en
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Open in Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Show more
1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለዱማቴዎስ ዘዓጽፈ ትጉሐን ዐጽፉ። እኅወ መክሲሞስ በሥጋ ወበመንፈስ ቅዱስ ሱታፉ። ሠራዊተ ሰይጣን ቀሪበ ዘኢክህሉ ዐውደ ምዕራፉ። ቦ መልአክ ዘይጼልሎ በክንፉ። ወቦ መልአክ ዘይሰድዶሙ በሰይፉ"። ትርጉም፦ ወደ ማረፊያው ዐደባባይ የሰይጣን ሰራዊት መቅረብን ያልቻሉ፤ በሥጋ የመክሲሞስ ወንድምና በመንፈስ ቅዱስም ተባባሪው የኾነ መጐናጸፊያው የትጉሃን መጐናጸፊያ ለኾነ ለዱማቴዎስ ሰላምታ ይገባል፤ በክንፉ የሚጋርደው መልአክ አለ፤ ጠላቶቹ አጋንንትንም በሰይፉ የሚያባርራቸው መልአክ አለ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 17። https://t.me/Eotcw

photo content

❤ "ነፍሴን አስይዤ እፋለማለሁ የአባቶች አደራ አለብኝና'' ❤ እኔ መጀመሪያ ስሾም የቀደስኩት በኦሮሚኛ ቋንቋ ነበር ብዙ አገልግሎቶችን በኦሮምኛ ቋንቋ ነው የምናከናውነው። የነዚህ ሰዎች አላማ ምንድነው? ቅዱስ ሲኖዶስን ማክበር ያስፈልጋል። ከዛ ያፈነገጠ አካሄድ ከባድ መለኮታዊ ቅጣት አለው። እኔ በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን፥ በአንድ ቤተክህነት አምናለው ከዚህ ውጭ የሚደረግን እንቅስቃሴ ነፍሴን አስይዤ እፋለመዋለው የአባቶቼ አደራ አለብኝና። ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ❤ የብፁዕነታቸው አባታችን በረከታቸው ይደርብን!። https://t.me/Eotcw

photo content

❤ ለሦስት ዓመትም ያህል ሳይጎበኙት በመቅረታቸው አባታቸው አባ መቃርስ በተጋድሎ መኖራቸውን አይቶ አደነቀ፡፡ ሥራቸውንም ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነ፡፡ ጸሎቱንም ከጨረሰ በኋላ ተነሥቶ ወደ ቅዱስ መክሲሞስና ቅዱስ ዱማቴዎስ ዘንድ ሄደ፡፡ እነርሱም በመምጣቱ ደስ ተሰኙበትና በዚያች ሌሊት አብረው አደሩ፡፡ ሌሊትም ለጸሎት በተነሡ ጊዜ የእሳት ሀብል ከቅዱስ መክሲሞስና ከቅዱስ ዱማቴዎስ አፍ ሲወጣና ወደ ሰማይ ሲያርግ ሰይጣናትም እንደዝንቦች ሲከቡት ነገር ግን ቅዱሳን መላአክት በእሳት ሰይፍ ዝንቦቹን ሲቆርጧቸው አባ መቃርስ ተመለከተ፡፡ በነጋም ጊዜ አባ መቃርስ ጸልዩልኝ ብሏቸው ሊሄድ ሲነሳ አንተ ጸልይልን እንጂ ብለው ግድ አሉት፡፡ ❤ እነዚህ የከበሩ ቅዱሳን ተጋድሎአቸውን በፈጸሙ ጊዜ በመጀመሪያ ቅዱስ መክሲሞስ ታመመ፡፡ አባ መቃርስም መጥቶ ባጽናናው ጊዜ በዙሪያው ቅ ዱሳንን ከበውት ተመለከተ፡፡ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ መጥምቁ ዮሐንስ፣ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እነዚህንና ሌሎችንም በአባ መክሲሞስ ዙሪያ ተመለከታቸውና "መክሲሞስ ሆይ የተመሰገንህ ነህ" አለው፡፡ ቅዱስ ዱማቴዎስም ወዲያው በአባ መቃርስ ፊት ተምበርክኮ "ከወንድሜ ጋር ዐርፍ ዘንድ ጸልይልኝ" አለው፡፡ ቅዱስ መክሲሞስም ከተቀበረ በኋላ ቅዱስ ዱማቴዎስም ታመመ፡፡ አባ መቃርስም ወደ እርሱ ሲሄድ በመንገድ ላይ ሳለ አስቀድሞ በአባ መክሲሞስ የዕረፍቱ ጊዜ ያያቸው ቅዱሳን ሁሉ አሁንም መጥተው የአባ ዱማቴዎስ ነፍስ በክብር ሲያሳርጓት ተመለከተ፡፡ አባ መቃርስም ከቅዱሳኑ ማረፊያ በደረሰ ጊዜ አባ ዱማቴዎስን ዐርፎ አገኘው፡፡ ወስዶም ከወንድሞ ጋር በአንድ መቃብር በክብር ቀበረው፡፡ የቅዱስ መክሲሞስ የዕረፍቱ ቀን በጥር ዐሥራ አራት ነው፣ የቅዱስ ዱማቴዎስ ዕረፍት ግን በጥር ዐሥራ ሰባት ቀን ሆነ፡፡ ❤ የከበረ አባ መቃርስም ያ ቦታ በስማቸው እንዲጠራ አዘዘ። እንዲሁም ደብረ በርሞስ ተብሎ እስከዛሬ የሚጠራ ሆነ ለዘላለሙም መታሰቢያቸው ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 17 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ። ከመ ይዕቀቡከ በኲሉ ፍናዊከ። ወበእደዊሆሙ ያነሥኡከ"። መዝ 90፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 8፥16-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥8-15 እና የሐዋ ሥራ 19፥8-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥1-17 ወይም ማር 16፥19-ፍ.ም የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ዱማቴዎስ የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፯ (17) ቀን። ❤ እንኳን ለለውንድዮስ ለሮም ንጉሥ ልጅ ለሆኑ ለከበሩና ለተመሰገኑ ወድማማቾች ለቅዱስ ዱማቴዎስ ለዕረፍት በዓልና ለቅዱስ መክሲሞስ ለመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ሁለት ወድማማቾች ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ አባ መክሲሞስና አባ ዱማቴዎስ፦ እነዚህም ቅዱሳን ለሮም ንጉሥ ለለውንድዮስ ልጆቹ ናቸው። ይህም ንጉሥ ሃይማኖቱ የቀና እግዚአብሔር የሚፈራ በእውነትም የቀና ፍርድን የሚፈርድ ነበር ስለዚህም እሊህን ሁለት ቅዱሳን እግዚአብሔር ሰጠው እነርሱም ከታናሽነታቸው ጀምሮ በንጽሕና እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆኑ። ❤ ትሕትናን ፈሪሀ እግዚአብሔርን በማስተማር አሳደጋቸው የሚጾሙና የሚጸልዩ በቀንና በሌሊትም የብሉይና የሐዲስ መጽሐፍቶችን የሚያነቡ ሆኑ። ከዚህም በኋላ ይህ ዓለም ይተውት ዘንድ የመላእክት ልብስ ይለብሱ ዘንድ እርሷም የከበረች የምንኵስና ልብስ ናት ከዚያም ሀሳብ መጣባቸው ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ አስራ ስምንት አባቶች ወደ ተሰበሰቡባት ወደ ኒቂያ ሔደው ይጸልዩ ዘንድ እንዲያሰናብታቸው ለአባታቸው ምክንያት አቀረቡ። ይህንም ከእርሷቸው በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው። ከብዙ አገልጋዮችና ከብዙ ሠራዊት ጋር አሰናበታቸው ከኒቅያ አገርም በደረሱ ጊዜ ከከበረ ቦታ በረከትን ተቀበሉ ሠራዊቱንም ወደ ንጉሥ አባታቸው ጌታችን ንጉሥ ሆይ "እኛ ከዚህ ጥቂት ቀን መቆየት እንሻለን" የሚል ጽሑፍ ጋር ጽፈው ላኩ። ❤ ከዚህም በኋላ ለአንድ ጻድቅ መነኰስ ኀባቸውን ገለጡ እንዲህም አሉት "ከአንተ ዘንድ የምንኵስናን ልብስ እንድንለብስ እንሻለን" እርሱም "እኔ ከንጉሥ አባታችን የተነሣ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ሶርያ ሒዱ ስሙ አጋብዮስ የሚባል ከዚያ ሃይማኖቱ የቀና ካህን ደግ መነኰስ አለ" አላቸው ይህንንም ሲላቸው ምክሩን ተቀብለው ወደ ሶርያ ተጒዘው ወደ ቅዱስ አባ አጋብዮስ ደርሰው ኀሳባቸውን ገለጡለት እርሱም ተቀብሎ የምንኵስና ልብስን አለበሳቸው እስከሚአርፍበት ቀን ከእርሱ ዘንድ ኖሩ። ከዕረፍቱም አስቀድሞ ያየውን ራእይ ነገራቸው ታላቁ አባ መቃርስ ወደርሱ እንደመጣና "ልጆችህ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ለኔ ልጆቼ ይሁኑኝ ዘንድ ወደ እኔ ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመጡ ከመሞቴ በፊት እዘዛቸው" አለው። ዳግመኛም እንዲህ አላቸው ልጆቹ "እኔ ይህን ሰው አባ መቃርስን በሥጋው አየው ዘንድ እመኝ ነበር እነሆ በመንፈስ አየሁት እናንተም ከሞትኩ በኋላ ወደርሱ ሒዱ"። ❤ ከዐረፈም በኋላ አልሔዱም በዚያ በሶርያ አገር ኖሩ እንጂ እግዚአብሔር ሀብተ ፈውስ ሰጥቷቸው በሽተኞችን የሚፈውሱ ሆነ ወሬያቸውም በአገሮች ሁሉ ተሰማ በባሕርና በየብስ ከሚነግዱ ነጋድያንም የመርከብ መዛነቢያዎችን መሥራት ተምረው ከድካም ወጋቸው በጥቂቱ የሚመገቡና የተረፈውን ለድኆችና ለችግረኞች የሚሰጡ ሆኑ። እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ከሚሠራቸው ድንቆች ተአምራቶች የተነሣ የቅዱሳን መክሲሞስና ዱማቴዎስን ስም መናፍስት ርኵሳን በማሰሚ ጊዜ ከሰዎች ወጥተው ይሸሻሉ ሰዎችም ያን ጊዜ በጌታ ኃይል ይድናሉ ጤነኞችም ይሆናሉ። እጅግ ታላቅ የሆነ በጐዳና አጠገብ የሚኖር ከይሲ ነበር ብዙዎች ሰዎችንም አጥፍቷል የአገር ሰዎችም ወደ ከበሩ መክሲሞስና ዱማቴዎስ መጥተው ከዚያ ከይሲ ያድኗቸው ዘንድ ለመኗቸው አባ መክሲሞስም ክርታስ አንሥቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ "የብፁዕ መቃርዮስ አምላክ በሆነ መንፈስ ቅዱስንም በለበሰ በአባታችን በአጋብዮስ አምላክ ሕያው እግዚአብሔር አካላዊ ቃል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደብዳቤ ከዋሻህ ደጅ ሲደርስ አንተ ወጥተህ ሙት የሰማይ ወፎችም ይብሉህ"። ❤ አንድ ሰውም ያቺን ደብዳቤ ተቀብሎ ሔደ በዚያም የዘንዶ ዋሻ ደጃፍ አኖራት በዚያንም ጊዜ ዘንዶው ወጥቶ ሞተ የሰማይ ወፎችም በሉት ሕዝቦችም ሁሉ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርም።እግዚአብሔርም በእነዚህ ሁለት ቅዱሳን እጆች ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረገ፡፡ በአንዲትም ዕለት ከአባታቸው መኳንንቶች አንዱ ወደ ባሕር ዳርቻ ደረሰ፡፡ ከመርከቦችም በአንደኛው መርከብ ላይ መክሲሞስና ዱማቴዎስ የሚል ጽሑፍ ባየ ጊዜ የመርከቡን ሹም የጠቀው፡፡ የመርከቡ ሹምም "ማዕበል በተነሣ ጊዜ በጸሎታቸው ከመስጠም እግዚአብሔር እንዲያድነኝ የእነዚህን ሁለት ወንድማማቾች ቅዱሳን ስማቸውን በመርከቤ ላይ ጻፍኩ" አለው፡፡ መኰንኑም "መልካቸው ምን ይመስላል?" አለው፡፡ እርሱም የመልካቸውን ነገር ነገረው፡፡ መኮንኑም የንጉሡ ልጆች መሆናቸውን ዐውቆ ያንን ነጋዴ ወደ ንጉሡ ዘንድ ወሰደው፡፡ ንጉሡም የሁለቱን ቅዱሳን ነገር ነጋዴውን የጠቀው፡፡ እርሱም ስለ ቅዱሳኑ የሚያውቀውን ሁሉ የመልካቸውንም ነገር ነገረው፡፡ ንጉሡም ልጆቹ እንደሆኑ ተረዳ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ እናታቸውንና እኅታቸውን ወደ ልጆቹ ዘንድ ከብዙ ሠራዊት ጋር ላከ፡፡ ደርሰው ባዩአቸውም ጊዜ ጮኸው አለቀሱ፡፡ እናታቸውም ቅዱሳኑን ወደ አባታቸው ዘንድ እንዲሄዱ ለመነቻቸው፡፡ ቅዱሳኑም "ራሳችንን ለእግዚአብሔር አሳልፈን ሰጥተናልና ይህን ማድረግ አይቻለንም" አሏት፡፡ "ነገር ግን ወደ ቤተ መንግሥትሽ ተመለሺና ሂጂ፣ አንቺንም አባታችንንም እግዚአብሔር ከመከራ ሁሉ እንዲጠብቃችሁ እንጸልያለን" ብለው አረጋጓትና ሸኟት፡፡ እርሷም ወደ ንጉሡ ባሏ በደረሰች ጊዜ የሆነውን ነገረችው፡፡ እርሱም ለሚስቱና ለባለሟሎቹ ሁሉ "በዓለም ውስጥ ያለ ክብር ሁሉ እንደ ሕልም ኃላፊ ጠፊ ነውና ልጆቼ ግን የማያልፈውን መንግሥት መርጠዋልና ለእግዚአብሔር ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋዮቹ ይሆኑ ዘንድ እንተዋቸው፣ በጸሎታቸውም እኛን ይጠብቁናል" አላቸው፡፡ ❤ በዚያም ወራት የሮሜው አገር ሊቀ ጳጳሳት ዐረፈና በእርሱ ፈንታ የሚሾሙትን ይማከሩ ዘንድ ኤጲስቆጶሳትና ጳጳሳቱ ሁሉ ተሰበሰቡ፡፡ የከበረ መክሲሞስንም አሰቡትና "ለዚህች ለከበረች ሹመት የተገባው እርሱ ነው" ተባባሉ፡፡ ቅዱስ መክሲሞስ ብዙ ድንቅ ተአምራትን እንደሚያደርግ፣ ክርስቶስም በውስጡ ስላደረ በዕውቀትና በበጎ ሥራ በሕግና በሥርዓት ፍጹም እንደሆነ ሁሉም ዐውቀዋልና፡፡ ❤ አባቱና እናቱም የቅዱስ መክሲምያኖስን ለሹመት መመረጥ በሰሙ ጊ ዜ እጅግ ደስ ብሏቸው የከበሩ ቅዱስ መክሲሞስንና ቅዱስ ዱማቴዎስን ወደ ሮሜ አገር ይልካቸው ዘንድ ለሶርያው አገረ ገዥ ደብዳቤ ጽፈው ከብዙ ሠራዊት ጋር ላኩ፡፡ ቅዱስ መክሲሞስና ቅዱስ ዱማቴዎስም ይህንን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ አባታቸው አጋብዮስ የመከራቸውን አስታውሰው ለብሳቸውን ለወጡና ተነሥተው ሸሽተው ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ አካባቢ ሄዱ፡፡ ነገር ግን እነርሱ ሳያስቡት የእግዚአብሔር ኃይል ወደ አባ መቃርስ አደረሰቻቸው፡፡ ❤ አባ መቃርስም በጸጋ የለመለሙ እነዚህን ሁለት ቅዱሳን ባያቸው ጊዜ ደስ ብሎት በክር ተቀበላቸው፡፡ እነርሱም በምንኩስና ተጋድሎ ከእርሱ ዘንድ መኖር እንደሚፈልጉ ሲነግሩት ፈተናው ከባድ መሆኑን ነገራቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰሌን መሥራትን አስተማራቸውና ሰሌን የሚቆርጡበትን ወንዝም አሳያቸው፡፡ የእጅ ሥራቸውን የሚሸጥላቸውና ምግባቸውን የሚያመጣላቸው አንድ ሕዝባዊ ሰው አምጥቶ አገናኛቸው፡፡ እነርሱም ከሰው ሳይገናኙ ሦስት ዓመት በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለኢየሉጣ ዘወጽአ እምከርሣ ጽጌ ረዳ እምዕነቶ እሳት ዘድኅነት በወልዳ"።ትርጉም፦ ከእሳት ምድጃ በልጇ የዳነች ከማሕፀኗ ጽጌ ረዳ የተባለው ቂርቆስ የወጣ ለኾነች ለኢየሉጣ ሰላምታ ይገባል። + + + ❤ "ሰላም ለአባ ዳንኤል ወፈጸመ ርሥኣኖ በሠናይ ገድል በእንተ ጽድቅ ውርዝው መሃይምን ከመ አበው"። ትርጉም፦ እንደ አባቶች የታረመነ፤ ስለ ጽድቅ ጐልማሳ ኾኖ እርግናውን በመልካም ተጋድሎ የፈጸመ ለኾነ ለአባ ዳንኤል ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content
+3

ኑ ፊላታዎስ ለአማልክት ሲሠዋ ታዩ ዘንድ" አሕዛብም ሁሉ ወደ ፍርድ አደባባይ ተሰብሰቡ። ❤ ጣዖታቱም በጐዳና ውስጥ ሲያመጡአቸው የከበረ ፊላታዎስ የክብር ባለ ቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ጣዖታቱንና አገልጋዮቻቸውን ጣዖት አምላኪዎችንም ሁሉንም ምድር አፍዋን ከፍታ ትውጣቻው ዘንድ ለመነው ዋጠቻቸውም። በአደባባዩም ውስጥ ታላቅ ጭኸትና ሽብር ሆነ። ይህንን ድንቅ ሥራ አይተው ብዙዎች በክብር ባለ ቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ንጉሡም ተቆጥቶ ራሳቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ቆረጡአቸውም የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀብለው ወደ ዘላለም ሕይወት ገቡ። የከበረ ፊላታዎስንም ማሠቃየቱን ንጉሡ በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ፊላታዎስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ጰላድዮስ፦ ይህም ቅዱስ ከዋሻው ሳይወጣ የሴቶችን ፊት ሳያይ ሃምሳ ዓመት ኖረ ድንቆች ተአምራቶቾን የማድረግና የትንቢት መናገር ሀብት ተሰጠው ዜናውም በቦታው ሁሉ ተሰማ። ❤ በምስር አገር አንድ ነጋዴ ነበር፡፡ እርሱም ይነግድ ዘንድ በመርከብ ተጭኖ ሄዶ ሳለ ማዕበል ተነሥቶበት ለመስጠም ደረሰ፡፡ በዚህም አስጨናቂ ጊዜ ያ ነጋዴ "በአባ ጰላድዮን ጸሎት ተማጽኛለሁ፣ ከሞት ከዳንኩ መቶ የወርቅ ዲናር ለእርሱ እሰጣለሁ" ብሎ ጨኸ፡፡ እንዲህም ብሎ በተናገረ ጊዜ ወዲያው መርከቡን በመስቀሉ ሲቀዝፍ አባ ጰላድዮንን አየው፤ ከመስጠምም አድኖት ወደ ወደብ በሰላም አደረሰው፡፡ ነጋዴውም የተሳለውን መቶ ወርቅ ዲናሩን ይዞ ወደ አባ ጰላድዮን ሄደ፡፡ በመንገድም ሳለ መሽቶበት በእንግዶች ማደሪያ አደረ፡፡ በዚያም ሞሪት የሚባል አንድ ሰው አገኘና በልቡ ያሰበውን ምሥጢሩን ነገረው፡፡ ሞሪትም "እኔ ቦታውን ዐውቀዋለሁና አድርስሃለሁ" ብሎት በማግሥቱ ሁለቱም ተያይዘው ወደ አባ ጰላድዮን ዘንድ ሄዱ፡፡ ❤ ነጋዴውም ይዞ የመጣውን መቶ የወርቅ ዲናር ለአባ ጰላድዮን ሰጠው፣ ነገር ግን አባ ጰላድዮን ባረከውና ወርቁን እንደማይስድ ነገረው ይልቁንም ወስዶ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች እንዲበትነው ነገረው፡፡ ነጋዴውም ከአባ ጰላድዮን እግር ሥር ወድቆ በለመነው ጊዜ ለበረከት ይሆንለት ዘንድ ጥቂት ወሰደለትና ለድኆች ወስዶ እንዲሰጥ ነገረውና ባርኮ አሰናበተው፡፡ ነጋዴውም ወርቁን ይዞ በተመለሰ ጊዜ ከተራራው ወርዶ ከወንዝ እንደደረሰ ሰይጣን በሞሪት ልብ አደረና ወርቁን ሊወስድ ወደደ፡፡ ነጋዴውንም ገደለውና ወርቁን ወሰደ፡፡ በሌሊትም የነጋዴውን አስክሬን ተሸክሞ ወስዶ በአባ ጰላድዮን ደጅ ጣለው፡፡ በማግስቱም ወደ አገረ ገዥው ሄዶ ነጋዴውን አባ ጰላድዮን እንደገለደው አስመስሎ አወራ፡፡ አገረ ገዥው መኮንንም ሄዶ አባ ጰላድዮንን አሠረውና ስለ ነጋዴው ግድያ መረመረው፡፡ አባ ጰላድዮንም "እኔ አልገደልኩትም" ቢለው አላምን አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ጰላድዮን ወደ አስክሬኑ ቀርቦ ቃሬዛውን ይዞ ከጸለየ በኋላ "አንተ በድን ሆይ ማን እንደገደለህ ተነሥተህ ትናገር ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አዝሃለሁ" አለ፡፡ ወዲያውም ያ የሞተው ነጋዴ ከሞት አፈፍ ብሎ ተነሣና ስለ ወርቁ ብሎ ሞሪት በወንዙ ዳር እንደገደለው ተናገረ፡፡ ❤ መኰንኑም ይህንን ተአምር ባየ ጊዜ ደንግጦ ለአባ ጰላድዮን ሰገደለት፡፡ በላዩም ክፉ ስላደረገ ተጸጽቶ ሞሪትን ሊገድለው ወደደ ነገር ግን አባ ጰላድዮን አስተወው፡፡ አባ ጰላድዮንም ከብዙ ተጋድሎ በኋላ እግዚአብሔርን ደስ ሲያሰኝ ኖሮ በሽምግልናው ወቅት በዚሀች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጰላድዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ "ሰላም ለዳንኤል እንተ ብፅዓተ። ጡከመ ኢይርአይ አንስተ። አመ ንጉሠ ዓምድ አኀዞ እንዘ ይሰምዕ ውዴተ። ዜና ቀታሊሁ ከመ ይንግር ክሡተ። በኃይለ ጸሎቱ አንሥአ ብእሴ ምዉተ"። ትርጉም፦ ሴትችን እንዳያይ ብፅዐት ያደረገ ለኾነ ለዳንኤል ሰላምታ ይገባል፤ ሐሜትን (ሰብቅን) ሰምቶ የዐምድ አገር ንጉሥ በያዘው የገዳዩን ዜና በግልጥ ይናገር ዘንድ በጸሎቱ ኃይል የሞተውን ሰው አነሣ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 16። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ብፁዕ ብእሲ ዘስመ እግዚአብሔር ትውክልቱ። ወዘኢነጸረ ውስተ ከንቱ ውስተ መዓት ወሐሰት። ብዙኀ ገበርከ እግዚኦ አምላኪየ መንክረከ"። መዝ 39፥4-5 ወይም መዝ 105፥39-40። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 13፥12-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 3፥1-7 እና የሐዋ ሥራ 20፥9-13። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 5፥25-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ጽምሐና የቅድስት ኢየሉጣ የዕረፍት በዓል በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፮ (16) ቀን። ❤ እንኳን ከዘጠኙ ቅዱሳን ለአንዱ ለታላቁ አባት ለአቡነ ጽሕማ ለዕረፍት በዓላቸው፣ ለከበረ ሕፃን ለቅዱስ ቂርቆስ እናት ለብፅዕት ቅድስት ኢየሉጣ ሰማዕትነቷን ለፈጸመችበት ለዕረፍቷ በዓል፣ ለከበረ አባት ተጋዳይ ለሆነ ከዋሻው ሳይወጣ የሴቶች ፊት ሳያይይ ሃምሳ ዓመት ለኖረ ለአባ ጰላድዮስ ለዕረፍት በዓል፣ የስሙ ትርጒም የእግዚአብሔር ወዳጅ ለሆነ በላም ላይ አድሮ ይመለክ የነበረውን መረግድ የሚባለውን ሰይጣንና አምኮተ ጣዖትን ሰባብሮ ላጠፋው ለከበረ ለታላቁ ሰማዕት ለቅዱስ ፊላታዎስ ለዕረፍት በዓልና ዓምድ ከሚባል አገር ለየሶርያ ሰው የሞተውን ሰው አስነሥተው ያስመሰከረ ለሊቅ ለአባ ዳንኤል ዕረፍት በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱስ ፊላታዎስ ማኅበር ከሆኑ ዐሥር ሺህ አምስት መቶ ሦስት መኳንንቶችም በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ ከቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር ከሆኑ ከዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሠራዊት በሰማዕትነት ከዐረፉና ከእስክድርያ አርባ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳስ ከከበረ አባት ለአባ ዮሐንስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ "ሰላም ለአባ ጽሕማ ዘፈጸመ ገድሎ በጻማ"። ትርጉም፦ ገድሉን በትጋት የፈጸመ ለኾነ ለአባ ጽሕማ ሰላምታ ይገባል። + + + ❤ ሊቅ አባ ዳንኤል፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ በወርቅና በብር ባለጸጋ የሆነ ነው። አባቱም በሞተ ጊዜ የአገረ ዓምድ ጳጳስ አባ ዲዮናስዮስ ይህን ቅዱስ አሳደገው የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማረው ከዚህም በኋላ ዲቁና ቅስና ሾመው የምንኵስና ልብስንም አለበሰው ሀብተ ፈውስም እስከተሰጠው ድረስ ከሰንበት እስከ ሰንበት ሳይበላ በጾም በጸሎት ጸንቶ ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ የሴቶችን ፊት እንዳያይ ፈጽሞ ስዕለት አደረገ እናቱም ወሬውን በሰማች ጊዜ ወደርሱ መጣች ታየውም ዘንድ ላከችበት እርሱም የሴቶችን ፊት እንዳላይ ስዕለትን ተስያለሁ አላት። እርሷም "እኔ እናትህ አይደለሁምን እንዴት እንደ ሌሎች ሴቶች ታስመስለኛለህ" አለችው እምቢ በአላትም ጊዜ ከንብንቧን ገልጣ "ሁለት ሴቶች አንድ ልብስ ለብሰው እያዩህ ሲጠቃቀሱብህ እግዚአብሔር ያሳየኝ"ብላ ረገመችው። ❤ ከጥቂት ቀንም በኋላ አንድ ምእመን ሰው ለሊቅ ዳንኤል ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ወሰደለት በማታም ጊዜ ከሊቅ ዳንኤል ደጃፍ ሲደርስ ከእርሱ ጋር ያለ ወዳጁ ስለ ገንዘብ ፍቅር በላዩ ተነሥቶ ገደለው። ስለ ሟቹም የዓምድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ አባ ዳንኤልን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ በውሽባ ቤት ያሉ ሁለት ሴቶች የአባ ዳንኤልን መምጣት ወሬ በሰሙ ጊዜ ከችኮላቸው ብዛት የተነሣ ያዩት ዘንድ አንድ ልብስ ለብሰው ወጡ አባ ዳንኤልም እናቱ የተናገረችው ስለደረሰበት ፈገግ ብሎ ሣቀ። ❤ ንጉሡም ስለ ሞተው ሰው አባ ዳንኤልን በመረመረው ጊዜ "እኔ አልገደልሁትም ነገር ግን የገደለውን ራሱ ይናገር" አለ። በዚንም ጊዜ ሟቹ በአባ ዳንኤል ጸሎት ተነሥቶ ገዳዩን ተናገረ ይህንንም ድንቅ ተአምር ንጉሡና ሕዝቡ ሁሉ አይተው በአባ ዳንኤል ፊት ሰገዱ። በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ❤ ከዚህም በኋላ ለአባ ዳንኤል እጅ መንሻ ንጉሡ ብዙ ወርቅን አመጣ አባ ዳንኤልም ከርሱ መቀበልን እምቢ ባለ ጊዜ ንጉሥ ገዳምን ሠራለትና ብዙ መነኰሳት ተሰበሰቡ። ወደ መልካም ሽምግልናም በደረሰ ጊዜ ጥቂት ታመመና ጥር16 ቀን በሰላም ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን። + + + ❤ ሰማዕቱ ቅዱስ ፊላታዎስ፦ የስሙ ትርጉም የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ወገን ነው ወላጆቹም መረግድ የሚባል ላም ያመልኩ ነበር የተፈተገና የበሰለ በሰሊጥ ቅባትና በማር የተለወሰ ስንዴ ይመግቡታል ሁል ጊዜ ሦስት ጊዜ የተወደደ ሽቶ ቅባት ይቀብታል የወይን ጠጅም ያጠጡታል ለክረምትና ለበጋም ማደሪያ አለው በአንገቱሜ የወርቅ ዛንጅርና ድሪ አለ። ❤ ይህ ቅዱስ ፊላታዎስ መልኩ እጅግ የሚአምር ነበር ዐሥር ዓመትም በሆነው ጊዜ ለዚያ በሬ ይሰግድ ዘንድ ወላጆቹ ተናገሩት ሕፃን ፊላታዎስም ቃላቸውን አልሰማም እነርሱም እርሱን ስለሚወዱት ልቡን ሊያሳዝኑት ስለአልፈለጉ አላስገደዱትም። የከበረ ፊላታዎስም ያን ጊዜ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አያውቀውም ነበር በፀሐይም ፊቱ ቁሞ እንዲህ አለ "አንተ ፀሐይ አምላክ ከሆንክ ታስረዳኝ ዘንድ እለምንሃለሁ" አለው። በዚያንም ጊዜ ከወደላይ እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ "እኔ አንተ ልታወቀውና ስለ ከበረ ስም ደምህ ይፈስ ዘንድ ያለህ አምላክ አይደለሁም"። ❤ ሕፃን ፊላታዎስም ይህን በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና ዳግመኛም በዚያች ሰዓት ወደርሱ መልአክ ተላከ እርሱም የአምላክን ምሥጢር አስረዳው የሚነግረውንም ያስታውል ዘንድ ልቡናውን ከፈተለት ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ ሰው እስከሆነበት ድረስ የሆነውን ይነግረው ጀመረ በልቡናውም እጅግ ደስ አለው። ከዚያችም ዕለት ወዲህ ሁል ጊዜ አብዝቶ የሚጾምና የሚጸልይ ሆነ ከብቻው እንጀራና ጨው በቀር አይበላም ለድኆችም ለምስኪኖችም ምጽዋት ይሰጣል። ❤ ከዓመትም በኋላ ወላጆቹ አሰቡ ለልጅቻው ባልንጀሮች ምሳ አዘጋጁ ሳይበሉና ሳይጠጡ አስቀድሞ ልጃቸው ፊላታዎስ ለዚያ በሬ ዕጣን እንዲአሳርግ ፈለጉ ሕፃኑ ፊላታዎስ በበሬው ፊት ቁሞ "ሰዎች የሚያመልኩህ አንተ በእውነት አምላክ ነህን" አለው። ያን ጊዜ ከበሬው እንዲህ የሚል ቃል ወጣ "እኔ አምላክ አይደለሁም ሰይጣን በእኔ ላይ አድሮ ሰዎችን እንዳስት አደረገኝ እንጂ" ይህንንም ብሎ ያ በሬ ተነሥቶ የቅዱስ ፊላታዎስን ወላጆች በቀንዶቹ ወግቶ ገደላቸው ፊላታዎስም ያንን በሬ ይገድሉት ዘንድ አመድ እስከሚሆንም በእሳት አቃጥለው በነፋስ ይበትኑት ዘንድ አገልጋዮቹን አዘዛቸው እርሳቸውም እንዳዘዛቸው አደረጉ። የወላጆቹም በድኖቻቸው ወድቀው ነበር እግዚአብሔርም ጸጋውን አሳድሮበታልና ቅዱስ ፊላታዎስ በወላጆቹ በድኖች ላይ ጸለየ ነፍሳቸውም ተመልሳ በዚያን ጊዜ ተነሡ በሲኦልም ከአዩት ሥቃይ ነገሩት። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፊላታዎስና ወላጆቹ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት በጸሎቱ በሽተኞችን የሚፈውስ ሆነ። ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ተሰማ መልክተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስቀረበውና ለአጵሎን ዕጣን ያሳርግ ዘንድ አዘዘው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት ባልሰማውም ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ። በአላንጋዎች ገረፉት በሆዱም ላይ የሚከብዱ ደንጊዎችን አደረጉ እርሱ ግን በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል የጸና ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሡንና የረከሱ አማልክቶችን ሊረግማቸው ጀመረ ንጉሡም አፉን ይመቱት ዘንድ ምላሱንም ይቆርጡ ጥርሶቹንም ይሰብሩ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ያለ ጥፋት ጤነኛ አደረገው። ከዚህም በኋላ ንጉሡ ይሸነግለው ዘንድ መልካም ቃል ሊናገረው ጀመረ የከበረ ፊላታዎስ ግን ሲዘብትበት ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ ቃል ገባለት ንጉሡም እውነት ስለመሰለው ደስ አለው አጵሎንንና አገልጋዮቹን ለጣዖትም የሚገዙትን ሁሉንም እንዲአመጡአቸው አዘዘ ዳግመኛም በከተማው ውስጥ ዓዋጅ ነጋሪ ይዞር ዘንድ አዘዘ እንዲህ እያለ "ሁላችሁ አሕዛብ

photo content
+2

+++++ሰሜን ሸዋ መንዝናይፋት መዘዞ አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ በኢትዮጵያ በአለም ትልቁ ታቦት ከሰማይ የወረደ አፍሮ አይገባ መስቀል ያለበት መስቀሉ የሚያለቅስበት ከለሩን የሚቀያይርበት ። በረከቱ ይደርባችሁ! ጥር13/2015 SHARE!ያደረገውን ያሳወቀውን ገዳሙን አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ያሰበውን ይፈጽምለት። አንብቡት በረከት ነው ንገሩት የውስጣችሁን ተሳሉ አታፍሩም ወድያው ምላሽ እናገኛለን፤በየአላችሁበት ይስማችሁ!አሜን!!!shareበውጭ ያላችሁ መሳል መንገር ብቻ ይህ" አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ" ገዳም ቀደምት እና ጥንት በመላዕክት የመጣ በኢትዮጵያ በአለም ትልቁ ታቦት ነው። በጣም ስለት ስለሚሰማ የምትረሱ አትሳሉ ምክንያቱም ስለት በዕለት የነገሩትን ስለሚመልስ ነው ከረሳችሁ ቁጡ ነው አደጋ አለው። ጸበሉ /ከዛፍ ውስጥ/ነው ከዛፍ ውስጥ የሚወጣው ጸበል ቀይ ሲሆን ጸበሉም ቃልኪዳን ያለው "ለአይንና ለጆሮ ህመም "ብቻ ነው፤በዚህ ጸበል የማያየው አይነ ስውራን አይናቸው የበራው እረ ብዙ ነው ለቁጥርም ያዳግታል።ጆሮ የማይሰማው እረ ስንቱ ሰምቷል።ሌላም የምንጠመቀው ከገደል ውስጥ የሚፈልቅ ጸበል ስንቱ በሽተኛ ነው የዳነው በተለይ የአናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ "እምነቱን የተቀደሰበት"የታመመን በዕለት የሚፈውስ እምነት ነው።በእምነቱ እኔም ምስክር ነኛ የሄደ ሁሉ የሚመሰክርበት ገዳም ነው የስለቱ ነገር አይነሳ። ጾም ባልሆነ ወቅት ስለት የተሳሉ ሰዎች ለምሳሌ በግ ከሆነ በጉን ወስደው ቤተክርስትያን ውስጥ ሲያርዱ ለክብረ በዓል የመጣው ሰው ሁሉ ቢላ ጩቤ ይዞ ነው የሚመጣው ምክንያቱም ያ የስለት በግ የተሳለው ስውየ በጉን እንዳረደው አንገቱን እንዳረደ በገዳሙ ውስጥ ለክብረ በዓል የመጣው ሰው ሁሉ ይከበዋል አንገቱ እንዳረደ ሌላውን ህዝብ በሽሚያ ነው የሚናጠቀው ግማሹ እግሩ ሌላ የተለያዩ የስጋውን አካል በሽሚያ ቢላ ጩቤ የያዘ ሁሉ እየገነጣጠሉ የሚሻሙበት ገዳም ነው ምክንያቱም የስለት በግ ስጋው በጣም ብዙ የታመሙን አልጋ ላይ ያሉ በመንፈስ የሚሰቃዩን ስለሚፈውስ ነው።ስለት የማይገባ የለም ያለውን ሰዉ ያለዉን ይሰጣል ድመት ፣ዶሮ ፣የተለያዩ የጥሪ እህሎች፣ቅቤ ወዘተ የሚገባበት አስደናቂ ገዳም ነው። ያዉ ለገዳሙ ገቢ ሆኑ ተሸጦ ለካህናት ደሞዝ ይሆናል በአመት ደሞዛቸዉ ለአንድ ከከህን 600ብር ነዉ። አባቶች እደሚሉት ገዳሙ አካባቢ ወረርሽኞ ያበደ የዉሻ በሽታ እና ከብት በሽታ ሲኖር ታቦቱ ሲወጣ ወረርሽኞ በሽታዉ ይጠፍል።እርሱ ባለቤቱ በሃገራችን የመጣዉን ወረርሽኞ ያጥፋልን ይቅር ይበል።አሜን! ወዳጆቼ በተለይ ውጭ ያላችሁና መሄድ የማትችሉ ስለት የማትረሱ፨ "አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ"፨ብላችሁ ተሳሉ ንገሩ ወድያው በዕለት ነው ለአዘነ ሰው ሲደርስ ደግሞ ምንም ጥያቄ የለም ስሙን ብቻ መጥራት ወድያው አፋጣኛ ምላሽ የምናገኛበት ገዳም ነው። ይህንን ገዳም ነሐሴ 13ቡሄ በዚህ ገዳም ትልቅ ክብረበዓል ነው። ይህንን ገዳም የረገጠ ደብረ ታቦርን እንደረገጠ እቆጥርለታለሁ ይላል ቃልኪዳኑ። በዚህ በደብረ ታቦር በዓል ቀን፤ እንዲሁም ወንድ ልጅ እንደ 40ቀን;ሴት ልጅ እንደ 80ቀን አድርጌ እቆጥራቸዋለሁ ይላል የገዳሙ የቦታው ቃልኪዳን ወዳጆቼ እርሱ ባለቤቱ እግዚአብሔር አብ ነው ታቦቱ።ለደጁ ለበረከቱ ያብቃችሁ !የውስጣችሁን እንቆቅልሽ ይፍታላችሁ! ሃገራችንን ሰላም ያርግልን! ሽታውን ከአለም ላይ ያጥፉልን!አሜን!!! ገዳሙ እርዳታ ያስፈልገዋል መርዳት የምትፈልጉ እግዚአብሔር የፈቀዳችሁ እርዱ..... Account no-1000241841317/ደብረ ምህረት አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስትያን/ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ(Commercial Bank of Ethiopia) ወላዲት አምላክ እምየ ንጽሕት ንጹሃን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጃችን አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ዘጠገሮ ጤናችሁን ይስጧችሁ፤ሃገራችን ሰላም ያድርጉልን፤ረሃቡን አንበጣውን ጦርነቱን ያጥፉልን፤ፍቅርን አንድነትን ይስጡን።አሜን! የገዳሙ ሰበካ! የገዳሙ ኮሚቴ! ሀ/0911190212 ለ/0911481388 ሐ/0979986969 መ/0901002929 "በመከራህ ግዜ እግዚአብሔር ይስማህ"።መዝ 20:1 ቦታው/_ሰሜን ሸዋ መንዝ መንገድ ከአዲስ አበባ 195ኪሜ መዘዞ ከተማ አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ዘፀገሮ ገዳም መውረጃ እንደደረስን ከመዘዞ ከተማ የ1ሰዓት የእግር መንገድ አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ።

ለኦርቶዶክሳውያንና የቤተ ክርስቲያን ህልውና ለሚያሳስባችሁ ሁሉ ይህንን የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ አቀርባለሁ:: ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን መቆማችንን ለማሳየት ሁላችንም ፕሮፋይላችንን በዚህ የብፁዕ ወቅዱ
ለኦርቶዶክሳውያንና የቤተ ክርስቲያን ህልውና ለሚያሳስባችሁ ሁሉ ይህንን የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ አቀርባለሁ:: ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን መቆማችንን ለማሳየት ሁላችንም ፕሮፋይላችንን በዚህ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፎቶ እንድንቀይርና ከታች ያሉትን ሃሽታጎችም አብረን ፖስት እንድናደርግ እጠይቃለሁ:: #አንዲት_ቤተ_ክርስቲያን #አንድ_ሲኖዶስ #አንድ_ፓትርያርክ #eotc_one_holy_synod #one_church #one_patriarch #his_holiness_abune_mathias #oriental_orthodox "ሐዋርያት በሰበሰቡአት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን" ጸሎተ ሃይማኖት በተረፈ ይህ ሁሉ ፈተና ስለ በደላችን የመጣ ነውና ንስሓ እንግባ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ሰላምም እንጸልይ::

ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና እና ፈቃድ ውጭ በ"አባ" ሳዊሮስ አማካኝነት የተሾሙት ወደተለያዩ አህጉረ ስብከቶች መመደባቸውን ገልጸዋል። 1.አባ ገ/ማርያም ነጋሳ- ምዕራብ ወለጋ ሀ/ስብከት 2.አባ ተ/ሃይማ
ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና እና ፈቃድ ውጭ በ"አባ" ሳዊሮስ አማካኝነት የተሾሙት ወደተለያዩ አህጉረ ስብከቶች መመደባቸውን ገልጸዋል። 1.አባ ገ/ማርያም ነጋሳ- ምዕራብ ወለጋ ሀ/ስብከት 2.አባ ተ/ሃይማኖት ወልዱ- ድሬዳዋ ሀ/ስብ 3.አባ ገብርኤል ወ/ዮሐንስ- ጉራጌ ሶዶ ሀ/ስብ 4.አባ ገ/እግዚአብሄር ታደለ- ምዕራብ አርሲ ሀ/ስብ 5.አባ ሚካኤል ገ/ማርያም- ከምባታ ሀ/ስብ 6.አባ ኃይሉ እንዳለ- ምሥራቅ ሐረርጌ ሀ/ስብ 7.አባ ተ/ማርያም ስሜ- ጉጂ ሊበን ሀ/ስብ 8.አባ ኃ/ኢየሱስ መንግስቱ-  ከፋ ሀ/ስብ 9.አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ- ቄለም ወለጋ ሀ/ስብ 10.አባ ጳውሎስ ከበደ- ሀዲያ ሀ/ስብ 11.አባ ኃ/ኢየሱስ ተስፋዬ- ምሥራቅ ወለጋ ሀ/ስብ 12.አባ ገ/ኢየሱስ ገለታ- ሆሮ ጉዱሩ ሀ/ስብ 13.አባ ጸጋዘአብ አዱኛ- ምሁር ኢየሱስ ገዳም "የበላይ ጠባቂ" 14.አባ ኃ/ማርያም ጌታቸው- ምዕራብ ሐረርጌ ሀ/ስብ 15.አባ ወ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል - ከሚሴ ሀ/ስብ 16.አባ እስጢፋኖስ ገብሬ- ባሌ ሀ/ስብከት ረዳት 17.አባ ገ/መድኅን ገ/ማርያም- ጎፋ ባስኬቶ ሀ/ስብ 18.አባ ኃ/ሚካኤል ንጉሤ- ጊኒር ሀ/ስብ 19.አባ አብርሃም መስቀሌ- ዳውሮ,ኮንታ ሀ/ስብ 20.አባ ንዋየ ሥላሴ አክሊሉ- ምዕራብ ጉጂ ሀ/ስብ 21.አባ ኪ/ማርያም ቶሎሳ-  ጅማና የም ሀ/ስብ 22.አባ ወ/ማርያም ጸጋ- ቦረና ሀ/ስብ 23.አባ አምደሚካኤል ኃይሌ- አርሲ(አሰላ) ሀ/ስብ 24.አባ መርሐጽድቅ ኃ/ማርያም -ጌዴኦ,ቡርጁ,አማሮ ሀ/ስብ 25.አባ ሞገስ ኃ/ማርያም -መናገሻ አምባ ቅ/ማርያም ፣ ጋራ መ/ዓለምና ደ/ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ "የበላይ ጠባቂ" 26.አባ ገ/ኢየሱስ ንጉሤ - ቡኖ በደሌ ሀ/ስብ በየአካባቢው የምትገኙ ካህናትና ምዕመናን መንበረ ጵጵስና አህጉረ ስብከቱን እንድትጠብቁ ጥሪ ቀርቧል ! @leyumerga

እኔ ከቤተ ክርስቲያኔ ጎን ቆማለሁ! በስልጣን ጥማት #በዘረኝነት የሰከሩ ሕገወጥ ሰዎችን አልቀበልም።እንደ አባትም አልቆጥራቸውም በክርስቶስ  ያገኘሁትን ልጅነት በዘር አሳንሰዉብኛልና።የሐዋርያትን አስተምህሮ ክደዉ በናዚ ጀርመን እሳቤ ተስበዋልና። #እኔ የቡነ ጴጥሮስ ልጅ ነኝ።አቡነ ጴጥሮስ ደግሞ ለኦርቶዶክሳዊያንና ለኢትዮጵያዊያን ሲሉ ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጥተዋልና። # አንዲት ቤተክርስቲያን_የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ #አንድ መንበር _መንበረ ተክለ ሃይማኖት # አንድ ሲንዶስ~የኢኦተቤ #አንድ ፓትርያርክ __ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ * Ani Mana Kirstaanaa Koo Cinaa Nan Dhaabadha! Namoota Dheebuu Aangoon ,Ilaalcha Sanyummaan Machaa'an duuka hin bu'u. Akka Abbaa Hafuuraawaattis hin Lakkaa'u  Surraa Mucummaa Kiristoosiin Argadhe  Sanyummaan na Jalaa xineessaniiru waan ta'eefi. barumsa Duuka Bu'oota gananii ilaalcha Naazii Jarmaaniitiin Harkifamaniiru! Ani Ilma Abune Pheexroisiitii.Abuna Pheexroos immoo Orthodoksootaa Fi Itoophiyaanootaaf Jecha Lubbuu Isaa Dabarsee Laateera! #Manni Kiristaana Tokkittiidha~Mana Kiristaanaa Ortodoksi Tawaahidoo Kan Itoophiyaa! #Teessoo Tokko~ kan Abuna Takla Hayimaanootii #Siinoodoosii Tokko~ Mana Kiristaana Ortodoksi Tawaahidoo  Kan Itoophiyaa #paatriyaarkii Tokko~Eebbiifamoo fi Qulqulluu Kan Abbaa Keenya Aabba Maatiyaas!

photo content
+1

❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእሰሰክድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህ አለ "ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዩን ከርሱ አራቀ። ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም አስነሥቶ አዳናቸው። ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው "በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ በእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታላቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ። በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲአደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ "በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው"። ❤ ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ። መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ አፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈራች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቃዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኲራኵር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እስከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በሕይወት አወጣቸው። ❤ መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጊዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቅዱስ ቂርቆስንም "የምትሻውን ለምነኝ" አለው። ሕፃኑም "ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ አባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን"። ❤ መድኃኒታችንም "የለመንከኝ ሁሉ አስጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ" አለው ሕፃን ቂርቆስ በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳረገ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቂርቂቆስና በእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ነቢዩ ቅዱስ አብድዩ፦ ይህም ነቢይ የሐናንያ ልጅ ነው በንጉሥ ኢዮሳፍጥም ዘመን ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም ስለ ትንሣኤና ስለ ፍርድ ቀን በቃሉ ነገረው። ሁለተኛም ከእስራኤል ልጆች የሚሆነውን ከአሕዛብም ለቀሩት አጸናቸው አብዝቶ መከራቸውም ገሠጻቸውም። ❤ ይህም ንጉሥ አካዝያስ ይጠሩት ዘንድ ወደ ኤልያስ ከላከቸው ሦስተኛ መስፍን ነው ከእርሱ አስቀድመው የመጡ እነዚያን ሁለት መስፍኖች በኤልያስ ቃል አሳት ከሰማይ ወርዳ ከእነርሳቸው ጋር ካሉ ወታደሮች ጋር በላቻቸው። ይህ ግን ወደ ኤልያስ በመጣ ጊዜ በፊቱ ተንበርክኮ ሰግዶ ተገዛለት እንዲህም አለው "የእግዚአብሔር ሰው ተገዛሁልህ የእሊህ የባሮችህ ሰውነትና የኔ ሰውነት በፊትህ ትክበር" በእግዚአብሔር ነቢይ ላይ ፈጽሞ አልታበየምና ነቢዩ ኤልያስም ራራለት ወርዶም ከርሱ ጋር ወደ ንጉሡ ሔደ። ❤ ይህም አብድዩ ከምድራዊ ንጉሥ አገልግሎት የኤልያስ አገልግሎት እንደምትበልጥ የኤልያስ አገልግሎት ለሰማያዊ ንጉሥ አገልግሎት ታደርሳለችና ይህን በልቡ ዐወቀ ስለዚህ ምድራውያን ነገሥታትን ማገልገል ትቶ ነቢዩ ኤልያስን ተከትሎ አገለገለው በላዩም ከእግዚአብሔር ሀብተ ትንቢት አደረበትና ትንቢትን የሚናገር ሆነ የትንቢቱም ወራት ሃያ ዓመት ነው ከጌታችን ሥጋዌ በፊት በዘጠኝ መቶ ዓመት በሰላም በፍቅር አንድነትም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ነቢያት ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 15 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም። ወከዐዉ ደሞሙ ከመ ማይ ዐውዳ ለኢየሩሳሌም። ወኃጥኡ ዘይቀብሮሙ። መዝ 78፥2-3። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "አኅለፍከነ ማእከለ እሳት ወማይ። ወአውጻእከነ ውስተ ዕረፍት። እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ"። መዝ 65፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 4፥11-15 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-19። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቂርቆስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፲፭ (15) ቀን። ❤ እንኳን ለከበረ ሕፃን በሦስት ዓመቱ ተጋድሎውን ለፈጸመ ለቅዱስ ቂርቆስ ለዕረፍቱ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ ለቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች ሰማዕትነት ለተበቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ለሐናንያ ልጅ ለዕውተኛ ነቢይ ለቅዱስ አብድዩ ለዕረፍት በዓል። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በሶርያ አገር ያሉ የክርስቲያን ወገኖች ለቅዱስ ጎርጎርዮስ የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ከመያከብሩት፣ ከጴጥሮስ፣ ከሶፍያ ከአድምራና፣ ከይስሐቅ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ዘንጉሥ ሄጣ ጸለየ ላቲ ወልደ ተዝካሮሙ ንግበር ለቂርቆስ ወለኢየሉጣ እለ በተአምኖ ወረሱ ተስፋሆሙ ፈድፋደ እምስብእ የዓቢ ዕሴቶሙ"። ትርጉም፦ ንጉስ ሸነገላት ልጇ ጸለየላት (ለመነላት) የቂርቆስና የኢየሉጣ መታሰቢያ እናድርግ በሃይማኖት ተስፋቸውን ወረሱ (አገኙ) ዋጋቸው ከሰው ይበልጣል። + + + ❤ የዕለቱ እግ.ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ዘምስለ እግዚኡ ኪዳነ ዘአቀመ ወብዙኃነ ሕዝበ አእመነ ለብፁዕ ቂርቆስ አልቦ ዘይሞግሶ አክሊለ ነሥአ ዲበ ርእሱ"። ትርጉም፦ ከጌታው ጋር ቃል ኪዳንን አደረገ ብዙዎችን ህዝቦች አሳመነ ንዑድ ክቡር ቂርቆስን ባለሟል የሚያደርገው የለም በራሱ አክሊል ተቀናጅቷል ወስዷል። + + + ❤ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ፦ በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮሜ ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በአገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች። ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት። ❤ መኰንኑም "ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው አገርሽስ ወዴት ነው" አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት "የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ" አለችው። መኰንኑም "በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን" አላት "አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ" የከበረች ኢየሉጣም አለችው "ለረከሱ አማልክት እኔ አልሠዋም" አለችው መኰንኑም "ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት እርሷም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው" አለችው። መኰንኑም "ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው" ብላ መለሰችለት። መኰንኑም "ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳያመጡ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "ዕውነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ አገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይነገረን" አለችው። ❤ ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የአገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን "የስንት ዓመት ልጅ ነው" ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም "ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው" አሏቸው። ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየ ጊዜ "ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል" አለው። ሕፃኑም "እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን "ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን" አለው። ሕፃኑም "ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ" አለው። ❤ መኰንኑም "ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ "ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው" ብሎ መለሰለት። መኰንኑም "ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ" አለው የከበረ ሕፃንም "ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው" በማለት መለሰለት፡፡ መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን "እሺ በለኝና እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ" አለው። ሕፃኑም "የሰይጣ መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ" አለው። መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲግፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣሜ የልጅዋን ትዕግሥት በአየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ "ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ። የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ "ትእዛዝህ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ" ብሎ ጮኸ። ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት ጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፋ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም "ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው" አለ። ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ "የሥቃይ መሣሪያን ይሠራ ዘንድ እንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ" አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣን ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው። ❤ ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ "እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩ በትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህ ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም" አለው። ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ" አለው። ሕፃኑም ቅዱስ ቂርቆስ እያዘዘው...። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከአገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀምረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።