብረ ማሕው ከተገለጠችበት፣ ከነቢዩ ከቅዱስ ኤርምያስ፣ ከዮሐንስና ከአባ እስክንድር፣ በዋሻ ከቅዱስ ኒቆላዎስና ከኤጲስቆጶስ ከአባ ፊቅጦር ከሁሉም ከመታሰቢያቸው፣ በናፍቁ ንጉሥ በመርቅያን ዘመን በሰማዕትነት ከዐረፉ ከቅዱሳን ጳውሎስና ከቀሲስ ሲላስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ ዘድንግል መናሥግተ እያርኂዎ ዘኪሩቤል ኢርእዮ"። ትርጉም፦ እኛ የእግዚአብሔር የቤቱ ሰዎች እንግዶች መፃተኛ አልሆንም የቅዱሳን ሀገር የሆነው አምላክ ክርስቶስ በሥጋ ተወሰነ፤ ኪሩቤል ያላየው ያልመረመረው የእመቤታችን ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይከፍት በመወለዱም ከምልአቱ ሳይወን ተወለደ። + + + ❤ የዕለቱ እግ. ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "እንተ ክርስቶስ በግዕት እንተ ታስተርኢ እምርኁቅ ብሔር በቤተ ልሔም አስተብረከት ዕጓል አንበሳ ግሩመ ወለደት"። ትርጉም፦ የክርስቶስ በግዕት ከሩቅ ሀገር የምትታይ በቤተ ልሔም ሁሉን አሰገደች፤ ግሩም የአንበሳ ልጅ ወለደች። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ ። + + + ❤ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት፦ ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃብሩ ቦታ ትጸልይ ነበር ከዚህም ዓለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኋላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው። በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ጸለየች "ልጄ ወዳጄም ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚያች ሰዓት አምጣው። እንዲህም ሕያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሃቸውን አምጣቸው አንተ የሕያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን"። ❤ በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት "ሰላምታ ይገባሻል ጌታችን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ጸጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ ዓለም ሕይወት ትሒጂአለሽና። ይህም ስሙ ክቡር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ገለጠ በኋላ ነው"። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላት እግዚአብሔርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው "ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀበለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊሳርጓት ከሚመጡ መላእክቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ"። ❤ በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሐዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ"። ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነሥተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት "አምላካችን ከአንቺ የተወለደ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ ዓለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር የሳርግሻልና" አሏት። ❤ በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በዐልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትም እንዲህ አለቻቸው "ፈጣሪዬ ፈጣሪያችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኋችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከሥጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ሕይወት እሔዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም ዓለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ?"። "ጴጥሮንና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥንን ደረስን" አሏት። ❤ እመቤታችን ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ "ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈጽሜ አመሰግናለሁ። የእኔ የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል"። ጸሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው "ዕጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙን ጥሩት" እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፋት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ ዕውሮች አይተዋልና ሐንካሶች ቀንተው ሒደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምጻሞች ነጹ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሔዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለችበት ቤት በቀረቡ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና። ❤ ከዚህም በኋላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው "በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሣ ከእሳት ባሕርም እፈራለሁ" ጌታችንም "እርሳቸው ለማንም በአንቺ ላይ ስልጣን የለውም" አላት። ከሥጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጅዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንጽሕት ነፍሷን ከሥጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሃን ልብስ አጐናጽፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ሥጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሐዋርያትን አዘዛቸው። ❤ ነፍሷ ከሥጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሃንን እያያች ነበር በክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም "እንግዲህ ሥጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ሥጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነሥቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሁነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ" አላት። እመቤታችንም እንዲህ አለች "አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሠራህ አመሰግንሃለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሃለሁ በስሜ ወዳንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሁኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በሥራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉባትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መሥዋዕታቸውን ተቀበል"። ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት "የለመንሺኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ጸጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

የምንኩስና እና የክህነታዊ ሕይወቱን አነዋወር የክርስትናውን አነዋወር አስተዳደሩን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን እና እንደሚገባ መተግበር አለብን፡፡ ይኸንንም በማድረግ እንደ ፈቃዱ ለመኖር :- ከዘረኝነት ጎጠኝነት ከራስ ወዳድነት ከጥቅም ፈላጊነት በአጠቃላይ ከስነ ምግባር ብልሹነት / ከሥጋ ሥራዎች ራሳችንን መለየት ያስፈልጋል። ገላ 5፥19-21 ለዚህም ከቅዱስ ፓትርያርካችን ጀምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ሁላችን የቤተክርስቲያን አካላት በእውነት መንገድ ላይ ቆመን ተጋድሏችንን ልንፈጽም ግድ ይለናል፡፡ ይህ ሲሆን ደግሞ እኛም አብረን ቤተክርስቲያንንም ወደ ቀድሞ ማንነቷ ስትመለስ እናያለን፡፡ አቤቱ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ᎓᎓ ኤር 5፥21 ስለድፍረታችን ሁላችሁንም በክርስቶስ ስም ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ነገር ግን “ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፡፡" 1ኛ ዮሐ 4፡18 የሚለውን አምላካዊ ቃል አብነት አድርገን ነው፡፡ ችግሮቻችን ሁሉ ተፈትተው በምድር የእግዚአብሔር ልጆች በሰማይም የመንግስቱ ወራሾች እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር ቸርነት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ጠባቂነት የቅዱሳን ሁሉ ተራዳኢነት በዚህም ዘመን ያሉ የእውነተኞቹ አበው እና እማት ጸሎት የህጻናቱ በረከት ከእኛ ጋር ይሁን፡፡ አምላከ ቅዱሳን ቤተክርስቲያንና ሀገራችንን ህዝቡን ሁሉ ይጠብቅ :: አሜን፡፡ 【ማሳሰቢያ- መልእክቱን ያስተላለፉላችሁ ገዳማት በርካታ ሲሆኑ ከቦታ መራራቅ አንጻር እነዚህን ማህተሞች ብቻ አድርገናል፡፡】 https://t.me/Eotcw

፰. ለሕጻናት: - በእናንተ በረከት እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን እና ሀገራችንን ከገጠማት ፈተና እንደሚታደጋት እምነት አለን፡፡ ስለሆነም እናንተም በሕጻን ማንነታችሁ ወደ እግዚአብሔር እንድትለምኑ ቤተሰቦቻችሁንም እንድታተጉ በዚሁም ቂርቆሳውያን መሆናችሁን እንድታስመሰክሩ እኛ ገዳማውያን አባቶቻችሁና ገዳማውያት እናቶቻችሁ እናንተ ሕጻናት ወደ እርሱ ትመጡ ዘንድ በወደዳችሁ አምላክ ስም አደራ እንላችኋለን፡፡ የነገይቱ ቤተ ክርስትያን የእናንተ ነችና ከዚህ ዘመን የተሻለች ቤተ ክርስቲያን ትኖራችሁ ዘንድ በጸሎታችንም እንለምናለን፡- / ማሳሰቢያ መልእክቱን ማንበብ የሚችሉ ህጻናት እራሳቸው እንዲያነቡ ማንበብ ለማይችሉ ደግሞ ቤተሰቦቻቸው እንድታነቡላቸው አደራ እንላለን፡፡/ ፱. ለአኀት አብያተ ክርስቲያናት፡ - ሃይማኖት ዘር፣ሀገር እና ባንዲራ/አርማ/ የለውም፡፡ ዘሩ ክርስትና፣ ሀገሩ ሰማያዊ ባንዲራው /አራማው መስቀል ነው፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የገጠማት ፈተና የእናንተም ነው እና በጸሎታችሁ፣በሀሳባችሁ በምክራችሁ፣በመልዕክታችሁ፣ በሚያስፈልገው ነገር ሁሉ ከእውነተኛዋ ቅድስት ቤተክርስቲያን መከራ ተካፋይ እንድትሆነ ክርስቶስ በደሙ በዋጃት ቤተክርስቲያን ስም እኛ ደካሞቹ ገዳማውያን አደራ እንላችኋለን፡፡ ፲. ለመንግስት፡ - ምድራውያን መንግስታት በምድር የሚያስተዳድሩትንና የሚመሩትን ሁሉ በእውነትና በፍትሕ እንዲመሩ የተቀበሉተ ኃላፊነት ግድ ይላቸዋል፡፡ ስለሆነም እስካሁን የሰራችሁትን ክፉም ሆነ በጎ እንተወውና ሰሞኑን ለተፈጠረው ችግር የመንግስት አስተዋጽኦ እንዳለው ይሰማናል። ምክንያቱም በችግሩ ውስጥ ተዋናይ መሆን ወይም ችግሩን አይቶ እንዳላየ ማለፍ አንዲት ሀገርን ከሚያስተዳድር አካል አይጠበቅም። ይልቁንም የቤተክርስቲያኗን ዶግማና ቀኖና በጠበቀ መልኩ ቤተክርስቲያኒቱ ችግሩን ለመፍታት በምትሄድበት መንገድ ሁሉ ተባባሪ መሆን ይጠበቅበታል። ያለበለዚያ የችግሩ ፈጣሪ እና ለችግሩ ዱላ አቀባይ ከመሆን ተለይቶ አይታይም᎓᎓ ሕዝበ ክርስቲያኑ መንግስት በምድራዊ ነገር በእኩልነት እና በፍትሕ እንዲመራው ይፈልጋል እንጂ ሃይማኖቱን ለማዳከም የሚሰራ ሆኖ ሲያገኘው የመንግስትና የሕዝበ ክርስቲያን ግንኙነት እግዚአብሔር እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ከሚያደርጉት ግንኙነት አይበልጥምና መከራን በመቀበል ሰማያዊን ዋጋ ለማግኘት ምዕመናንና ምዕመናት የሚጠበቅባቸውን ሃይማኖታዊ ግዴታ ለማድረግ ወደኋላ እንደማይሉ ሊታወቅ ይገባል። መንግስት ምድራዊውን ዓለም ሲመራልን ሃይማኖት ደግሞ ሰማያዊውን ሀገር ያወርሰናልና፡፡ ቤተክርስቲያን ሰማያዊት ብትሆንም ተጋዳይቱ ቤተክርስቲያን በሀገር እና በምድር ላይ ነው ያለችው᎓᎓ ስለሆነም ምድራውያን መንግስታት ህልውናዋንና መብትዋን አክብረው ሊያስከብሩላት የተገባ ነው᎓᎓የመንግስት ትንሹ ግዴታ ህግን ማስከበር ነው ስለሆነም በቤተ ክርስቲያን ላይ የተፈጠረውን ህገ ወጥ ድርጊት ማስቆምና ህገወጥ ድርጊት ፈጻሚዎችንና ተባባሪዎችን ሥርአት ማስያዝ ከመንግስት የሚጠበቅ መንግስታዊ ግዴታ ነው፡፡ ፲፩.ለፓለቲከኞች፡ - ፖለቲከኞች ከቤተክርስቲያን መንፈሳዊ መአድ እንካፈል ሲሉ ቅድስት ቤትክርስቲያን የፖለቲካ እሳቢያቸውን ሳትመለከት ከመሶቧ ትመግባቸዋለች ነገር ግን ቤተክርስቲያኒቱን ወደ ፖለቲካቸው ከረጢት ሊያስገቧት ሲሉ ችግሮች ይፈጠራሉ፡፡ስለሆነም የፖለቲካ ፓርቲ እና ፖለቲከኞች የቆማችሁለትን ርዕዮተ ዓለም በእውነት መሥረትነት ላይ እንድትተገብሩና ሰው የምድርና የሰማይ ፍጥረት መሆኑን አውቃችሁ በምድር በሚኖርበት ጊዜ ሁሉ ሃይማኖቱን በነጻነትና በሥርዓት እንዲያከናውን በችግሩም ጊዜ መፍትሔ ለማምጣት የድርሻችሁን ትወጡ ዘንድ አደራ እንላለን፡፡ ፲፪.ለኢትዮጵያውያን በሙሉ፡ - ኢትዮጵያውያን ታሪካችን እንደሚነግረን ሃይማኖተኛነት ፍትሕ፣መከባበር፣ መረዳዳት እና የመሳሰሉት የበጎ ሰው ተግባራትን ገንዘብ ያደረግን ነን:: ዛሬ ግን የኛ መገለጫ ያልሆኑ እኩይ ተግባራት ተዋናይ ከሆን ሰነበትን፡፡ ስለሆነም በሰውም በእግዚአብሔርም ዘንድ የተጠላውን ተግባራት ሁሉ ከእኛ በማራቅ የቀድሞ በጎ ተግባራችንን አጽንተን በመያዝ ምድራዊ የጋራ ቤታችንን በፍቅር እንኑርባት ያለበለዚያ ❤ ሰው የሚያምንበትን ሰማያዊ ቤት አፈርስብሃለሁ ሲሉት ወይም ለማፍረስ ተባባሪ ሲሆኑ ዘላለማዊ ሕይወቱን ለማግኘት በሚያደርገው ተጋድሎ ሀገራችን ለምድራዊ ኑሮአችን እሾክ እንዳትሆን ያሰጋል። ኢትዮጵያውያን ሆይ ምድራዊ ቤታችንን በአንድነት እና በፍቅር እንኖርባት ዘንድ አንዱ በአንዱ ላይ ከመነሳሳት ተቆጥበን የኅብረት ቤታችንን የጋራ ሰላማችንን ለመጠበቅ የሰውነት ግዴታችንን እንወጣ፡፡ ❤ ማጠቃለያ የችግራችን መፍቻ ቁልፍ ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብሮ መገኘት ነው፡፡ ስለሆነም የገጠመንን ችግር ለመፍታት ሁለት አበይት ተግባራትን እነርሱም ፡- 1. ጾምና ጸሎት 2. ሰማዕትነትን (መከራ መቀበልን) ለመፈፀም ወደ ኋላ ማፈግፈግ የለብንም፡፡ ጾምና ጸሎት እንኳን በቤተክርስቲያንና በሀገር ላይ ፈተና ተጋርጦ ይቅርና በየእለቱ የምንተገብረው ክርስቲየናዊ ተግባራችን ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ እግዚአብሔር ችግሩን እንዲፈታልን በግል፣በቤተሰብ፣በኅብረት በመሆን በጾም በጸሎት መበርታት ይጠበቅብናል፡፡ ይኸውም . ሳናቋርጥ በመጸለይ ፤ 1ኛ ተሰ 5፡17-18 . ከጥሉላት ምግብ በመራቅና መናኛውን በመመገብ ፤ መዝ 108፡24 ፤ዳን 10፡2-3 . ከአልጋችን ወርደን መሬት ላይ በመተኛት ዳን 9፥3 ፤ አስቴር 4፡3 በተሰበረ ልብ ከልቅሶ ጋር ሆኖ ፤ ኢዮኤል 2፡12 ። እግዚአብሔር በምህረቱ ይጎበኘን ዘንድ ተግተን እንለምን፡፡ ሰማእትነት (መከራ መቀበል) የቤተክርስቲያን ጌጥ፣ ዘር ነውና ከቅዱስ ፓትርያርካችን ጀምሮ ሁላችንም ሰውነታችንን ለሰማእትነት እናዘጋጅ ዘንድ እኛ ደካሞች ገዳማውያን በአምላከ ቅዱሳን ስም አደራ እንላለን ፡፡ ይኸውም፡- የጊዜ የገንዘብ የእውቀት የአካል የጉልበት - የሕይወት ሰማእትነት ለሚጠይቀው ሁሉ ምንም ሳናመነታ በእውነት ፣ በጥብአት (ክርስቲያናዊ ድፍረት)፣ በፍቅር (ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ ) የሚጠበቅብንን ማድረግ ነው :: ሮሜ 8 ፥ 35 ምንአልባት አንዳንዶች ሰማእትነት ለመቀበል ንሰሐ ስለአልገባሁ እፈራለሁ ልትሉ ትችላላችሁ። ነገር ግን የቤተክርስቲያናችን የሰማእትነት አስተምህሮ እንደሚነግረን አንድ ሰው ንሰሐ ሳይገባ በመጣው መከራ ውስጥ እራሱን በሰማእትነት በማሰለፉ _ ሰማእትነቱ ኀጢአትን ማስተሰርይ ብቻ ሳይሆን ከቅዱሳን ሰማዕታት እንደ አንዱ ያስቆጥረዋል፡፡ ስለሆነም መከራን ፣ ሰማዕትነትን ለመቀበል ሰውነታችንን ጨክነን ማዘጋጀት ያስፈልገናል፡፡ ይህ ሲሆን ደግሞ የቤተክርስቲያን ትንሳኤ ይሆናል፡፡ ወደፊት ምን ይደረግ ? አሁን የገጠመን ሰሞነኛ ችግር እኛ የሚጠበቅብንን ካደረግን ይፈታል ብለን እናምናለን፡፡ ነገር ግን ችግሮቻችን ስር የሰደዱና ለችግሮቹም ሁላችን ተጠያቂዎች ነን፡፡ ስለሆነም የነገይቱን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ወደ ቀድሞ ማንነቷ ትመለስ ብሎ ለመፍትሔው ያለምንም ማመንታት፡-

❤ የኢትዮጵያ ገዳማት መልእክት ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ቀን፡ - 18/05/2015 ❤ “በዓለም ሳለችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።” 【ዮሐ 6፥33】 ❤ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን የአንድነት ገዳማት ኅብረት መልእክት፦ ❤ ከቅዱስ ፓትርያርካችን ጀምሮ በየደረጃው ያላችሁ የመንጋው እረኞቻችንና ሕዝበ ክርስቲያን፣ ለአኀት አብያተ ክርስቲያናት፣ እውነተን ለምትፈልጉ እና ለምትከተሉ የሰው ልጆች በሙሉ ሰላምታችን ከያለንበት ቅዱሳን መካናት ይድረሳችሁ። ❤ የምናስተላልፈውን መልዕክትም ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ጊዜያችሁን በመስጠት እንድትመለከቱት እኛ ታናሽ እና ደካማ የሆን ገዳማውያንና ገዳማውያት በአምላከ ቅዱሳን ስም እንማጸናችኋለን፡፡ ❤ መልዕክታችንም ለሚከተሉት አካላት ይሆናል፡ - ፩. ለቅዱስ ፓትርያርካችን፡ - እስካሁን በአደረጉት በዕንባ የታገዘ የእረኝነት ተግባርዎት የረዳዎትን አምላክ እናመሰግናለን ወደፊትም እንለምናለን፡፡ ነገር ግን ይህ የተቀደሰ የመንጋው ጥበቃ ተግባርዎት በዚህ ከባድ የፈተና ጊዜ ይበልጡኑ ከዕንባዎት ጋር ለእርስዎ እና ለእኛ ይሆን ዘንድ እስከ አሁን ድረስ ከባዱን ፈተና ሁሉ በእግዚአብሔር ቸርነት እንደተወጡት አሁንም እግዚአብሔር በሚወደው እውነት ብቻ ጸንተው እንዲቆሙ እና በዚህም የሚቀበሉት መከራ ካለ የእውነተኛ እረኛነት ምድራዊ ደሞዙ ይኸው ነው እና ከእረኝነትና አባትነት ተግባርዎ አንዲትም እርምጃ ወደ ኋላ እንዳያፈገፍጉ እኛ ደካማ ልጆችዎት በቅዱሳኑ ስም እንማጸንዎታለን፡፡ ፪. ለብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፡ - እስካሁን በዘመነ ሲመተ ክህነታችሁ ክፉውንም በጎውንም አሳልፋችኋል። የአሁነ ግን ከሁሉ የከፋ ይመስላል፤ የሚከፋው ግን በእውነት በመኖር እና ለእውነትም የሚከፈለውን መከራ የምትሸሹ የምታፈገፍጉ ከሆነ እንጂ በእውነት ላይ ለእውነት ከቆማችሁ እናንተም ከብራችሁ ቤተ ክርስቲያንንም የምታስከብሩበት ጊዜ አሁን ስለሆነ ደስ ሊላችሁ ይገባል። ይህ ግን ፍርሐትን፣ምቾትን፣ማስመሰልን ይጠላል በምትኩም ጥብአት፣መከራ እና እውነት ይስማማዋል። ስለዚህም የእስካሁኑን ሁሉ ድክመታችሁን አስወግዳችሁ ማስፈራሪያቸውን ሳትፈሩ እውነትን እንድትገዟት እንጂ እንዳትሸጧት ደካሞች ልጆቻችሁ አደራ እያልናችሁ ምናልባትም አንድ አንድ ደካማ ጎኖችንና ማስመስያን እየፈለጉ የሚጠቃቅሱ ቢኖሩም በምትባሉት ነገር ሁሉ ግድ ሳይሰጣችሁ ለመንጋው እረኝነት ያበቃቻችሁን ቤተ ክርስቲያን ከማስከበር የበለጠ ምንም ተልዕኮ እንደማይኖራችሁ ታውቃላችሁና እውነትን በመኖር ለእኛ ለበጎቹ ምሳሌ ሁኑን፡፡ በቅድሚያ ስለልጅነት ድፍረታችን ይቅርታ አድርጉልንና ይህ ሁሉ የሆነው በእናንተ በእረኞቹ እና በእኛ በበጎቹ የክርስትናውን ዓላማ እና ተግባር እንደሚገባ ያለመኖር ነው፡፡ ስለሆነም ወደፊት እንዴት መኖር እንደሚገባን ከራሳችሁ ጋር እና በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤያት ምከሩ። እኛንም መንገዱን በማሳየት ምሳሌ ትሆነን ዘንድ ደካሞች ልጆቻችሁ በቅዱሳን ስም እንማጸናችኋለን፡፡ ፫. ሲመተ ኤጲስ ቆጶስ ሰጥተናል ላላችሁ ሊቃነ ጳጳሳት እና “ኤጲስ ቆጶስነት ተሹመናል" ላላችሁ መነኮሳት፡ - በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የፈጸማችሁት ተግባር ስህተት መሆኑን እኛ ደካሞች ገዳማውያን በትህትና ድፍረት ልንነግራችሁ እንወዳለን፡፡ ስለሆነም ያለው አማራጭ ሁለት ነው - አንደኛው በፍጹም ንስሐ ያሳዘናችኋትን ቤተክርስቲያን ደስ ማሰኘት እና እናንተም ምድራዊ እና ሰማያዊ ሰላም ማግኘት፤ ሁለተኛው ደግሞ ከቅድስት ቤተክርስቲያናችን አንድነት መለየት ነው᎓᎓ ነገር ግን ሁለተኛው አማራጭ ለእናንተም ለእኛም ሀዘን ነውና የመጀመሪያውን አማራጭ ትተገብሩት ዘንድ እኛ ደካሞቹ በፍፁም ፍቅርና ትህትና በአምላከ ቅዱሳን እንማጸናችኋለን፡፡ በዚህም ቤተክርስቲያን /የሰማይ መላእክትና ምድራውያን ክርስቲያኖች/ ደስ ይስኙ፤ጠላት ዲያብሎስም ይፈር በቤተክርስቲያን ውስጥ ችግር እንዳለ ሁላችንም እናውቃለን፤ስለምን ችግር ኖረ ብንል ግን ምክንያቱ ሁለት ነው፡ - • እኛ /እረኞቹና በጎቹ ክርስትናውን እንደሚገባ ስለ አልኖርነው᎓᎓ • በምድር ያለችው ቤተክርስቲያን ተጋድሎዋን ያልጨረሰች በፈተና ውስጥ ያለች ስለሆነች:: ታድያ ይህን ችግር ለመፍታት የሄዳችሁበት መንገድ በእኛ በደካማ አእምሮአችን ኢኦርቶዶክሳዊ፣ኢሃይማኖታዊ መንገድ መሆኑ ነው እና ትልቁ ስህተት እባካችሁን ወደ ኦርቶዶክሳዊ መንገድ ወደ ሃይማኖታዊ መንገድ ተመለሱ ብለን በአምላከ ቅዱሳን ስም እንለምናችኋለን፡ መመለሳችሁም ከልብ እንዲሆን ስለፍቅር አምላክ እንማጸናችኋለን። ፬. ለአበው ካህናት፣መምህራን፣ሰባክያነ ወንጌል እና ዲያቆናት፡ - እናንተም የሰሞኑን እና የእስካሁን /የቆየውን የቤተክርስቲያን ችግር ለመፍታት መጀመሪያ ከራሳችሁ ጀምሩ፣ ሰውነታችሁን ለመንፈሳዊ ነገር አሰልጥኑት፡፡ ከዚያም ለምትመሩት፣ ለምታስተምሩት ሁሉ በእውነት እና በፍቅር ምሳሌ ሁኑ፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑም ከእውነት ጋር እንዲቆምና ለእውነት ዋጋ እንዲከፍል /ከመከራው እንዲሳተፍ እና ከመከራዉም እንዳይሸሽ/ እናንተ ቀዳምያን በመሆን አትጉት፡፡ አለበለዚያ ለዚህ ጊዜ ያልሆነ ክህነት እና ኃላፊነት ባትይዙትና ባትቅበሉት የተሻለ ነበር። ከፊታችሁ እግዚአብሔር መልካም ዕድል አመቻችቶላችኋል እና ይህን በመከራ ውስጥ ያለን በረከት ትሳተፉ ዘንድ እኛ ደካሞች ገዳማውያን ለተልዕኮ በምትፋጠኑላት ቤተ ክርስቲያን ስም አደራ እንላችኋለን፡፡ ፭. ለአብነት ተማሪዎች እና ለመንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት፡ - የወደፊት የቤተክርስቲያን ተረካቢዎች ስለሆናችሁ ሙሉ ሕይወታችሁን ለቅድስና፣ ለንጽህና የተዘጋጀ አድርጉ። ምክንያቱም ክህነታዊ አገልግሎት ዋናው መሰረቱ የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በጸሎት እየተጋችሁ የእውነተኛ ደቀ መዝሙር ተግባር በመፈጸም፣በማስተዋል የድርሻችሁን ትወጡ ዘንድ አደራ እንላለን፡፡ ፮. ለቤተክርስቲያን ማኅበራት፣ሰ/ት/ቤት እና ወጣቶች፡ - ዘመኑን ዋጅቶ በመስራት እስካሁን ባደረጋችሁት ሱታፌ ቤተክርስቲያን ታመሰግናችኋለች᎓᎓ ነገር ግን ዛሬ እና ነገ /አሁንና ወደፊት/ ከዚህ በላይ መሥራት እንዳለባችሁ ልናሳስባችሁ እንወዳለን፡፡ ደግሞም የተከሰተውን ችግር ለመፍታት፡- • ከማንኛውም የቤተክርስቲያን አካል ጋር ተግባብቶ በመስራት • ሕዝበ ክርስቲያኑን ግንዛቤ በማስጨበጥ • በጾምና በጸሎት ተግቶ በማትጋት • ጎሰኝነትን በመጸየፍና በማስወገድ • እርስ በእርሳችሁ ተቀናጅቶ፣ተግባብቶ እና ተናቦ በመስራት • ይህን በመሳሰለው በጎ ሥራ ሁሉ የድርሻችሁን ትወጡ ዘንድ በቤተክርስቲያናችን ስም አደራችን የጠበቀ ነው፡፡ ፯. ለምዕመናን እና ምዕመናት /ሕዝበ ክርስቲያን/ ፡- እስካሁን ቤተክርስቲያን በምትፈልጋችሁ ሁሉ የልጅነት አስተዋጽኦዋችሁን አበርክታችኋል፡ ነገር ግን ካለፈው ይልቅ የወደፊቱ ተግባራችሁ ለእናንተ እና ለቤተክርስቲያን ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም ትህትናን ገንዘብ በማድረግ ሃይማኖትን ከምግባር በማስተባበር ቤትክርስቲያን ከእናንተ የምትጠብቀውን ሁሉ በማድረግ እራሳችሁ በምትከብሩበት እና ሰማያዊ ዋጋ በመታገኙበት መከራ ውስጥ ለማለፍ አታመንቱ ከምድራዊ ይልቅ ሰማያዊውን አስቡ በዚህም ሐሰትን፣ፍርሐትን ግብታዊ ስሜትን እና ማመንታትን ከእናንተ አርቃችሁ በእውነትና በእምነት ከእረኞቹ ጋር በመተባበር ለእናታችን ቤተክርስቲያን የሚጠበቅባችሁን ተግባራት ሁሉ እንድትወጡ ደካሞች ገዳማውያን በአምላከ ቅዱሳን ስም አደራ እንላችኋለን፡፡

20 tir.mp34.12 MB

photo content

photo content
+2

❤ በዚያን ጊዜም የመኰንኑ የአርያኖስ ወንድ ልጁ ሞተበትና እጅግ አዘነ፡፡ የከበረ አባ አክሎግም በዚህ ጊዜ "ፈጣሪዬን ለምኜ ልጅህን ከሞት ባስነሣልህ ምን ትሰጠኛለህ?" አለው፡፡ መኰንኑም እጅግ አዝኖ ተጨንቋልና ቅዱስ አክሎግን "የመቶ አለቃ አድርጌ ሾሜ በታላቅ ክብር ወደ አገርህ እልክሃለሁ" አለው፡፡ ቅዱስ አክሎግ ግን "ይህንንስ ፈጽሞ አልሻም ይልቁንም አሠቃይተህ ገድለህ ሰማዕትነቴን ትፈጽምልኝ እሻለሁ፣ ሥጋዬንም ወደ አገሬ እንድትልከው ማልልኝ" አለው፡፡ መኰንኑ አርያኖስም በቅዱስ አክሎግ ቃል እጅ ተገርሞና አዝኖ እንደምኞቱ ሊፈጽምለት እሺ ብሎ ማለለት፡፡ ❤ ቅዱስ አክሎግም ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ" ብሎ በሕፃኑ ላይ በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወዲያው የሞተው ሕፃን አፈፍ ብሎ ተነሣ፡፡ ይህንንም ታላቅ ተአምር ያዩ አሕዛብ ሁሉ "በእውነት ከቅዱስ አክሎግ አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እኛም በቅዱስ አክሎግ አምላክ አምነናል" ብለው ጮኹ፡፡ መኰንኑም ይህንን ባየጊዜ ተቆጣ፡፡ ከከተማም አውጥተው ሰፊ ጉደጓድ ቆፍረው በውስጡ እሳት አንድደው እንዲጨምሯቸው አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም አደረጉባቸውና ምስክርነታቸውን በድል ፈጽመው የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ቁጥራቸውም ስምንት መቶ ዘጠኝ ሆነ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ ቅዱስ አክሎግን በጽኑ ሥቃይ አሠቃየው፡፡ ወደ ሀገሩም ወስደው በዚያ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ ቅዱስ አክሎግም ይህንን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው፡፡ ወደጌታችንም በጸለየ ጊዜ ጌታችን በክብር ተገለጠለትና "ወዳጄ የምወድህ የአባቴና የመንፈስ ቅዱስ ወዳጅ ሰላም ለአንተ ይሁን" አለው፡፡ ዳግመኛም "ዋጋህን ልከፍልህ በመንግሥቴም ውስጥ ላሳርፍህ መጣሁ፤ ሦስት አክሊላትንም አዘጋጀሁልህ፣ አንደኛው ስለ ድንግልናህ፣ ሁለተኛው ስለ ሥቃይህ፣ ሦስተኛውም የዚህም ዓለም ክብር ንቀህ ስለተውህ ነው፡፡ በዚህች ዕለት ከእኔ የምትሻውን ሁሉ አደርግልሃለሁ፡፡ ስለ ስሜ ስለተሠቃየህ የማያልቅ ተድላን እሰጥሃለሁ፣ የመላእክት ሠራዊትም እንዲያገለግሉህ አደርጋለሁ፡፡ ዘላለማዊ ሕይወት ባለው በማዕዴ ውስጥ ከሁሉ ቅዱሳን ጋር ደስ አሰኝሃለሁ፡፡ ሥጋህ ባለበት የሚማልደውን ሁሉ ርዳታ የሚሻውንም በእግር ውስጥ ያለውንም በደዌ የተያዘውንም ሁሉ እኔ አድነዋለሁ፡፡ ልጁንም በስምህ የሚሰይመውን ሁሉ እኔ ልጁን እባርክለታለሁ፣ በበጎ አስተዳደግም አሳድገዋለሁ፣ ከክፉ ነገር እጠብቀዋለሁ፡፡ በስምህ መባ የሚያገባ ለጦም አዳሪዎቸም እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ምጽዋት የሰጠውን ኃጢአቱን ይቅር ብዬ የዘላለም ሕይወትን አርሰዋለሁ፡፡ ተክል ተክሎ፣ ዘር ዘርቶ በስምህ የሚለምነኝን ዘሩን እባርክለታለሁ፣ ፍሬውንም አበዛለታለሁ" አለው፡፡ ጌታችንም ከቅዱስ አክሎግ ጋር መነጋገርን በፈጸመ ጊዜ ባረከውና ከቀስሉ ሁሉ ፈውሶ ጤነኛ አደረገው፡፡ ሰማዕትነቱንም በትዕግስት እንዲፈጽም ነግሮት በክብር ዐረገ፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ አክሎግ ወደ ወታደሮቹ መለስ ብሎ "የታዘዛችሁትን ፈጽሙ" ብሎ ራሱን እንዲሰይፉት ሰጣቸው፡፡ ወታሮቹም በዚህ ጊዜ የቅዱስ አክሎግ ፊቱ እንደፀሐይ ሲያበራ አዩት፡፡ ከፊቱም የብርሃን ግርማ የተነሣ ወደ እርሱ መቅረብ ተሳናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ አንደኛው ወታደር እጁን ዘርግቶ የቅዱስ አክሎግን አንገት በሰይፍ መታውና ቅዱሱ ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም የቅዱስ አክሎግን ነፍስ በክብር ተቀብለው በዝማሬ ወደ ሰማይ አሳረጓት፡፡ ❤ ወታደሮቹም የአባ አክሎግን ሥጋ ከባሕሩ ዳርቻ ትተው በመርከብ ተሳፍረው ወደ አገራቸው ተመለሱ፡፡ ከዚያም ጐልማሶች ነበሩ ስለ ከበረ አባ አክሎግን በሰማዕትነት መሞት ወደ አገር ውስ ገብተው ለሕዝቡ ነግሩዋቸው። ሕዝቡም በሰሙ ጊዜ ተሰብስበው ከካህናቱ ጋር ሔዱ አንሥተው ተሸክመውም ወደ አገር ውሰሰጥ አድርሰው በአማረ ቦታ አኖሩት፡፡ ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በአባ አክሎግ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ "ሰላም ለመርምህናም ሰማዕት ፍጹም ኄር ገባሬ ተአምር"። ትርጉም፦ ፍጹም ደግ ተአምራትን አድርጊ ለኾነ ለሰማዕቱ መርምህናም ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም እብል አብሮኮሮስሃ ክቡረ። ዘአድምዐ በኒቆምድያ ዘኤጲስቆጶስ መንበረ። እንዘ ይስዕም አምላክ ለአፈ ዮሐንስ ምዕረ። ስምዐ ኮነ በሰማይ ከመ ውእቱ ነጸረ። እስመ ውእቱ ረድእ ዘይተሉ መምህረ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 20። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ደቂቀ እጓለ እምሕያው ይትዌከሉ በታሕተ ክነፊከ። ወይረውዩ እምጠለ ቤትከ። ወትሰቅዮሙ እምፈለገ ትፍሥሕትከ"። መዝ 35፥7፥8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 12፥28-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 2፥1-22። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥12-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አብሮኮሮስና የቀሲስ የቅዱስ አክሎግ የዕረፍታቸው በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳ (20) ቀን። ❤ እንኳን ጌታችን ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ በሽተኞችንም ይፈውሱ ዘንድ መርጦ ወደ ዓለም ከላካቸው ቁጥሩ ከሰብዓ ሁለቱ አርድእትና ከሰባቱ ዲያቆናት ለሆነ ለቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊው ደቀ መዝሙር ለሐዋርያው ለቅዱስ አብሮኮሮስ ለዕረፍት በዓል፣ ልጁን በስምህ የሚሰይመውን ሁሉ እኔ እባርከዋለሁ ብሎ ጌታችን ቃል ኪዳን ለገባለት በግብጽ አገር እልፈንት ከሚባል ከተማ ለከበረ ቀሲስ ለቅዱስ አክሎግ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ለታላቁ ሰማዕት ለመምህናም ቤተ ክርስቲያኑ ለከበረችበትና ተአምራቱ ለተገለጠበት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰማዕቱ ቅዱስ ብሕኑ ከመታሰቢያው፣ ከወንጌሉ ዘወርቅ ከቅዱስ ዮሐንስም ቤተ ክርስቲያኑ ከከበረችበትና ሥጋው ወደ ሮሜ ከፈለሰችበት፣ ከአባ ኖኅ፣ ከአባ ስልዎኖስና ከአባ አብድዩ ከመታሰቢያቸው ረድኤት በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ቅዱስ አብሮኮሮስ፦ ይህም ቅዱስ በጽርሐ ጽዮን ከሐዋርያት ጋር ሁኖ ሳለ የአጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተመላ። እርሱም ሐዋርያት መርጠውት ከሰባቱ ዲያቆናት ጋር የተቆጠረ ሆነ እነርሱ መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ዕውቀትም ያላቸው እንደሆኑ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ስርሳቸው ምስክር ሆነ። ❤ ከዚህም በኋላ ለወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝመሩ ሆነ ከእርሱም ጋር ወደ ብዙ አገሮች ሔደ በቢታንያ አገር በኒቆምድያ ከተማ ላይ በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሾመው። እርሱም የክብር ባለ ቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት አስተማረ ከዮናናውያንም ብዙዎችን መልሶ ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው የወንጌልንም ትእዛዞች እንዲጠብቁ አስተማራቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሠርቶ ቀሳውስትን ዲያቆናትን ሾመላቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ያቺን አገር ወደሚከቧት አገሮች ወጣ በውስጣቸውም የከበረ ወንጌልን ሰበከ ብዙዎችንም ከስሕተት መለሳቸው አይሁድንም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ነገር ግን ብዙ መከራና ስደት ደረሶበታል ስለ ክርስቶስ ስም ተጋድሎ በመልካም ሽምግልና ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ በቅዱስ አብሮኮሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቀሲስ አባ አክሎግ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዲዮስቆሮስ የእናቱ ስም አፎምያ ነው እነርሱም ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናቸው በወርቅ በብር ባላሞችና በበጎች በፈረሶችና በግመሎች እጅግ የበለጸጉ ናቸው ነገር ግን ልጅ የላቸውም ስለዚህም ያዝኑ ነበር። ልጅምንም ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ሲለምኑ ኖሩ ልመናቸውንም ተቀብሎ ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም አክሎግ ብለው ጠሩት ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ ጣዕም ያለው ይሆናል ማለት ነው። ❤ ስምንት ዓመትም በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔርን ሕግ ይማር ዘንድ ለመምህር ሰጡት የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሁሉ ተማረ ሁል ጊዜም ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ ምስጋናዎችንና ጸሎቶችን ይሰማል ይህንንም የሚያደርግ ወደ መምህር ከመሔዱ አስቀድሞ ነው። ❤ በአንዲትም ዕለት ከመምህሩ ዘንድ ወጣ ወደ ቤቱም ሊሔድ በፈረስ ተቀምጦ ሁለት አገልጋዮችም ተከትለውት ሲጓዙ ብዙ ወንዶችና ሴቶች ተሰብስበው ሲጮሁ አያቸው የሆነውንም ሊያይ ወደ ርሳቸው ቀረበ። እባብ የነከሰውና ለሞትም የቀረበ አንድ ሕፃን በመካከላቸው ወድቆ አገኘ። የከበረ አክሎግም "ይቺ ምልክት በስሜ የሚያምኑትን ትከተላቸዋለች በስሜም አጋንትን ያስወጣሉ አዳዲስ ቋንቋን ይናገራሉ የምድር አራዊቶችን በእጃቸው ይይዛሉ የሚጐዳቸውም ነገር የለም" ያለውን የከበረ የወንጌልን ቃል አሰበ። በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን እጅ ይዞ "በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም" ብሎ በላዩ በመስቀል አማተበና "ሕፃን ሆይ ከዚህ ክፉ እባብ መርዝ ትድን ዘንድ እናገርሃለሁ ጌታችን ንጹሕና እውነት በሆነ ቃሉ እባቡን ጊንጡን የጠላትን ኃይል ሁሉ ትረግጡ ዘንድ እነሆ ሥልጣን ሰጠኋችሁ ምንም የሚጐዳችሁ ነገር የለም ብሏልና" አለ ወዲያውኑ ያ ልጅ ዳነ ከክፉ ነገርም ምንም ምን እንዳልደረሰበት ሆነ። ሕዝቡም ይህን ተአምር በአዩ ጊዜ እጅግ አደነቁ በቅዱሳኑ አድሮ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት የዚችም ተአምር ወሬዋ በአገሩ ሁሉ ተሰማ። ❤ ከመምህሩም ዘንድ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አራቱን ወንጌሎች የሐዋርያት ሥራ ዐሥራ አራቱን የቅዱስ ጳውሎስን መልእክቶች ሰባቱን የሐዋርያት መልክታት የቅዱስ ዮሐንስንም ራእይ መቶ ሃምሳውን የቅዱስ ዳዊትን መዝሙራት የነቢያትንና የሰሎሞንን መኀልይ ጠንቅቆ አጠና። ሁል ጊዜ በቀንና በሌሊት ያነባል በእሑድ ሌሊትም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያገለገለ ያድራል ሁል ጊዜም አዘውትሮ ይጾማል ይጸልያል። ❤ ወላጆቹም ከአረፉ በኋላ ሰዎች መልካም ተጋድሎውን በአዩ ጊዜ ስለ እነርሱ ይጸልይ ዘንድ ቅስና እንዲሾምላቸው ኤጲስቆጶሱን ለመኑት እርሱ በዘመኑ ሁሉ በየሁለት ቀን በየሦስት ቀን በየሱባዔው ይጾማልና በልብሱም ውስጥ ማቅ ይለብሳልና። ቅስና ይሾም ዘንድ የእግዚአብሔር ጸጋ ጠራቸውና ኤጲስቆጶሱም ወስዶ ሳይወድ በግድ ቅስና ሾመው በተሾመ ጊዜም ለአባ አክሎግ የክህነት ሹመት ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያለ ሲጮህ ሕዝቡ ቃልን ሰሙ ኤጲስቆጶሱና ሕዝቡ ቃልን ሰሙ ኤጲስቆጶሱና ሕዝቡም እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ❤ ከእነዚያ ወራቶችም በኋላ በአገሩ ሁሉ በክርስቲያን ወገኖች ላይ ከከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ አብያተ ክርስቲያናትንም አፈረሰ ብዙዎችም በሰማዕትነት ሞቱ። ምስክርም ይሆን ዘንድ አባ አክሎግን እግዚአብሔር ጠራው እነርሱም ቆመ ወደሰማይም ቀና በማለት እንዲህ ብሎ ጸለየ "ዓለሙን ሁሉ የያዝክ ጌታዬ ፈጣርዬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በአገርህ በሁለመናዋ ላሉ ሕዝብ ቸርነትህን ይቅርታህንና ሰላምህን አድርግ። ትባርካቸውም ዘንድ ከሰይጣናትም ስሕተት ታድናቸው ዘንድ ለእኔም ስለ ከበረው ስምህ ታጋድሎዬን እስከምፈጽም ያጸናኝ ዘንድ ቸር መልአክህን እንድትልክልኝ እለምንሃለሁ ኃይል ክብር ገንዘብህ የሆነ ለዘላለሙ አሜን"። ❤ ከዚህም በኋላ በዙሪያው ወዳሉ ሰዎች ተመልሶ "የሚሻ ይምጣ ከእኔ ጋር ይሒድ" አለ የእርሱ ሰዎችና የአገሩ ሰዎች ሦስት መቶ አርባ ተከተሉት በከፍታ ቦታ ላይም ቁመው "እኛ በግልጥ ክርስቲያን ነኝ" ብለው ጮኹ። የንጉሡም የሠራዊት አለቃ ሰምቶ አዘነ አባ አክሎግንም አሥሮ ለመኰንኑ ለአርያኖስ ሰጠው እርሱም "ለአማልክት ስገድ" አለው አባ አክሎግም "ለክብር ባለቤት እሰግዳለሁ እንጂ እኔ ለረከሱ አማልክት አልሰግድም" አለ። ❤ በዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስም ተቆጣ ይዞ እጅግ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎች አሠቃየው፡፡ ብዙ ካሠቃየውም በኋላ እንዲሞት ከእሳት ምድጃ ውስጥ በከተተው ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እሳቱን እንደ ውኃ አቀዘቀዘለት፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ 340ውን ሰዎች ጠርቶ ለአማልክት እንሰግዱ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱም "የምሰግድለት አምላካችን እግዚአብሔር ብቻ ነው" በማለት ጣዖታቱን ረገሙበት፡፡ መኰንኑም ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ እንደትእዛዙም በየተራ ቆረጧቸውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ የከበረቸ በረከታቸው ትደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡