en
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Open in Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Show more
1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
23 tir.mp32.36 MB

photo content

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳፫ (23) ቀን። ❤ እንኳን ከሰባ ሁለቱ አርድእት ለአንዱ ለሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ (በመንፈስ ልጁ) ለሆነው ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ለዕረፍት በዓልና ለጻድቁ ንጉሥ ለቴዎዶስዮስ ለመታሰቢያ በዓሉ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ ሰማዕታት ከቅዱሳን ጌርሎስና አትናቴዎስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ "ሰላም ለቴዎዶስዮስ ንጉሥ ዘፈጸመ መንግሥቶ በሕገ ቈስጠንጢኖስ ዘኮኖሙ ለክርስቲያን ዐምደ ዘኢይጸንን፤ በመዋዕሊሁ ዘተከሥተ መድፍን"። ትርጉም፦ በርሱ ዘመን የተሰወረው ወርቅ የተገለጠ፤ ለክርስቲያን የማያዘነብል (የማያጋድል) ምሰሶ የኾናቸው መንግሥቱንም በቈስጠንጢኖስ ሕግ የፈጸመ ለኾነ ለንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ ቅዱስ ጢሞቴዎስ፦ የዚህም ቅዱስ ልደቱና እድገቱ ልስጥራን ከሚባል አገር ነው አባቱም ከዋክብትን የሚያመልክ ዮናናዊ ነው እናቱ ግን በኦሪት ሕግ ጥላ ሥር ያለች ናት። የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም በልስጥራን አገር በሰበከ ጊዜ ይህ ጢሞቴዎስ ስብቱንና ትምህርቱን ሰማ እግዚአብሔርም በቅዱስ ጳውሎስ እጅ የሚደያደርጋቸውን ድንቆች ተአምራቶችን አይቶ እሊህም ተአምራቶች አስተዋዮችን አይቶ እሊህም ተአምራቶች አስተዋዮችና ጥበበኞች የሚደነግጡባቸው ናቸው ስለዚህም ወደ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ሒዶ በእርሱ ትምህርት በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቆ የሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ ሆነ ወደ ብዙ አገሮችም ተከትሎት በመሔድ ከእርሱ ጋር ደከመ ታላቅ መከራና ብዙ ኀዘንም ደርሶበታል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኤፊሶን ውስጥ በአንዲት አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው። ❤ በዚያንም ጊዜ ወደርሷ ገብቶ ለሰዎቿ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ብዙዎችንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ከዚህም በኋላ በዙሪያዋ ወዳሉ ብዙዎች አገሮች በርቀትም ለሚገኙ አገሮችም የከበረ ወንጌልን ሰበከላቸው። የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ሁለት መጻሕፍቶችን ጽፎ ወደርሱ ልኳል እርሳቸውም ሕዝቡን የሚያስተምርባቸው ራሱም ከቢጽ ሐሳውያን የሚጠብቅባቸው ቅስና ወይም ዲቁና ሊሾም የሚገባውንና የማይገባውን የሚለይበት ክህነት በማይገባው እጁን እንዳይጭን የሚያስጠነቅቁ ናቸው ጢሞቴዎስን ደግሞ ለርሱ ተወዳጅ ልጁ አድርጎ ይጠራዋል መልእክቶቹንም በእርሱ እጅ ወደ አገሮች ልኳል። ❤ በላያቸው የተሾመባቸውን የክርስቶስን መንጋዎች ፈጽሞ በጠበቀ ጊዜ በትምህርቶቹ በተግሣጾቹና በድርሰቶቹ ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ አይሁድንና ዮናናውያንን ይገሥጻቸውና ይዘልፋቸው ነበር እነርሱም ቀንተውበት ሁሉም በጠላትነት ተነሡበት ተሰብስበውም ጥር23 ቀን ገደሉት ምእመናንም ሥጋውን አንሥተው ቀበሩት ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከ ነገሠ በዚያው ኖረ እርሱም ስለ ሥጋው አስቦ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ በጥር ወር በሃያ ሰባት ቀን አፈለሰው በዚያችም ቀን በዓል አደረገለት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 23 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለጢሞቴዎስ ዘተሠይመ ቀዋሜ። በመልእክተ ጳውሎስ መምህረ ሮሜ። ለዮናናውያን ኮኖሙ ዘላፌ ወለአይሁድ ረጋሜ። እስከ አድምዐ እዴሆሙ ዘስምዐ ሞቱ ፍጻሜ። እንተ ተወሰነ ሎቱ ሶበ በጽሐ ዕድሜ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 23። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወበመንፈስ አዚዝ አፅንዐኒ። ከመ እምሐሮሙ ለኃጥአን ፍኖተከ። ወረሲዓን ይትመየጡ ኀቤከ። መዝ 50፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 1፥1-10፣ 1ኛ ጴጥ 3፥13-18 እና የሐዋ ሥራ 16፥1-13። የሚነበበው ወንጌል 12፥17-35። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ጢሞቴዎስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

#ጉድና_ጅራት_ከወደ_ኋላ_ነው! ዘንድሮ መቼስ የማናየው ጉድ የለም፡፡ ፍርድ ቤት ከመች ጀምሮ ነው የምንኩስና ስም መስጠት/ማጽደቅ የጀመረው? ስለዚህ ምንኩስና ተሾምኩ ያለው በፍርድ ቤት ነው ማለት ነ
+1
#ጉድና_ጅራት_ከወደ_ኋላ_ነው! ዘንድሮ መቼስ የማናየው ጉድ የለም፡፡ ፍርድ ቤት ከመች ጀምሮ ነው የምንኩስና ስም መስጠት/ማጽደቅ የጀመረው? ስለዚህ ምንኩስና ተሾምኩ ያለው በፍርድ ቤት ነው ማለት ነው?

በእነ አቶ አካለወልድ ስለተሾመው ሰውዬ (አቶ ጌታሁን ሞርኪ) የተረጋገጡ መረጃዎች፦ 1ኛ) መነኩሴም፣ ቄስም አልነበረም (የፌስቡክና የመታወቂያ ፎቶውን ይመልከቱ) 2ኛ) ባለትዳር ነው (ልጅም አለው)
+5
በእነ አቶ አካለወልድ ስለተሾመው ሰውዬ (አቶ ጌታሁን ሞርኪ) የተረጋገጡ መረጃዎች፦ 1ኛ) መነኩሴም፣ ቄስም አልነበረም (የፌስቡክና የመታወቂያ ፎቶውን ይመልከቱ) 2ኛ) ባለትዳር ነው (ልጅም አለው) 3ኛ) የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ አይደለም። የፕሮቴስታንት ተሀድሶ አባል ነው (መታወቂያውን እና በሰውየው ስም የተፈረመውን ደብዳቤ ይመልከቱ) 4ኛ) በገንዘብ ምዝበራና ሥራ በመበደል ከሚሰራበት ወረዳ ቤተ ክህነት የተባረረ ነው (ሌላኛውን ደብዳቤ ይመልከቱ)

አጋልጥ ሸር ሸር "በህገወጥ ከተሾሙት ውስጥ ተሐድሶዎችም ተካተዋል!" " ነገሮች ሁሉ ቀስ እያሉ ጉድ ይዘው እየወጡ ነው:፡ ይህ የምታዩት ሰው ከአዲሶች ጳጳስት አንዱ ነው:፡ ምንም እንኳን ሁሉም የእምነት ችግር የለባቸውም ባንልም ይህ ሰው ግን በግልፅ ተሃድሶ የነበረ የተሃድሶ መታወቂያ ያለው ሰው ነው:፡ የሚገርመው ደግሞ ሚስት አግብቶ የነበረ ሰው መሆኑ እጅግ የሚደንቅ ነው:፡ እንግዲህ ስብስባቸው ይህን ይመስላል፡፡ " በትክክል እነዚህ ሰዎች ቤተክርስትያንን አዳራሽ ለማድረግ እየሰሩ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ እስከመጨረሻው እንታገላለን፡፡ ለእምነታችን እንሞታለን:፡ ለእምነት ካልተሞተ ለማን ይሞታል: ሰማዕትነት ክብር ነው:፡ ለእምነት መሞት ደግሞ ሰማዕትነት ነውና በቤተክርስቲያን ቀልድ የለም:፡ ከ26ቱ ሲመተ ጵጵስና ውስጥ አንዱ ያገባና የተሐድሶ እምነት ስም፡ቄስ ጌታሁን ሞርኪ ዕድሜ 41 (1964) የአገልግሎት ስፍራ፡ደቡብ ኢትዮጵያ ስልክ፡091222379.... የተሠጠበት ጊዜ፡ሕዳር 15/2015 ያረጋገጠው አካል፡በኢትዮጵያ አለም ዓቀፋዊ የተሐድሶ ህብረት (የደቡብ ኢትዮጵያ ተሐድሶ ንቅናቄ ህብረት ሊቀመንበር, ዶ/ር ደርብ ሹምየ )

ጥር 22 በቅዳሴ ጊዜ የዕለቱ ምስባክ ፡ ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር መዝ ፺፩፥፲፪ @EOTCW ትርጕም፦ ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል። እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይበዛል። በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ የተተከሉ ናቸው። #Share https://t.me/Eotcw #ሼር

22 tir.mp32.29 MB

**👉ዘ ነግህ

photo content

🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 አመ ፳ወ፪ ለጥር በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ዑራኤል ስርዓተ ማኅሌት 🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀 የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ) ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሉ አለም፤በአሐቲ ቃል @EOTCW @EOTCW ገባሬ ኩሉ፦ @EOTCW ሰላም ለአብ ገባሬ ኩሉ ዓለም ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም። 👉@EOTCW 👉@EOTCW ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ዘመላእክት ዘይትሜነዩ ርእየቶ፣ በላዕለ ማይ ዘጠፈረ ቤቶ፤ተወልደ እምድንግል ያርኢ ኅሩቶ ለዘከመዝ ንጉስ ነአምን ልደቶ ነግሥ፦ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ። 👉@EOTCW 👉@EOTCW ዚቅ፦ በኀበ ኩሉ ዘተሰምየ መካነ ሰማእት መዋዕያን ፤ወመካነ ጻድቃን ቡሩካን፤ መመላእክት ትጉሃን፤ በኀበ ኩሉ መካን ርስት አንቲ፤ ወሥሎጥ ስምኪ በኀበ እግዚአብሔር 👉@EOTCW 👉@EOTCW መልክአ ዑራኤል፦ ሰላም ለዝክረ ስምከ እምኀሊበ ዕጉልት ዘይጥዕም፤ዓዲ እምወይን ዘውስተ ኤዶም፤ዑራኤል ክፍለከ ዘተሴረየ በደም፤ ሤመከ ወአልዓልከ የማነ እግዚአብሔር ግሩም፤ መድኀኒት ትኩን ለኩሉ አለም ወረብ፦ ከመ ሀሊብ ዘዕጉልት ወከመ ወይን ዘገነት ፪ ስምከ ይጥዕም 'ኡራኤል '፪ መልአክ ፪ 👉@EOTCW 👉@EOTCW ዚቅ፦ የማነ እግዚአብሔር ሢመከ ወአልዓለከ፣ሊቀ መላእክት ዑራኤል መልክአ ዑራኤል፦ ሰላም ለአዕይንቲከ ወአዕዛኒከ ሰማዕያን፤ ለመላትሒከ ቀይህ ወለአዕናፊከ ምዑዛን፤ዑራኤል ኮከብ ለሰብአ ሰገል ኄራን ፤መርሆሙ ወአብጽሆሙ እስከ ቤተልሔም መካን፤በአስተርዮቱ ለወልድ ዘድንግል ህፃን 👉@EOTCW ዚቅ፦ ወሀለው ኖሎት ውስተ ውእቱ መካን ይተግሁ ወይሔለው ወየዓቅቡ በራእይሆሙ ወስብሐት እግዚአብሔር ሠረቀ ላዕሌሆሙ ወይቤሎሙ መልአክ ኢትፍርዑ እዜንወክሙ ዓቢየ ፍስሐ ዘይከውን ለክሙ ፤ ወበጽሐ በጽሐ ዕለተ ወሊዶታ ወወለደት ወልደ ዘበኰራ 👉@EOTCW መልክአ ዑራኤል፦ ሰላም ለገብዋቲከ ስርግዋነ አክናፍ ዘእሣት፤ ወለከርሥከ ልኩዕ መብልዐ ቅዳሴ ሕይወት፤ዑራኤል ስዩም ላዕለ ኩሎሙ ብርሃናት፤ አድኅነነ ወቤዘወነ እምዕለት እኪት፤ወባልሐነ እምኩሉ መንሱት። 👉@EOTCW 👉@EOTCW ዚቅ፦ ረሰዮ እግዚኦ ለውእቱ ዑራኤል፤ እምኲሎሙ መላእክት ይትለዓል መንበሩ፤ ስዩም በኀበ እግዚኡ ምእመን 👉@EOTCW 👉@EOTCW መልክአ ዑራኤል፦ ዕምርት እለት በአለ ሲመትከ ዛቲ ፤ድህረ ዕረፍተ እምኪዳነ እስመ ተወክፈከ ባቲ፤ ዑራኤል ስዩም ካህነ መስቀል አሐቲ፤ ማህበርነ ዕቀብ ኩለሄ እምቅኔት ሰይጣን መስሐቲ፤ወጽዋዕ እዴከ ፈኑ ጽሙአን ታስቲ። 👉@EOTCW 👉@EOTCW ዚቅ፦ እምርት ዕለት በአልነ ነያ፤ ዑራኤል አብ ዘተመነያ፤ ስብሐ ወበዓለ ሰመያ 👉@EOTCW 👉@EOTCW ምልጣን፦ ይሰግዱ በብረኪዎሙ ወያሌዕሉ ሕሊናሆሙ በጥንቃቄ ወበኃሰስ ኃበ እግዚአሙ ንጉስ ቀዋምያን ለነፍሳት እሙንቱ ሊቃናት ዑራኤል ወሩፋኤል ይትፌነው ለሣህል እምኃበ ልዑል 👉@EOTCW አመላለስ፦ ይትፌነው ለሣህል፤ ለሣህል እምኃበ ልዑል 👉@EOTCW ወረብ ዘምልጣን፦ ቀዋምያን ለነፍሳት እሙንቱ ሊቃናት ዑራኤል ወሩፋኤል፤ ይትፌነው ለሣህል ይትፌነው ለሣህል እምኃበ ልዑል @EOTCW ዘሰንበት ተወልደ ክርስቶስ እምድንግል ወአስተረአየ በሥጋ ሰብእ፤መላእክት ይሰግዱ ሎቱ ወአምኁ ስብሐተ ልደቱ፤ ወርኢነ ወአስተርአየ ብዕለ ስብሐቲሁ፤ማ፦ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ ወይቤ ለልየ ርኢኩ፤በውስተ ምጥማቃት ከመ ርግብ 🍀🍀🍀 መዝሙር በ፮- እሙነ ኮነ ልደቱ እሙነ ኮነ ልደቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ እሙነ ኮነ ልደቱ እሙነ ኮነ ልደቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ እምሰማያት ወረደ ወእመላእክት ተአኵተ ወእማርያም ተወልደ እሙነ ኮነ ልደቱ እሙነ ኮነ ልደቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ወአስተርአየ ገሃደ እሙነ ኮነ ልደቱ እሙነ ኮነ ልደቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ ውእቱ አክሊለ ሰማዕት ውእቱ መድኃኔ ነገሥት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ ፤ማ፦እሙነ ኮነ ልደቱ ብርሃነ ኮነ ምጽአቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ። 👇👇👇👇 👉@EOTCW👈 👉@EOTCW👈 👉@EOTCW👈 👆👆👆👆👆 @EOTCW #Join & share

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ዋዜማ ዘጥር ዑራኤል 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁 ሱራፌል ወኪሩቤል ኢርእይዎ፤አዕላፍ መላእክት ይትለአክዎ፤ እንዘ ኢየሐፅፅ እምላዕሁ ወረደ፤ሰማይ ወምድር ዘኢያገምሮ ማህጸነ ድንግል እፎ እንከ ፆሮ፤ማ፦ ፆረቶ፤ወአግመረቶ ማርያም @EOTCW @EOTCW ለእግዚአብሔር ምድር በምላህ፦ ትጉሃን እለ ይነውው መላእክት በበስርአቶሙ ትጉሃን እለ ይነውው @EOTCW @EOTCW እግዚአብሔር ነግሰ፦ ዑራኤል መልአክ ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ ወበእንተ ነፍሰ ኩልነ መልአኪየ ይቤሎ መልአክት ሠምሮ መልአከ ኪዳኑ ለክርስቶስ አኮኑ @EOTCW ይትባረክ፦ ትጉሃን እለ ይነውው መላእክት በበስርአቶሙ ኪያከ አበ ይሴብሑ @EOTCW @EOTCW ሰላም፦ ዘሰበከ ሙሴ በኦሪት ወረደ ወልድ እምሰማያት ዘይስዕሎሙ ለህፃናት ወይነግሥ ለመላእክት አንሦስወ ዲበ ምድር ወይቤ ሰላም ለክብረ ቅዱሳን ቤዛ ብዙሃን ሎቱ ይደሉ ስብአት ወአኰቴት 👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCW👈 👉@EOTCW👈 👉@EOTCW👈 🇪🇹👆👆👆🇪🇹 @EOTCW #Join & share

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአባ እንጦንስ ርእሶሙ ለመነኰሳት ዘተውህቦ አስኬማ መላእክት እንተ ለብስዋ ሐዋርያት፤ ኮከበ ሐቅል፤ ዘበጽሐ እስከ መስፈርተ አካል"። ትርጉም፦ እስከ መጠመ አካል የደረሰ የበረሓ ኮከብ ሐዋርያት የተጐናጸፏት የመላእክት አስኬማ የተሰጠው ለኾነ፤ ለርእሰ መነኰሳት ለአባ እንጦንስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content
+4

❤ ከዚህም በኋላ በጻድቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ ዜናው በተሰማ ጊዜ በጸሎቱ ያስበው ዘንድ ንጉሡ እየለመነው ደብዳቤ ጻፈለት የከበረ እንጦንዮስ ግን ወደ ንጉሥ ደብዳቤ ዘወር አላለም ለወገኖቹ እንዲህ አላቸው እንጂ "የንጉሠ ነገሥት ደብዳቤ እነሆ በላያችን ይነበባል" ወንድሞችም እንዲህ ብለው ለመኑት "ይህ ንጉሥ የክርስቲያንን ወገኖች የሚወድ ጻድቅ ሰው ነው በደብዳቤ ጽፈህ ልታጽናናው ይገባል ከዚህም በኋላ እያጽናናውና እየባረከው ቤተ መንግሥቱንና ሠራዊቱንም እየባረከ ጻፈለት። ❤ ዳግመኛም በአፍርንጊያ ንጉሥ ዘንድ ዜናው በተሰማ ጊዜ ወደ ከበረ እንጦንዮስ እንዲህ ብሎ ጻፈ "ወደ እኛ መጥተህ በእኛ ላይ በአገራችንና በሠራዊታችን ላይ በረከትን ታሳድር ዘንድ ስለ ጌታችን ክርስቶስ መከራዎች እኔ ወዳንተ ፈጽሜ እማልዳለሁ"። የከበረ እንጦንዮስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ቁሞም እንዲህ ብሎ ጸለየ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እለምንሃለሁ በአፍርጊያ ውሰሰጥ ወዳለ ወደ በርኪኖን አገር ግለጥልኝ ነገር ግን ያንተ ፈቃድ ይሁን" ይህንንም ባለ ጊዜ ብርህት ደመና መጣች በዚያችም ሰዓት ተሸክማ ወደ አፍርንጊያ አገር አደረሰችው ንጉሡም ደስ አለው ሕዝብና ሠራዊቱም ሁሉ በሽቶኞችንም አቀረቡለትና ሁሉንም ፈወሳቸው የጽድቅና የሕይወትንም መንገድ እያስተማራቸው ከእነርሳቸው ዘንድ ስድስት ወር ኖረ። በእሁድም ዕለት ያቺ ብርህት ደመና ተሸክማ ወደ ገዳሙ ታደርሰውና ከልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ያረጋጋቸዋል በማግሥቱም ዳግመኛ ተሸክማ ወደ አፍርንጊያ አገር ትመልሰዋለች። ከዚህም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ በደመና ተጭኖ ወደ ገዳሙ አንደኛውን ተመለሰ። ❤ በአንዲት ዕለትም ስንፍና መጣበት እንዲህ የሚለውም ቃል መጣ "ታይ ዘንድ ወደ ውጭ ውጣ" በወጣ ጊዜም መልአኩን አየው በላዩም የምንኵስና ልብስ አለ መታጠቂያ ቅናት የመስቀል ምልክት ያቸው ቀሚስ በወገቡም አስኬማ በራስ ቊር አምሳልም በራሱ ላይ ቆብ አለ እርሱም ተቀምጦ ሰሌን ይታታል ከዚያም ተነሥቶ ይጸልያል ዳግመኛም ተቀምጦ ሰሌን ይታታል በየሰዓቱም እንዲህ በማድረግ ይጸልያል። ሁለተኛም እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ "እንጦንዮስ ሆይ እንደዚሆ ሥራ አንተም ከስንፍና ከሰይጣናት ጦርነት ታርፋለህ" ያንን ያየውንም ተቀብሎ እንዲሁ አስመስሎ የሚሠራ ሆነ ከዚያችም ዕለት ወዲህ ስንፋናና የሰይጣናት ውጊያ አልመጣበትም። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ብዙ ጊዜ ተገልጾ አረጋግታል አጽንቶታልም። አሁንም እንዲህ አለው "የመረጥሁህ እንጦንዮስ ሆይ እውነት እነግርሃለሁ እኔን ስለመውደድህ በዚች በረሀ ውስጥ ብቻህን በመጋደልህና በማገልገልህ ስለ ድካምህ ስምህን ከፍ ከፍ አደርጋለሁ ሥልጣንህንም በዓለም ዳርቻ ሁሉ ከፍ አደርገዋለሁ። ገዳትንና አድባራትንም መነኰሳትን የተመሉ ሁነው ቅኖች የዋሃን ጻድቃን እንደሚኖሩባቸው አደርጋቸዋለሁ ይልቁንም ያንተ ገዳማት እነርሱ እስከ ፍጻሜ ይኖራሉ። መታሰቢያህንም የሚያደርገውን ሁሉ ለድኆች ምጽዋትን ለቤተ ክርስቲያን መባ በስምህ የሚሰጠውን ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ ከቶ ሥቃይን አያያትም በውስጡ ሥጋህ የሚቀበርበትንም ገዳም እጅግ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ በውስጡም እንደ መላእክት የሆኑ ደጋጎች መነኰሳት እንዲኖሩበት አደርጋለሁ ከእርሳቸውም እስከ ዓለም ፍጻሜ አለቃ የሚሆን አይታጣም የምድር ነገሥታት መሳፍንትና ሹማምንት ለገዳምህና ፍለጋህን ለሚከተሉ ልጆችህም እጅ መንሻ ተሸክመው እንዲመጡ አደርጋለሁ" ጌታችንም ይህን ከተናገረው በኋላ ከእርሱ ዘንድ ወደ ሰማያት በታላቅ ክብር ዐረገ አባ እንጦኒም ፈጽሞ ደስ አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ስለ ቤተ ክርስቲያን መፍረስ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "መናፍቃን በላይዋ ይሠለጥናሉ ከዚህም በኋላ ወደቀድሞ ሥርዓቷ ትመሰላለች" ዳግመኛም ስለ መነኰሰሠት እነርሱ እጅግ እንደሚበዙ ገዳማቻቸውንና አድባራቶችን በመተው ወርደው ከዓለማውያን መካከል በከተማዎችና በቦታዎች ውስጥ እንደሚኖሩ ስለ ዓለም ፍጻሜም ትንቢት ተናገረ። ❤ ይህም አባ እንጦንዮስ አባ መቃርስን አስኬማንና የምንኵስና ልብስን ያለበሰው የረጋጋውና ያጽናናው ከእርሱ የሚሆነውንም ያስረዳው ነው ደቀ መዝሙሩና ልጁ ስለሆነ። ከዚህም በኋለሠ የገዳማውያን አለቃ ወደሆነ ወደ አባ ቡላ ሒደ እርሱም ለሥጋው ያሰበና በሐዋርያዊ አትናቴዎስ ልብስ የገነዘው ነው። ❤ ዕረፍቱም እንደቀረበ በአወቀ ጊዜ በትሩን ለልጁ ለአባ መቃርስ ምንጣፉን ለአባ አትናቴዎስ የፍየል ሌጦ ዐጽፉን ለልጁ ለኤጲስቆጶሱ ለአባ ሰራብዮን እንዲሰጡ ልጆቹን አዘዛቸው። ከዚህም በኋላ በምድር ላይ ጋደም አለ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ ወደርሱም ሁሉም የመላእክት ማኅበር መጥተው በክብ በምስጋና ፍጹም ተድላ ደስታ ወዳለበት ዘላለማዊ ዕረፍት ተቀብለው አሳረጉት። ሥጋውን ግን ልጆቹ እንዘዛቸው ሰወሩት እርሱ የቅዱሳን ሰማዕታትን ሥጋቸውን የሚገልጡትን ይገሥጻቸው ነበርና ስለ እነርሱ ሥጋ ብዙ ገንዘብ እስከ መቀበል ደርሰው ዓለማዊ ጥሪት ያደርጉታልና። ❤ ይህም የከበረ የተመሰገነ አባት እንጦንዮስ እሰሰከ መልካም ሽምግልና ደረሰ እጅግም አረጀ ግን ወደ ወደደውም ክርስቶስ እስከ ሔደ ድረስ መልኩ አልተለወጠም ብርታቱ ጽናቱም መላው ዕድሜውም መቶ ሃያ ዓመት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ አባት በአባ እንጦንዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር22 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለብሕታዌሁ እንበ ሕጸጽ ወንትጋ። ውስተ ናሕስ ከመ ዖፍ ወበቤት አምሳለ ጉጋ። ብእሴ ሰማይ እንጦኒ ወመልአከ ምድር በጸጋ። ለቤተ ብለኔ እንዘ ይሜንን ሕጋ። መዋዕለ ሕይወት ኢተኀዕበ ሥጋ"። ትርጉም፦ ያለፍጹም ጒድለት ለብቸኝነቱ ሰላምታ ይገባል፤ እንደ ዎፍ በሰገነት እንደ ጒጒት(ቊንጫ) በቤት ውስጥ ኾኖ፤ በጸጋ የምድር መልአክና የሰማይ ሰው የኾነ እንጦኒ የመታጠቢያ ቤት ሕጓን እየናቀ መላ ዘመኑን አካሉን አልታጠበም። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 22። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳፪ (22) ቀን። ❤ እንኳን በግብጽ አገር ከቅማን ከተማ ለከበረና ለገነነ ለመነኰሳት ሁሉ አባት በገዳም ለሚኖሩ እንደ ኮከብ ለሚያበራላቸው ለአባ እንጦንስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከማፍን ኤጲስቆጶስ ከአባ ሚናስ እግዚአብሔር አምላክ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ ምልጣን ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ነፍሰከ መላእክት አዕረጉ በስብሐት እምድር ውስተ ሰማያት እንዘ ይብል በአርያም ስብሐት አማን እንጦንዮስ መሠረት። ትርጉም፦ በእውነት መሠረት የኾንክ እንጦንዮስ ሆይ መላእክት በአርያም ምስጋና ይሁን እያሉ ነፍስህን በምስጋና ከምድር ወደ ሰማያት አሳረጉ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ ርእሰ መነኰሳት አባ እንጦስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ንጹሐን ክርስቲያን ናቸው እርሱም ከታናሽነቱ ጀምሮ ተንኰል ሽንገላ በልቡ ውስጥ የለውም ከወላጆቹም ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ በቆረበ ጊዜ ከሕፃናት ጋር በመጫወት ከቶ አይስቅም ነበር። ጥቂት በአደገም ጊዜ ራሱን ዝቅ አድርጎ ለወላጆቹ ይታዘዝ ነበር ሰባት ዓመትም በሆነው ጊዜ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን ተማረ ያን ጊዜም የእስክንድር አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ቲዎናስ የተሾመበት ዘመን ነበር የእንጦንዮስንም ወሬውን ሰምቶ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ባረከውና ስርሱ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "ይህ ሕፃን በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናል ዜናውም በዓለሙ ሁሉ ይወጣል" እጁንም በላዩ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ❤ ከዚህም በኋላ ወላጆቹ በሞቱ ጊዜ ታናሽ ብላቴ እኅት ትተውለት ነበር። ከሰባት ወርም በኋላ እንደ ልማዱ ወደ ቤተ ክርስቲያን በሔደ ጊዜ የመንፈስ ቅዱስ ፍቅር በልቡ አደረበትና በኀሳቡ በዓለም የሚሠራውን ሁሉ አባቶቻችን ሐዋርያት ሁሉን ዓለምን ሥራ ትተው ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት ተከትሉት በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍም እንደተጻፈ ጥሪታቸውን እየሼጡ የሽያጩንም ዋጋ በሐዋርያት እግር ሥር ያኖሩትን አሰበ "እግዚአብሔር በሰማያት ያዘጋጀላቸው ዋጋቸው ምን ያህል ይሆን" አለ ይህም ኀሳብ በልቡ ውስጥ የሚወጣ የሚወርድ ሆነ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደ የክብር ባለቤት ጌታችን በከበረ ወንጌል ለባለጸጋው የተናገረውን ሰማ እንዲህ ሲል "ፍጹም ትሆን ዘንድ ከወደድክ ሒድ ጥሪትህን ሁሉ ሽጠህ ለድኆች ስጥ በሰማይም ላንተ ድልብ አድርገው መጥተህም ተከተለኝ"። ከእግዚአብሔር ዘንደሰ ይህን ልዩ ኀሳብ አግኝቶ ይህ ቃል ስለርሱ እንደተነገረ አሰበ በዚያንም ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን ወጣ ለአባቲም ያማረ ሰፊ ምድር ነበረው ለአገሩም ሰዎች ሰጣቸው ለርሱ የተዉለትንም ጥሪታቸውን ሁሉ ሽጦ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጣቸው እኅቱንም ወስዶ ከደናግል ገዳም አስገባት። ❤ በዚያንም ወራት የምንኵስና ሥርዓት አልተገለጸም ነበር እግዚአብሔርንም ለማገልገል የሚሻ ከመንደር ጥቂት ወጣ ብሎ ብቻውን በመቀመጥ በጾም በጸሎት ተወስኖ ይጋደላል የከበረ እንጦንዮስም እንዲሁ አደረገ ሰይጣናትም በስንፍናና በዝሙት ጦር የሚዋጉት ሆነ በሕልሙም የሴት ገጽ በማሳየት አብራውም እንደምትተኛ ያደርጓታል። ❤ ከዚህም በኋላ ባበባህር ዳርቻ ወዳለች የመቃብር ቤት ሒዶ በዚያ የሚኖር ሆነ በላዩ በአደረ በእግዚአብሔርም ረድኤት በተጋድሎ በረታ ምግቡንም ከዘመዶቹ ወገን ያመጡለት ነበር ሰይጣናትም ሲጋደል አይተው ቀኑበት ታላቅ ድብደባንም ደብድበው ጥለውት ሔዱ ዘመዶቹም ሲመጡ እንደ ሞተ ሁኖ ወድቆ አገኙት ተሸክመውም ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት ጌታችንም አዳነው በነቃም ጊዜ ወደ ቦታው ተመልሶ ይጋደል ዘንድ ተጋድሎውን ጀመረ። ❤ በዚያንም ጊዜ ሰይጣናትን ወደርሱ ሲመጡ አያቸው በአራዊት አምሳል በአንበሶችና በተኵላዎች የተመሰሉ አሉ በእባቦችና በጊንጦችም የተመሰሉ አሉ ያስፈሩትም ዘንድ አንዱም አንዱ በላዩ ተነሣሡ እንጦንዮስም "በእኔ ላይ ለእናንተ ሥልጣን ካላችሁ ከእናንተ አንዲ ያቸንፈኝ ነበር" ብሎ ዘበተባቸው ወዲያውኑ እንደ ጢስ ተበተኑ በሰይጣናት ላይ ድልን እግዚአብሔር ሰጥቶታልና ሰይጣናትም ከሚያመጡበት መከራና ሥቃይ ዐረፈ። ምግቢንም በየዓመቱ ሁለት ጊዜ ያበስላል በፀሐይም ያደርቀዋል ወደበዓቱም ማንም እንዲገባ አያሰናብትም የሚሻውም ሁሉ በውጭ ይቆምና ድምፁን ይሰማል እንጂ ሃያ ዓመትም እንዲህ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ በገድል ተጠምዶ ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ ፍጹም የሆነ እግዚአብሔርን መፍራትንና አምልኮቱን ለሰዎች ወጥቶ ያስተምር ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው ስለዚህም ወደ ፍጹም አገር ወጥቶ ብዙዎች ደቀ መዛሙርትን ሰብስቦ አስተማራቸው በእግዚአብሔርም ሕግ አጸናቸው ደቀ መዛሙርቶቹ በውስጣቸው የሚኖሩባቸው በዙዎች ገዳማት ተሠሩለት። ❤ ስለ ሃይማኖት ስደት በሆነበት ወራት በሰማዕትነት መሞትን ወዶ እስክንድርያ አገር ሔዶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ ከቶ አልያዙትም በክርስቶስም ስም የታሠሩ እሥረኞችን በመጐብኘት ቢአረጋጋቸውና ቢአጽናናቸውም አልያዙትም መኰንኑም እንደማይፈራ በአየው ጊዜ ከፍርድ አደባባይ ውስጥ እንዳይታይ አዘዘው እርሱ ግነሰ ሁል ጊዜ መታየትን አልተወም እንደመአሠየውና በሰማዕትነትም እንዲሞት የሚያስቆጣውን ነገር ይናገረው ነበረሰ መኰንኑም በእርሱ ላይ ምንም ክፉ ነገር አላደረገም አምላካዊት ኃይል ከልክላዋለችና። ❤ ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስ ለሰማዕታት ፍጻሜ ሁኖ የመከራው ወራት ከአለፈ በኋላ እንጦኒ ወደ ገዳሙ ተመለሰ ይህም በአምላክ ፈቃድ ሆነ የሚለብሰውም ማቅ ነበር በዘመኑ ሁሉ ገላውን በውኃ አልታጠበም ብዙዎች በሽተኞችም ወደርሱ ይመጣሉ በላያቸው ሲጸልይ ይድናሉ። ብዙዎች ሕዝቦችም ትምህርቱን ሊሰሙ ወደርሱ ሲመጡ በአያቸው ጊዜ ብቻውንም ይኖር ዘንድ እንዳልተውት አይቶ ከእርሱ ስለሚደረገው ነገር ልቡ እንዳይታበይ ፈራ እነርሱ ወደማያውቁት ቦታ ወደላይኛው ግብጽ ይሔደሰ ዘንድ ወዶ ወደ ባሕሩም ወደብ ደርሶ መርከብ እየጠበቀ ተቀመጠ ከሰማይም ወደርሱ ቃል መጣ እንዲህም አለው "እንጦንዮስ ሆይ ወዴት ትሒዳለህ ከዚህስ ምን ትሻለህ" አለው እርሱም "ብዙዎች ወደእኔ ስለሚመጡ እንደምፈልገው ለብቻ መኖር አልተቻለኝም ስለዚህም ወደ ላይኛው ግብጽ እሔድ ዘንድ ወደድኩ" አለ ያም ቃል መልሶ እንዲህ አለው ወደ "ላይኛው ግብጽ ብትሔድ ድካምህ ደግሞ እጥፍ ይሆናል ብቻህን መኖር ከወደድክ ግን የሦስት ቀን ጐዳና ያህል ወደ ውስጠኛው በረሀ ተጓዝ"። ❤ በዚያንም ጊዜ በዚያች ጐዳና ሊጓዙ የሚሹ የዓረብ ሰዎችን አብርአቸው ወደ እርሳቸውም ሒዶ አብሮአቸው ይሔድ ዘንድ ለመናቸው እነርሱም በደስታ ተቀበሉት ወደ አንድ እጅግ ረጅም ወደሆነ ተራራ እስከሚያደርስ የሦስት ቀን ጐዳና ተጓዘ በዚያም የጠራና የቀዘቀዘ ውኃ አለ ደግሞም የሰሌን የተምር ዕንጨቶች መቃዎችም በብዛት አሉበት እንጦንዮስም ያንን ቦታ ወደደው ዓረቦችም ምግቡን የሚያመጡለት ሆነ ብዙዎች የከፉ አራዊትም ነበሩ በጸሎቱም እግዚአብሔር አስወገዳቸው ወደዚያም ቦታ ከቶ አልተመለሱም። አንዳንድ ጊዜም ወደ ባሕሩ ዳርቻ በመውጣት ደቀ መዛሙርቶቹን ጐብኝቶና አረጋግቶ በበረሀ ውስጥ ወደአለው ቦታው ይመለሳል።

photo content
+2

❤ ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በመልአኩ አማላጂነት እጅግ ብዙ ድርሰቶችን የደረሱት መልአኩ ጽዋ ሕይወትን ካጠጣቸው በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያም አባ ጊዮርጊስ የተወለዱት በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት ነው፡፡ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሠረቱ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፡፡ ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡ የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ እየመራ ወደ ግብጽ እና ወደ አገራችንን ኢትዮጵያ ያመጣቸው ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ እመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር በደመና ጭኖ መላ ኢትዮጵያን ካስጎበኛት በኋላ ቅድስት አገራችንን ለእመቤታችን የዓሥራት አገር እንድትሆን ያደረገው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ❤ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በዓመት 3 ዓበይት በዓላት አሉት፡፡ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡ ከሊቀ መላእክት ከቅዱስ ዑራኤል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። አማላጅነቱ አይለየን! በጸሎቱ ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ። ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ። ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር"። መዝ 91፥12-13 ወይም መዝ 44፥8-9። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥5-19 ወይም ማቴ 11፥28-ፍ.ም። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ። ግበሩ በዓለ በትፍሕትሥ በኀበ እለ ያስተሐምምዎ። እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ"። መዝ 117፥27። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 1፥13-ፍ.ም፣ 1ኛ 2፥22-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥20-28። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 2፥42-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ዑራኤልና የሲመት በዓልና የአባ እንጦንስ የዕረፍት ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw