ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለኄኖክ ዘአእመረ ኅቡኣቲሁ ለእግዚአብሔር ወኵሎ መዛግብቲሁ፤ ወኮነ በቊዔተ ለልቡባን፤ ወከበቶ እግዚአብሔር ውስተ ብሔረ ሕይወት"። ትርጉም፦ የእግዚአብሔርን የተሰወሩ ነገሮችን እና መዛግብቱን ኹሉ ያወቀ፤ ለአስተዋዮችም የሚጠቅም ለኾነና፤ እግዚአብሔርም በሕይወት ሀገር ውስጥ ለሰወረው ለኄኖክ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላ በአውሲም ከተማ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ፡፡ የሀገሩን ታላላቅ ሰዎችንም አቅርቦ ስለከበረ ቅዱስ ቢፋሞን ጠየቃቸው፡፡ የአገር ሽማግሎችም ስለእርሱ አዘኑ-እርሱ ተአምራትን የሚያደርግ አማልክትንም የሚረግም መሆኑን ያውቃሉና፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ቢፋሞን ቤተሰቦቹን ተሰናብቶ ያማሩ ልብሶቹን ለብሶ ፈረስ ጋልቦ የሀገሩ ሽማግሎችና መኮንኑ ካሉበት ቦታ ደረሰ፡፡ መኮንኑ አርያኖስም ባየው ጊዜ ደስ ብሎት በክብር ሰላምታ ሰጠው፡፡
❤ ቅዱስ ቢፋሞንም "የሰላም ትርጓሜው ደስታ ነው፣ እኔ በጌታዬና በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ አለኝ አንተና ባልንጀሮችህ ግን በሰማያት ደስታ የላችሁም" አለው፡፡ አርያኖስም "እኔ ክፉ ነገርን እንድትነግረኝ አልመጣሁም፣ ለአማልክት እንድትሠዋ በንጉሡ ደብዳቤ ታዝዤ መጣሁ እንጂ" አለው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም "አማልክቶቻችሁ አፍ እያላቸው የማይናገሩ፣ እጅ እያላቸው የማይዳስሱ፣ ጆሮ እያላቸው የማይሰሙ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ፣ አፍ እያላቸው የማይተነፍሱ ናቸውና የሠሩአቸውና የሚያመልኳቻም እንደ እነርሱ ይሁኑ፡፡ እኔ ግን ሰማይንና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ለፈጠረ ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አሰግዳለሁ" አለው፡፡ መኰንኑ አርያኖስም ይህንን ነገር ከቅዱስ ቢፋሞን አፍ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎችም አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም በፈረሶች ላይ አሥሮ መሬት ለመሬት እየጎተተ ከተማውን ሁሉ አዞረው፡፡ የቅዱስ ቢፋሞን እናቱና አገልጋዩ በመጡ ጊዜ በከበረች የወንጌል ቃል አጽናናቸው፡፡ እነርሱና ሌሎችም የከተማው ሰዎች "እኛም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ የምናምን ነን፣ ሰማዕትም እንሆን ዘንድ እንወዳለን" ብለው ጮኹና የመኰንኑን ለወንበር ገለበጡት፡፡ መኰንኑም ጥልቅ ጉድጓድ አስቆሮ እሳት አስነድዶ ከዚ ውስጥ ጨመራቸውና ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክልሊን ተቀዳጁ፡፡ ቁጥራቸውም አምስት መቶ ሆነ፡፡ እነዚህም 500 ቅዱሳን ምስክርነታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ቅዱስ ቢፋሞን ያጽናናቸውና ያበረታቸው ነበር፡፡ የከበረች እናቱም በላይዋ ላይ እንዲጸልይ ለመነችው፣ እርሱም በመስቀል ምልክት በላይዋ አማተበና በሰላም ሂጂ አላት፡፡ እርሷም ወዲያው ማንም ሳይነካት ዘላ ከእሳቱ ገባች፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡
❤ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንን ግን አርያኖስ ወደ ንጉሡ መክስምያኖስ ሰደደው፡፡ ንጉሡም "የነገሥታቱን ትእዛዝ የምትተላፍ ለአማልክት የማትሠግድ ሥራየኛው ቢፋሞን አንተ ነህን?" አለው፡፡ ቅዱሱም "እኔ ሥራይን አላውቅም፣ ለረከሱ አማልክትህ ግን አልሰግድም፣ አንተም እነርሱም በአንድነት ወደ ገሃነመ እሳት ትወርዳላችሁ" አለው፡፡ ንጉሡም ይዞ በእጅጉ አሠቃው፡፡ ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ወደ መኮንኑ ኄሬኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም ካሠቃው በኋላ መልሶ ለአርያኖስ ላከው፡፡ በእነዚህም ጊዜ ቅዱስ ቢፋሞን ምንም አልበላም ነበር፡፡ አርያኖስም በብረት ችንካሮች ቸነከረውና "ለአማልክት ካልሰገድክ አጠፋሃለሁ" አለው፡፡ ቅዱሱም ንጉሡንና አማልክቱን ረገማቸው፡፡ መኰንኑም በዚህ ጊዜ አሥሮ እየጎተተ በከተማው ሁሉ አዞረው፡፡ ከእንዴና ከተማ ውጭ አውጥቶ በእሳት አቃጠለው፤ ነገር ግን ጌታችን ቅዱስ ቢፋሞንን ከእሳቱ ውስጥ ያለምንም ጉዳት በደህና አወጣው፡፡ ቅዱሱም በእሳት ቆሞ ሳለ ከእግሮቹ ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐይነ ሥውርና ለምጻም ሰው ነበረ፡፡ እርሱም ከቅዱስ ቢፋሞን ደም ወስዶ ዐይኑን ቢቀባው ወዲያው ማየት ቻለ፣ ከለምጹም ነጻ፡፡ ከዚህም በኋላ "እኔም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኛለሁ" ብሎ ጮኸ፡፡ ወዲያውም መኰንኑ ተናዶ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ አርያኖስ የቅዱስ ቢፋሞንንም አንገት በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም አገልጋዩን ዲዮጋኖስን ወደ እርሱ አቅርቦ ሥጋውን በስውር እንዲጠብቅ ደሙንም በበፍታ ልብስ እንዲቀበል ይኸውም ከመከራው ዘመን በኋላ ለበረከት እንዲሆን ነገረው፡፡ ገድሉንም ለምእመናን እንዲነገር ከነገረው በኋላ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበና ወደ ጭፍሮቹ ሄዶ "የታዘዛችሁትን ፈጽሙ" በማለት እንዲሰይፉት ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ወደ ላይኛው ግብጽ አጥማ አውራጃ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ የተዘጋጀለትንና አስቀድሞ ያየውን የክብር አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ከአንገቱም ብዙ ደም በፈሰሰ ጊዜ አገልጋዩ ዲዮጋኖስ በፍታውን ዘርግቶ ደሙን ተቀበለ፡፡ በቦታው መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ ሽታ በሸተተ ጊዜ ችፍሮቹ ደንግጣና ፈርተው ከቦታው ሸሹ፡፡ ምእመናንም መጥተው ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዘው ቀበሩት፡፡ ከመቃብሩም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡
❤ አገልጋዩም ያችን በፍታ ወደ አገሩ ወስዶ ምን እንደሚያደርግ እያሰበ ሳለ ቅዱስ ቢፋሞን ተገለጠለትና ለወዳጁ ለቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎችም ሁሉ ገድሉን እንዲነግር አዘዘው፡፡ እርሱም በመርከብ ተሳፍሮ ሲሄድ በመርከብ ሳለ ጌታችን በዚያች በቅዱስ ቢፋሞን ደም በታለለች በፍታ ብዙ ተአምር አደረገ፡፡ ዲዮጋኖስም የቅዱሱን ገድል ነገራቸው፡፡ እነርሱም እያደነቁ ወደ አገሩ አውሲም አደረሱት፡፡ ዲዮጋኖስም አውሲም እንደደረሰ ለቅዱስ ቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎች ሁሉ የቅዱስ ቢፋሞንን ገድል ነገራቸው፣ ያችንም በደሙ የታለለች በፍታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ብዙ ተአምራት እያደረገችላቸው ከእነርሱ ጋር በክብር አኖሯት፡፡
❤ የመከራው ዘመን አልፎ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ከነገሠ በኋላ እግዚአብሔርም የከበረ የቅዱስ ቢፋሞንን ሥጋ ለምእመናን አለኝታና መጽናኛ ለበሽተኞችም የሚፈውስ ኃይል እንዲሆን ሊገልጠው ወደደና ገለጠው እርሱም በላይኛው ግቡጽ በጥማ አውራጃ በቃው ከተማ በጥር ሃያ ሰባት በዚች ቀን በሰማዕትነት የሞተ ነው ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በተጋዳይ በቅዱስ ቢፋሞን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን፡፡ ምንጭ፦ የጥር 27 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለከ እንተ ረከብከ ሞገሰ። ኅቡአተ ትፍትን ወዘማዕቅት ከርሠ። ሱርያል መልአክ እንዘ ትስእል መንፈሰ። ፍጥረታተ ኵሎ አመ በማየ አይኅ ደምሰሰ። እግዚአብሔር አትረፈ ሰማኒተ ነፍሰ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 27።
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ። ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ንቃህ እግዚኦ ለምንት ትነውም"። መዝ 43፥22። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥5-20፣ ይሁ 1፥11-16 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 11፥8-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የመልአኩ የቅዱስ ሱርያል የመታሰቢያ በዓልና የቅዱስ ኄኖክ የዕርገቱ መታሰቢያ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ከዚህም በኋላ የከበረ ሰራብዮንን ወደ አገሩ ከእርሱ ጋር ወስዶ ያሠቃየው ዘንድ ከኀሳቡም ካልተመለሰ ራሱን በሰይፍ ይቆርጥ ዘንድ ኄሬኔዎስ አንዱን መኰንን አዘዘው። መኰንኑም ከርሱ ጋር በመርከብ ወሰደው ሌሊትም በሆነ ጊዜ ወደ አንድ ወደብ ደርሰው በዚያ ተኙ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ያቺ መርከብ ወደ ቅዱስ ሰራብዮን አገር ደረሰች በጥዋትም በነቁ ጊዜ የመሔጃቸው አቅጣጫ ተለውጦ አገኙ እጅግም አደነቁ ወደ ሰራብዮንም "እነሆ ይቺ አገርህ ናት" የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ከመርከብም አውርደው ታላቅ ሥቃይን አሠቃይተው ጥር27 ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። መኰንኑም ልብሶቹን አውጥቶ ገንዞ ለዘመዶቹ ሰጠው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ሰራብዮን በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ሰማዕቱ ቅዱስ ቢፋሞን፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ድንግል የሆነ እግዚአብሔርን የሚወድ ለድኆችና ለችግረኞች የማሚመጸውት ይህንንም ዓለም ንቆ የተወ ነው። አባቱም ከከበሩ ወገኖች የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ የእናቱም ስም ሶስና ነው። እነርሱም መመጽወትን የሚወዱ ክርስቲያኖች ናቸው የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችንን ድንግል ማርያምን የከበሩ ሰማዕታትንም ሁሉ በዓላት ለድኆችና ለምስኪኖች ምጽዋትን በመስጠት ያከብራሉ የሚኖሩትም በምስር አውራጃ አውሲም በሚባል አገር ውስጥ ነው።
❤ እግዚአብሔርም ደግነታቸውን ተመልክቶ መልኩ እጅግ ያማረ ልጅ ቅዱስ ቢፋሞንን ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ገና ሲወልድ ጀምሮ ብዙ ተአምራት አድጎላቸዋልና እጅግ አላቸው፡፡ በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው አሳደጉት፡፡ ዘጠኝ ዓመትም በሆነው ጊዜ ሃይማኖትንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲማር ለአንድ መምህር ሰጡት፡፡ ከመምህሩም ዘንድ ጥበብንና ተግሣጽን የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ሁሉ አጠና፡፡ ከልጅነቱም ጀምሮ በጾም በጸሎት በስግደት ይጋደል ነበር፡፡ እግዚአብሔር ለቅዱስ ቢፋሞን ገና በልጅነቱ በእጆቹ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን የማድረግ ጸጋ ሰጠው፡፡ በቁስል ደዌ እጆቹንና እግሮቹን የታመመ አንድ ድኃ ቅዱስ ቢፋሞንን ምጽዋት ቢለምነውና ቅዱሱም በእጆቹ ቢነካው ወዲያው ከደዌው ድኖ ጤነኛ ሆነ፡፡
❤ ሁለተኛም በሌላ ጊዜ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር ሲያመሰግን ከዚያ አንድ ጋኔን የሚጥለው ሰው ነበረና "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ተወኝ፣ ከዚህ ቦታ ልጥፋ" ብሎ ጮኸ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ወደ ጌታችን ጸልዮ ያንን ጋኔን ያደረበትን ሰው አዳነው፡፡ መምህሩም ይህን አይቶ በዚህ ሕፃን ልጅ ያደረውን ጸጋ አደነቀ አከበረውም፡፡ በመምህሩም ዘንድ 8 ዓመት ኖረ፡፡ ጌታችንም ቅድስት እናቱን ድንግል ማርያምንና ቅዱሳኑን እያስከተለ እየመጣ ይገለጥለት ነበር፡፡
❤ ቅዱስ ቢፋሞን በየሰባት ቀን በመጾም ተጋድሎውን ጨመረ፡፡ ከሰንበት በቀር አይበላም ነበር፡፡ ዕድሜው ከፍ ሲል ወላጆቹ ሚስት ሊያጋቡት አሰቡ፡፡ እርሱ ግን "በዚህ እንደጤዛ በሚያልፍ ዓለም ከሴት ጋር መኖር ለእኔ ምኔ ነው? ፍላጎቱም ዓለሙም ሁሉም ያልፋል" አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በሰባተኛው ወር አባቱ ሲያርፍ ቅዱስ ቢፋሞን ንብረቱን ሁሉ አውጥቶ ለጦም አዳሪዎች ሰጣቸውና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተጠመደ ሆነ፡፡ በዚያም ወራት የፋርስ ሰዎች በሮም ሰዎች ላይ ጦርነት አስነሥተው ነበር፡፡ የሮሙ ንጉሥ በጦርነቱ ስለሞተ ሮም ያለንጉሥ ቀረች፡፡ መኳንንቱና የመንግሥት ታላላቅ ሰዎችም ተሰብስበው ከአገሮች ሁሉ ተዋጊዎች የሆኑ አርበኞችን ይሰበስቧቸው ዘንድ በየአገሩ አዘዙ፡፡ ከላይኛው ግብፅ ልበ ደንዳና የሆነ ስሙ አግሪጳዳ የሚባል ሰይጣን በልቡ ያደረበት ፍየል ይጠብቅ የነበረ ኃይለኛ ሰው ተገኘ፡፡ እርሱንም ወደ አንጾኪያ አገር ወስደው የፈረሶች ባልደራስ አድርገው ሾሙት፡፡
❤ በአንዲት ዕለትም ሸንበቆ አንሥቶ ዋሽንት ሠርቶ ሲነፋ በፈረሶቹ ላይ ሰይጣን አደረባቸውና ፈረሶቹም እያሽካኩ ይጨፍሩ ጀመር፡፡ በጦርነት የሞተው ንጉሥ ሴት ልጅም በቤተ መንግሥት አዳራሽ ሆና ሲዘፍንና ዋሽንት ሲነፋ አግሪጳዳን አይታ ወደደችው፡፡ ሰይጣንም በልቧ የዝሙትን ፍላጻ ጨመረባትና ወደ እርሷ አስመጣችውና አገባችው፡፡ ስሙንም ዲዮቅልጥያኖስ ብላ ሰየመችውና አነገሠችው፡፡ ታናሽ እኅቷም በእርሷ ቀንታ መክስምያኖስ የሚባለውን አንዱን መኮንን መልምላ አገባችና ልብሰ መንግሥት አልብሳ አነገሠችው፡፡ መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስም በአንጾኪያና በሮም ተስተካከለው ነገሡ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ሰይጣን ተገለጠላቸውና እንዲህ አላቸው፡- "በንጉሡ ሴቶች ልጆች ላይ የዝሙትን ፍቅር በልባቸው ላይ አሳድሬ እንዲወዷችሁና እንዲያገቧችሁ ያደረኩት እኔ ነኝ፤ አሁንም ትእዛዜን ከሰማችሁ በምድር የሚኖረውን ሕዝብ ሁሉ በእጃችሁ ውስጥ አደርግላችኋለሁ፤ እናንተም ስገዱልኝ የብርና የወርቅ ምስልም ሠርታችሁ አማልክት በሏቸው፡፡ ስማቸውንም አጵሎን አርዳሚስ ብላችሁ ጥሯቸው፡፡ ሰዎችም ሁሉ ዕጣን እንዲያሳርጉላቸውና እንዲሰግዱላቸው እዘዙ፤ ያልሰገዱላቸውንም ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ ቁረጡ፤ ይህን ካደረጋችሁ መንግሥታችሁን አሰፋላችኋለሁ ካለዚያ ግን መንግሥታችሁ ታልፋለች" አላቸው፡፡ እነዚህም ሁለት ሰነፎች መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስም ለሰይጣን ሰገዱለትና "ያዘዝከንን ሁሉ እናደርጋለን ብቻ መንግሥታችንን አጽናልን" አሉት፡፡ በዚህም ጊዜ ኄሬኔዎስንና አርያኖስን በግብጽ አገር ላይ መኳንንት አድርገው ሾሟቸው፡፡ ለጣዖት የማይሰግዱትን ሁሉ እንዲገድሉ አዘዟቸው፡፡ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንም ይህንን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ወዳጁን ቴዎድሮስን ጠራውና በክብር ባለቤት በጌታችን ስም ደማቸው አፍስሰው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡
❤ የቅዱስ ቢፋሞን ዜናው በሁሉ ዘንድ የታወቀ ነውና ወሬው ከሃዲው ንጉሥ መክስምያኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ መኳንንቶቹም "በምስር አውራጃ በአውሲም ከተማ የሚኖር ስሙ ቢፋሞን የሚባል ሰው አለ፣ እርሱም የነገሥታትን ትእዛዝ የሚተላለፍ አማልክትን የሚረግምና የሚያቃልል ነው" ብለው ለንጉሥ መክስምያኖስ ነገሩት፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ቢፋሞን ለአማልክት ካልሰገደ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጠው ትእዛዝ ጽፎ ለጨካኙ መኮንን ለአርያኖስ ላከለት፡፡ ደብዳቤውም ከመኮንኑ ዘንድ ሳይደርስ የታዘዘ የእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ቢፋሞን ተገልጠለትና በሰማዕትነት እንደሚሞት እናቱና አገልጋዩ ዲዮጋንዮስም አብረውት እንደሚሞቱ ከነገረው በኋላ ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም ነገረው፡፡ የተዘጋጀላቸውንም የክብር አክሊላት አሳየው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ተነሥቶ ለእናቱ መልአኩ የነገረውን ነገራት፡፡ መልአኩ ለእርሷም ተልጦ ይህንኑ እንደነገራት ለልጇ ነገረችውና ለሰማዕትነት በመመረጣቸው በአንድነት እጅግ አላቸው፡፡ ሲጸልዩ አደሩና በነጋታው ቅዱስ ቢፋሞን ወዳጁን ቴዎድሮስን አስጠራውና ሁሉን ነገረው፡፡ ቀጥሎም "የመከራው ጊዜ ካለፈ በኋላ አንተ በዚህች አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ትሾማለህ ያንጊዜም በስሜ ቤተ ክርስቲያን ትሠራለህ" ብሎ ትንቢት ነገረው፡፡ ወዲያም ሰላምታ ተሰጣጡና ተሳስመው ተለያዩ፡፡
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን ሳፍራ ለሚባል ለመልአክ ለቅዱስ ሱርያል ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ በሞት ፋንታ ለተሰውረው ለነቢዩ ቅዱስ ኄኖክ ለዕርገቱ መታሰቢያ በዓል፣ ለከበረ ሐዋርያ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን አገር ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ ለሥጋው ፍልሰት በዓል፣ ከግብጽ ደቡብ ከታችኛዪቱ ምስር አውራጃ በብኑዲ ከምትባል መንደር ለሆነ ለከበረ ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ከታናሽነቱ ድንግል ለሆነ እግዚአብሔርን ለሚወድ ለድኆችና ለችግረኞች ለሚመጸውት ይህንንም ዓለም ንቆ ለተወ በእሳት ተቃጥሎ ሰማዕትነት ለተቀበለ ለከበረ ቅዱስ ቢፋሞን ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቸሩ መድኃኔዓለም ከስቅለቱ ከወራዊ መታሰቢያ፣ ከሰማዕታት ትውፍሎን፣ ከዮስና ከሰርኒስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ በዚች ቀን ሳፍራ የሚባል የመልአክ ሱርያል በዓል ነው እርሱም ከነቢይ እዝራ ጋር የኖረ የተሠወረ ምሥጢርንም የገለጠለት ነው እርሱም ስለ ሰው ልጆች ወደ እግዚአብሔር የሚለምን ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሱርያል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ በዚችም ዕለት የያሬድ ልጅ ኄኖክን የመላልኤል ልጅ የቃይናን ልጅ የኄኖስ ልጅ የሴት ልጅ የአዳም ልጅ ኄኖክን መላእክት ይዘው አሳረጉት ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ትእዛዝ ጸሐፊ ተባለ።
❤ እንዲህም አለ "ከማደሪያው ከሚወጣው ከቅዱሱና ከገናናው በጸናች ኃይሉ ከሠራዊቱ ጋር በሲና ተራራ ከሚገለበጠው ጋር በመነጋገር ተመላለስኩ። ሁሉም ይፈሩ ነበር በውኃ ዳርም ሳለሁ የልመናቸውን መታሰቢያ ጻፍኩ እስከ አንጎላቸሁና ሕልም እንደሚያይ እስከምሆን ይችም በአርሞን ግራና ቀኝ ያለች አገር ናት"። በደብር ቅዱስ ለነበሩ ለኃጢአት ለሚተጉ ለሴት ልጆች ይዘልፋቸው ዘንድ ቃል እንደጠራውና እንዳሳየው ተናገረ።
❤ እንዲህ አለ "በበረድ ደንጊያ ወደ ተሠራ ታላቅ ቤት ቀረብኩ በበረድ ደንጊያ የተሠራ የዚያ ቤት ግድግዳ እንደ ሳንቃ ልዝብ ነው ከዚህ ቤት የሚበልጥም ሌላ ቤት አየሁ ደጃፉም የተከፈተ ነው በእሳት ቅጽርም የተሠራ በክብር ከሁሉ የሚበልጥ ነው። በውስጡም ከፍ ያለ የእግዚአብሔርን ዙፋን አየሁ መልኩም እንደ ውርጭ ነው አጎበሩም እንደሚያበራ ፀሐይ ነው ከዙፋኑም በታች የኪሩቤል ድምፅ ይሰማል። ዳግመኛም ወደ ሰባት ተራራዎች ደረስኩ ሦስቱ በምሥራቅ በኵል ሦስቱ በአዜብ በኵል ናቸው የመካከለኛው ግን ሰማይ ጠቀስ ነው የመላእክትም ጌታ በላዩ አለ"። ሌሎች አራት ገጾች ኪሩቤልን አየ ስለ ክርስቶስም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "የዘመናት አለቃ ወደ ሆነው የሰው ልጅ ተጠራ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የነበረ ሆነ" ሁለተኛም "ለጻድቃን የጽድቅ በትር ለአሕዛብም ብርሃን ተስፋ ለሌላቸወሰ አለኝታ ይሆናል" አለ።
❤ በሰማይ ገጽ ስለሚመላለሱ ብርሃናት እንዲህ አለ "አንዱም አንዱ በየወገናቸው በሠለጠኑበትና በተሠየሙበት ጸንተው ይኖራሉ" ስለ ነፋሳትም መውጫዎች እንዲህ ብሎ ተናገረ "ሦስቱ በሰማይ ገጽ ሦስቱ በምድር ገጽ ሦስቱ በግራ ናቸው"። ስለ አዳምም እንዲህ አለ "እነሆ በሬ ከምድር ወጣ ፀዓዳም ሆነ" ስለ ሔዋንም "ሴት እምቦሳ ከርሱ ወጣች" አለ።
❤ ስለ ምኵራብም "ያንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ"። ስለ ቤተ ክርስቲያንም "ጌንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ"። ስለ ቤተ ክርስቲያንም "ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ እስቲሠራ ድረስ አየሁ ከቀድሞውም ቤት የበለጠ ነው በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሠማራሉ" አለ። ስለ ምእመናንም "የእሊህም በጎች ፀጒራቸው ንጹሕ ነጭ ነው የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሠማራሉ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሁነዋልና"። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ኄኖክ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ የሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን አገር ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ የሥጋው ፍልሰት፦ ጻድቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም መንግሥትን በያዘ ጊዜ የከበሩ የሐዋርያትን ሥጋቸውን ከሰማዕታትም ብዙዎችን ከቦታቸው ሁሉ ወደ ቊስጥንጥንያ አፈለሳቸው ስለ ሐዋርያ ጢሞቴዎስም ሥጋ በኤፌሶን አገር እንዳለ ሰምቶ ካህናትንና ምእመናንን ላከ እነርሱም አፍልሰው ወደ ቊስጥንጥንያ አድርሰው በከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅደስ ውስጥ አኖሩት። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን።
+ + +
❤ ሰማዕቱ ቅዱስ ሰራብዮን፦ ይህም ቅዱስ ከግብጽ ደቡብ ከታችዪቱ ምስር አውራጃ በብኑዲ ከምትባል መንደር ነው። ቅዱሱም ብዙ የገንዘብ ጥሪት እንስሳትም አሉት አብዝቶ መመጽወትንም የሚወድ ነው ስደትም በሆነ ጊዜ የክርስቲያን ወገኖችን ፈልጎ ያሠቃይ ዘንድ መኰንኑ ኄሬኔዎስ በየአገሩ እንደሚዞር ሰማ ለርሱም ስማቸው ቴዎድሮስና ሁለተኛውም በግ አርቢ ሰርማ የሚባሉ ወዳጆች ነበሩት እነርሱም ተከተሉት ይህም ቅዱስ መኰንኑን ሊገናኘው ከአገሩ ወጣ መኲንኑንም በአገኘው ጊዜ በፊቱ ቁሞ ከወገኖቹ ጋር በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ሁሉንም አሠራቸው።
❤ የአገር ሰዎችም በሰሙ ጊዜ ሁሉንም ተሰበሰቡ መኰንኑን ገድለው ቅዱስ ሰራብዮንን ከእጁ ሊወስዱ ሽተው የጦር መሣሪያ በመያዝ ለጦርነት የተሰለፉ ሠራዊት ሁነው ደረሱ ቅዱሱ ግን ከለከላቸው እንዲህም አላቸው "እኔ በጌታዬ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈስ ዘንድ በፈቃዴ የመጣሁ አይደለምን" መኰንኑም በመርከብ ተሳፍሮ ከዚያ ሔደ ቅዱሳኑም አብረውት ሔዱ። ወደ እስክንድርያ አገርም በደረሰ ጊዜ የከበረ ሰራብዮንን በመንኰራኵር ውስጥ ጽኑዕ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት ወደ እሳት ማንደጃም ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ። ከዚህም በኋላ ከነዳጅ ድፍድፍና ቅመማ ቅመም ጋር በወጭት ውስጥ ቀቀሉት የሥጋውንም ሥሮች ቆረጡ በብረት ዐልጋ ላይም አስተኝተው በችንካር ቸነከሩት ይሁን ሁሉ ሥቃይም የሚታገሥ ሆነ የእግዚአብሔርም መልአክ ሥቃዩን ከላዩ ይቀበልለት ነበር።
❤ ከዚህም በኋላ ከእንጨት ላይ ሰቅለው በፍላፃዎች ነደፉት የእግዚአብሔርም መልአክ እርሱን ከተሰቀለበት አውርዶ በእርሱ ፈንታ መኰንኑን አሥሮ ሰቀለው። የከበረ ሰራብዮንም እንዲህ አለው "ሕያው እግዚአብሔርን በክርስቶስ ስም የታሠሩትን ሁሉንም እስከምታወጣቸውና የሞታቸውን ፍጻሜ እስከምታዝዝ አንተ ከእዚህ ከተሰቀልክበት ዕንጨት እንደማትወርድ ዕወቅ"። በዚያንም ጊዜ ሁሉንም አውጥተው ራሷቻቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው አምስት መቶ አርባ ነፍስ ሆነ።
1 161
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የጾምና የምሕላ አዋጅ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
"የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ!
ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።"
ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ 3 ቁጥር 5
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በተከሰተው ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮቿን በመጣስ መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመት በሰጡትና በተሾመ ግለሰቦች ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥር 18 ቀን 2015ዓ.ም. ቃለ ውግዘት ማስተላለፉ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ እነዚህ ሕገወጥ ቡድኖች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ካለመቻላቸውም በላይ በመንግሥት ኃይሎች በመታገዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተዳድራቸውን መንበረ ጵጵስናዎችንና ቢሮዎችን በኃይል በመውረርና በመስበር ከፍተኛ ጥፋት እያደረጉ ከመሆኑም በላይ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችን ሠራተኞች ካህናትና ምእመናን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛል፡፡ መንግሥትም ሕግ ከማስከበር ይልቅ ለሕገ ወጥ ቡድኖች ድጋፍ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና መብት ሊያስከብር ስላልቻለ ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው አምላካችን በመማፀን ጸሎትና ምሕላ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተረድቷል።
በመሆነም ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
ጥቁር ልብስ የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ጥቁር የእውቀት ምልክት ነው ተማሪዎች አውቀናል ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛ ከእውቀት በላይ የሆነውን አምላካችንን በመማፀን ከዚህም ማንም ሊያናውጽን እንደማይችል የምናረጋግጥበት፤ ጥቁር የእውነት ምልከት ነው ዳኞች እውነት እንፈርዳለን ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛም መከራው የሚያሰቅቀን ሳይሆን ይበልጥ ልንጸናና ልንበረታ የሚገባ መሆኑን ለዓለም ሕዝብ የምናሳይበት በመሆኑ ከጥር 29 እስከ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ለሦስት ቀናት በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነን ወደ ፈጣሪያችንን እንድንጮህ አደራ እንላለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ጥር 26 ቀን 2015ዓ.ም. አዲስ አበባ
1 161
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ሰላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ እንደሚታወቀው ይህ ግሩፕ ከከፈትነው አመት ቢሻገርም እስካሁን ድረስ ያለን ቤተሰብ በጣም አናሳ ነው ። እኛ ሁላችንም ቢያንስ ለምንወዳቸው 5 ሰዎች ብናቀላቅል ቁጠራችን ከፍ ይላል ። በዚህም ሰዎችን ቤተሰብ እንድታደርጉ በእግዚአብሔር ስም በትህትና እንጠይቃለን ።
በተጨማሪም በዘህ ግሩፕ እና ቻናል ላይ ያሎትን ማንኛውም ቅሬታ፣እንዲቀርቡ የሚፈልጉትን ተጨማሪ ፕሮግራሞች ፣እንዲሁም እንዲስተካከል የሚፈልጉት ማንኛውም ሀሳብ በዚህ ግሩፕ ልታጋሩን ትችላላችሁ እኛም ተቀባይ ነን እናመሰግናለን ።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ልጆቿን ይባርክ።
https://t.me/EOTCWW
1 161
❤ ነነዌን እና የጥር ፳፬ቱን መግለጫ አስመልክቶ ከቤተክርስቲያናችን የአንድነት ገዳም ኅብረት የተላከ ተጨማሪ መልእክት!።
❤ "ማንንም ቸል አትበሉ፣ ከታላላቆች ጋር አትወዳጁ፣ መኳንንቱን አትከተሉ፣ እግዚአብሔርን ፍሩ፣ ጾምን ቸል አትበሉ፣ ለመብላትም ምክንያት አታድርጉ"። ዲድስቅልያ ፬፥፳፪
1 161
❤ "ሰውን ብትታገልና ብትዋጋ ታሽንፈዋለህ ወይም ያሸንፍሃል ቤተክርስቲያንን ግን ማሸነፍ አይቻልም። ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ ትዋጋለች ተሸንፋ ግን አታውቅም ዲያብሎስ ዝናሩን አራገፈ ቀስቱንም ጨረስ ቤተክርስቲያንን ግን አልጉዳትም"። ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ።
❤ የአባቶቻችን ጸሎት ሁል ጊዜ አሸናፊ ነው። ሁላችንም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች ከአባቶቻችን ጎን እንሰለፍ።
https://t.me/Eotcw
