ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
😭 "ኩላዊት እንጂ ክልላዊት ቤተክርስቲያን የለችንም!!! አንድ ሲኖዶስ አንድ መንበር ፤መንበረ ተክለሃይማኖት አንድ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ ፤ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ!።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ።
😭 (ኢኦተቤ ቴቪ ጥር ፩፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ) መግለጫውን ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት; ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።
😭 ቅዱስነታቸው ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕገ ወጥ "ሢመተ ጳጳሳት" ጉዳይ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በሕገወጥነት የተከናወነ መሆኑን በመግለጽ :-
1. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።
2. መንግሥት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር።
የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ። ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
3. ምዕመናን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም ጊዜ በላይ በንቃት በሀሣብና በጸሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል። ምንጭ፦ EOTC TV።
https://t.me/Eotcw
1 161
😭 እጅግ አሳዛኝ ዜና።
😭 ለካ እግዚአብሔር ይህን ያህል ነው ያዘነብን መከራችን አያበቃም ! ? "እባክህ አምላኬ ስለ አዛኝቷ ድንግል ብለህ እኔን ኃጢዓተኛውን ማረኝ"።
😭 ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የምስካየኅዙናን መድኃኒአለም ገዳም የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት እራሳቸውን ፓትሪያርክ በማድረግ 25 ኤጲስ ቆጶሳትን ሾመዋል!!!
😭 በዛሬው ዕለት በወሊሶ መድኃኒአለም ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እራሳቸውን ፓትሪያርክ በማድረግ ለስልጣን ጥማት ያደረባቸውን 25 ኤጲስ ቆጶሳት አድርገው ሾመዋል።
😭 ከአንድ የቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የማይጠበቅ እና ህገ ቤተክርስቲያንን የሚፃረር ድርጊት ይፈፅማሉ ብለን የማንጠብቃቸው አቡነ ሳዊሮስ ይሄንን አድርገዋል።
😭 ቤተክርስቲያኒቷ በራሷ ስርዓት እና ህግ የምትገዛ ሆኖም ሲኖዶሳዊት የሆነችውን ይቺ ሀገር የሆነችውን ቤተክርስቲያን ብትንትኗን ለማውጣት ይሄን ያህል መንገድ መራመዳቸው እጅግ የሚያሳዝን ተግባር ነው።
😭 በአስቸኳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለምመናኗ መፍትሔ ሊሰጥ እንደሚገባ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።
https://t.me/Eotcw
1 161
😭 ዜና ዕረፍት።
😭 ቀኝ ጌታ ተክለ ያሬድ አሰፋ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
😭 በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ለረዥም ዓመታት ያገለገሉት ቀኝ ጌታ ተክለ ያሬድ አሰፋ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
😭 ቀኝ ጌታ ተክለ ያሬድ አሰፋ በ1933 ዓ.ም በደቡብ ወሎ ክፍለ ሀገር ጃማ ወረዳ አህያ ፈጅ ቁስቋም ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ በአካባቢያቸው ከሚገኘው ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን ፊደልና ጸዋትወ ዜማ የተማሩ ሲሆን በመንዝ ክፍለ ሀገር ዘብር ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ከየኔታ አክሊሉ ዘንድ ዜማ ተምረዋል።
😭 ከዚያም በኤሊሻማ መድኃኔዓለም ከመልአከ ብርሃን ቤተ ማርያም ግዛው የተክሌ አቋቋም የተማሩ ሲሆን በመቀጠልም በሰደድኩላ ሚካኤል በቅዳሴ መምህርነት አስመስክረዋል።
😭 ቀኝ ጌታ ተክለ ያሬድ አሰፋ ለቤተ ክርስቲያን ትምህርት ካላቸው ብርቱ ፍላጎት የተነሳ የቅኔ ትምህርታቸውን በጎጃም ብቸና ጊዮርጊስ የተማሩ ሲሆን ከዚያ ተመልሰውም በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ከየኔታ በትረ ማርያም ዘንድ አስቀጻይ ሆነው የተክሌ አቋቋም ሲማሩ ቆይተው በ1965 ዓ/ም ወደ እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል በመምጣት በቅዳሴ መምህርነት አገልግለዋል።
😭 ቀኝ ጌታ ተክለ ያሬድ አሰፋ ከሕዳር 1967 ዓ.ም ጀምሮ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ መምህር በመሆን ወደ ደብሩ ከመጡ በኋላ እስከ 1974 ዓ.ም በቅዳሴ መምህርነት አገልግለዋል። በማያያዝም የአካባቢ ወጣቶችን ፊደል በማስቆጠር ብዙ ልጆችን አፍርተዋል።
😭 ከዚያም ወደ ቅኔ ማኅሌት ሥራ ተዛውረው በቅኔ ማኅሌቱ ቀኝ ጌታ ሆነው ተሾመው ለ7 አመታት ደብሩን ያገለገሉ ሲሆን እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ድረስ ለ አርባ ስምንት አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ መድኃኔዓለምን ሲያገለግሉ ኖረው ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም በተወለዱ በ82 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
😭 ሥርዓተ ቀብራቸው ለረዥም ዓመታት ባገለገሉበት በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት ጥር 14 2015 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ ይፈጸማል።
😭 የአባታችንን ነፍስ እግዚአብሔር አምላክ ከደጋጋጎቹ መዘምራን ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ ከአባ ጽጌ ድንግል አጠገብ ያሳርፍልን። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል።
https://t.me/Eotcw
1 161
ዛሬ በማለደው"ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሳዊሮስ 26 ኤጲስ ቆጶሳት ሾሙ"
የሚል ዜና ሳይ ወዴት እየሄድን እንደ ሆነ አሳስቦኛል፣
ምን አለ የቅዱስ ሲኖዶሱ ሥር ለቅዱስ ሲኖዶሱ ብንተው። ለእራስ የፓትርያርክ ማዕረግ መስጠት አይከብድምን?
ለማንኛውም የተዋህዶ ልጆች አትረበሹ ብፁዓን አባቶች የሚሉት በትግስት እንጠብቅ።
1 161
አባ ሳዊሮስ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን በመሰንጠቅ በታሪክ የመጀመርያው ከሀዲ ይሆናሉ
**
ባቡነ መርቆርዮስ ግዜስ እንዳትሉኝ፡፡ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ነበሩ፡፡ በግፍ ነው የተሰደዱት፡፡ ይሄንን አሳዶቻቸው ራሳቸው ተናግረዋል፡፡ ታምራት ላይኔን ይጠቅሷል፡፡ በዛ ላይ ስደተኛው ሲኖዶስ ብለው የመሰረቱትም በውጭው ዓለም ነው፡፡
አባ ሳዊሮስ ግን ይሄን ነውረኛ ተግባር የፈጸሙት ፣ ፓትያርክ ሆነው በግፍ ተሰደው ወይ ተበድለው አይደለም፡፡የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ናቸው፡፡ ሊያስሾሙ የፈለጉትን መነኩሴ ጠቁመው ትክከኛ መዋቅሩን ተከትለው ማስሾም ይችሉ ነበር፡፡
የሳቸው ዓላማ ግን ሌላ ነው፡፡ ቤተ ክርስያኗን ገንጥለው ፓትርያርክ መሆን ነው፡፡
ከዚህ በስተጀርባም ያሉትና ከወታደራዊ እስከ ፖለቲካው ድጋፍ የሰጧቸውና ጃስ ያሏቸው ፣ ባለግዜ ነን ፖለቲከኞች ናቸው፡፡ እነ ሽመልስ !
እንደ ጠላት የሚያዩአትን ቤተ ክርስትያን ለማፈራረስና አንድነቷን ለመበተን ፣ እንደ አባ ሳዊሮስ አይነትን ከእምነቱ ይልቅ የብሔሩ ጉዳይ የገነነበትን ጥቁር እርግብ ተጠቅመው እነ ሽመልስ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ለማዳከም የሰሩት ሴራ ነው፡፡
እቅዱም ግልጽ ነው፡፡ቤተ ክርስትያኗእሺ ብላ ይሄን ሹመት ከተቀበለች ፣ የራሳችንን ሰው በግድም ቢሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ እናስገባለን፡፡ ካወገዘችን ደግሞ እንደ በይፋ ሁለተኛ ሲኖዶስ መስርተን እንበጠብጣለን ነው፡፡
ሌላው አማራጭ ደግሞ እንደ ውጭው ሲኖዶስ እርቅ ተብሎ ሲኖዶስ እንገባለን ነው፡፡
እንኳን ለጵጵስና ፣ለመቃብር ዘበኛነትን የማይመጥኑ የካድሬ መንጋ ሰብስቦ ፣ የጵጵስና ቆብ አጥልቆ በጳጳስ ስም ፖለቲካ እንዲያራምዱና ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ከውስጥ እንዲቦረብሩ የታሰቡ ሰዎን ናቸው ዛሬ ጳጳስ ተደርገው የተሾሙት፡፡
አባ ሳዊሮስን አንተ ከመባል አንቱ ያሰኘቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስትያን ናት፡፡ከምን እንደተነሱ ረስተው ፣ ያከበረቻቸውንና ያስከበረቻቸው ቤተ ክርስትያን ላይ ተነስተዋል፡፡ገመናቸውን ሸፍና አክብራና ትልቅ አድርጋ ባኖረች፣ ቤተ ክርስትያንን ለመክፈል ከፖለቲከኞች ጋር አሲረው በቤተ ክርስትያን ላይ ተነስተዋል;፡፡
የቤተ ክርስትያን አምላክ ግን ይፈርዳል፡፡
የባለግዜ ፖለቲከኞች መሳርያ ሆነው ቤተ ክርስትያንን ለመሰንጠቅ ፣ ቅድስት ቤተ ክርስትያን ላይ ስለት ና ጦር ያነሱት አባ ሳዊሮስና መሰሎቻቸው አይቀጡ ቅጣት እንደሚወድቅባቸው ርግጥ ነው፡፡ የሚያሳዝነው ግን ጳጵስና ደረጃ ላይ ደርሰው ከእግዚአብሔር ጋር አወዳድረው ለፖለቲከኞቹ ማደራቸው ነው፡፡
አብይም፣ ሽመልስም ልክ እንደ መለስና ታምራት ላይኔ ስም አጠራራቸው አይገኝም፡፡ ሁሌም የስልጣን መንበሩ ለማይናጋው አምላክ ማደር ይሻላቸው ነበር፡፡
@..,
1 161
በጉባኤ ከለባት በህገወጡ ቡድን ከተሾሙት የስልጣን ጥመኞች ዝርዝር መካከል 👇👇የሚገኙበት
1. አባ ተክለ ሃይማኖት ።።።።።።። የቀድሞ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ
2. አባ ገብረ እግዚአብሔር ።።።።።። የአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት አስተዳዳሪ
3. አባ ሽኖዳ ።።።።።።።።። አለም ገና ኢየሱስ አስተዳዳሪ
4. አባ ወልደ ጊዮርጊስ ።።።።።።። ወለቴ ዮሐንስ አስተዳዳሪ
5. አባ ገብረ ኢየሱስ ።።።።።። አለም ገና ሚካኤል አስተዳዳሪ
6. አባ ገብረማርያም ነጋሳ ።።።።። የኦሮምያ ቤተ ክህነት መስራች
7. አባ ጳውሎስ ከበደ ።።።።። የሐረር ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበረና በተሐድሶነት የተባረረ
8. አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ።።።።።።። የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መጽሐፍ መምህር
ይቀጥላል
ሠናይ ሚዲያ
1 161
🌺መዝሙር ሖረ ኢየሱስ ከጥር ፲፪ - ፲፰
መዝሙር🌺
(በ፫/ሙ) ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አሕዛብ (ሖ) አርአዮሙ ስብሐቲሁ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ (ሖ) ወይቤሎሙ ቅድሑ ማየ ወምልዕዎን ለመሳብክት እስከ አፉሆን (ሖ) ጥዒሞ አንከረ ሊቀ ምርፋቅ በረከተ ዘአምላክ ገብረ (ሖ) ቤዛነ ተስፋነ ወልደ አምላክ ወለማይኒ ረሰዮ ወይነ።
https://t.me/Eotcw
#Join & share
