ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
ቅድስት ቤተክርስቲያንን ያስደሰቷትና የታመኑላት እኚህ አስተዋይ አባት ማን ናቸው?
#የወፍ_ዘራሹን_ሹመትና_ሺ_ሞት እንዲቀላቀሉ ሲጠየቁ
ቅድስት ቤተክርስቲያንንና #መንፈስ_ቅዱስን_ዋሽቼ ፣ #ቅዱሱን_ሲኖዶስ_ሸውጄ ፣ ቤተክርስቲያንን በድዬና ምእመናንን አሳዝኜ የምቀበለው ጵጵስና የለም ያሉት የድጓውና የአቋቋሙ ፣ የቅኔውና የምሥጢሩ ባለቤት የሆኑትና ወርቀ ቤተ ክርስቲያን በመባል የሚታወቁት የማኅሌቱ መልአክ #መልአከ_መዊዕ_ቆሞስ_አባ_ናትናኤል ናቸው።
ታማኙና ተወዳጁ አባታችን የደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል አስተዳዳሪ እርስዎን አምላከ ቤተ ክርስቲያን በክብር ያኑርልን።
ያከበሯት ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታክብርልን ።
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 5:1-17፡ "ወሶበ ርእየ ብዙኃነ አሕዛብ" - "ሕዝቡንም፡አይቶ፡ወደ፡ተራራ፡ወጣ፤በተቀመጠም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡እርሱ፡ቀረቡ፤ አፉንም፡ከፍቶ፡አስተማራቸው፡እንዲህም፡አለ። በመንፈስ፡ድሃዎች፡የሆኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና። የሚያዝኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መጽናናትን፡ያገኛሉና። የዋሆች፡ብፁዓን፡ናቸው፥ምድርን፡ይወርሳሉና። ጽድቅን፡የሚራቡና፡የሚጠሙ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይጠግባሉና። የሚምሩ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይማራሉና። ልበ፡ንጹሖች፡ብፁዓን፡ናቸው፥እግዚአብሔርን፡ያዩታልና። የሚያስተራርቁ፡ብፁዓን፡ናቸው፥የእግዚአብሔር፡ልጆች፡ይባላሉና። ስለ፡ጽድቅ፡የሚሰደዱ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና። ሲነቅፏችሁና፡ሲያሳድዷችሁ፡በእኔም፡ምክንያት፡ክፉውን፡ዅሉ፡በውሸት፡ሲናገሩባችሁ፡ብፁዓን፡ናችሁ። ዋጋችሁ፡በሰማያት፡ታላቅ፡ነውና፥ደስ፡ይበላችሁ፥ሐሴትም፡አድርጉ፤ከእናንተ፡በፊት፡የነበሩትን፡ነቢያትን፡እንዲሁ፡አሳደ፟ዋቸዋልና። እናንተ፡የምድር፡ጨው፡ናችሁ፤ጨው፡ዐልጫ፡ቢሆን፡ግን፡በምን፡ይጣፍጣል፧ወደ፡ውጭ፡ተጥሎ፡በሰው፡ከመረገጥ፡በቀር፡ወደ፡ፊት፡ለምንም፡አይጠቅምም። እናንተ፡የዓለም፡ብርሃን፡ናችሁ።በተራራ፡ላይ፡ያለች፡ከተማ፡ልትሰወር፡አይቻላትም። መብራትንም፡አብርተው፡ከእንቅብ፡በታች፡አይደለም፡እንጂ፡በመቅረዙ፡ላይ፡ያኖሩታል፡በቤት፡ላሉት፡ሁሉም፡ያበራል። መልካሙን፡ሥራችሁን፡አይተው፡በሰማያት፡ያለውን፡አባታችሁን፡እንዲያከብሩ፡ብርሃናችሁ፡እንዲሁ፡በሰው፡ፊት፡ይብራ። እኔ፡ሕግንና፡ነቢያትን፡ለመሻር፡የመጣሁ፡አይምሰላችሁ፤ልፈጽም፡እንጂ፡ለመሻር፡አልመጣሁም።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
17/5/2015 ዓ.ም (፲፯/፭/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ።
ከመ ይዕቀቡከ በኲሉ ፍናዊከ።
ወበእደዊሆሙ ያነሥኡከ። መዝ 90፥11
🕯 ትርጉም
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ፤
መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋልና።
እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ዮሐ 1፥24-29 "ወእለሰ ተፈነዉ" -"የተላኩትም ከፈሪሳውያን ነበሩና። እንኪያስ አንተ ክርስቶስ ወይም ኤልያስ ወይም ነቢዩ ካይደለህ፥ ስለ ምን ታጠምቃለህ? ብለው ጠየቁት። ዮሐንስ መልሶ እኔ በውኃ አጠምቃለሁ፤ ዳሩ ግን እናንተ የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሞአል፤እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ፥ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ከእኔ ይልቅ የሚከብር ይህ ነው አላቸው። ይህ ነገር ዮሐንስ ያጠምቅበት በነበረው በዮርዳኖስ ማዶ በቢታንያ በቤተ ራባ ሆነ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
17/5/2015 ዓ.ም (፲፯/፭/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወአዐውድ ምሥዋዒከ እግዚኦ ።
ከመ እስማዕ ቃለ ስብሐቲከ።
ወከመ እንግር ኲሎ መንክረከ። መዝ 25:6
🕯 ትርጉም
አቤቱ፥መሠዊያህን እዞራለሁ።
የምስጋናን ድምፅ እሰማ ዘንድ።
ተኣምራትህንም ሁሉ እነግር ዘንድ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
